ገንደውሃ🔝
ትናንት መከላከያ ሰራዊት በምዕራብ ጎንደር ዞን የፈጸመውን ግድያ #በመቃወም በመተማ ገንደውሃ የተቃውሞ ሰልፍ በመደረግ ላይ ይገኛል። ሰልፈኞቹ ሰራዊቱ አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ ጠይቀዋል። ሰልፈኞቹ መከላከያ 'ሪፎርም' ሊደረግ የማይችል ተቋም ስለሆነ፣ የሰራዊቱ አባል የሆኑ የአማራ ብሔር ተወላጆች ከሰራዊቱ እራሳቸውን እንዲያገሉም ጠይቀዋል።
Via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትናንት መከላከያ ሰራዊት በምዕራብ ጎንደር ዞን የፈጸመውን ግድያ #በመቃወም በመተማ ገንደውሃ የተቃውሞ ሰልፍ በመደረግ ላይ ይገኛል። ሰልፈኞቹ ሰራዊቱ አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ ጠይቀዋል። ሰልፈኞቹ መከላከያ 'ሪፎርም' ሊደረግ የማይችል ተቋም ስለሆነ፣ የሰራዊቱ አባል የሆኑ የአማራ ብሔር ተወላጆች ከሰራዊቱ እራሳቸውን እንዲያገሉም ጠይቀዋል።
Via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የአየርላንዱ ጠቅላይ ሚንስትር ሊዮ ቫራድከር ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገቡ፡፡ ጠቅላይ ሚንስትሩ ቦሌ አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ድኤታ ዶ/ር ማርቆስ ታከለ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ጠቅላይ ሚስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የአየርላንዱን ጠቅላይ ሚንስትር ሊዮ ቫራድከር ዛሬ በፅፈት ቤታቸው እንደሚያናግሩ ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
University College Run,Jan 13,2019 ~ Starting Point- Adams Pavilion - Laphto Mall (End Point)
More፦
0911449805
0912688755
More፦
0911449805
0912688755
#Update የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች መስከረም 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ፣ በመስቀል አደባባይ አቀባበል ለማድረግ ወደ ‹‹አዲስ አበባ እንዳንገባ ተከልክለናል›› ባሉ ግለሰቦች በተፈጠረ ረብሻ ለ49 ሰዎች ሞት ምክንያት በመሆን ተጠርጥረዋል በተባሉ 68 ግለሰቦች ላይ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክስ ተመሠረተ፡፡
ምንጭ፦ ሪፖርተር
https://telegra.ph/ዓቃቤ-ሕግ-በ49-ሰዎች-ሞት-በተጠረጠሩ-68-ግለሰቦች-ላይ-ክስ-መሠረተ-01-09
ምንጭ፦ ሪፖርተር
https://telegra.ph/ዓቃቤ-ሕግ-በ49-ሰዎች-ሞት-በተጠረጠሩ-68-ግለሰቦች-ላይ-ክስ-መሠረተ-01-09
Telegraph
ዓቃቤ ሕግ በ49 ሰዎች ሞት በተጠረጠሩ 68 ግለሰቦች ላይ ክስ መሠረተ
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች መስከረም 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ፣ በመስቀል አደባባይ አቀባበል ለማድረግ ወደ ‹‹አዲስ አበባ እንዳንገባ ተከልክለናል›› ባሉ ግለሰቦች በተፈጠረ ረብሻ ለ49 ሰዎች ሞት ምክንያት በመሆን ተጠርጥረዋል በተባሉ 68 ግለሰቦች ላይ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክስ ተመሠረተ፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በሦስት የክስ መዝገቦች አዘጋጅቶ ለፌዴራል ከፍተኛ…
#Update የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ ለማውጣት መረጃውን/ዳታ/ የማስገባት ሥራ #በገለልተኛ አካል እየተሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የጽሕፈት ቤት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሥራ ሂደት መሪ አቶ ጋሻው ተፈራ፣ ቀደም ሲል ዕጣ የማውጣቱ ሥራ በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ(ኢንሳ)ይሠራ እንደነበር አስታውሰው፣ አሁን ግን የግንባታው ባለቤት የሆነው የአዲስ አበባ ቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ ሥራውን ተረክቦ እየሠራ ይገኛል ብለዋል፡፡
Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአማራ ክልል...
