The Jasiri Talent Investor is back!
We want young dreamers like you. If you believe you are a problem solver who can solve problems through high-impact entrepreneurship, then this opportunity is for you.
Don’t hesitate. Apply today!
👉 https://bit.ly/40Ai4oR
For more information @jasiri4africa
We want young dreamers like you. If you believe you are a problem solver who can solve problems through high-impact entrepreneurship, then this opportunity is for you.
Don’t hesitate. Apply today!
👉 https://bit.ly/40Ai4oR
For more information @jasiri4africa
አቢሲንያ ባንክ
4ኛ ዙር እችላለሁ! ማርች 8 እየደረሰ ነው ! ዝግጁ !
የሴቶች የሥራ ፈጠራ፣ የሙዚቃና የቲክቶክ ቪዲዮ ውድድር !
ባንካችን በየአመቱ የሚከበረውን ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8 ምክንያት በማድረግ እ.አ.አ ከማርች 3 ቀን እስከ ማርች 31 ቀን 2025 ድረስ በሁለት የተከፈሉ ውድድሮችን አዘጋጅቶ ለተሳታፊዎች ክፍት አድርጓል፡፡
1) የሙዚቃ ተሰጥዖ ውድድር
ባንካችን የሙዚቃ ተሰጥኦ ያላቸውን ሴት ተሳታፊዎችን በማወዳደር በባለሙያና በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰጥ የህዝብ ድምጽ የተለዩ አሸናፊዎችን በየደረጃው ይሸልማል፡፡ አንደኛ ለምትወጣው የብር 100,000፣ ሁለተኛ ለምትወጣው የብር 75,000 እንዲሁም ሶስተኛ ለምትወጣው የብር 50,000 ሽልማት አዘጋጅቷል።
በሙዚቃው ዘርፍ ተሰጥኦዬን ያሳያል የምትሉትን ከሶስት (3) ደቂቃ ያልበለጠ የሙዚቃ ሥራ ያለ ሙዚቃ መሣሪያና የድምፅ ማዳመጫ (Earphone) ሳይደረግ በቪዲዮ ሰርታችሁ ከዚህ በታች በተቀመጠው ቴሌግራም መላክ ይኖርባችኋል፡፡ የቴሌግራም አድራሻ------------ 0919857373
2) የቲክቶክ ቪዲዮ ተሰጥዖ ውድድር
እንዲሁም በተመረጡ ቲክቶከሮች መካከል ባንካችን ለሴት ደንበኞቻችን ያዘጋጃቸውን አደይና ዘሃራ የቁጠባ ሂሳቦችን በተለየ መንገድ የማስተዋወቅ ውድድር ይካሄዳል፡፡በዚህም ውድድር አንደኛ ለምትወጣው የብር 100,000፣ ሁለተኛ ለምትወጣው የብር 75,000 እንዲሁም ሶስተኛ ለምትወጣው የብር 50,000 ሽልማት አዘጋጅቷል።
3) የሥራ ፈጠራ ውድድር
የሴት ሥራ ፈጣሪዎችን ለማበረታት ባንኩ ባሉት ዲስትሪክቶች የሥራ ፈጣሪ ሴቶችን በመምረጥ በአነስተኛ የወለድ ምጣኔን ካለመያዣ እስከ ብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ) የብድር አገልግሎት ለመስጠት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ፍላጎቱ ያላችሁና መስፈርቶችን የምታሟሉ የሥራ ፈጣሪዎች አቅራቢያችሁ ባሉ ቅርንጫፎችና የዲስትሪክት ፅ/ቤቶች በመቅረብ ከየካቲት 19 ቀን እስከ መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓም. ባሉት ቀናት ብቻ በፁሑፍ ጥያቄያችሁን እንድታቀርቡ በአክብሮት እንጠይቃለን።
በዚህም መሠረት በመርሃ-ግብሩ መሳተፍ የምትፈልጉ ሴት ተወዳዳሪዎች አስቀድማችሁ የአቢሲንያ ባንክ የፌስቡክ ገፅን https://www.facebook.com/BoAeth/ መወዳጀት ይኖርባችኋል፡፡
ዝርዝር የብድር እንዲሁም የመወዳደሪያ መስፈርቶችን ለመመልከት ከታች የሚገኘውን የቴሌግራም ሊንክ መጠቀም የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ https://yangx.top/BoAEth
4ኛ ዙር እችላለሁ! ማርች 8 እየደረሰ ነው ! ዝግጁ !
የሴቶች የሥራ ፈጠራ፣ የሙዚቃና የቲክቶክ ቪዲዮ ውድድር !
