TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መሪዎች በምን ጉዳዮች ላይ መከሩ ፤ ምንስ ተስማሙ ? የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ በአዲስ አበባ የሁለትዮሽ ምክክር አድርገዋል። ከውይይቱ በኃላ የጋራ መግለጫ ወጥቷል። ምን ተባለ ? - በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። - በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ያለውን ወንድማማችነትና ግንኙነት በማጠናከር…
#Ethiopia #Somalia

የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ለአንድ ቀን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ትላንት አዲስ አበባ የገቡት የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ወደ ሀገራቸው ሲመለሱም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው ሸኝተዋቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በይፋዊ ጉብኝታቸው ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቶቻችንን ለማጠናከር ውጤታማ ውይይቶች አድርገናል " ብለዋል።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
ቅዳሜ ጥር 10 ከረፋዱ 4:30 ቀጣይ ዙር የጥያቄ እና መልስ ውድድር በቴሌግራም ቻናላችን ላይ ይደረጋል። በየሳምንቱ አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀልና ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ 👇
https://yangx.top/BoAEth

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#Telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በአቢሲንያ የቨርቹዋል ባንኪንግ ማዕከሎች የATM ካርድ በቆማችሁበት በሰከንዶች ውስጥ ማግኘት ትችላላችሁ።

#Banking #BanksinEthiopia  #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#EthiopianAirlines🇪🇹

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ቦይንግ 777F እቃ ጫኝ አውሮፕላን መረከቡን ገልጿል።

ይህ አውሮፕላን የካርጎ ጭነት አገልግሎት አድማስን ለማሳደግ የራሱ አስተዋፅዖ ከማበርከቱ በተጨማሪ እያደገ የመጣውን የካርጎ አገልግሎት ለማስተናገድ የራሱ አስተዋፅዖ ይኖረዋል ብሏል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ያለውን የላቀ የአየር እቃ ጭነት አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።

አሁን የገባው አዲስ የካርጎ አውሮፕላን አየር መንገዱ ማህበራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ረገድ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን የሚያግዙና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ ተቋማት የሚለገሱ ቁሳቁሶችን ወደ ሀገር ውስጥ ይዞ መምጣቱ ተገልጿል።

#Ethiopia🇪🇹

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Ethiopia

ግምሩክ ኮሚሽን አምራቾች ወደ አገር ዉስጥ እቃዎችን ሲያስገቡ በሚያቀርቡት ህጋዊ የግብይት ዋጋ ብቻ እንዲስተናገዱ ፈቅዷል።

ኮሚሽኑ በአምራቾች ወደ አገር ዉስጥ የሚገቡ ዕቃዎች የዋጋ አተማመን ስርዓት ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታውቋል።

158/2011 የተደነገገውን በጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ዋጋ አተማመን መመሪያ እንዲከለስ ማድረጉን ነዉ የተገለጸው።

ይህ መመሪያ በአምራቾች ወደ አገር የሚገቡ ዕቃዎች ዋጋ በሚወስንበት ወቅት የሚወስደው ጊዜ ከአምራቾች ከፍተኛ ቅሬታ እያስነሳ ይገኛል።

ይሄን ተከትሎ በአምራቾች ወደ አገር የሚገቡ ዕቃዎች ዋጋ አተማመን ሥርዓት ላይ ማሻሻያ ማድረግ ማስፈለጉን ተነግሯል።

መመሪያ ቁጥር 158/2011 እስኪሻሻል ድረስ በክሊራንስ ጊዜ የዋጋ ማጣራት ሃደቱ የሚወስደውን ጊዜ ለማስቀረት በሚል አምራቾች እቃዎችን ወደ አገር ውስጥ ሲያስገቡ በሚያቀርቡት ህጋዊ የግብይት ዋጋ እንዲስተናገዱ ኮሚሽኑ በላከው ሰርኩላር ፈቅዷል።

ይህ ሰርኩላር ፦
- አምራቾች
- ልዩ መብት የተሰጣቸው የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ፕሮግራም ተጠቃሚ ድርጅቶች፥
- ለኢንቨስትመንት ሥራ ዕቃዎችን በቀረጥ ነፃ የሚያስገቡ ድርጅቶች፤
- የመንግስት ፕሮጀክትን ለመስራት በግል ድርጅቶች የሚገቡ ዕቃዎች፣
- የመንግስት የልማት ድርጅቶች እና የፌዴራልና የክልል መንግስታት ተቋማትን ይመለከታል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካቲፓል ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia
ብልህ ለራሱ ያውቃል ... በአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ ህይወትን ቀለል አድርጎ ይመራል።#Banking #BanksinEthiopia  #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#AU #Ethiopia

46ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ የአስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ዛሬ ተጀምሯል።

በዚህም ዛሬ በተካሄደው ምርጫ #ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #Somalia ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የ #AUSSOM ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳወቀ። በመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በሶማሊያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጉ ተነግሯል። ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባሰራጨው መረጃ ፥ የልዑካን ቡድኑ ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ማህሙድ ጋር ውጤታማ ውይይት…
#Ethiopia 🤝 #Somalia

በሶማሊያ በሁለትዮሽ ስምምነት መሠረት ተሰማርቶ የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሁኔታን በተመለከተ አሠራር ለመዘርጋት የሁለቱ አገራት የጦር አዛዦች ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

በኢትዮጵያው መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና በሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ኃይሎች የመከላከያ ሠራዊት አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ኦዳዋ ዩሱፍ ራጌ መካከል የተደረሰው ስምምነት በሶማሊያ ያለው የኢትዮጵያ ጦር ስምሪትን፣ እንቅስቃሴዎችን እንዲሁም አጠቃላይ ክንዋኔዎች የሚመለከተውን 'ስታተስ ኦፍ ፎርስ አግሪመንት' ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ነው።

አንዲት አገር ጦሯን በሌላ ውጭ አገር በምታሰማራበት ወቅት የጦሩ ስምሪት፣ ተግባራት፣ ኃላፊነት፣ መብቶችን የሚመለከተው በአገራቱ መካከል የሚደረስ አሳሪ (ሕጋዊ ስምምነት) ስታተስ ኦፍ ፎርስ አግሪመንት ይሰኛል።

ይህ 'ስታተስ ኦፍ ፎርስ' ስምምነት በአውሮፓውያኑ 2023 በአገራቱ መካከል የተፈረመው የመከላከያ ትብብር የመግባቢያ ስምምነት ዋና አካል እንደሚሆን ተነግሯል።

በፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የሚመራ ልዑክ በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ የካቲት 15/2017 ዓ.ም. ባደረገው የአንድ ቀን ይፋዊ ጉብኝት ይህንን ስምምነት ጨምሮ ከአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በሶማሊያ እና በቀጠናው ሰላም፣ ደኅንነት፣ ፀጥታ እና የመረጋጋት ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

ሁለቱ የጦር አዛዦች የአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ (ኤዩሶም) ጅማሮ አድንቀው ከዚህ ቀደም በነበረው የአፍሪካ ኅብረት የሰላም እና የፀጥታው ምክር ቤት አትሚስ ስኬቶች ማስቀጠል አስፈላጊ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል በኤዩሶም ስምሪት ላይ እንዲካተት የጦር አዛዦቹ በዚህ ወቅት ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።

በሶማሊያ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው ውዝግብ በአንካራ ስምምነት መፈታቱን ተከትሎ ሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደሮችን በአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ (ኤዩሶም) ውስጥ ላለማካተት አሳልፋው የነበረውን ውሳኔ ልትቀለብስ እና በተልዕኮው ለማካተት እያጤነች እንደሆነ ከዚህ ቀደም ተዘግቦ ነበር።


#SomaliaNationalTV #BBCAMAHRIC

@tikvahethiopia
ወደ አቢሲንያ ፖስ ማሽን ስልክዎን ጠጋ ብቻ በማድረግ ይክፈሉ !
ፈጣንና አስተማማኝ የሆኑት የአቢሲንያ ባንክ ፖስ ማሽኖች ሁሉንም የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርዶች የሚቀበሉ ከመሆናቸውም በተጨማሪ የተለያዩ የዲጂታል የክፍያ አማራጮችን ያስተናግዳሉ። እርስዎ ብቻ ይፈልጉን - በየቦታው አለን! የሁሉም ምርጫ መሆናችን በምክንያት ነው!
#BankOfAbysinia #POSMachine #DigitalPayments #CashlessTransactions
#BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#Ethiopia #Somalia

