TIKVAH-ETHIOPIA
“የተነሳበትን አካባቢ ጉዳት አድርሷል። ግን አሁንም ሙሉ ለሙሉ አልጠፋም” - ባለስልጣኑ በአፋር ክልል ሃላይዳጌ አሰቦት ብሔራዊ ፓርክ ከተነሳ ቀናት ያስቆጠረው ቃጠሎ በቁጥጥር ሥር ባለመዋሉ ለማጥፋት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ። የተቋሙ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ናቃቸው ብርሌው በሰጡን ማብራሪያ፣ የእሳት ቃጠሎ በተነሳበት…
#Update
" እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል " - የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን
በሃላይደጌ አሰቦት ዕጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የነበረው የእሳት ቃጠሎ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር እንደዋ ለየኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን አሳውቋል።
ላለፉት ሶስት ቀናት በብሔራዊ ፓርኩ ውስጥ ተከስቶ ነበረው የእሳት ቃጠሎ ለመቆጣጠር የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን መ/ ቤቱ የሃላይደጌ እና የአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ሠራተኞች፣ የገቢ ራሱ ዞን እና አሚባራ ወረዳ ነዋሪዎችና አመራሮች እንዲሁም የሃላይደጌና አንዲዶ ቀበሌ ነዋሪዎች ርብርብ ማድረጋቸው ተገልጿል።
" እሳቱን ለማጥፋት በተደረገው ርብርብ ትናንት ከሰዓት ጀምሮ በፓርኩ ላይ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተችሏል " ሲል ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
" እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል " - የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን
በሃላይደጌ አሰቦት ዕጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የነበረው የእሳት ቃጠሎ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር እንደዋ ለየኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን አሳውቋል።
ላለፉት ሶስት ቀናት በብሔራዊ ፓርኩ ውስጥ ተከስቶ ነበረው የእሳት ቃጠሎ ለመቆጣጠር የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን መ/ ቤቱ የሃላይደጌ እና የአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ሠራተኞች፣ የገቢ ራሱ ዞን እና አሚባራ ወረዳ ነዋሪዎችና አመራሮች እንዲሁም የሃላይደጌና አንዲዶ ቀበሌ ነዋሪዎች ርብርብ ማድረጋቸው ተገልጿል።
" እሳቱን ለማጥፋት በተደረገው ርብርብ ትናንት ከሰዓት ጀምሮ በፓርኩ ላይ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተችሏል " ሲል ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና ተያያዥ ስብሰባዎች እስከሚጠናቀቁ ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ክልክል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
የመሪዎች ጉባኤ እስከሚጠናቅ ድረስ ባሉ ቀናቶች ውስጥ በየትኛውም የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ፍፁም ክልክል መሆኑን ነው ፖሊስ አሳስቧል።
ትእዛዝ በመተላለፍ ሲንቀሳቀሱ በሚገኙ የሞተር አሽከርካሪዎች ላይ ሆነ ባለ ንብረቶች ላይ እርምጃ እንዳሚወሰድ አስገንዝቧል።
@tikvahethiopia
የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና ተያያዥ ስብሰባዎች እስከሚጠናቀቁ ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ክልክል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
የመሪዎች ጉባኤ እስከሚጠናቅ ድረስ ባሉ ቀናቶች ውስጥ በየትኛውም የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ፍፁም ክልክል መሆኑን ነው ፖሊስ አሳስቧል።
ትእዛዝ በመተላለፍ ሲንቀሳቀሱ በሚገኙ የሞተር አሽከርካሪዎች ላይ ሆነ ባለ ንብረቶች ላይ እርምጃ እንዳሚወሰድ አስገንዝቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " - ፓርኩ
በሃላይደጌ አሰቦት እጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የቆየውና ለቀናት ከቁጥጥር ውጪ ለማድረግ አስቸግሮ የነበረው ቃጠሎ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፓርኩና የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ይህን ተከትሎም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ በአደጋው የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል እንደሆነ የጠየቀ ሲሆን፣ እንስሳት መቃጠላቸውንና ከ350 እስከ 400 ሄክታር የሚገመት ሳራማ ቦታ መቃጠሉን ሰምቷል።
የፓርኩ ኃላፊ አቶ አሕመድ እንድሪስ ምን አሉ ?