ባንካችን በየአመቱ የሚከበረውን ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8 ምክንያት በማድረግ እ.አ.አ ከማርች 3 ቀን እስከ ማርች 31 ቀን 2025 ድረስ በሁለት የተከፈሉ ውድድሮችን አዘጋጅቶ ለተሳታፊዎች ክፍት አድርጓል፡፡
1) የሙዚቃ ተሰጥዖ ውድድር
ባንካችን የሙዚቃ ተሰጥኦ ያላቸውን ሴት ተሳታፊዎችን በማወዳደር በባለሙያና በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰጥ የህዝብ ድምጽ የተለዩ አሸናፊዎችን በየደረጃው ይሸልማል፡፡ አንደኛ ለምትወጣው የብር 100,000፣ ሁለተኛ ለምትወጣው የብር 75,000 እንዲሁም ሶስተኛ ለምትወጣው የብር 50,000 ሽልማት አዘጋጅቷል።
በሙዚቃው ዘርፍ ተሰጥኦዬን ያሳያል የምትሉትን ከሶስት (3) ደቂቃ ያልበለጠ የሙዚቃ ሥራ ያለ ሙዚቃ መሣሪያና የድምፅ ማዳመጫ (Earphone) ሳይደረግ በቪዲዮ ሰርታችሁ ከዚህ በታች በተቀመጠው ቴሌግራም መላክ ይኖርባችኋል፡፡ የቴሌግራም አድራሻ------------ 0919857373
2) የቲክቶክ ቪዲዮ ተሰጥዖ ውድድር
እንዲሁም በተመረጡ ቲክቶከሮች መካከል ባንካችን ለሴት ደንበኞቻችን ያዘጋጃቸውን አደይና ዘሃራ የቁጠባ ሂሳቦችን በተለየ መንገድ የማስተዋወቅ ውድድር ይካሄዳል፡፡በዚህም ውድድር አንደኛ ለምትወጣው የብር 100,000፣ ሁለተኛ ለምትወጣው የብር 75,000 እንዲሁም ሶስተኛ ለምትወጣው የብር 50,000 ሽልማት አዘጋጅቷል።
3) የሥራ ፈጠራ ውድድር
የሴት ሥራ ፈጣሪዎችን ለማበረታት ባንኩ ባሉት ዲስትሪክቶች የሥራ ፈጣሪ ሴቶችን በመምረጥ በአነስተኛ የወለድ ምጣኔን ካለመያዣ እስከ ብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ) የብድር አገልግሎት ለመስጠት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ፍላጎቱ ያላችሁና መስፈርቶችን የምታሟሉ የሥራ ፈጣሪዎች አቅራቢያችሁ ባሉ ቅርንጫፎችና የዲስትሪክት ፅ/ቤቶች በመቅረብ ከየካቲት 19 ቀን እስከ መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓም. ባሉት ቀናት ብቻ በፁሑፍ ጥያቄያችሁን እንድታቀርቡ በአክብሮት እንጠይቃለን።
በዚህም መሠረት በመርሃ-ግብሩ መሳተፍ የምትፈልጉ ሴት ተወዳዳሪዎች አስቀድማችሁ የአቢሲንያ ባንክ የፌስቡክ ገፅን https://www.facebook.com/BoAeth/ መወዳጀት ይኖርባችኋል፡፡
ዝርዝር የብድር እንዲሁም የመወዳደሪያ መስፈርቶችን ለመመልከት ከታች የሚገኘውን የቴሌግራም ሊንክ መጠቀም የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ https://yangx.top/BoAEth
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
“ የጤና መድን ክፍያ በሚል ማህበረሰቡ ከ3,000 ብር በላይ በግዴታ እንዲከፍል እየተደረገ ነው ” - የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች
የጤና መድን ክፍያ በሚል ማህበረሰቡ ከ3,000 ብርና ከዚያ በላይ፣ ለኮሪደር ልማት ከ500 እስከ 20 ሺሕ ብር በግዴታ እንዲከፍል እየተደረገ መሆኑን የባሕር ዳር ከተማ ነዋረዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
“ ከትንንሽ ምግብ ቤት ጀምሮ በማንኛውም የንግድ ሥራ የተሰማራ ቤተሰብ የሌለውንም ጨምሮ ነው እያስገደዱና የማይከፍለውን እያሸጉ ያሉት ” ሲሉ ገልጸዋል።
“ ከዚህ ቀደም ትዳር መስርቶ፣ ወልዶ የሚኖር ሰው አባል ሆኖ የአባልነት ክፍያ ነበር የሚከፍለው ለጤና መድን አሁን ግን ትዳር የሌላቸው በንግድ ሥራ የተሰማሩ ወጣቶችን ጭምር አባል ሳያደርጉ ብር ብቻ እያስከፈሉ ነው ” ብለዋል።
በሌላ በኩል፣ “ ለኮሪደር ልማት በሚል በማንኛውም ንግድ ሥራ የተሰማራ ሰው ተገዶ እንዲከፍል እየተደገ ነው ” ሲሉ ነዋሪዎቹ አማረዋል።
አክለውም ፦
“ ነዋሪውበኑሮ ውድነት እየተሰቃየ ነው ያለው። በአነስተኛ ንግድ የተሰማራው ነጋዴም ስራ ቆሞበታል። ምክንያቱም ተጠቃሚ የለም።
ህዝቡ ግብር ከፍሎ እንደገና ‘ለኮሪደር ልማት፣ ለጤና መድን’ ሲጨምርበት ከአቅም በላይ ሆኖበታል። ይሄ ነገር ከተጀመረ ቆይቷል። ግዳጁ አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል።
የማህበረሰቡም፣ ‘የኑሮ ውድነት ጫናው ቢኖርብንም በህግ አግባብ የተጣለብንን ግብር በሰዓቱ እየከፈልን ነው የምንሰራው። አሁን ላይ ስራ ተቀዛቅዟል። ተጨማሪ ክፍያ የመክፈል አቅም የለንም’ የሚል ቅሬታ አለው።
የኮሪደር ልማቱን ክፍያ በሚመለከት የከተማ አስተዳደሩ ከከፍተኛ ባለሀብቶች ጋር ውይይት አድርጎ ልማቱን እንደሚደግፉ ተስማምተዋል። ነገር ግን ዝቅተኛ ነጋዴዎች ተሳታፊ አልነበሩም። እነሱም ቢሆኑ ልማቱን ይደግፋሉ ነገር ግን ክፍያው አቅምን ያገናዘበ አይደለም።
በካሬታ ውሃና ሌሎች ሥራዎችን የማጓጓዝ ስራ ከሚሰሩ ልጆች ጀምሮ እስከ ቤት አከራይ ለኮሪደር ልማት መዋጮ እየተጠየቀ ነው። ዝቅተኛው 500 ብር ሲሆን፣ እስከ 20,000 ብር የተጠየቁ አሉ። 20 ሺሕ ብር አከራይ ብቻ ነው የሚከፍለው ” ሲሉ አማረዋል።
ነዋሪዎቹ ቅሬታውን ምላሽ እንዲሰጥበት የባሕርዳር ከተማ አስተዳደርን የጠቆሙ ሲሆን ምን ምላሽ እንዳላቸው የጠየቅናቸው የከተማው ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ቅሬታውን ከሰሙ በኋላ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ጤና መድን አገልግሎትን የጠየቀ ሲሆን፣ ምላሹ ሲገኝ የሚቀርብ ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የጤና መድን ክፍያ በሚል ማህበረሰቡ ከ3,000 ብርና ከዚያ በላይ፣ ለኮሪደር ልማት ከ500 እስከ 20 ሺሕ ብር በግዴታ እንዲከፍል እየተደረገ መሆኑን የባሕር ዳር ከተማ ነዋረዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