"በአዊ ዞን እንጂባራ ከተማ በተፈጠረ የሹፌሮች አድማ የመኪና እንቅስቃሴ ከጥዋት ጀምሮ ቆሟል ወደ አዲስ አበባ፣ ባህር ዳር፣ ቻግኒ የሚሄድ ህዝብ እየተጉላላ ይገኛል።"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በአዊ ዞን እንጂባራ ከተማ በተፈጠረ የሹፌሮች አድማ የመኪና እንቅስቃሴ ከጥዋት ጀምሮ ቆሟል ወደ አዲስ አበባ፣ ባህር ዳር፣ ቻግኒ የሚሄድ ህዝብ እየተጉላላ ይገኛል።"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ብሮድካ ስት ባለስልጣን‼️
ፈቃድ ወስደው ወደ ስርጭት ያልገቡ 17 የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያዎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ካልገቡ ፍቃዳቸው እንደሚሰረዝ የብሮድካስት ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
የማይጨው ከተማና የደብረብርሀን ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ሬድዮ ፍቃድ #መሰረዙንም ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡
አክሱም ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያ ለማቋቋም የጠቅላላ ጉባኤ እና የቦርድ ምርጫ መድረክ ባለፈው ሳምንት አካሂዷል፡፡
በመድረኩ ላይ የተገኙት በባለስልጣኑ የመገናኛ ብዙሃን ምዝገባና ፈቃድ ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሲሳይ እንዳሉት በሀገሪቱ ለ50 የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያዎች ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
ፍቃድ ከወሰዱት ውስጥ 31 የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያዎች ወደ ስርጭት መግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡
የማይጨው እና የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬድዮ ፈቃድ ወስደው ከአምስት ዓመት በላይ ስርጭት ባለመጀመራቸው ፈቃደቸው መሰረዙን ገልጸዋል፡፡
ፈቃድ ወስደው እስካሁን ወደስርጭት ያልገቡ 17 የማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያዎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ወደ ስርጭት መግባት እንዳለባቸውም አቶ ሙሉጌታ አመልክተዋል፡፡
የኢሮብ፣ ኩናማ፣ ከሚሴ፣ እንጅባራ፣ ሸካ፣ ስልጤና ሌሎችን ጨምሮ 17 የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያዎች በዚህ ዓመት ስርጭት እንዲጀምሩ በመንግስት በኩል ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
ባለስልጣኑ በስልጠና፣ በአሰራርና በሙያ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የገለጹት አቶ ሙሉጌታ፣ ጣቢያዎቹ በተባለው ጊዜ ውስጥ ወደስርጭት ካልገቡ የተሰጣቸው ፍቃድ እንደሚሰርዝም አስገንዝበዋል፡፡
የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያ ለማቋቋም ከባለስልጣኑ ፈቃድ ለማገኘት የፈቃድ ጠያቂውን ማህበረሰብ ፊርማ ማሰባሰብ እንዳለበትም አመልክተዋል፡፡
”ጣቢያው ህጋዊ ተቋም መሆኑን የሚያረጋግጥና የሚተዳደርበት ህግና መመሪያ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀት እንዲሁም፣ የማሰራጫ መሳሪያዎችን አስመልክቶ ዩኒቨርሲቲው በአግባቡ የተደራጀ መረጃ ማዘጋጀት አለበት” ብለዋል፡፡
የጣቢያው የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው የተመረጡት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ጸሐየ አስመላሽ በሰጡት አስተያየት ጣቢያው ሥራውን ሲጀምር ለአካባቢው እና ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ ሆኖ እንደሚያገለግል ገልጸዋል። “በዋናነት የህብረተሰቡን ፍላጎትና ችግሮች መሰረት ያደረጉ ሥራዎች ይሰራል” ብለዋል።
የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያው የካባቢውን ባህል፣ ቋንቋ እና እምነት ከማሳደግ ባለፈ በልማት፣ ዴሞክራሲ ግንባታና መልካም አስተዳደርን በማስፈን በኩል የድርሻውን እንደሚወጣም አመልክተዋል፡፡
በተለይ ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸው የምርምር እና የማህበረሰባዊ ተኮር ሥራዎችን ለማስፋት ጣቢያው ጠቀሜታ እንዳለው ነው የገለጹት።
የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያው ከተለያዩ አካባቢዎች ልምድ በመቀመር በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደሥራ ለማስገባት እንደሚሰራም ዶክተር ጸሐዬ አመልክተዋል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፈቃድ ወስደው ወደ ስርጭት ያልገቡ 17 የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያዎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ካልገቡ ፍቃዳቸው እንደሚሰረዝ የብሮድካስት ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
የማይጨው ከተማና የደብረብርሀን ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ሬድዮ ፍቃድ #መሰረዙንም ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡
አክሱም ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያ ለማቋቋም የጠቅላላ ጉባኤ እና የቦርድ ምርጫ መድረክ ባለፈው ሳምንት አካሂዷል፡፡
በመድረኩ ላይ የተገኙት በባለስልጣኑ የመገናኛ ብዙሃን ምዝገባና ፈቃድ ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሲሳይ እንዳሉት በሀገሪቱ ለ50 የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያዎች ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
ፍቃድ ከወሰዱት ውስጥ 31 የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያዎች ወደ ስርጭት መግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡
የማይጨው እና የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬድዮ ፈቃድ ወስደው ከአምስት ዓመት በላይ ስርጭት ባለመጀመራቸው ፈቃደቸው መሰረዙን ገልጸዋል፡፡
ፈቃድ ወስደው እስካሁን ወደስርጭት ያልገቡ 17 የማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያዎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ወደ ስርጭት መግባት እንዳለባቸውም አቶ ሙሉጌታ አመልክተዋል፡፡
የኢሮብ፣ ኩናማ፣ ከሚሴ፣ እንጅባራ፣ ሸካ፣ ስልጤና ሌሎችን ጨምሮ 17 የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያዎች በዚህ ዓመት ስርጭት እንዲጀምሩ በመንግስት በኩል ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
ባለስልጣኑ በስልጠና፣ በአሰራርና በሙያ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የገለጹት አቶ ሙሉጌታ፣ ጣቢያዎቹ በተባለው ጊዜ ውስጥ ወደስርጭት ካልገቡ የተሰጣቸው ፍቃድ እንደሚሰርዝም አስገንዝበዋል፡፡
የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያ ለማቋቋም ከባለስልጣኑ ፈቃድ ለማገኘት የፈቃድ ጠያቂውን ማህበረሰብ ፊርማ ማሰባሰብ እንዳለበትም አመልክተዋል፡፡
”ጣቢያው ህጋዊ ተቋም መሆኑን የሚያረጋግጥና የሚተዳደርበት ህግና መመሪያ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀት እንዲሁም፣ የማሰራጫ መሳሪያዎችን አስመልክቶ ዩኒቨርሲቲው በአግባቡ የተደራጀ መረጃ ማዘጋጀት አለበት” ብለዋል፡፡
የጣቢያው የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው የተመረጡት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ጸሐየ አስመላሽ በሰጡት አስተያየት ጣቢያው ሥራውን ሲጀምር ለአካባቢው እና ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ ሆኖ እንደሚያገለግል ገልጸዋል። “በዋናነት የህብረተሰቡን ፍላጎትና ችግሮች መሰረት ያደረጉ ሥራዎች ይሰራል” ብለዋል።
የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያው የካባቢውን ባህል፣ ቋንቋ እና እምነት ከማሳደግ ባለፈ በልማት፣ ዴሞክራሲ ግንባታና መልካም አስተዳደርን በማስፈን በኩል የድርሻውን እንደሚወጣም አመልክተዋል፡፡
በተለይ ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸው የምርምር እና የማህበረሰባዊ ተኮር ሥራዎችን ለማስፋት ጣቢያው ጠቀሜታ እንዳለው ነው የገለጹት።
የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያው ከተለያዩ አካባቢዎች ልምድ በመቀመር በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደሥራ ለማስገባት እንደሚሰራም ዶክተር ጸሐዬ አመልክተዋል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሚመለከተው አካል...
