“ብዙ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ይኖራሉ። ነገር ግን ሁሉም ነገር በትክክል ከተካሄደ ሊበቃን ይችላል” - ምክትል ኮሚሽነር ሒሩት ገብረ ሥላሴ
ከቀናት በፊት አንድ አመት ተጨማሪ የሥራ ጊዜ በፓርላማ የተሰጠው የ3 አመታት የሥራ ዘመኑን ነገ ይጠናቅቅ የነበረው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ3 አመታት ክንውንና የቀጣይ አቅጣጫውን በተመለከተ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥቷል።
በዚህም ኮሚሽኑ የተሰጠው ተጨማሪ ጊዜ በቂ ነው? አጠቃላይ ሥራውስ መቼ ይጠናቀቃል? በሚል ከጋዜጠኞች ለቀረላቸው ጥያቄ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረ ስላሴ፣ “ብዙ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ይኖራሉ። ነገር ግን ሁሉም ነገር በትክክል ከተካሄደ ሊበቃን ይችላል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
"ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች አሉ” ያሉት፣ ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ይህን ይበሉ እንጂ ከቁጥጥር ውጪ ስለሆኑ ነገሮችን በዝርዝር አልገለጹም።
11 ኮሚሽነሮች እንዳሉና ሥራውን ተባብሮ ለመስራት እንደሚቻል ገልጸው፣ "ተጨማሪ አንዳንድ ሥራዎችን የሚያቃልሉ ነገሮች በመንግስትም ሆነ በሌሎች ከተፈጠሩልን ስራችንን ያጣድፋል" ብለዋል።
“ምክክር በዚህ ሰዓት ውስጥ ተመካክራችሁ በዚህ ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ስጡ የሚባልበት አይደለም። ህዝቦች ቁጭ ብለው ጊዜ ውስደው ተመካክረው የሚወሰኑት ሂደት ስለሆነ በቀላሉ የሚወሰኑ አጀንዳዎች ይኖራሉ። ጊዜ የሚፈጁም ሊኖሩ ይችላሉ” ሲሉም አስረድተዋል።
አክለው፣ “በዚህ ምክንያት በትክክል በዚህ ጊዜ ውስጥ ያልቃል ለማለት ያስቸግራል” ብለው፣ ሆኖም ግን ኮሚሽኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥራውን ለመጨረስ ጥረት እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
የተወሰኑ ፓርቲዎች ባልተሳተፉበት የምክክሩ ሂደቱ ሙሉ ይሆናል? በሚል ለቀረበው ጥያቄም፣ ፓርቲዎች በምክክሩ እንዲሳተፉ ጥረት መደረጉን ገልጸው፣ “ዳተኛ ሆነው” ያልገቡት እንዲገቡ ደግሞ ንግግር እንደተደረገ፣ አሁንም ጥረቱ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።
ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በበኩላቸው፣ በመግለጫው ባደረጉት ንግግር በሕጋዊ ከተመዘገቡ ወደ 70 ፓርቲዎች 57 የሚሆኑት ከኮሚሽኑ ጋር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ከታጣቂዎች ጋር ንግግር ተደርጎ እንደሆን ከጋዜጠኞች ጥያቄ ቀርቦላቸው በሰጡት ማብራሪያ ዋና ኮሚሽነሩ፣ የፋኖ ታጣቂዎችን እንዳነጋገሩ፣ “ሊከፋፍለን ነው” በሚል ስማቸው እንደሚነሳ አስታውሰው ተከታዩን ብለዋል።
ምን አሉ?
“ሀገራዊ ምክክሩ ማንንም መከፋፈል አይመኝም። የሚመኘው፣ መደረግ አለበት ብሎ የሚያምነውም ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን ነው።
እኔ ፋኖ መሆናቸውን አላውቅም አንድ ታጣቂ ቡድን ራሳቸው ደውለውልኝ ‘የምክክር ኮሚሽኑን ሥራ ተገንዝበናል። ‘በዚህ መሠረት ወደ ትግሉ የገባንበትን አጀንዳ ወደ እናንተ አምጥተን ወደ ውይይት የሚቀርብ ከሆነ መሳሪያችንን ለማስቀመጥ ዝግጁ ነን’ የሚል በቀጥታ በግሌ አቅርበውልኛል። ይሄን ሰው በተደጋጋሚ አግኝተዋለሁ።
እዛ ላሉትም የደኅንነት፣ አካላት በስልክ አግኝቼ እነዚህ ሰዎች በአግባቡ መሠረት ሰላማዊ ጥበቃ ተደርጎላቸው አጀንዳቸውን የሚያመጡበት መንገድ እንዲመቻች ይሄን አስተላልፌያለሁ።
ይህን ሳደርግ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በማሳወቅ ነው። እንጂ የፋኖ ናቸው ብዬ የተናገርኩት አንድም የለም” ብለዋል።
በሌላ በኩል በዛሬው መግለጫ የኮሚሽኑ የ3 አመታት ክንውኖች በኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን፣ ይህንኑ ሪፓርት ከቀናት በፊት አድርሰናችሁ ነበር።
(ተጨማሪ ዘገባ በቀጣይ የምናቀርብ ይህናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከቀናት በፊት አንድ አመት ተጨማሪ የሥራ ጊዜ በፓርላማ የተሰጠው የ3 አመታት የሥራ ዘመኑን ነገ ይጠናቅቅ የነበረው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ3 አመታት ክንውንና የቀጣይ አቅጣጫውን በተመለከተ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥቷል።
በዚህም ኮሚሽኑ የተሰጠው ተጨማሪ ጊዜ በቂ ነው? አጠቃላይ ሥራውስ መቼ ይጠናቀቃል? በሚል ከጋዜጠኞች ለቀረላቸው ጥያቄ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረ ስላሴ፣ “ብዙ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ይኖራሉ። ነገር ግን ሁሉም ነገር በትክክል ከተካሄደ ሊበቃን ይችላል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
"ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች አሉ” ያሉት፣ ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ይህን ይበሉ እንጂ ከቁጥጥር ውጪ ስለሆኑ ነገሮችን በዝርዝር አልገለጹም።
11 ኮሚሽነሮች እንዳሉና ሥራውን ተባብሮ ለመስራት እንደሚቻል ገልጸው፣ "ተጨማሪ አንዳንድ ሥራዎችን የሚያቃልሉ ነገሮች በመንግስትም ሆነ በሌሎች ከተፈጠሩልን ስራችንን ያጣድፋል" ብለዋል።
“ምክክር በዚህ ሰዓት ውስጥ ተመካክራችሁ በዚህ ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ስጡ የሚባልበት አይደለም። ህዝቦች ቁጭ ብለው ጊዜ ውስደው ተመካክረው የሚወሰኑት ሂደት ስለሆነ በቀላሉ የሚወሰኑ አጀንዳዎች ይኖራሉ። ጊዜ የሚፈጁም ሊኖሩ ይችላሉ” ሲሉም አስረድተዋል።
አክለው፣ “በዚህ ምክንያት በትክክል በዚህ ጊዜ ውስጥ ያልቃል ለማለት ያስቸግራል” ብለው፣ ሆኖም ግን ኮሚሽኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥራውን ለመጨረስ ጥረት እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
የተወሰኑ ፓርቲዎች ባልተሳተፉበት የምክክሩ ሂደቱ ሙሉ ይሆናል? በሚል ለቀረበው ጥያቄም፣ ፓርቲዎች በምክክሩ እንዲሳተፉ ጥረት መደረጉን ገልጸው፣ “ዳተኛ ሆነው” ያልገቡት እንዲገቡ ደግሞ ንግግር እንደተደረገ፣ አሁንም ጥረቱ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።
ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በበኩላቸው፣ በመግለጫው ባደረጉት ንግግር በሕጋዊ ከተመዘገቡ ወደ 70 ፓርቲዎች 57 የሚሆኑት ከኮሚሽኑ ጋር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ከታጣቂዎች ጋር ንግግር ተደርጎ እንደሆን ከጋዜጠኞች ጥያቄ ቀርቦላቸው በሰጡት ማብራሪያ ዋና ኮሚሽነሩ፣ የፋኖ ታጣቂዎችን እንዳነጋገሩ፣ “ሊከፋፍለን ነው” በሚል ስማቸው እንደሚነሳ አስታውሰው ተከታዩን ብለዋል።
ምን አሉ?