“ ከትንንሽ ምግብ ቤት ጀምሮ በማንኛውም የንግድ ሥራ የተሰማራ ቤተሰብ የሌለውንም ጨምሮ ነው እያስገደዱና የማይከፍለውን እያሸጉ ያሉት ” ሲሉ ገልጸዋል።
“ ከዚህ ቀደም ትዳር መስርቶ፣ ወልዶ የሚኖር ሰው አባል ሆኖ የአባልነት ክፍያ ነበር የሚከፍለው ለጤና መድን አሁን ግን ትዳር የሌላቸው በንግድ ሥራ የተሰማሩ ወጣቶችን ጭምር አባል ሳያደርጉ ብር ብቻ እያስከፈሉ ነው ” ብለዋል።
በሌላ በኩል፣ “ ለኮሪደር ልማት በሚል በማንኛውም ንግድ ሥራ የተሰማራ ሰው ተገዶ እንዲከፍል እየተደገ ነው ” ሲሉ ነዋሪዎቹ አማረዋል።
አክለውም ፦
“ ነዋሪውበኑሮ ውድነት እየተሰቃየ ነው ያለው። በአነስተኛ ንግድ የተሰማራው ነጋዴም ስራ ቆሞበታል። ምክንያቱም ተጠቃሚ የለም።
ህዝቡ ግብር ከፍሎ እንደገና ‘ለኮሪደር ልማት፣ ለጤና መድን’ ሲጨምርበት ከአቅም በላይ ሆኖበታል። ይሄ ነገር ከተጀመረ ቆይቷል። ግዳጁ አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል።
የማህበረሰቡም፣ ‘የኑሮ ውድነት ጫናው ቢኖርብንም በህግ አግባብ የተጣለብንን ግብር በሰዓቱ እየከፈልን ነው የምንሰራው። አሁን ላይ ስራ ተቀዛቅዟል። ተጨማሪ ክፍያ የመክፈል አቅም የለንም’ የሚል ቅሬታ አለው።
የኮሪደር ልማቱን ክፍያ በሚመለከት የከተማ አስተዳደሩ ከከፍተኛ ባለሀብቶች ጋር ውይይት አድርጎ ልማቱን እንደሚደግፉ ተስማምተዋል። ነገር ግን ዝቅተኛ ነጋዴዎች ተሳታፊ አልነበሩም። እነሱም ቢሆኑ ልማቱን ይደግፋሉ ነገር ግን ክፍያው አቅምን ያገናዘበ አይደለም።
በካሬታ ውሃና ሌሎች ሥራዎችን የማጓጓዝ ስራ ከሚሰሩ ልጆች ጀምሮ እስከ ቤት አከራይ ለኮሪደር ልማት መዋጮ እየተጠየቀ ነው። ዝቅተኛው 500 ብር ሲሆን፣ እስከ 20,000 ብር የተጠየቁ አሉ። 20 ሺሕ ብር አከራይ ብቻ ነው የሚከፍለው ” ሲሉ አማረዋል።
ነዋሪዎቹ ቅሬታውን ምላሽ እንዲሰጥበት የባሕርዳር ከተማ አስተዳደርን የጠቆሙ ሲሆን ምን ምላሽ እንዳላቸው የጠየቅናቸው የከተማው ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ቅሬታውን ከሰሙ በኋላ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ጤና መድን አገልግሎትን የጠየቀ ሲሆን፣ ምላሹ ሲገኝ የሚቀርብ ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#ነዳጅ #ቤንዚን
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተባባሰ የመጣዉን የነዳጅ ምርቶች ሕገወጥ ግብይት ለመከላከልና በየከተማዉ የሚስተዋሉ ረጃጅም ሰልፎችን በማስቀረትና የተጠቃሚዎችን ቅሬታ ለመፍታት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ።
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሳህረላ አቡዱላሂ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ በነዳጅ ምርቶች በተለይ በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ቅሬታዎች እንደሚነሱና ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ስለመኖራቸው ገልፀዋል።
" አንዱና መሠረታዊዉ ምክንያት ከዚህ ቀደም 80 በመቶ የሚሆነዉ የሀገራችንን የነዳጅ ፍጆታ ይሸፍን የነበረዉ በሱዳን ወደብ የሚገባዉ ቢሆንም አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ጅቡቲ ዞሯል " ብለዋል።
" ወደቡ ላይ ከፍተኛ መጨናነቆች ይስተዋላሉ የጅቡቲዉ ወደብ ከ20 ዓመታት በፊት የነበረን የሀገራችንን የነዳጅ ፍላጎትና አቅርቦትን ለማስተናገድ ታስቦ የተሰራ ስለነበር በቴርሚናሉ ላይ ያለዉ መጨናነቅ መንግስት በከፍተኛ ድጎማ የሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች በተለይም በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አሳድሯል " ሰሉ ገልፀዋል።
መንግስት አሁንም ድረስ ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማ በማድረግ ወደ ሀገር ዉስጥ በሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች ላይ አንዳንድ አከባቢዎች ሰዉ ሰራሽ አቅርቦት እጥረት እንዲፈጠር በማድረግ የግል ጥቅማቸዉን ለማካበት የሚጥሩ አካላት መኖራቸዉን ማረጋገጣቸውን ወ/ሮ ሰሃረላ ተናግረዋል።
በቴክኖሎጂ የታገዘ ቁጥጥርና የአሠራር ስርዓት በመዘርጋት ሕገወጥ ግብይቱን የመከላከልና በህገወጦች ላይ እርምጃ የመዉሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
" ከአቅርቦቱ ባሻገር ወደ ሀገር ዉስጥ የገባዉን ቤንዚን በአግባቡ በማሰራጨቱ በኩል በየክልሉ የተለያዩ ክፍተቶች አሉ " ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሁሉም ማዕቀፎች ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል መወሰድ በመጀመሩ በርከት ያሉ የንግድና ገበያ ልማት ባለሙያዎች ማደያዎችን ጨምሮ በሕገወጥ ግብይቱ ሰንሰለቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት ላይ በየደረጃው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አብራርተዋል።
ለአብነትም በሲዳማ ክልል ብቻ የግብይት ስርዓቱ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ በመፍጠር ሰዉ ሰራሽ እጥረት እንዲስፋፋ ያደረጉ 9 ማደያዎች ላይ ነዳጅ እንዳያገኙ እገዳ እንደተላለፈባቸው ገልፀዋል።