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ረፋድ በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።

ሁለቱ ሀገራት ገብተውበት ከነበረው የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ውጥረት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ መሆኑ ነው።

የሶማሊያው ፕሬዚደንት ሐሰን ሼክ መሐሙድም ቱርክ ሁለቱን ሀገራት አንካራ ላይ ካስማማች በኋላ ባለፈው ጥር 3 ቀን አዲስ አበባን ጎብኝተዋል።

አስከትለውም በአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ታድመው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ተነጋግረዋል።

በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በጋራ በወጣው መግለጫ " ይህ ጉብኝት ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ የተደረጉ ተከታታይ ግንኙነቶችን የተከተለ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነትም ወደ መደበኛ ሁኔታ የሚመልስ ነው " ብሏል።

ሁለቱ መሪዎች ለጋራ ጥቅም ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን ስለማረጋገጣቸው እና በዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትብብር " መተማመንን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል " ተብሏል።

የዚህ ጉብኝት እንደምታን በሚመለከት ቃላቸውን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ የሰጡት ፤ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት የአፍሪካ ጉዳዮች የሥራ ክፍል ኃላፊ እና ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ግዛቸው አስራት ፥ ሁለቱ ሀገራት መተማመን በሚያስችል ሁኔታ መነጋገር የሚችሉበት ዕድል እንደሚሆን ገልፀዋል።

" የቴክኒክ ቡድኑ (የአንካራ ስምምነት) ከሁለት ሳምንት በፊት አንካራ ላይ ተገናኝቶ ሲነጋገር ተመልክተናል። መስማማቶች እና መግባባቶች ላይ የደረሱበት፣ መተማመን በሚያስችል ሁኔታ ንግግሮች እያደረጉ ያሉበት ሂደት ነው " ብለዋል።

" የቱርክ መንግሥት አካባቢውን ካላስፈላጊ ውጥረት ታድጓል "  ያሉት ተመራማሪው እንዲህ ያሉ መልካም ልምዶች በዚህ ቀጣና ብዙም አይታዩም ብለዋል። ይህን መሳይ የውይይት፣ የድርድር እና የሰላም መንገዶች ሲታዩ ማመስገን ያስፈልጋል ብለዋል። 

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የጋራ ጥቅሞችን በማሳደግ፣ ሰላምና ደህንነትን በማስፈን እና የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በማጠናከር ለዜጎቻቸውና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውም ጉብኝቱን ተከትሎ በወጣው የጋራ መግለጫ ላይ ተጠቅሷል።

ዶክተር ግዛቸው አስራት " ቀጣናዊ ትብብርን " የተመለከቱ ውይይቶች እንደሚኖሩ ገልፀዋል።

የዛሬውን ጉብኝት በሚመለከት አስቀድመው የወጡ ዘገባዎች ሞቃዲሾ ውስጥ ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ መደረጉን ያመለክታሉ።
#DW

@TIKVAHETHIOPIA
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዓድዋ እንኳን ለ129ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ ! " ዓድዋ ዛሬ ናት ዓድዋ ትናንት መቼ ተነሱና የወዳደቁት ምስጋና ለእነርሱ ለዓድዋ ጀግኖች ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች የጥቁር ድል አምባ ዓድዋ አፍሪካ እምዬ #ኢትዮጵያ ተናገሪ የድል ታሪክሽን አውሪ !!  " - ጂጂ መልካም የድል በዓል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ !! @tikvahethiopia
#ዓድዋ129

ዛሬ የካቲት 23 መላ የኢትዮጵያ ህዝብና ጀግኖች አርበኞች በአንድነት የኢጣሊያንን ቅኝ ገዢ ጦር ዓድዋ ላይ ድል ያደረጉበት በዓል እየተከበረ ይገኛል።

ንጉሰ ነገስት አፄ ሚኒልክ የመሯቸዉ ኢትዮጵያዉን ጀግኖች ኢትዮጵያን የወረረ ጠላታቸዉን ዓድዋ ላይ መትተዉ አሳፍረዉ፣ አዋርደው ፣ አንገት አስደፍተው የመለሱት ልክ በዛሬው ዕለት ከ129 ዓመታት በፊት ነበር።

#ዓድዋ
#የመላአፍሪካውያንድል
#Ethiopia

@tikvahethiopia