"ከአዊ ከዳንግላ ከባህርዳር ተነስተን ወደ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለመሄ የተነሳን ተማሪዎች #እየተጉላላን ነው። የመግቢያ ጊዜ በጣም ቅርብ ነው የሚመለከተው አካል መፍትሄ እንድሰጠን እንፈልጋለን።"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ከአዊ ከዳንግላ ከባህርዳር ተነስተን ወደ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለመሄ የተነሳን ተማሪዎች #እየተጉላላን ነው። የመግቢያ ጊዜ በጣም ቅርብ ነው የሚመለከተው አካል መፍትሄ እንድሰጠን እንፈልጋለን።"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from LinkUp Addis
January 2019 issue of LinkUp Addis digital magazine. Expect the best and even more. Coming out this afternoon. @linkupaddis
Forwarded from LinkUp Addis
Linkup_January_2019.pdf
3.9 MB
#Update በሀገሪቱ እየተካሄደ ባለው ለውጥ ምክንያት የተከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለፀ። ተፎካካሪ ፓርቲዎች በዛሬው ዕለት በምርጫ ህግና በተፎካካሪ ፓርቲዎች መካከል የሚደረጉ ውይይቶች በሚመሩበት ደንብና ስርዓቶች ላይ እመከሩ ይገኛሉ። አሁን ላይ የተጀመረው ውይይትም በሀገሪቱ እየተካሄደ ባለው ለውጥ ምክንያት የተከሰቱ ችግሮች ላይ ተወያይቶ የመፍትሄ ሃሳቦችን ለማስቀምጥ የሚያስችል መሆኑን በውይይቱ የተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተናግረዋል።
Via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የአዲስ አበባን የውሃ ችግር ይፈታሉ የተባሉ ሶስት ፕሮጀክቶች በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ተጠናቀው ወደ ስራ እንደሚገቡ የመዲናዋ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታውቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አማራ ክልል‼️
በአማራ ክልል የትራፊክ ደህንነት መቆጣጠሪያ ህግን #በመቃወም የትራንስፖርት አገልግሎት #ተስተጓጉሏል፡፡
የክልሉ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ውቤ አጥናፉ ለኢዜአ እንደገለጹት የትራንስፖርት አገልግሎቱ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ተስተጓጉሏል።
በተለይም ከባህር ዳር አዊ፣ ምዕራብ ጎጃም፣ ምስራቅ ጎጃምና በእነዚህ መስመሮች ያሉ የትራንስፖርት አገልግሎት በመቋረጡ ህዝቡ መጉላላት እየደረሰበት መሆኑን ተናግረዋል።
ለአገልግሎቱ መቋረጥም ከጥር 1/2011 ዓ.ም. ጀምሮ ይተገበራል የተባለውን የ "ኤስ ኤም ኤስ" የትራፊክ ደህንነት መጠበቂያ ህግ በመቃወም እንደሆነ አመልክተዋል።
ሆኖም የቅድመ ዝግጅትና የስልጠና ስራዎች #ባለመጠናቀቃቸው ህጉን ተግባራዊ ማድረግ #እንዳልተጀመረ ጠቁመው፥ "ይህን #ሰበብ አድርጎ አገልግሎት ማቋረጥ ተቀባይነት የለውም" ብለዋል።
በህጉ ዙሪያ ለአስፈፃሚ ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠት መጀመሩን አመልክተው በቀጣይ ለአሽከርካሪዎች፣ ለባለሃብቶችና ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠርና የማሳወቅ ስራ በማከናወን እንደሚተገበር አስታውቀዋል።