በሌሎችም ክልልሎች በዚህ ረገድ እየተከናወኑ ያሉ የቁጥጥርና ክትትል ተግባራት በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀዉ አዲሱ የነዳጅ ምርቶች ቁጥጥር አዋጅ ጋር ተዳምረዉ በዘርፉ የሚስተዋለዉን ችግር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንሰዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተባባሰ የመጣዉን የነዳጅ ምርቶች ሕገወጥ ግብይት ለመከላከልና በየከተማዉ የሚስተዋሉ ረጃጅም ሰልፎችን በማስቀረትና የተጠቃሚዎችን ቅሬታ ለመፍታት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ።
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሳህረላ አቡዱላሂ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ በነዳጅ ምርቶች በተለይ በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ቅሬታዎች እንደሚነሱና ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ስለመኖራቸው ገልፀዋል።
" አንዱና መሠረታዊዉ ምክንያት ከዚህ ቀደም 80 በመቶ የሚሆነዉ የሀገራችንን የነዳጅ ፍጆታ ይሸፍን የነበረዉ በሱዳን ወደብ የሚገባዉ ቢሆንም አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ጅቡቲ ዞሯል " ብለዋል።
" ወደቡ ላይ ከፍተኛ መጨናነቆች ይስተዋላሉ የጅቡቲዉ ወደብ ከ20 ዓመታት በፊት የነበረን የሀገራችንን የነዳጅ ፍላጎትና አቅርቦትን ለማስተናገድ ታስቦ የተሰራ ስለነበር በቴርሚናሉ ላይ ያለዉ መጨናነቅ መንግስት በከፍተኛ ድጎማ የሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች በተለይም በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አሳድሯል " ሰሉ ገልፀዋል።
መንግስት አሁንም ድረስ ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማ በማድረግ ወደ ሀገር ዉስጥ በሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች ላይ አንዳንድ አከባቢዎች ሰዉ ሰራሽ አቅርቦት እጥረት እንዲፈጠር በማድረግ የግል ጥቅማቸዉን ለማካበት የሚጥሩ አካላት መኖራቸዉን ማረጋገጣቸውን ወ/ሮ ሰሃረላ ተናግረዋል።
በቴክኖሎጂ የታገዘ ቁጥጥርና የአሠራር ስርዓት በመዘርጋት ሕገወጥ ግብይቱን የመከላከልና በህገወጦች ላይ እርምጃ የመዉሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
" ከአቅርቦቱ ባሻገር ወደ ሀገር ዉስጥ የገባዉን ቤንዚን በአግባቡ በማሰራጨቱ በኩል በየክልሉ የተለያዩ ክፍተቶች አሉ " ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሁሉም ማዕቀፎች ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል መወሰድ በመጀመሩ በርከት ያሉ የንግድና ገበያ ልማት ባለሙያዎች ማደያዎችን ጨምሮ በሕገወጥ ግብይቱ ሰንሰለቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት ላይ በየደረጃው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አብራርተዋል።
ለአብነትም በሲዳማ ክልል ብቻ የግብይት ስርዓቱ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ በመፍጠር ሰዉ ሰራሽ እጥረት እንዲስፋፋ ያደረጉ 9 ማደያዎች ላይ ነዳጅ እንዳያገኙ እገዳ እንደተላለፈባቸው ገልፀዋል።
በሌሎችም ክልልሎች በዚህ ረገድ እየተከናወኑ ያሉ የቁጥጥርና ክትትል ተግባራት በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀዉ አዲሱ የነዳጅ ምርቶች ቁጥጥር አዋጅ ጋር ተዳምረዉ በዘርፉ የሚስተዋለዉን ችግር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንሰዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
#Mekelle
ለመቐለ የውሃ አቅርቦት በሚውል ትራንስፎርመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት አገልግሎቱ መቋረጡን የከተማዋ የውሃና ፈሳሽ አገልግሎት ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
የተዘረፈው ትራንስፎርመር ለከተማዋ በቀን 1.9 ሚሊየን ሊትር ውሃ ከጉድጓድ እንዲመነጭ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ ነው።
ፓሊስ አደገኛ የስርቆት ተግባሩን " እያጣራሁት ነው " ብለዋል።
የትራንስፎርመር ስርቆቱ የካቲት 24/2017 ዓ.ም ሌሊት ፤ ሐድነት ክፍለ ከተማ አይናአለም ቀበሌ ልዩ ቦታ ' ሻፋት ' ነው የተፈፀመው።
ፅ/ቤቱ በትራንፎርመሩ ስርቆት ምክንያት በቀን 1.9 ሚሊየን ሊትር ውሃ የሚያመነጨው ጉድጓድ ሙሉ በሙሉ ከአገልግሎት ወጪ መሆኑ ገልጾ " ህዝቡ የውሃ አቅርቦት አገልግሎቱ እስኪመለስ እንዲታገስ " ሲል ጠይቋል።
ትራንስፎርመሩ ጨምሮ ጠቅላላ የደረሰው ወድመት ከ5 ሚሊዮን ብር ላይ ይገመታል ሲልም አክሏል።
ፖሊስ ከባድ የስርቆት ተግባሩ የቦታውን ሁለት ጥበቃዎች ላይ የአካል ጉዳት በማድረስ መፈፀሙ ጠቅሶ ፈፃሚዎቹ በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል የቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው ብሏል።
ዘራፊዎቹ በጥበቃዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረሳቸው የተነገረ ሲሆን ተጣርጣሪዎቹ ለመያዝ በሚድረገው እንቅስቃሴ የህዝቡ ተሳትፎ እና ጥቆማ እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ ፓሊስ አመልክቷል።
@tikvahethiopia