“ሀገራዊ ምክክሩ ማንንም መከፋፈል አይመኝም። የሚመኘው፣ መደረግ አለበት ብሎ የሚያምነውም ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን ነው።
እኔ ፋኖ መሆናቸውን አላውቅም አንድ ታጣቂ ቡድን ራሳቸው ደውለውልኝ ‘የምክክር ኮሚሽኑን ሥራ ተገንዝበናል። ‘በዚህ መሠረት ወደ ትግሉ የገባንበትን አጀንዳ ወደ እናንተ አምጥተን ወደ ውይይት የሚቀርብ ከሆነ መሳሪያችንን ለማስቀመጥ ዝግጁ ነን’ የሚል በቀጥታ በግሌ አቅርበውልኛል። ይሄን ሰው በተደጋጋሚ አግኝተዋለሁ።
እዛ ላሉትም የደኅንነት፣ አካላት በስልክ አግኝቼ እነዚህ ሰዎች በአግባቡ መሠረት ሰላማዊ ጥበቃ ተደርጎላቸው አጀንዳቸውን የሚያመጡበት መንገድ እንዲመቻች ይሄን አስተላልፌያለሁ።
ይህን ሳደርግ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በማሳወቅ ነው። እንጂ የፋኖ ናቸው ብዬ የተናገርኩት አንድም የለም” ብለዋል።
በሌላ በኩል በዛሬው መግለጫ የኮሚሽኑ የ3 አመታት ክንውኖች በኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን፣ ይህንኑ ሪፓርት ከቀናት በፊት አድርሰናችሁ ነበር።
(ተጨማሪ ዘገባ በቀጣይ የምናቀርብ ይህናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#DStvEthiopia
የሳምንቱ ምርጥ ጨዋታ !
ማን ሲቲ በኢመሬትስ ስታዲዩም ከሊቨርፑል ጋር ይጫወታል!
⚽️ ከ60 ጨዋታዎች 26ቱን ሊቨርፑል ሲያሸነፍ 12ቱን ማን ሲቲ ድል ማረግ ችሏል! 22 ጨዋታዎችም አቻ ወጥተዋል!
61ኛውን ጨዋታዎቸውን የሚያደርጉት ሁለቱ ቡድኖች ማን 3 ነጥብ ማሸነፍ ይችላል?
🏆 ሊቨርፑል ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ማስፋት ይችላል?
👉 ይህንን ድንቅ ፍልሚያ ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።
🎊 እስከ መጋቢት 22 ባሉት ቀናት አሁን ካሉበት ጎጆ ፓኬጅ የቀጣዩን ቤተሰብ ፓኬጅ፣ የአንድ ወር ሙሉ ክፍያ ሲከፍሉ፣ ዲኤስቲቪ ደግሞ የሜዳ ፓኬጅን ፓኬጅ በነፃ ከፍ ያደርጎታል
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
የሳምንቱ ምርጥ ጨዋታ !
ማን ሲቲ በኢመሬትስ ስታዲዩም ከሊቨርፑል ጋር ይጫወታል!
⚽️ ከ60 ጨዋታዎች 26ቱን ሊቨርፑል ሲያሸነፍ 12ቱን ማን ሲቲ ድል ማረግ ችሏል! 22 ጨዋታዎችም አቻ ወጥተዋል!
61ኛውን ጨዋታዎቸውን የሚያደርጉት ሁለቱ ቡድኖች ማን 3 ነጥብ ማሸነፍ ይችላል?
🏆 ሊቨርፑል ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ማስፋት ይችላል?
👉 ይህንን ድንቅ ፍልሚያ ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።
🎊 እስከ መጋቢት 22 ባሉት ቀናት አሁን ካሉበት ጎጆ ፓኬጅ የቀጣዩን ቤተሰብ ፓኬጅ፣ የአንድ ወር ሙሉ ክፍያ ሲከፍሉ፣ ዲኤስቲቪ ደግሞ የሜዳ ፓኬጅን ፓኬጅ በነፃ ከፍ ያደርጎታል
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
#Tigray
ትናንተ የካቲት 12 /2017 ዓ.ም በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ በነዋሪዎችና በአከባቢው በሚገኘው የትግራይ ኃይል አባላት መካከል ግጭት ተከስተዋል።
በግጭቱ ምክንያት በ20 የቀበሌው ነዋሪዎችና ቁጥራቸው ባልታወቀ የትግራይ ኃይል አባላት ላይ ጉዳት ደርሷል።
ያጋጠመ ሞት የለም።
ግጭቱ እንዴት እና በምን ምክንያት አጋጠመ ?
በአዲስ አለም ቀበሌ ሁለት አስተዳዳሪዎች አሉ። አንዱ የቆየ ሲሆን ሌላው ደግሞ በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሾመ ነው።
ሁለቱም ማህተም ይዘው በየፊናቸው " እኔ ነኝ ህጋዊ የቀበሌው አስተዳደር " በማለት ህዝቡን ለሁለት መክፈላቸው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
ከዚህ ጋር በተያያዘ " ህዝቡ አማርሮ እንድንታደገው ጠይቆናል አዛዦቻችንም ይህንን እንድንፈፅም ልከውናል" ያሉ 9 የሰራዊት አባላት ወደ ቀበሌው ደርሰው ሁለቱ አስተዳዳሪዎች ማህተም እንዲያስረክቡ ይጠይቃሉ።
" ታስረክባላችሁ አናስረክም " በሚል እልህ በነዋሪዎች እና የትግራይ ኃይል አባላት መካከል ግጭት ይነሳል። ነዋሪውም ደንጋይ መወርወር ይጀምራል። የትግራይ ኃይል አባላትም ጥይት ይተኩሳሉ።
በዚህ መካከል በተተኮሰ ጥይት አንድ ሰው እጁ ላይ ተመትቶ ሆስፒታል ሲገባ ሌሎች 20 ሰዎች ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል። በትግራይ ኃይል አባላት ላይም ጉዳት የደረሰባቸው አሉ።
የወረዳው አስተዳደር ለክልሉ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ የካቲት 11/2017 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ 13 ታጣቂዋች ወደ ወረዳው አስተዳደር በመምጣት የጊዚያዊ አስተዳደር ማህተም እና የፅህፈት ቤት ቁልፍ እንዲያስረክቡዋቸው መጠየቃቸውን እና ይህንን ህገ-ወጥ ተግባር እንዲቆም ጠይቋል።
ከህወሓት ወደ ሁለት መሰንጠቅ በኋላ የክልሉ ዋና ከተማ መቐለ ጨምሮ በተለያዩ የገጠር እና የከተማ አስተዳደሮች ተመሳሳይ ስልጣን ያላቸው ሁለት አሰተዳዳሪዎች መስማት የተለመደ ነው።
በአንዳንድ ዞኖች ያሉ ወረዳዎች በጊዚያዊ አስተዳደሩ እና የደብሪፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት የተሾሙ አስተዳዳሪዎች ለሁለት ተከፋፍለው ይተዳደራሉ።
የትግራይ መሪዎች በተለይም የህወሓት አመራሮች ከዚህ መሰል ህዝብ የሚከፋፍል አደገኛ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ የሚመክሩ አስተያየት ሰጪዎች ፤ የትግራይ ኃይል አባላት አንዱን ቡድን ደግፈው ሌላው ቡድን ማውገዝ ተጨማሪ ቀውስ እና ጥፋት ስለሚያስከትል የገለልተኝነት ሚናቸው እንዱወጡ አበክረው እያሳሰቡ ናቸው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ትናንተ የካቲት 12 /2017 ዓ.ም በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ በነዋሪዎችና በአከባቢው በሚገኘው የትግራይ ኃይል አባላት መካከል ግጭት ተከስተዋል።
በግጭቱ ምክንያት በ20 የቀበሌው ነዋሪዎችና ቁጥራቸው ባልታወቀ የትግራይ ኃይል አባላት ላይ ጉዳት ደርሷል።
ያጋጠመ ሞት የለም።
ግጭቱ እንዴት እና በምን ምክንያት አጋጠመ ?