ህግ የሚወጣው የአብዛኛውን የህብረተሰብ ክፍል ደህንነት ለመጠበቅ እንጂ የተወሰኑ ሰዎችን ፍላጎት ለማሟላት እንዳልሆነ ተናግረው ህጉ አሁን በሰው ህይወት እየደረሰ ያለውን አደጋ ለመቀነስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
አሁን ችግሩን ለመፍታትና አገልግሎቱን ለማስጀመር ከአሽከርካሪ ማህበራትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው ብለዋል።
የዓባይ መደበኛ ደረጃ አንድ የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ዓባይነህ ማህሪ በበኩላቸው ለትራንስፖርት አገልግሎቱ መቋረጥ ማህበሩ እውቅና እንደሌለው ገልጸዋል።
የ"ኤስ ኤም ኤስ" ህግን በሚመለከት ቀደም ሲል ውይይት ማድረጋቸውን አስታውሰው፤ ሆኖም ይተገባራል የሚል መረጃ እንደሌላቸውና ሙሉ እውቅና ያልተፈጠረበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
አሽከርካሪዎቹ አገልግሎት እንደማይሰጡ ያሳወቀ አካል እንደሌለ የገለጹት ደግሞ የዘንባባ ደረጃ ሁለት የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ በላይ አፈወርቅ ናቸው።
"ገና ይተገባራል የሚባለውን የኤስ ኤም ኤስ የቅጣት ሪከርድ ህግ ቀድሞ በመፍራት የስራ ማቆማ ተገቢ አይደለም ፤በዚህ የተነሳም ህዝብ መጉላላት የለበትም" ብለዋል።
በአማራ ክልል 61 የአሽከርካሪ ማህበራት ያሉ ሲሆን ሰባት ሺህ 300 አገልግሎት የሚሰጡ መለስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ተሽከርካሪዎች እንዳሉም ታውቋል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአማራ ክልል የትራፊክ ደህንነት መቆጣጠሪያ ህግን #በመቃወም የትራንስፖርት አገልግሎት #ተስተጓጉሏል፡፡
የክልሉ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ውቤ አጥናፉ ለኢዜአ እንደገለጹት የትራንስፖርት አገልግሎቱ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ተስተጓጉሏል።
በተለይም ከባህር ዳር አዊ፣ ምዕራብ ጎጃም፣ ምስራቅ ጎጃምና በእነዚህ መስመሮች ያሉ የትራንስፖርት አገልግሎት በመቋረጡ ህዝቡ መጉላላት እየደረሰበት መሆኑን ተናግረዋል።
ለአገልግሎቱ መቋረጥም ከጥር 1/2011 ዓ.ም. ጀምሮ ይተገበራል የተባለውን የ "ኤስ ኤም ኤስ" የትራፊክ ደህንነት መጠበቂያ ህግ በመቃወም እንደሆነ አመልክተዋል።
ሆኖም የቅድመ ዝግጅትና የስልጠና ስራዎች #ባለመጠናቀቃቸው ህጉን ተግባራዊ ማድረግ #እንዳልተጀመረ ጠቁመው፥ "ይህን #ሰበብ አድርጎ አገልግሎት ማቋረጥ ተቀባይነት የለውም" ብለዋል።
በህጉ ዙሪያ ለአስፈፃሚ ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠት መጀመሩን አመልክተው በቀጣይ ለአሽከርካሪዎች፣ ለባለሃብቶችና ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠርና የማሳወቅ ስራ በማከናወን እንደሚተገበር አስታውቀዋል።
ህግ የሚወጣው የአብዛኛውን የህብረተሰብ ክፍል ደህንነት ለመጠበቅ እንጂ የተወሰኑ ሰዎችን ፍላጎት ለማሟላት እንዳልሆነ ተናግረው ህጉ አሁን በሰው ህይወት እየደረሰ ያለውን አደጋ ለመቀነስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
አሁን ችግሩን ለመፍታትና አገልግሎቱን ለማስጀመር ከአሽከርካሪ ማህበራትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው ብለዋል።
የዓባይ መደበኛ ደረጃ አንድ የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ዓባይነህ ማህሪ በበኩላቸው ለትራንስፖርት አገልግሎቱ መቋረጥ ማህበሩ እውቅና እንደሌለው ገልጸዋል።