ለመቐለ የውሃ አቅርቦት በሚውል ትራንስፎርመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት አገልግሎቱ መቋረጡን የከተማዋ የውሃና ፈሳሽ አገልግሎት ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
የተዘረፈው ትራንስፎርመር ለከተማዋ በቀን 1.9 ሚሊየን ሊትር ውሃ ከጉድጓድ እንዲመነጭ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ ነው።
ፓሊስ አደገኛ የስርቆት ተግባሩን " እያጣራሁት ነው " ብለዋል።
የትራንስፎርመር ስርቆቱ የካቲት 24/2017 ዓ.ም ሌሊት ፤ ሐድነት ክፍለ ከተማ አይናአለም ቀበሌ ልዩ ቦታ ' ሻፋት ' ነው የተፈፀመው።
ፅ/ቤቱ በትራንፎርመሩ ስርቆት ምክንያት በቀን 1.9 ሚሊየን ሊትር ውሃ የሚያመነጨው ጉድጓድ ሙሉ በሙሉ ከአገልግሎት ወጪ መሆኑ ገልጾ " ህዝቡ የውሃ አቅርቦት አገልግሎቱ እስኪመለስ እንዲታገስ " ሲል ጠይቋል።
ትራንስፎርመሩ ጨምሮ ጠቅላላ የደረሰው ወድመት ከ5 ሚሊዮን ብር ላይ ይገመታል ሲልም አክሏል።
ፖሊስ ከባድ የስርቆት ተግባሩ የቦታውን ሁለት ጥበቃዎች ላይ የአካል ጉዳት በማድረስ መፈፀሙ ጠቅሶ ፈፃሚዎቹ በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል የቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው ብሏል።
ዘራፊዎቹ በጥበቃዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረሳቸው የተነገረ ሲሆን ተጣርጣሪዎቹ ለመያዝ በሚድረገው እንቅስቃሴ የህዝቡ ተሳትፎ እና ጥቆማ እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ ፓሊስ አመልክቷል።
@tikvahethiopia
#CBE የብድር ወለድ መጠኖች ላይ ጭማሪ ተደረገ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር ወለድ መጠኖች ላይ ጭማሪ አደረገ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከየካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ በተለያዩ የብድር ዓይነቶች ላይ ጭማሪ ማድረጉን አስታዉቋል።
ይህ ጭማሪ የመጣው መንግስት የፋይናንስ ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት አካል እንደሆነ ባንኩ ገልጿል።
በተደረገው ማስተካከያ መሰረት፦
➡️ የግብርና ብድሮች እስከ 15.5%፣
➡️ የንግድ ብድሮች እስከ 18%፣
➡️ የወጪ ንግድ ብድሮች እስከ 14%፣
➡️ የግል ብድሮች ደግሞ እስከ 15% ጭማሪ አሳይተዋል።
ይሁን እንጂ ለኮንዶሚኒየም መኖሪያ ቤቶች ብድሮች የወለድ ምጣኔ በ12 በመቶ እንደነበረው ይቀጥላል ተብሏል።
የውጭ ምንዛሬ የሚያቀርቡ ድርጅቶች ሰራተኞች የግል ብድሮች በስምምነቱ ውል ላይ በመመስረት ከ11 በመቶ እስከ 13 በመቶ የሚደርስ ሲሆን፣ ለየት ያለ ከፍተኛ ዋጋ ላላቸው ደንበኞች ሰራተኞች የግል ብድሮች በ12 በመቶ እንደነበረው እንደሚቀጥልም ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
(የተሻሻለውን የብድር ወለድ መጠን ከላይ ይመለክቱ)
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር ወለድ መጠኖች ላይ ጭማሪ አደረገ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከየካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ በተለያዩ የብድር ዓይነቶች ላይ ጭማሪ ማድረጉን አስታዉቋል።
ይህ ጭማሪ የመጣው መንግስት የፋይናንስ ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት አካል እንደሆነ ባንኩ ገልጿል።
በተደረገው ማስተካከያ መሰረት፦
➡️ የግብርና ብድሮች እስከ 15.5%፣
➡️ የንግድ ብድሮች እስከ 18%፣
➡️ የወጪ ንግድ ብድሮች እስከ 14%፣
➡️ የግል ብድሮች ደግሞ እስከ 15% ጭማሪ አሳይተዋል።
ይሁን እንጂ ለኮንዶሚኒየም መኖሪያ ቤቶች ብድሮች የወለድ ምጣኔ በ12 በመቶ እንደነበረው ይቀጥላል ተብሏል።
የውጭ ምንዛሬ የሚያቀርቡ ድርጅቶች ሰራተኞች የግል ብድሮች በስምምነቱ ውል ላይ በመመስረት ከ11 በመቶ እስከ 13 በመቶ የሚደርስ ሲሆን፣ ለየት ያለ ከፍተኛ ዋጋ ላላቸው ደንበኞች ሰራተኞች የግል ብድሮች በ12 በመቶ እንደነበረው እንደሚቀጥልም ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
(የተሻሻለውን የብድር ወለድ መጠን ከላይ ይመለክቱ)
@tikvahethiopia
✨🎁 የአካል ጉዳተኞች የሞባይል ጥቅል!!
ከመደበኛ ጥቅል እስከ 35% በሚደርስ ታላቅ ቅናሽ የቀረቡትን ልዩ ጥቅሎች በ *999# ወይም 999 በመደወል ያገኟቸዋል፡፡
👉 ጥቅሎቹን በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ሲገዙ ከተጨማሪ 10% ስጦታ ጋር!
🚨 ጥቅሎቹን መግዛት የሚችሉት ከአካል ጉዳተኞች ማኅበር በተላከልንን ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ ብቻ ሲሆኑ መግዛት ያልቻሉ ደንበኞች አቅራቢያቸው በሚገኝ የማኅበሩ ቅርንጫፍ መመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡
✅ ማንኛውም ሰው ጥቅሎቹን ለተመዘገበ የማኅበሩ አባል መግዛትና በስጦታ መላክ ይችላል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፡ https://bit.ly/4b0vFub
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
ከመደበኛ ጥቅል እስከ 35% በሚደርስ ታላቅ ቅናሽ የቀረቡትን ልዩ ጥቅሎች በ *999# ወይም 999 በመደወል ያገኟቸዋል፡፡
👉 ጥቅሎቹን በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ሲገዙ ከተጨማሪ 10% ስጦታ ጋር!