በአዲስ አለም ቀበሌ ሁለት አስተዳዳሪዎች አሉ። አንዱ የቆየ ሲሆን ሌላው ደግሞ በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሾመ ነው።
ሁለቱም ማህተም ይዘው በየፊናቸው " እኔ ነኝ ህጋዊ የቀበሌው አስተዳደር " በማለት ህዝቡን ለሁለት መክፈላቸው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
ከዚህ ጋር በተያያዘ " ህዝቡ አማርሮ እንድንታደገው ጠይቆናል አዛዦቻችንም ይህንን እንድንፈፅም ልከውናል" ያሉ 9 የሰራዊት አባላት ወደ ቀበሌው ደርሰው ሁለቱ አስተዳዳሪዎች ማህተም እንዲያስረክቡ ይጠይቃሉ።
" ታስረክባላችሁ አናስረክም " በሚል እልህ በነዋሪዎች እና የትግራይ ኃይል አባላት መካከል ግጭት ይነሳል። ነዋሪውም ደንጋይ መወርወር ይጀምራል። የትግራይ ኃይል አባላትም ጥይት ይተኩሳሉ።
በዚህ መካከል በተተኮሰ ጥይት አንድ ሰው እጁ ላይ ተመትቶ ሆስፒታል ሲገባ ሌሎች 20 ሰዎች ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል። በትግራይ ኃይል አባላት ላይም ጉዳት የደረሰባቸው አሉ።
የወረዳው አስተዳደር ለክልሉ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ የካቲት 11/2017 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ 13 ታጣቂዋች ወደ ወረዳው አስተዳደር በመምጣት የጊዚያዊ አስተዳደር ማህተም እና የፅህፈት ቤት ቁልፍ እንዲያስረክቡዋቸው መጠየቃቸውን እና ይህንን ህገ-ወጥ ተግባር እንዲቆም ጠይቋል።
ከህወሓት ወደ ሁለት መሰንጠቅ በኋላ የክልሉ ዋና ከተማ መቐለ ጨምሮ በተለያዩ የገጠር እና የከተማ አስተዳደሮች ተመሳሳይ ስልጣን ያላቸው ሁለት አሰተዳዳሪዎች መስማት የተለመደ ነው።
በአንዳንድ ዞኖች ያሉ ወረዳዎች በጊዚያዊ አስተዳደሩ እና የደብሪፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት የተሾሙ አስተዳዳሪዎች ለሁለት ተከፋፍለው ይተዳደራሉ።
የትግራይ መሪዎች በተለይም የህወሓት አመራሮች ከዚህ መሰል ህዝብ የሚከፋፍል አደገኛ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ የሚመክሩ አስተያየት ሰጪዎች ፤ የትግራይ ኃይል አባላት አንዱን ቡድን ደግፈው ሌላው ቡድን ማውገዝ ተጨማሪ ቀውስ እና ጥፋት ስለሚያስከትል የገለልተኝነት ሚናቸው እንዱወጡ አበክረው እያሳሰቡ ናቸው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#ችሎት
" ንብረታችሁ ሊወረስ ነው " በማለት ባለሃብቱን አስፈራርተው በቼክ ገንዘብ ሲቀበሉ በፀጥታ አካላት የተያዙ 4 ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ተጠርጣሪዎቹ በብሔራዊ መረጃ ደህንነትና በፌደራል ፖሊስ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበትና በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የፋይናንስ ደህንነት ሰራተኞች ነን " በማለት አንድን ባለሃብት አስፈራርተው 5 ሚሊየን ብር ጉቦ ተደራድረው የ1 ሚሊየን ብር ቼክ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል ተብሏል።
ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ መዝገቦች ፍ/ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል።
በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ፦
1ኛ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በሞጆ ደረቅ ወደብ የጥበቃ ኃላፊ ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ፤
2ኛ በግል ስራ የሚተዳደሩት ተስፋ ሀታኡ ገምቴሳ፣
3ኛ ጁዋር አወል ጀማል
4ኛ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የአይቲ ባለሙያ ረ/ኢ/ር ኩሉሌ ጉዮ ቦሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ናቸው።
አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበት፣ በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበትና በጋዜጣ ባልታወጀበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " ደዘርት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር " ለተባለው ድርጅት ባለቤት አቶ ቢኒያም ሀደር እና ወኪላቸው ስራ አስኪያጅ መሐመድ እስማኤል አሊ ለተባሉት ግለሰቦች ስልካቸው ላይ ይደውላሉ።
ጥር 05 ቀን 2017 ጀምሮ ደግሞ በተለያዩ ቀናት ባለሃብቶቹን በአካል በማግኘት " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የመረጃ ደህንነት ሠራተኞች ነን " በማለት ይተዋወቃሉ።
" በአዲሱ ንብረት ማስመለስ አዋጅ መሰረት በንብረታችሁ ላይ እና የባንክ የሂሳብ እንቅስቃሴዎች ላይ ምርመራ ተደርጎ ንብረታችሁ ይወረሳል፤ የባንክ ሂሳብ እንቅስቃሴ እናግዳለን " በማለት ሲያስፈራሩ እንደነበረ በጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ላይ ተብራርቷል።
በተለይ መንግስት ሃብታቸውን እንዳይወርስባቸው እንደሚያደርጉ በመግለጽ ለዚህ ማስፈጸሚያነት የሚውል 5 ሚሊየን ብር በመደራደር በቅድሚያ 20 ሺህ ብር በባንክ ሂሳብ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል አኑዋር ምግብ ቤት ውስጥ አንድ ሚሊየን ብር የተዘጋጀ ቼክ ከደርጅቱ ወኪል ከሆነው ከአቶ ማሐመድ እስማኤል አሊ እጅ ሲቀበሉ በክትትል ላይ በነበሩ ጸጥታ ኃይሎች መያዛቸውን የፌደራል ፖሊስ መርማሪ አሳውቋል።
መርማሪ ፖሊስ በዚህ መልኩ ተጠርጣሪዎቹ የሙስና ወንጀል የምርመራ ማጣሪያ ስራ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ከእነዚህ ተጠርጣሪዎች መካከል ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ በሚመለከት የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ህግ ማስረከቡን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ፖሊስ አስታውቋል።
በፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ዐቃቤ ህግ በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርቦ የምርመራ መዝገቡን ከዐቃቤ ህግ መረከቡን ጠቅሷል።
ዐቃቤ ህግ የምርመራ መዘገቡን ተመልክቶ በተገቢው ሁኔታ ክስ ለመመስረት እንዲያስችለው የ15 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
በተጨማሪም ዐቃቤ ህግ በወንጀል ድርጊት ሊገኝ ከታሰበው የገንዘብ መጠን ወይም የደረሰው ጉዳት አንጻር ሲታይ ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣና ዋስትና የሚያስከለክል መሆኑን ጠቅሶ ፤ የተጠርጣሪው ዋስትናው ታልፎ ክስ እስኪመሰረት ባሉበት በእስር እንዲቆዩ እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ተጠርጣሪው የዐቃቤ ህግ ክስ መመስረቻ ጥያቄን በመቃወም ዋስትና እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