የ"ኤስ ኤም ኤስ" ህግን በሚመለከት ቀደም ሲል ውይይት ማድረጋቸውን አስታውሰው፤ ሆኖም ይተገባራል የሚል መረጃ እንደሌላቸውና ሙሉ እውቅና ያልተፈጠረበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
አሽከርካሪዎቹ አገልግሎት እንደማይሰጡ ያሳወቀ አካል እንደሌለ የገለጹት ደግሞ የዘንባባ ደረጃ ሁለት የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ በላይ አፈወርቅ ናቸው።
"ገና ይተገባራል የሚባለውን የኤስ ኤም ኤስ የቅጣት ሪከርድ ህግ ቀድሞ በመፍራት የስራ ማቆማ ተገቢ አይደለም ፤በዚህ የተነሳም ህዝብ መጉላላት የለበትም" ብለዋል።
በአማራ ክልል 61 የአሽከርካሪ ማህበራት ያሉ ሲሆን ሰባት ሺህ 300 አገልግሎት የሚሰጡ መለስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ተሽከርካሪዎች እንዳሉም ታውቋል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጄኔራል #ብርሃኑ_ጁላ፦
‹‹በውትድርና ዘመኔ በራስ ሕዝብ ላይ ጭካኔ የተሞላበት ዘግናኝ #ጥቃት ተፈጽሞ #ያየሁት በምዕራብ ወለጋ ነው››
‹‹ለረጅም ዓመታት በውትድርና አገልግያለሁ፣ እንዲህ ዓይነት #ጭካኔ በወለጋ ከተፈጸመው በስተቀር አይቼ #አላውቅም፤››
‹‹በምዕራብ ወለጋ የተፈጸመውን ጭካኔ በቅርቡ #በቪዲዮ ምሥል ጭምር #ታዩታላችሁ፤››
‹‹የመከላከያ ሠራዊቱ ወደ #ወለጋ ሲገባ ያገኘነው #ጉድ ዘግናኝ ነው፤››
https://telegra.ph/በውትድርና-ዘመኔ-በራስ-ሕዝብ-ላይ-ጭካኔ-የተሞላበት-ዘግናኝ-ጥቃት-ተፈጽሞ-ያየሁት-በምዕራብ-ወለጋ-ነው-01-09-2
‹‹በውትድርና ዘመኔ በራስ ሕዝብ ላይ ጭካኔ የተሞላበት ዘግናኝ #ጥቃት ተፈጽሞ #ያየሁት በምዕራብ ወለጋ ነው››
‹‹ለረጅም ዓመታት በውትድርና አገልግያለሁ፣ እንዲህ ዓይነት #ጭካኔ በወለጋ ከተፈጸመው በስተቀር አይቼ #አላውቅም፤››
‹‹በምዕራብ ወለጋ የተፈጸመውን ጭካኔ በቅርቡ #በቪዲዮ ምሥል ጭምር #ታዩታላችሁ፤››
‹‹የመከላከያ ሠራዊቱ ወደ #ወለጋ ሲገባ ያገኘነው #ጉድ ዘግናኝ ነው፤››
https://telegra.ph/በውትድርና-ዘመኔ-በራስ-ሕዝብ-ላይ-ጭካኔ-የተሞላበት-ዘግናኝ-ጥቃት-ተፈጽሞ-ያየሁት-በምዕራብ-ወለጋ-ነው-01-09-2
Telegraph
‹‹በውትድርና ዘመኔ በራስ ሕዝብ ላይ ጭካኔ የተሞላበት ዘግናኝ ጥቃት ተፈጽሞ ያየሁት በምዕራብ ወለጋ ነው››
የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ በኤርትራ ድንበር የሠፈረውን ሠራዊት የማንቀሳቀስ ተግባር እንዲቆይ ተወስኗል ብለዋል የመከላከያ ሠራዊቱን የውጭ ኃይሎች አሳንሰው እንዲገምቱት የሚያደርግ ማንቋሸሽ እንዲቆም አሳስበዋል በአሁኑ ወቅት በምዕራብ ወለጋ የተፈጠረውን ፖለታካዊ መነሻ ያለው የፀጥታ ችግር በተመለከተ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተያየታቸውን የሰጡት የጦር ኃይሎች…
ባህር ዳር🔝
ትናንት መከላከያ ሰራዊት በምዕራብ ጎንደር ዞን የፈጸመውን ግድያ #በመቃወም በባህርዳር ከተማ ሰልፍ ተደርጓል። እንዲሁም ከቤኒሻንጉል ጉምዝ እና ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው በባህርዳር የተጠለሉ ዜጎች መንግስት ይረዳቸው ዘንደ ለመጠየቅ ሰልፍ ተደርጓል።
via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትናንት መከላከያ ሰራዊት በምዕራብ ጎንደር ዞን የፈጸመውን ግድያ #በመቃወም በባህርዳር ከተማ ሰልፍ ተደርጓል። እንዲሁም ከቤኒሻንጉል ጉምዝ እና ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው በባህርዳር የተጠለሉ ዜጎች መንግስት ይረዳቸው ዘንደ ለመጠየቅ ሰልፍ ተደርጓል።