🚨 ጥቅሎቹን መግዛት የሚችሉት ከአካል ጉዳተኞች ማኅበር በተላከልንን ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ ብቻ ሲሆኑ መግዛት ያልቻሉ ደንበኞች አቅራቢያቸው በሚገኝ የማኅበሩ ቅርንጫፍ መመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡
✅ ማንኛውም ሰው ጥቅሎቹን ለተመዘገበ የማኅበሩ አባል መግዛትና በስጦታ መላክ ይችላል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፡ https://bit.ly/4b0vFub
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
" በ7 ወራት ውስጥ ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት ተፈጽሟል " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ባለፉት 7 ወራት፣ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ሰርቆት ተፈጽሞበታል።
በአዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት ለአገልግሎት መቋረጥ ምክንያት መሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።
የአገልግሎቱ ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ታዬ ለዶቸቨለ ሬድዮ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
የተቋማቸው ተግባር፣ የኤሌክትሪክ ሀይልን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በጅምላ ገዝቶ ለደንበኞች ማቅረብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ሆኖም፣ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሀይል መሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትልቅ ተግዳሮት እየፈጠረ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውም ጉዳት እንደዚሁ እየከፋ መምጣቱንም አመልክተዋል፡፡
በተያዘው የበጀት አመት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት መፈፀሙን አስታውቋል፡፡
በዋና ከተማ አዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በሀይል ማስተላለፊያ መስመሮች፣ በትራንስፎርመር እና በሀይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል።
እነዚህ በውጭ ምንዛሪ የሚገቡ ሀብቶች በመሆናቸው የሚያስከትለው ጉዳት ትልቅ ነው ብለዋል፡፡
የሰርቆት ድርጊቱ በአገልግሎት ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ እንዳለውም አመልክተዋል፡፡
"/በመሰረተልማቶች ላይ በሚደርሰው ጉዳት ምክንያት የሀይል አቅርቦት ሲቋረጥ፣ ተጎጅዎቹ ደንበኞች ብቻ አይደሉም ’ተቋሙም ከፍተኛ ጉዳት ያስተናግዳል " ያሉ ሲሆን " ይህ ድርጊት ከደንበኞች የምናገኘውን ገቢ ያሳጣናል፣ የወደሙትን መሰረተልማቶች መልሰን ለመጠገን የምናወጣው ወጪም ከፍተኛ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡
" የስርቆት ድርጊቱን ከመከላከል አኳያ፣ በአሁኑ ጊዜ መጠነኛ መሻሻል አለ " ያሉ ሲሆን ሆኖም አሳሳቢነቱ በመቀጠሉ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ይህን ችግር ለማስቆምና እነዚህን የሀገር ሀብቶች ከውድመት ለመታደግ ሊተባበሩ ይገባል ብለዋል።
የኤለኤክትሪክ መሰረተልማቱ እየተሰረቀ ያለው ተቀባዮች ስላሉ ነው፣ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ‘ የሚሉት አቶ መላኩ፣ መንግስትም አጥፊዎችን ለህግ በማቅረቡ በኩል እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
#DW
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ባለፉት 7 ወራት፣ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ሰርቆት ተፈጽሞበታል።
በአዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት ለአገልግሎት መቋረጥ ምክንያት መሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።
የአገልግሎቱ ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ታዬ ለዶቸቨለ ሬድዮ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
የተቋማቸው ተግባር፣ የኤሌክትሪክ ሀይልን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በጅምላ ገዝቶ ለደንበኞች ማቅረብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ሆኖም፣ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሀይል መሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትልቅ ተግዳሮት እየፈጠረ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውም ጉዳት እንደዚሁ እየከፋ መምጣቱንም አመልክተዋል፡፡
በተያዘው የበጀት አመት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት መፈፀሙን አስታውቋል፡፡
በዋና ከተማ አዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በሀይል ማስተላለፊያ መስመሮች፣ በትራንስፎርመር እና በሀይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል።
እነዚህ በውጭ ምንዛሪ የሚገቡ ሀብቶች በመሆናቸው የሚያስከትለው ጉዳት ትልቅ ነው ብለዋል፡፡
የሰርቆት ድርጊቱ በአገልግሎት ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ እንዳለውም አመልክተዋል፡፡
"/በመሰረተልማቶች ላይ በሚደርሰው ጉዳት ምክንያት የሀይል አቅርቦት ሲቋረጥ፣ ተጎጅዎቹ ደንበኞች ብቻ አይደሉም ’ተቋሙም ከፍተኛ ጉዳት ያስተናግዳል " ያሉ ሲሆን " ይህ ድርጊት ከደንበኞች የምናገኘውን ገቢ ያሳጣናል፣ የወደሙትን መሰረተልማቶች መልሰን ለመጠገን የምናወጣው ወጪም ከፍተኛ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡
" የስርቆት ድርጊቱን ከመከላከል አኳያ፣ በአሁኑ ጊዜ መጠነኛ መሻሻል አለ " ያሉ ሲሆን ሆኖም አሳሳቢነቱ በመቀጠሉ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ይህን ችግር ለማስቆምና እነዚህን የሀገር ሀብቶች ከውድመት ለመታደግ ሊተባበሩ ይገባል ብለዋል።
የኤለኤክትሪክ መሰረተልማቱ እየተሰረቀ ያለው ተቀባዮች ስላሉ ነው፣ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ‘ የሚሉት አቶ መላኩ፣ መንግስትም አጥፊዎችን ለህግ በማቅረቡ በኩል እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
#DW
@tikvahethiopia
#የአርሶአደሮችድምጽ🔈
🔴 “ ለሦስት ዓመታት ምንም የካሳ ክፍያ አልተከፈለንም፡፡ የምንመገበው አጥተን ለልመና ተዳርገናል” - አርሶ አደሮች
➡️ “ ክፍያዎቹን በተገቢው በሚፈለገው አግባብ እየከፈልን አይደለም ” - የአማራ ክልል መንገዶች ቢሮ
በደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ወረዳ ከቸና እስከ መካነ ኢየሱስ ከተማ ባለው የመንገድ ፕሮጀክት መሬት የተወሰደባቸው ወደ 40 አርሶ አደሮች ለ3 ዓመታት የካሳ ባለመከፈሉ ለልመና መዳረጋቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
አርሶ አደሮቹ ስለቅሬታቸው ምን አሉ?