የግራ ቀኝ ክርክሩን የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የተጠርጣሪውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ለዐቃቤ ህግ የዘጠኝ ቀናት ክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል።
መረጃው የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።
@tikvahethiopia
" ንብረታችሁ ሊወረስ ነው " በማለት ባለሃብቱን አስፈራርተው በቼክ ገንዘብ ሲቀበሉ በፀጥታ አካላት የተያዙ 4 ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ተጠርጣሪዎቹ በብሔራዊ መረጃ ደህንነትና በፌደራል ፖሊስ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበትና በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የፋይናንስ ደህንነት ሰራተኞች ነን " በማለት አንድን ባለሃብት አስፈራርተው 5 ሚሊየን ብር ጉቦ ተደራድረው የ1 ሚሊየን ብር ቼክ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል ተብሏል።
ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ መዝገቦች ፍ/ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል።
በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ፦
1ኛ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በሞጆ ደረቅ ወደብ የጥበቃ ኃላፊ ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ፤
2ኛ በግል ስራ የሚተዳደሩት ተስፋ ሀታኡ ገምቴሳ፣
3ኛ ጁዋር አወል ጀማል
4ኛ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የአይቲ ባለሙያ ረ/ኢ/ር ኩሉሌ ጉዮ ቦሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ናቸው።
አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበት፣ በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበትና በጋዜጣ ባልታወጀበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " ደዘርት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር " ለተባለው ድርጅት ባለቤት አቶ ቢኒያም ሀደር እና ወኪላቸው ስራ አስኪያጅ መሐመድ እስማኤል አሊ ለተባሉት ግለሰቦች ስልካቸው ላይ ይደውላሉ።
ጥር 05 ቀን 2017 ጀምሮ ደግሞ በተለያዩ ቀናት ባለሃብቶቹን በአካል በማግኘት " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የመረጃ ደህንነት ሠራተኞች ነን " በማለት ይተዋወቃሉ።
" በአዲሱ ንብረት ማስመለስ አዋጅ መሰረት በንብረታችሁ ላይ እና የባንክ የሂሳብ እንቅስቃሴዎች ላይ ምርመራ ተደርጎ ንብረታችሁ ይወረሳል፤ የባንክ ሂሳብ እንቅስቃሴ እናግዳለን " በማለት ሲያስፈራሩ እንደነበረ በጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ላይ ተብራርቷል።
በተለይ መንግስት ሃብታቸውን እንዳይወርስባቸው እንደሚያደርጉ በመግለጽ ለዚህ ማስፈጸሚያነት የሚውል 5 ሚሊየን ብር በመደራደር በቅድሚያ 20 ሺህ ብር በባንክ ሂሳብ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል አኑዋር ምግብ ቤት ውስጥ አንድ ሚሊየን ብር የተዘጋጀ ቼክ ከደርጅቱ ወኪል ከሆነው ከአቶ ማሐመድ እስማኤል አሊ እጅ ሲቀበሉ በክትትል ላይ በነበሩ ጸጥታ ኃይሎች መያዛቸውን የፌደራል ፖሊስ መርማሪ አሳውቋል።
መርማሪ ፖሊስ በዚህ መልኩ ተጠርጣሪዎቹ የሙስና ወንጀል የምርመራ ማጣሪያ ስራ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ከእነዚህ ተጠርጣሪዎች መካከል ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ በሚመለከት የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ህግ ማስረከቡን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ፖሊስ አስታውቋል።
በፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ዐቃቤ ህግ በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርቦ የምርመራ መዝገቡን ከዐቃቤ ህግ መረከቡን ጠቅሷል።
ዐቃቤ ህግ የምርመራ መዘገቡን ተመልክቶ በተገቢው ሁኔታ ክስ ለመመስረት እንዲያስችለው የ15 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
በተጨማሪም ዐቃቤ ህግ በወንጀል ድርጊት ሊገኝ ከታሰበው የገንዘብ መጠን ወይም የደረሰው ጉዳት አንጻር ሲታይ ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣና ዋስትና የሚያስከለክል መሆኑን ጠቅሶ ፤ የተጠርጣሪው ዋስትናው ታልፎ ክስ እስኪመሰረት ባሉበት በእስር እንዲቆዩ እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ተጠርጣሪው የዐቃቤ ህግ ክስ መመስረቻ ጥያቄን በመቃወም ዋስትና እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
የግራ ቀኝ ክርክሩን የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የተጠርጣሪውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ለዐቃቤ ህግ የዘጠኝ ቀናት ክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል።
መረጃው የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
🚨" ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ1 ሚሊየን 293 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ አባላት ብቻ ተቀጥተዋል !! "
እንደ ሸገር ሬድዮ ዘገባ ፥ በአዲስ አበባ በየቀኑ በአማካይ 7,183 አሽከርካሪዎች በትራፊክ ደንብ መተላለፍ በትራፊክ ፖሊስ ብቻ ይቀጣሉ።
ይህ በሌሎች የትራፊክ ደንብ ታላፊዎችን የሚቀጡትን አይጨምርም።
ባለፉት በ6 ወራት ውስጥ በተለያዩ የደምብ መተላለፍ ጥፋቶች ከ1 ሚሊየን 293 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ አባላት ብቻ ተቀጥተዋል፡፡
ይህም በየቀኑ 7,183 አሽካርካሪዎች መቀጣታቸውን ያሳያል፡፡
በሌላ በኩል " የታጠፈ የደበዘዘ የተፋፋቀ እና በአጠቃላይ ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር አደርጋለሁ " ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ተናግሯል፡፡
ባለፈው በጥር ወር ብቻ ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ በተደረገ ቁጥጥር ከ2,100 በላይ አሽከርካሪዎች ተቀጥተዋል ተብሏል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በየጊዜው እየተባባሰ ለመጣው የመንገድ ትራፊክ አደጋ ልዩ ልዩ የደምብ መተላለፍ ጥፋቶች እንደ ምክንያትነት የሚገለጹ ቢሆንም ለእይታ ግልፅ ያልሆኑ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች መበራከት ለአደጋ ብቻ ሳይሆን የወንጀል ስጋት እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ አስረድቷል፡፡