via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ገንደ ውሃ‼️
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን በገንዳ ውሃ ከተማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በትላንትናው ዕለት #በከፈቱት ተኩስ ዘጠኝ ሰዎች መሞታቸው እና 15 መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ለDW ገለጹ። ድርጊቱን በመቃወም ዛሬ ሰላማዊ ሰልፍ የወጡት የከተማይቱ ነዋሪዎች በአካባቢያቸው የሰፈረው የመከላከያ ሰራዊት ከስፍራው ለቅቆ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የመንግስት ሰራተኛ የሆኑ አንድ የዓይን እማኝ እንደተናገሩት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በነዋሪው ላይ ተኩስ የከፈቱት በነዋሪዎች ታግተው የነበሩ የሱር ኮንስትራክሽን ድርጅት ተሽከርካሪዎችን ለማስለቀቅ በሚል ነበር። “የመከላከያ ሰራዊት የእሩምታ ተኩስ ተኩሶ ጉዳት አድርሷል። ባለኝ መረጃ መሰረት ህጻናትን ጨምሮ ወደ 15 ገደማ የሚሆኑ የቆሰሉ ሲሆን የሟቾቹ ቁጥር ዘጠኝ ደርሷል” ሲሉ እኚሁ የከተማይቱ ነዋሪ ተናግረዋል።
የሞቱትም ሆነ የተጎዱ ሰዎች ወደ ገንዳ ውሃ መተማ ሪፈራል ሆስፒታል መወሰዳቸውን የሚናገሩት የዓይን እማኙ ከማቾቹ ውስጥ የስድስት ሰዎችን አስክሬን መመልከታቸውን ገልጸዋል። “እኔ ስድስት ሰዎች ተመልክቻለሁ። እስከ ምሽት ሁለት ሰዓት እስከነበርኩበት ድረስ ከገንደ ውሃ ከተማ አንዲት ህጻንን ጨምሮ ሶስት ሰዎች፣ ከኮኪት ከተማ ደግሞ ሶስት ሰዎች ነበሩ” ሲሉ እማኝነታቸውን ሰጥተዋል። ከቆሰሉት ውስጥ በእርሻ ስራ ላይ ቆይተው ሲመለሱ የነበሩ የቀን ሰራተኞች አሉበት ብለዋል።
የገንደ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች የመከላከያ ሰራዊትን እርምጃ በመቃወም ዛሬ አደባባይ ወጥተዋል። ከጠዋት እስከ እኩለ ቀን ድረስ በዘለቀው ተቃውሞ ይሰሙ ከነበሩት መፈክሮች ውስጥ “የወህሓት መከላከያ እኛን አይወክልም፤ በፍጥነት ይውጣልን”፣ “በአማራነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ይቁም” የሚሉ እንደሚገኙበት ከሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች አንዱ ተናግረዋል።
ሰልፈኞቹ ትላንት ወደ ኮኪት ከተማ እንዲወሰዱ የተደረጉት የሱር ኮንስትራክሽን ተሽከርካሪዎች ወደ ገንደ ውሃ ከተማ እንዲመለሱ እንዲደረግ እና አስፈላጊውን ማጣራት እንዲደረግባቸው መጠየቃቸውን የከተማይቱ ነዋሪ ገልጸዋል። በተቃውሞ ምክንያት ከአዘዞ እስከ መተማ የሚዘልቀውን አውራ ጎዳና መዘጋቱንም ጨምረው አስረድተዋል። ለተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ምላሽ ለመስጠት የአካባቢው አስተዳደርም ሆነ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮች በስፍራው አለመገኘታቸውንም አክለዋል።