“ ከቸና እስከ መካነ ኢየሱስ ከተማ ድረስ ባለው ፕሮጀክት ለተወሰደው መሬት 2014 ዓ/ም የካሳ ክፍያ ብናውቅም 40 አርሶ አደሮች ለ3 ዓመታት ካሳ አልተከፈለም፡፡
በአሰራሩ መሰረት የካሳ ክፍያ እንደወቅቱ ሁኔታ እየታዬ በየስድስት ወሩ ማሻሻያ ይደረግበታል ክፍያ ሳይፈጸም ከቆዬ። የኛ ግን ለ3 ዓመት ማሻሻያ አልተደረገበትም፡፡
ከዓመታት በፊት የተገመተው ካሳ አሁንም ባለበት ነው። ከ3 ዓመታት በፊት የነበረው የገንዘብ ዋጋ ከአሁኑ ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት አለው። ያም ሆኖ ግን ከዓመታት በፊት የነበረው ካሳም እየተከፈለን አይደለም፡፡
የመካነ ኢየሱስ ከተማ ነዋሪም ቤቱን ሽጦ እንዳይመገብ መስመር ዳር ሊፈርስ ምልክት ስለተደረገበት መሸጥ አይቻልም፡፡ የገጠሩ አርሶ አደርም የተወሰደብን መሬት የአትክልት ማምረቻ ጭምር ማሳ ነው፡፡
አርሶ አደሩ እስከ 3 ማሳ ነበረው በግራና ቀኝ መንገድ ፕሮጀክቱ የደረደበት፡፡ አርሶ አደሩ ወይ አርሶ አልተጠቀመ ወይ የካሳ ክፍያ አላገኘ፡፡ አትክልቱ እንኳ አድጎ ጥቅም እንዳይሰጥ በለጋው ተቀጭቷል ” ብለዋል።
በ2014 ዓ/ም በነበረው የካሳ ተመን መሰረት ከ200 ሺሕ እስከ 1 ሚሊዮን ብር በላይ የተገመተላቸው አርሶ አደሮች እንዳሉ ገልጸው፣ በአሁኑ የገንዘብ የመግዛት አቅም ዋጋ ተተምኖ በቶሎ ካሳው እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለምን የአርሶ አደሮቹ ካሳ በወቅቱ አልተከፈለም፣ መቼስ ይከፈላለቸዋል? ሲል የአማራ ክልል መንገዶች ባለስልጣንን ጠይቋል።
የአማራ ክልል መንገዶች ቢሮ ምን መሰለ?
“ የወሰን ማስከበር ክፍያዎች በመንግስት በጀት ከምንከፍላቸው ክፍያዎች አንዱ ነው። ግን ክፍያዎቹን በተገቢው በሚፈለገው አግባብ እየከፈልን አይደለም።
ይሄ ደግሞ የተፈጠረው ለመስሪያ ቤታችን ከመንግስት በሚለቀቀው በጀት ጋር ተያይዞ እየገጠመን ባለው የበጀት ችግር ነው።
ይሄን ችግር እናውቀዋለን። ለመፍታት እየታገልን ያለነው ነው። ስለዚህ የበጀት ችግሩ እንደተፈታልን፣ መፈታት ብቻም ሳይሆን እንደተቃለልን ቀሪ ክፍያዎችን ባለው ፕራዮሪቱ ኦርደር መሠረት እንከፍላለን ” ብሏል።
(ጉዳዩን እስከመጨረሻው የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ ለሦስት ዓመታት ምንም የካሳ ክፍያ አልተከፈለንም፡፡ የምንመገበው አጥተን ለልመና ተዳርገናል” - አርሶ አደሮች
➡️ “ ክፍያዎቹን በተገቢው በሚፈለገው አግባብ እየከፈልን አይደለም ” - የአማራ ክልል መንገዶች ቢሮ
በደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ወረዳ ከቸና እስከ መካነ ኢየሱስ ከተማ ባለው የመንገድ ፕሮጀክት መሬት የተወሰደባቸው ወደ 40 አርሶ አደሮች ለ3 ዓመታት የካሳ ባለመከፈሉ ለልመና መዳረጋቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
አርሶ አደሮቹ ስለቅሬታቸው ምን አሉ?
“ ከቸና እስከ መካነ ኢየሱስ ከተማ ድረስ ባለው ፕሮጀክት ለተወሰደው መሬት 2014 ዓ/ም የካሳ ክፍያ ብናውቅም 40 አርሶ አደሮች ለ3 ዓመታት ካሳ አልተከፈለም፡፡
በአሰራሩ መሰረት የካሳ ክፍያ እንደወቅቱ ሁኔታ እየታዬ በየስድስት ወሩ ማሻሻያ ይደረግበታል ክፍያ ሳይፈጸም ከቆዬ። የኛ ግን ለ3 ዓመት ማሻሻያ አልተደረገበትም፡፡
ከዓመታት በፊት የተገመተው ካሳ አሁንም ባለበት ነው። ከ3 ዓመታት በፊት የነበረው የገንዘብ ዋጋ ከአሁኑ ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት አለው። ያም ሆኖ ግን ከዓመታት በፊት የነበረው ካሳም እየተከፈለን አይደለም፡፡
የመካነ ኢየሱስ ከተማ ነዋሪም ቤቱን ሽጦ እንዳይመገብ መስመር ዳር ሊፈርስ ምልክት ስለተደረገበት መሸጥ አይቻልም፡፡ የገጠሩ አርሶ አደርም የተወሰደብን መሬት የአትክልት ማምረቻ ጭምር ማሳ ነው፡፡
አርሶ አደሩ እስከ 3 ማሳ ነበረው በግራና ቀኝ መንገድ ፕሮጀክቱ የደረደበት፡፡ አርሶ አደሩ ወይ አርሶ አልተጠቀመ ወይ የካሳ ክፍያ አላገኘ፡፡ አትክልቱ እንኳ አድጎ ጥቅም እንዳይሰጥ በለጋው ተቀጭቷል ” ብለዋል።
በ2014 ዓ/ም በነበረው የካሳ ተመን መሰረት ከ200 ሺሕ እስከ 1 ሚሊዮን ብር በላይ የተገመተላቸው አርሶ አደሮች እንዳሉ ገልጸው፣ በአሁኑ የገንዘብ የመግዛት አቅም ዋጋ ተተምኖ በቶሎ ካሳው እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለምን የአርሶ አደሮቹ ካሳ በወቅቱ አልተከፈለም፣ መቼስ ይከፈላለቸዋል? ሲል የአማራ ክልል መንገዶች ባለስልጣንን ጠይቋል።
የአማራ ክልል መንገዶች ቢሮ ምን መሰለ?