በየጊዜው የታጠፈ የደበዘዘ እና የተፋፋቀ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደ ቢሆንም በሚፈለገው ደረጃ ችግሩን መቅረፍ አልተቻለም ያለው ፖሊስ አሁንም ጠንካራ የቁጥጥርና አደርጋለሁ ብሏል፡፡
ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ላይ ጥፋቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ 1500 ብር ያስቀጣል፡፡
መረጃው የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
🚨" ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ1 ሚሊየን 293 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ አባላት ብቻ ተቀጥተዋል !! "
እንደ ሸገር ሬድዮ ዘገባ ፥ በአዲስ አበባ በየቀኑ በአማካይ 7,183 አሽከርካሪዎች በትራፊክ ደንብ መተላለፍ በትራፊክ ፖሊስ ብቻ ይቀጣሉ።
ይህ በሌሎች የትራፊክ ደንብ ታላፊዎችን የሚቀጡትን አይጨምርም።
ባለፉት በ6 ወራት ውስጥ በተለያዩ የደምብ መተላለፍ ጥፋቶች ከ1 ሚሊየን 293 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ አባላት ብቻ ተቀጥተዋል፡፡
ይህም በየቀኑ 7,183 አሽካርካሪዎች መቀጣታቸውን ያሳያል፡፡
በሌላ በኩል " የታጠፈ የደበዘዘ የተፋፋቀ እና በአጠቃላይ ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር አደርጋለሁ " ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ተናግሯል፡፡
ባለፈው በጥር ወር ብቻ ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ በተደረገ ቁጥጥር ከ2,100 በላይ አሽከርካሪዎች ተቀጥተዋል ተብሏል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በየጊዜው እየተባባሰ ለመጣው የመንገድ ትራፊክ አደጋ ልዩ ልዩ የደምብ መተላለፍ ጥፋቶች እንደ ምክንያትነት የሚገለጹ ቢሆንም ለእይታ ግልፅ ያልሆኑ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች መበራከት ለአደጋ ብቻ ሳይሆን የወንጀል ስጋት እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ አስረድቷል፡፡
በየጊዜው የታጠፈ የደበዘዘ እና የተፋፋቀ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደ ቢሆንም በሚፈለገው ደረጃ ችግሩን መቅረፍ አልተቻለም ያለው ፖሊስ አሁንም ጠንካራ የቁጥጥርና አደርጋለሁ ብሏል፡፡
ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ላይ ጥፋቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ 1500 ብር ያስቀጣል፡፡
መረጃው የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba 🚨" ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ1 ሚሊየን 293 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ አባላት ብቻ ተቀጥተዋል !! " እንደ ሸገር ሬድዮ ዘገባ ፥ በአዲስ አበባ በየቀኑ በአማካይ 7,183 አሽከርካሪዎች በትራፊክ ደንብ መተላለፍ በትራፊክ ፖሊስ ብቻ ይቀጣሉ። ይህ በሌሎች የትራፊክ ደንብ ታላፊዎችን የሚቀጡትን አይጨምርም። ባለፉት በ6 ወራት ውስጥ በተለያዩ የደምብ መተላለፍ…
" አንዳንዴ ቀን ሙሉ የሰራነውን ገንዘብ ያለ አንዳች ጥፋት ተቀጥተን ባዶ እጃችንን ቤታችን እንገባለን ! " - አሽከርካሪዎች
በአዲስ አበባ በርካታ አሸከርካሪዎች ከትራፊክ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ ወቀሳ እና ቅሬታ ያቀርባሉ።
ለአብነትም ፤ አንዳንድ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ያለ አንዳች ምክንያት እየሄደ ያለን ተሽከርካሪ ማስቆም ፤ ጥፋት ሲያጡ ጥፋት ወደ መፈለግ መግባት ከዛ የቅጣት ወረቀት ላይ መፃፍ ስራቸው ያደረጉ አሉ።
ከዚህ ባለፈ ለዜጎች ክብርን ያለመስጠት ፤ ዝቅ ብሎ አለማገልገል፣ አሽከርካሪዎችን መናቅ ፣ ምንም የምታመጡት ነገር የለም ማለት፣ በስርዓት አለማናገር፣ ጥፋትን አለማስረዳት ... የመሳሰሉ ባህሪዎችም ይታይባቸዋል።
አንዳንድ ትራፊክ ፖሊስ አባላት የትራፊክ ሁኔታውን ማሳለጥ ሲገባቸው እንቅፋትም ይሆናሉ።
መሃል መንገድ ላይ፣ አደባባይ ላይ ሳይቀር የትራፊክ እንቅስቃሴን በሚያውክ መልኩ ተሽከርካሪ አስቁመው መንገድ እንዲዘጋጋም ያደርጋላ።
በተለያየ ጊዜ ቃላቸውን አሽከርካሪዎች ቁጥጥር መኖሩን ግዴታ ቢሆንም በአግባቡ እና በስርዓት መሄን እንዳሚገባው ያነሳሉ።
" ቅጣቱ ለተላለፈ ደንብ መቅጫ ሳይሆን ከዜጎች ገንዘብ መሰብሰቢያ ሆኗል " የሚሉት የሜትር ታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ አሽከርካሪዎች " ቀን ሙሉ የሰራነውን አንዳንዴ ያለ አንዳች ጥፋት ተቀጥተን ባዶ እጃችንን ቤታችን እንገባለን " ብለዋል።
" በተለይ የቅጣት ብሩ ከጨመረ ወዲህ በሆነው ባልሆነው መኪና እያስቆሙ መቅጣት ተበራክቷል " ሲሉም ገልጸዋል።
በተላይ አዳዲስ በተሰሩ የመንገድ ዳሮች ማቆም ስላማይቻል ስራቸውን ለመስራት እንደተቸገሩ ሆኖ ሳለ ያለ አግባብ በትራፊክ ፖሊስ እና የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የሚጣለው ቅጣት ቀን ሙሉ ለፍተው ማታ ባዶ እጃቸውን ወደ ቤት እንዲገቡ እያስገደደ መሆኑን አመልክተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ በርካታ አሸከርካሪዎች ከትራፊክ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ ወቀሳ እና ቅሬታ ያቀርባሉ።
ለአብነትም ፤ አንዳንድ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ያለ አንዳች ምክንያት እየሄደ ያለን ተሽከርካሪ ማስቆም ፤ ጥፋት ሲያጡ ጥፋት ወደ መፈለግ መግባት ከዛ የቅጣት ወረቀት ላይ መፃፍ ስራቸው ያደረጉ አሉ።
ከዚህ ባለፈ ለዜጎች ክብርን ያለመስጠት ፤ ዝቅ ብሎ አለማገልገል፣ አሽከርካሪዎችን መናቅ ፣ ምንም የምታመጡት ነገር የለም ማለት፣ በስርዓት አለማናገር፣ ጥፋትን አለማስረዳት ... የመሳሰሉ ባህሪዎችም ይታይባቸዋል።
አንዳንድ ትራፊክ ፖሊስ አባላት የትራፊክ ሁኔታውን ማሳለጥ ሲገባቸው እንቅፋትም ይሆናሉ።
መሃል መንገድ ላይ፣ አደባባይ ላይ ሳይቀር የትራፊክ እንቅስቃሴን በሚያውክ መልኩ ተሽከርካሪ አስቁመው መንገድ እንዲዘጋጋም ያደርጋላ።
በተለያየ ጊዜ ቃላቸውን አሽከርካሪዎች ቁጥጥር መኖሩን ግዴታ ቢሆንም በአግባቡ እና በስርዓት መሄን እንዳሚገባው ያነሳሉ።
" ቅጣቱ ለተላለፈ ደንብ መቅጫ ሳይሆን ከዜጎች ገንዘብ መሰብሰቢያ ሆኗል " የሚሉት የሜትር ታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ አሽከርካሪዎች " ቀን ሙሉ የሰራነውን አንዳንዴ ያለ አንዳች ጥፋት ተቀጥተን ባዶ እጃችንን ቤታችን እንገባለን " ብለዋል።
" በተለይ የቅጣት ብሩ ከጨመረ ወዲህ በሆነው ባልሆነው መኪና እያስቆሙ መቅጣት ተበራክቷል " ሲሉም ገልጸዋል።