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን በገንዳ ውሃ ከተማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በትላንትናው ዕለት #በከፈቱት ተኩስ ዘጠኝ ሰዎች መሞታቸው እና 15 መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ለDW ገለጹ። ድርጊቱን በመቃወም ዛሬ ሰላማዊ ሰልፍ የወጡት የከተማይቱ ነዋሪዎች በአካባቢያቸው የሰፈረው የመከላከያ ሰራዊት ከስፍራው ለቅቆ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የመንግስት ሰራተኛ የሆኑ አንድ የዓይን እማኝ እንደተናገሩት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በነዋሪው ላይ ተኩስ የከፈቱት በነዋሪዎች ታግተው የነበሩ የሱር ኮንስትራክሽን ድርጅት ተሽከርካሪዎችን ለማስለቀቅ በሚል ነበር። “የመከላከያ ሰራዊት የእሩምታ ተኩስ ተኩሶ ጉዳት አድርሷል። ባለኝ መረጃ መሰረት ህጻናትን ጨምሮ ወደ 15 ገደማ የሚሆኑ የቆሰሉ ሲሆን የሟቾቹ ቁጥር ዘጠኝ ደርሷል” ሲሉ እኚሁ የከተማይቱ ነዋሪ ተናግረዋል።
የሞቱትም ሆነ የተጎዱ ሰዎች ወደ ገንዳ ውሃ መተማ ሪፈራል ሆስፒታል መወሰዳቸውን የሚናገሩት የዓይን እማኙ ከማቾቹ ውስጥ የስድስት ሰዎችን አስክሬን መመልከታቸውን ገልጸዋል። “እኔ ስድስት ሰዎች ተመልክቻለሁ። እስከ ምሽት ሁለት ሰዓት እስከነበርኩበት ድረስ ከገንደ ውሃ ከተማ አንዲት ህጻንን ጨምሮ ሶስት ሰዎች፣ ከኮኪት ከተማ ደግሞ ሶስት ሰዎች ነበሩ” ሲሉ እማኝነታቸውን ሰጥተዋል። ከቆሰሉት ውስጥ በእርሻ ስራ ላይ ቆይተው ሲመለሱ የነበሩ የቀን ሰራተኞች አሉበት ብለዋል።
የገንደ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች የመከላከያ ሰራዊትን እርምጃ በመቃወም ዛሬ አደባባይ ወጥተዋል። ከጠዋት እስከ እኩለ ቀን ድረስ በዘለቀው ተቃውሞ ይሰሙ ከነበሩት መፈክሮች ውስጥ “የወህሓት መከላከያ እኛን አይወክልም፤ በፍጥነት ይውጣልን”፣ “በአማራነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ይቁም” የሚሉ እንደሚገኙበት ከሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች አንዱ ተናግረዋል።
ሰልፈኞቹ ትላንት ወደ ኮኪት ከተማ እንዲወሰዱ የተደረጉት የሱር ኮንስትራክሽን ተሽከርካሪዎች ወደ ገንደ ውሃ ከተማ እንዲመለሱ እንዲደረግ እና አስፈላጊውን ማጣራት እንዲደረግባቸው መጠየቃቸውን የከተማይቱ ነዋሪ ገልጸዋል። በተቃውሞ ምክንያት ከአዘዞ እስከ መተማ የሚዘልቀውን አውራ ጎዳና መዘጋቱንም ጨምረው አስረድተዋል። ለተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ምላሽ ለመስጠት የአካባቢው አስተዳደርም ሆነ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮች በስፍራው አለመገኘታቸውንም አክለዋል።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሚ ተሸጠ‼️
ዛሚ FM 90.7 በ16 ሚሊዮን ብር #ተሽጧል። ገዥውም የናሁ ቴሌቪዥን መሆኑ ታውቋል እንዲሁም በመጪዎቹ ሁለት ወራት ውስጥ ራዲዮ ጣቢያውን ይረከባል ሲል ኳፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
"Zami FM was bought by Nahoo TV for 16 million birr. Nahoo TV will take over the Radio station after two months."
via Capital
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሚ FM 90.7 በ16 ሚሊዮን ብር #ተሽጧል። ገዥውም የናሁ ቴሌቪዥን መሆኑ ታውቋል እንዲሁም በመጪዎቹ ሁለት ወራት ውስጥ ራዲዮ ጣቢያውን ይረከባል ሲል ኳፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
"Zami FM was bought by Nahoo TV for 16 million birr. Nahoo TV will take over the Radio station after two months."
via Capital
@tsegabwolde @tikvahethiopia