“ የወሰን ማስከበር ክፍያዎች በመንግስት በጀት ከምንከፍላቸው ክፍያዎች አንዱ ነው። ግን ክፍያዎቹን በተገቢው በሚፈለገው አግባብ እየከፈልን አይደለም።
ይሄ ደግሞ የተፈጠረው ለመስሪያ ቤታችን ከመንግስት በሚለቀቀው በጀት ጋር ተያይዞ እየገጠመን ባለው የበጀት ችግር ነው።
ይሄን ችግር እናውቀዋለን። ለመፍታት እየታገልን ያለነው ነው። ስለዚህ የበጀት ችግሩ እንደተፈታልን፣ መፈታት ብቻም ሳይሆን እንደተቃለልን ቀሪ ክፍያዎችን ባለው ፕራዮሪቱ ኦርደር መሠረት እንከፍላለን ” ብሏል።
(ጉዳዩን እስከመጨረሻው የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
" ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ወንዝ ላይ የጣለ ግለሰብ 500 ሺህ ብር ይቀጣል " - የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለት መከላከል ደንብ
በአዲስ አበባ ወደ ተግባር የገባው የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለት መከላከል ደንብን መተላለፍ የሚያስከትለው ቅጣት ስንት ነው ?
➡️ በባህሪው አደጋኝነት የሆነ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ በወንዝ ዳርቻ ያሰወገደ ድርጅት አንድ ሚሊዮን ብር ይቀጣል።
➡️ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ወንዝ ላይ የጣለ ግለሰብ 500 ሺህ ብር ይቀጣል።
➡️ ፍቃድ የወሰዱም ሆነ ሳይወስዱ ፍሳሽን ቀጥታ በወንዞች ዳርቻ ሲያስወግዱ ቢገኙ 100 ሺህ ብር ይቀጣሉ።
➡️ በወንዝ ዳርቻና አካባቢ መጸዳዳት ሁለት ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ የፈሳሽ ማጣሪያ ሳይኖር በወንዝ ዳርቻና አካባቢ ተሽከርካሪ ማጠብ 400 ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ እንስሳትን ማሰማራት፣ ማስገባት ከተፈቀደው ውጪ ተሽከርካሪ ማሽከርከር 30 ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ ለመዝናኛ፣ ለመናፈሻና ለፖርክ ከተፈቀደ ውጪ ግንባታ መገንባት 200 ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ ከአምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ማንኛውም ያልታከመ ቆሻሻ መልቀቅ 300 ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ ኬሚካል ነክ ቆሻሻዎችን የማከሚያ ዘዴ ሳይጠቀም የለቀቀ ግለሰብ 50 ሺህ፤ ድርጅት 300 ሺህ ብር ይቀጣሉ።
➡️ ማንኛውም በካይ ቆሻሻ ከተፈቀደ የፈሳሽ ማጠራቀሚያ ውጪ ያፈሰስ ግለስብ 50 ሺህ ፤ ድርጅት 400 ሺህ ብር ይቀጣል።
➡️ የአትክልትና ፍራፍሬ ተረፈ ምርቶችን በወንዝ ዳርቻ ማስወገድ ግለሰብ 20 ሺህ፣ ድርጅት 100 ሺህ ይቀጣሉ።
➡️ ዘይት፣ ጨዋማ ፈሳሽ፣የሞተር ዘይት፣ ነዳጅ ሳሙና ነክ ነገሮችን በወንዝ ዳርቻ ያስወገደ 400 ሺህ ብር ይቀጣል።
➡️ ማንኛውም ያልተጣራ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ ግለሰብ 150 ሺህ ድርጀት 300 ሺህ ይቀጣል።
➡️ ፍቃድ ሳይሰጠው ያልታከመ ቆሻሻን ወደ ወንዝ ያስወገደ ግለሰብ 15 ሺህ ብር ድርጅት 40 ሺህ ብር ይቀጣል።
(የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት)
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ወደ ተግባር የገባው የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለት መከላከል ደንብን መተላለፍ የሚያስከትለው ቅጣት ስንት ነው ?
➡️ በባህሪው አደጋኝነት የሆነ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ በወንዝ ዳርቻ ያሰወገደ ድርጅት አንድ ሚሊዮን ብር ይቀጣል።
➡️ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ወንዝ ላይ የጣለ ግለሰብ 500 ሺህ ብር ይቀጣል።
➡️ ፍቃድ የወሰዱም ሆነ ሳይወስዱ ፍሳሽን ቀጥታ በወንዞች ዳርቻ ሲያስወግዱ ቢገኙ 100 ሺህ ብር ይቀጣሉ።
➡️ በወንዝ ዳርቻና አካባቢ መጸዳዳት ሁለት ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ የፈሳሽ ማጣሪያ ሳይኖር በወንዝ ዳርቻና አካባቢ ተሽከርካሪ ማጠብ 400 ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ እንስሳትን ማሰማራት፣ ማስገባት ከተፈቀደው ውጪ ተሽከርካሪ ማሽከርከር 30 ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ ለመዝናኛ፣ ለመናፈሻና ለፖርክ ከተፈቀደ ውጪ ግንባታ መገንባት 200 ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ ከአምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ማንኛውም ያልታከመ ቆሻሻ መልቀቅ 300 ሺህ ብር ያስቀጣል።
➡️ ኬሚካል ነክ ቆሻሻዎችን የማከሚያ ዘዴ ሳይጠቀም የለቀቀ ግለሰብ 50 ሺህ፤ ድርጅት 300 ሺህ ብር ይቀጣሉ።
➡️ ማንኛውም በካይ ቆሻሻ ከተፈቀደ የፈሳሽ ማጠራቀሚያ ውጪ ያፈሰስ ግለስብ 50 ሺህ ፤ ድርጅት 400 ሺህ ብር ይቀጣል።
➡️ የአትክልትና ፍራፍሬ ተረፈ ምርቶችን በወንዝ ዳርቻ ማስወገድ ግለሰብ 20 ሺህ፣ ድርጅት 100 ሺህ ይቀጣሉ።
➡️ ዘይት፣ ጨዋማ ፈሳሽ፣የሞተር ዘይት፣ ነዳጅ ሳሙና ነክ ነገሮችን በወንዝ ዳርቻ ያስወገደ 400 ሺህ ብር ይቀጣል።
➡️ ማንኛውም ያልተጣራ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ ግለሰብ 150 ሺህ ድርጀት 300 ሺህ ይቀጣል።
➡️ ፍቃድ ሳይሰጠው ያልታከመ ቆሻሻን ወደ ወንዝ ያስወገደ ግለሰብ 15 ሺህ ብር ድርጅት 40 ሺህ ብር ይቀጣል።
(የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት)
@tikvahethiopia