በተላይ አዳዲስ በተሰሩ የመንገድ ዳሮች ማቆም ስላማይቻል ስራቸውን ለመስራት እንደተቸገሩ ሆኖ ሳለ ያለ አግባብ በትራፊክ ፖሊስ እና የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የሚጣለው ቅጣት ቀን ሙሉ ለፍተው ማታ ባዶ እጃቸውን ወደ ቤት እንዲገቡ እያስገደደ መሆኑን አመልክተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray ትናንተ የካቲት 12 /2017 ዓ.ም በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ በነዋሪዎችና በአከባቢው በሚገኘው የትግራይ ኃይል አባላት መካከል ግጭት ተከስተዋል። በግጭቱ ምክንያት በ20 የቀበሌው ነዋሪዎችና ቁጥራቸው ባልታወቀ የትግራይ ኃይል አባላት ላይ ጉዳት ደርሷል። ያጋጠመ ሞት የለም። ግጭቱ እንዴት እና በምን ምክንያት አጋጠመ ? በአዲስ አለም ቀበሌ ሁለት…
#UPDATE
" ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " - የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር
" ሃይል በመጠቀም የመንግስት መዋቅር ለማፍረስ የሚደረግ ህገ-ወጥ እርምጃ ተቀባይነት የለውም " አለ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ የካቲት 13 /2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ፤ በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ ገበሬ ማህበር የትግራይ ኃይል አባላት በነዋሪ አርሶ አደሮች ላይ ያደረሱትን ጥቃት አውግዟል።
" የተወሰኑ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ መዋቅር ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ እየታዘብን ነው " ያለው መግለጫው " በሰሓርቲ ወረዳ የተከሰተው አሳዛኝ ተግባር እንደ አንድ ማሳያ መውሰድ ይቻላል " ብሏል።
" ሰራዊቱ የህዝብ ህልውና ለመጠበቅ እንጂ የአንድ ቡድን የስልጣን ጥማት ለማርካት የተሰለፈ አይደለም " ያለው ጊዚያዊ አስተዳደሩ " ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " ሲል አስጠንቅቋል።
" ማንኛውም የህግ ወይም የአስራር ክፍተት ሲኖር የሚሊሻና የፓሊስ ሃይል ከህዝባቸው በመተባበር የሚፈቱት እና የሚያርሙት እንጂ ሰራዊት ወደ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ማሰማራት የሚያስገድድ ሁኔታ ፈፅሞ እንደሌለ የለም " ሲል ገልጿል።
" ይህንን ህገ-ወጥ አካሄድ የሚያበረታቱ እና የሚያግዙ ፓለቲከኞች እና የሰራዊት አመራሮች አደብ እንዲገዙ " ሲልም አስጠንቅቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " - የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር
" ሃይል በመጠቀም የመንግስት መዋቅር ለማፍረስ የሚደረግ ህገ-ወጥ እርምጃ ተቀባይነት የለውም " አለ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ የካቲት 13 /2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ፤ በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ ገበሬ ማህበር የትግራይ ኃይል አባላት በነዋሪ አርሶ አደሮች ላይ ያደረሱትን ጥቃት አውግዟል።
" የተወሰኑ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ መዋቅር ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ እየታዘብን ነው " ያለው መግለጫው " በሰሓርቲ ወረዳ የተከሰተው አሳዛኝ ተግባር እንደ አንድ ማሳያ መውሰድ ይቻላል " ብሏል።
" ሰራዊቱ የህዝብ ህልውና ለመጠበቅ እንጂ የአንድ ቡድን የስልጣን ጥማት ለማርካት የተሰለፈ አይደለም " ያለው ጊዚያዊ አስተዳደሩ " ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " ሲል አስጠንቅቋል።
" ማንኛውም የህግ ወይም የአስራር ክፍተት ሲኖር የሚሊሻና የፓሊስ ሃይል ከህዝባቸው በመተባበር የሚፈቱት እና የሚያርሙት እንጂ ሰራዊት ወደ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ማሰማራት የሚያስገድድ ሁኔታ ፈፅሞ እንደሌለ የለም " ሲል ገልጿል።
" ይህንን ህገ-ወጥ አካሄድ የሚያበረታቱ እና የሚያግዙ ፓለቲከኞች እና የሰራዊት አመራሮች አደብ እንዲገዙ " ሲልም አስጠንቅቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
🔊 #የጤናባለሙያዎችድምጽ
🔴 “ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች
➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ” - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ አካላት ድብደባና እስራት ተፈጽሞባቸዋል ” ሲሉ ሠራተኞቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ተፈጽሟል ስላሉት እስራትና ድብደባ ምክንያት ምን እንደሆነ ሲገልጹ፣ እንደ ሀገር የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ መደረጉን ተከትሎ መሆኑን ሠራተኞቹ አስረድተዋል።
የአራት ወራት የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ከ150 በላይ ለሚሆኑ የሆስፒታሉ ሠራተኞች አለመፈጸሙን፣ እስከ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ/ም እንዲፈጸምላቸውና እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ካልተፈጸመላቸው ሥራ የማቆም አድማ ለማድረግ እንደሚገደዱ በደብዳቤ ጭምር ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም ክፍያው ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ እንዳደረጉ፣ የተወሰኑት ሥራ ማቆም አድማ ያላደረጉ ሰራተኞች ቢሮ ባሉበት “ አድማ አስመትታችኋል ” በሚል እስራትና ድብደባ እንደተፈጸመባቸው በመግለጽ አማረዋል።
በዚህም፣ “የካቲት 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ/ም ሥራ አልገባንም። በቀን 12/2017 ዓ/ም ደግሞ ሙሉ ፓትሮል ፓሊስ መጥቶ በሥራ ላይ የነበሩ የማኔጅመንት አባላትን ይዘው ወጡ ” በማለት ተናግረዋል።
አክለው፣ “ ከየቤቱ ያሉት ሠራተኞችም መረጃው ደርሷቸው ‘ካሰራችሁ ሁላችንንም እሰሩን የሁላችንም ጉዳይ ነው’ ብለው እስሩ ከተፈጸመበት ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል ” ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።
የታሰሩት ምን ያክል ግለሰቦች ናቸው? ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በሰጡት ምላሽ፣ “የታሰሩት የሆስፓታሉ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት ናቸው፡፡ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ 9 ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠራተኞቹን ቅሬታ በመያዝ፣ ድርጊቱ ለምን እንደተፈጸመ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮን ምላሽ የጠየቀ ሲሆን፣ እስራቱ መፈጸሙን እና ደመወዙ አለመከፈሉን አምኖ ምላሽ ያለውን ሰጥቷል።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ በዝርዝር ምን መለሱ ?
“ ባለሙያዎቹ የካቲት 7 መጥተው ነበር። ከኛ ጋ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይት ካደረግን በኋላ ፕሮሰስ እያደረግን ለማክሰኞ ጠዋት ክልል ቀጠሮ እንደነበረ ገልጸንላቸው ነበር፡፡ ማክሰኞ ሂደን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ምላሽ ታገኛላችሁ ብለናቸው ነበር፡፡
እነሱ ጋ ብቻ አይደለም ክፍያው ያልተከፈለው ከ2000 በላይ ሰራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ፡፡ እንደ ዞንም ሶስት ሆስፒታል ላይ ነው ክፍያው ያልተከፈለው፡፡ የተለያዩ የጤና ባለሙያዎችም በወረዳ ደረጃ ያልተከፈላቸው አሉ፡፡
በሦስቱ ሆስፒታሎች ነው ያልተፈጸመው። ግን ሁለቱ ሆስፒታሎች የስራ ማቆም አድማ አላደረጉም፡፡ እነርሱ ግን ለማክሰኞ ቀጥረናቸው እያለ ቀጠሮውን አንቀበልም ብለው ሙያዊ ሥነ ምግባር በማይፈቅድ መንገድ ስራ የማመጽ ነገር አድርገው ነበር።
ግን የተወሰኑ ልጆች ደግሞ ስራ ገበታ ላይ ተገኝተው ነበር፡፡ ስለዚህ ኦሬዲ ድስከስ አድርገን ጉዳዩን ፈተን ልጆቹ ስራ ጀምረዋል አሁን፡፡ ስራ ላይ ናቸው ሁሉም ” ብለዋል።
ታሰሩ የተባሉት የሆስፒታሉ ባልደረቦች ሳይፈቱ እንዴት ሁሉም ስራ ላይ ሊገኙ እንደቻሉ ምላሽ የጠይቅናቸው ኃላፊው፣ “እነርሱ ያልተገባ አካሄድ የሄዱ አሉ፡፡ ከስነ ስርዓት ውጭ ያልተፈቀደ ሰልፍ የወጡበት ሂደትም አለ፡፡ እንግዲህ ከእስር እንዲወጡ እየተሰራ ያለበት ሂደት አለ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ሠራተኞቹ ቅሬታ ያቀረቡት የአራት ወራት ገደማ ደመወዝ አለመጨመሩን ተከትሎ ነውና የመብት ጥያቄ በመቅረቡ እስርና ድብደባ መፈጸም አግባብ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።
አቶ አንዷለም በሰጡት ማብራሪያ፣ “ሠራተኞቹና ባለሙያዎቹ፣ ‘የፈጸምናቸው ድርጊቶች ትክክል አይደሉም ህዝቡን በድለናል ብለው’ ይቅርታ ጠይቀው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ውይይት ተደርጎ ጤናማ ስራ ጀምረዋል አሁን” ሲሉ አስተባብለዋል።
ይቅርታ የጠየቁት ማን ናቸው? ሰራተኞቹ ወይስ አሳሪዎቹ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ኃላፊው፣ “ሰራተኞቹ ” ሲል የመለሰ ሲሆን፣ ታስረው እያለ እንዴት ይቅርታ ይጠይቃሉ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል።
እሳቸውም፣ “ሙያዊ ክብር በጣሰ መልኩ ሰልፍ የወጡትም ይቅርታ እየጠየቁ ነው ያሉት አሁን፡፡ ‘እነርሱ ናቸው ጥፋተኛ’ በሚል ልከውልናል ቤተሰቦቻቸው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
የተወሰኑት ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር፤ በአንጻሩ ደግሞ የተወሰኑት ደግሞ ስራ ላይ ተገኝተው ነበር፤ ነገርግን ‘ሌሎቹን አሳምጻችኋል’ በሚል ስራ የገቡትም ናቸው የታሰሩት። ሥራ ላይ እያሉ ታስረው ሳለ “ይቅርታ ጠይቀዋል” መባሉ ምን ማለት እንደሆም በድጋሚ ምላሽ ጠይቀናል።
አቶ አንዷለም በምላሻቸው፣ “ነገሩ እንግዲህ እንደዚሁ ነው። አሁን ውይይት ላይ ነን፡፡ እነርሱ የሰሩት ጥፋት ስለነበረ ነው የተጠየቁት። አሁን ይቅርታ ጠይቀው ውይይት ላይ ነን ችግሩን ለመፍታት” ነው ያሉት፡፡
እንዳጠቃላይ ችግሩን ለመፍታትስ ምን እየተሰራ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “አሁን በጀቱ እውቅና አግኝቷል፡፡ ለሰራተኞች የጸደቀላቸው በጀት እጃችን ላይ ገብቷል፡፡ የክፍያ ሂደት ለማመቻቸት ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።
“ከክልል ፋይናንስ ገንዘብ እንድለቀቅ ሂደት ላይ እንደሆነና ያው ከዚያ እንደተለቀቀ ክፍያ እንደሚከፈል ተግባቦት ላይ ተደርሷል” ሲሉም አክለዋል፡፡
(ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች
➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ” - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ አካላት ድብደባና እስራት ተፈጽሞባቸዋል ” ሲሉ ሠራተኞቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ተፈጽሟል ስላሉት እስራትና ድብደባ ምክንያት ምን እንደሆነ ሲገልጹ፣ እንደ ሀገር የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ መደረጉን ተከትሎ መሆኑን ሠራተኞቹ አስረድተዋል።
የአራት ወራት የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ከ150 በላይ ለሚሆኑ የሆስፒታሉ ሠራተኞች አለመፈጸሙን፣ እስከ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ/ም እንዲፈጸምላቸውና እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ካልተፈጸመላቸው ሥራ የማቆም አድማ ለማድረግ እንደሚገደዱ በደብዳቤ ጭምር ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም ክፍያው ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ እንዳደረጉ፣ የተወሰኑት ሥራ ማቆም አድማ ያላደረጉ ሰራተኞች ቢሮ ባሉበት “ አድማ አስመትታችኋል ” በሚል እስራትና ድብደባ እንደተፈጸመባቸው በመግለጽ አማረዋል።
በዚህም፣ “የካቲት 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ/ም ሥራ አልገባንም። በቀን 12/2017 ዓ/ም ደግሞ ሙሉ ፓትሮል ፓሊስ መጥቶ በሥራ ላይ የነበሩ የማኔጅመንት አባላትን ይዘው ወጡ ” በማለት ተናግረዋል።
አክለው፣ “ ከየቤቱ ያሉት ሠራተኞችም መረጃው ደርሷቸው ‘ካሰራችሁ ሁላችንንም እሰሩን የሁላችንም ጉዳይ ነው’ ብለው እስሩ ከተፈጸመበት ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል ” ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።
የታሰሩት ምን ያክል ግለሰቦች ናቸው? ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በሰጡት ምላሽ፣ “የታሰሩት የሆስፓታሉ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት ናቸው፡፡ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ 9 ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠራተኞቹን ቅሬታ በመያዝ፣ ድርጊቱ ለምን እንደተፈጸመ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮን ምላሽ የጠየቀ ሲሆን፣ እስራቱ መፈጸሙን እና ደመወዙ አለመከፈሉን አምኖ ምላሽ ያለውን ሰጥቷል።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ በዝርዝር ምን መለሱ ?
“ ባለሙያዎቹ የካቲት 7 መጥተው ነበር። ከኛ ጋ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይት ካደረግን በኋላ ፕሮሰስ እያደረግን ለማክሰኞ ጠዋት ክልል ቀጠሮ እንደነበረ ገልጸንላቸው ነበር፡፡ ማክሰኞ ሂደን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ምላሽ ታገኛላችሁ ብለናቸው ነበር፡፡
እነሱ ጋ ብቻ አይደለም ክፍያው ያልተከፈለው ከ2000 በላይ ሰራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ፡፡ እንደ ዞንም ሶስት ሆስፒታል ላይ ነው ክፍያው ያልተከፈለው፡፡ የተለያዩ የጤና ባለሙያዎችም በወረዳ ደረጃ ያልተከፈላቸው አሉ፡፡
በሦስቱ ሆስፒታሎች ነው ያልተፈጸመው። ግን ሁለቱ ሆስፒታሎች የስራ ማቆም አድማ አላደረጉም፡፡ እነርሱ ግን ለማክሰኞ ቀጥረናቸው እያለ ቀጠሮውን አንቀበልም ብለው ሙያዊ ሥነ ምግባር በማይፈቅድ መንገድ ስራ የማመጽ ነገር አድርገው ነበር።
ግን የተወሰኑ ልጆች ደግሞ ስራ ገበታ ላይ ተገኝተው ነበር፡፡ ስለዚህ ኦሬዲ ድስከስ አድርገን ጉዳዩን ፈተን ልጆቹ ስራ ጀምረዋል አሁን፡፡ ስራ ላይ ናቸው ሁሉም ” ብለዋል።
ታሰሩ የተባሉት የሆስፒታሉ ባልደረቦች ሳይፈቱ እንዴት ሁሉም ስራ ላይ ሊገኙ እንደቻሉ ምላሽ የጠይቅናቸው ኃላፊው፣ “እነርሱ ያልተገባ አካሄድ የሄዱ አሉ፡፡ ከስነ ስርዓት ውጭ ያልተፈቀደ ሰልፍ የወጡበት ሂደትም አለ፡፡ እንግዲህ ከእስር እንዲወጡ እየተሰራ ያለበት ሂደት አለ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ሠራተኞቹ ቅሬታ ያቀረቡት የአራት ወራት ገደማ ደመወዝ አለመጨመሩን ተከትሎ ነውና የመብት ጥያቄ በመቅረቡ እስርና ድብደባ መፈጸም አግባብ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።
አቶ አንዷለም በሰጡት ማብራሪያ፣ “ሠራተኞቹና ባለሙያዎቹ፣ ‘የፈጸምናቸው ድርጊቶች ትክክል አይደሉም ህዝቡን በድለናል ብለው’ ይቅርታ ጠይቀው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ውይይት ተደርጎ ጤናማ ስራ ጀምረዋል አሁን” ሲሉ አስተባብለዋል።
ይቅርታ የጠየቁት ማን ናቸው? ሰራተኞቹ ወይስ አሳሪዎቹ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ኃላፊው፣ “ሰራተኞቹ ” ሲል የመለሰ ሲሆን፣ ታስረው እያለ እንዴት ይቅርታ ይጠይቃሉ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል።
እሳቸውም፣ “ሙያዊ ክብር በጣሰ መልኩ ሰልፍ የወጡትም ይቅርታ እየጠየቁ ነው ያሉት አሁን፡፡ ‘እነርሱ ናቸው ጥፋተኛ’ በሚል ልከውልናል ቤተሰቦቻቸው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
የተወሰኑት ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር፤ በአንጻሩ ደግሞ የተወሰኑት ደግሞ ስራ ላይ ተገኝተው ነበር፤ ነገርግን ‘ሌሎቹን አሳምጻችኋል’ በሚል ስራ የገቡትም ናቸው የታሰሩት። ሥራ ላይ እያሉ ታስረው ሳለ “ይቅርታ ጠይቀዋል” መባሉ ምን ማለት እንደሆም በድጋሚ ምላሽ ጠይቀናል።
አቶ አንዷለም በምላሻቸው፣ “ነገሩ እንግዲህ እንደዚሁ ነው። አሁን ውይይት ላይ ነን፡፡ እነርሱ የሰሩት ጥፋት ስለነበረ ነው የተጠየቁት። አሁን ይቅርታ ጠይቀው ውይይት ላይ ነን ችግሩን ለመፍታት” ነው ያሉት፡፡
እንዳጠቃላይ ችግሩን ለመፍታትስ ምን እየተሰራ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “አሁን በጀቱ እውቅና አግኝቷል፡፡ ለሰራተኞች የጸደቀላቸው በጀት እጃችን ላይ ገብቷል፡፡ የክፍያ ሂደት ለማመቻቸት ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።
“ከክልል ፋይናንስ ገንዘብ እንድለቀቅ ሂደት ላይ እንደሆነና ያው ከዚያ እንደተለቀቀ ክፍያ እንደሚከፈል ተግባቦት ላይ ተደርሷል” ሲሉም አክለዋል፡፡
(ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#MoE
" በዚህ ዓመት 150 ሺህ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ (ኦንላይን) ይወስዳሉ " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
ባለፈው ዓመት ወደ ተግባር የገባው የኦንላይን ብሔራዊ ፈተና ዘንድሮም እንደሚቀጥል ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በዚህ ዓመት 150 ሺ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ (ኦንላይ ) እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅ እየተደረገ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ያሉት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ ነው።
ከዚህ ባለፈ በመድረኩ " ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥራት ያለው ትምህርት በማግኘት ረገድ እኩል እድል እንዲኖረው ፤ በድሃና ሃብታም መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ ሥራ መስራት አለብን " ብለዋል።
" ይችን ሀገር መለወጥ የሚቻለው የትምህርት ሥርዓቱን መቀየር ሲቻል " ነው ሲሉም ገልጸዋል።
በመንግስት ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር ማስተማር እንዲኖር ማድረግ ላይ መሥራት እንደሚገባና ' በትምህርት ለትውልድ ' የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል የተጀመረው ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ የመምህራንን አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከተመረቁ ዜጎች ውስጥ ልዩ የማስተማር ሙያ (pedagogy) ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ሙያው እንዲገቡ እንደሚደረግ ይፋ አድርገዋል።
#MoE
@tikvahethiopia
" በዚህ ዓመት 150 ሺህ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ (ኦንላይን) ይወስዳሉ " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
ባለፈው ዓመት ወደ ተግባር የገባው የኦንላይን ብሔራዊ ፈተና ዘንድሮም እንደሚቀጥል ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በዚህ ዓመት 150 ሺ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ (ኦንላይ ) እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅ እየተደረገ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ያሉት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ ነው።
ከዚህ ባለፈ በመድረኩ " ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥራት ያለው ትምህርት በማግኘት ረገድ እኩል እድል እንዲኖረው ፤ በድሃና ሃብታም መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ ሥራ መስራት አለብን " ብለዋል።
" ይችን ሀገር መለወጥ የሚቻለው የትምህርት ሥርዓቱን መቀየር ሲቻል " ነው ሲሉም ገልጸዋል።
በመንግስት ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር ማስተማር እንዲኖር ማድረግ ላይ መሥራት እንደሚገባና ' በትምህርት ለትውልድ ' የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል የተጀመረው ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ የመምህራንን አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከተመረቁ ዜጎች ውስጥ ልዩ የማስተማር ሙያ (pedagogy) ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ሙያው እንዲገቡ እንደሚደረግ ይፋ አድርገዋል።
#MoE
@tikvahethiopia
#NationalExam
" ፈተናው ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት እየተዘጋጀ እንደሆነ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
አገልግሎቱ ፤ " የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ብሏል።
" ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ሲል ገልጿል።
በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የሚፈተኑ እንዳሉም ጠቁሟል።
በዚህም " የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " ሲል አሳውቋል።
የፈተና ዝግጅቱ፡-
1) ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣
2) ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
3) ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
4) ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ እንደሆነ ተገልጿል።
ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ እንደሆነ ተመላክቷል።
በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አገልግሎት መ/ቤቱ አሳስቧል።
ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል።
የዘንድሮ ሀገር አቀፉ የ12ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና መቼ እንደሚሰጥ እስካሁን የተወሰነ ነገር የለም።
@tikvahethiopia
" ፈተናው ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት እየተዘጋጀ እንደሆነ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
አገልግሎቱ ፤ " የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ብሏል።
" ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ሲል ገልጿል።
በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የሚፈተኑ እንዳሉም ጠቁሟል።
በዚህም " የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " ሲል አሳውቋል።
የፈተና ዝግጅቱ፡-
1) ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣
2) ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
3) ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
4) ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ እንደሆነ ተገልጿል።
ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ እንደሆነ ተመላክቷል።
በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አገልግሎት መ/ቤቱ አሳስቧል።
ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል።
የዘንድሮ ሀገር አቀፉ የ12ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና መቼ እንደሚሰጥ እስካሁን የተወሰነ ነገር የለም።
@tikvahethiopia
የቀድሞ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት ተሰጣቸው።
የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ኅብረተሰቡ ለተቀላቀሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ኃላፊነት ተሰጥቷል።
በዚህም መሠረት ፡-
1. አቶ ያደሳ ነጋሣ - በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የደኅንነት አማካሪ፣
2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ ተሰማ - የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ምክትል ኃላፊ፣
3. አቶ ቶሌራ ረጋሣ - የኦሮሚያ አስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።
@tikvahethiopia
የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ኅብረተሰቡ ለተቀላቀሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ኃላፊነት ተሰጥቷል።
በዚህም መሠረት ፡-
1. አቶ ያደሳ ነጋሣ - በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የደኅንነት አማካሪ፣
2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ ተሰማ - የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ምክትል ኃላፊ፣
3. አቶ ቶሌራ ረጋሣ - የኦሮሚያ አስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።
@tikvahethiopia