" የካቲት 1/2017 ዓ/ም መንስኤው ባልታወቀ ምክንያት የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ነበር። ትላንት 10 ሰዓት በቁጥጥር ስር ተደርጓል። ዛሬም ከጠዋቱ 11 ሰዓት ጀምረን ጫካ ነበርን ሙሉ በመሉ መጥፋቱን አረጋግጠናል።
ተራማጅ የሆኑና መሮጥ የሚችሉ የዱር እንስሳት ብዙዎቹ አምልጠዋል። ግን መራመድ የማይችሉ፣ አዲስ የተወለዱ የዱር እንስሳት ጉዳት ሊያደርስ ችሏል።
እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ግን የጉዳቱን መጠን ሰርቨይ መሰራት አለበት " ብለዋል።
የፓርኩ ምን ያክል ክፍል እንደተቃጠለ ታውቋል? ለሚለው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ " መለካት ያስፈልጋል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
" ደረቃማ ሳር ስላለ በትንሹ ነው የሚቀጣጠለውና በሰው ኃይል ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎት፣ በሰው ኃይል ከመቆጣጠር በላይ ሆኖ ነው በግሬደርና፣ ከእሳቱ ርቆ በሎደር የማስራብ ሥራ የተሰራው” ሲሉ አስታውሰዋል።
ፖርኩ ወደ 244 የአእዋፍ ዝርያዎች፣ 42 አጥቢዎችና ሌሎች እንስሳት እንዳሉበት አስረድተው፣ “የተመሰረተው በኬንያና በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን ትልቁ የሜዳ አህያ ለመጠበቅ ነው” ብለዋል።
ኮቪድ ከመከሰቱ በፊት እስከ 200 ሺሕ፣ ኮቪድ ተከስቶ ከቆዬ በኋላ የቱሪስት ቁጥር በመቀነሱ ከ50 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ገቢ የሚገኝበት እጩ ፓርክ መሆኑ ተነግሯል።
ፓርኩ ከአዲስ አበባ በ27ዐ ርቀት ላይ ያለ፣ ኤሪያው 1099 ስኩየር ኪሎሜትር የሆነ፣ ወይራ፣ የሀበሻ ጽድ፣ ዝንባ የመሳሰሉ እፅዋቶች ያሉበት፣ 40 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሜዳ ላይ ያረፈ ሳር ያለበት ነውም ተብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " - ፓርኩ
በሃላይደጌ አሰቦት እጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የቆየውና ለቀናት ከቁጥጥር ውጪ ለማድረግ አስቸግሮ የነበረው ቃጠሎ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፓርኩና የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ይህን ተከትሎም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ በአደጋው የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል እንደሆነ የጠየቀ ሲሆን፣ እንስሳት መቃጠላቸውንና ከ350 እስከ 400 ሄክታር የሚገመት ሳራማ ቦታ መቃጠሉን ሰምቷል።
የፓርኩ ኃላፊ አቶ አሕመድ እንድሪስ ምን አሉ ?
" የካቲት 1/2017 ዓ/ም መንስኤው ባልታወቀ ምክንያት የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ነበር። ትላንት 10 ሰዓት በቁጥጥር ስር ተደርጓል። ዛሬም ከጠዋቱ 11 ሰዓት ጀምረን ጫካ ነበርን ሙሉ በመሉ መጥፋቱን አረጋግጠናል።
ተራማጅ የሆኑና መሮጥ የሚችሉ የዱር እንስሳት ብዙዎቹ አምልጠዋል። ግን መራመድ የማይችሉ፣ አዲስ የተወለዱ የዱር እንስሳት ጉዳት ሊያደርስ ችሏል።
እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ግን የጉዳቱን መጠን ሰርቨይ መሰራት አለበት " ብለዋል።
የፓርኩ ምን ያክል ክፍል እንደተቃጠለ ታውቋል? ለሚለው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ " መለካት ያስፈልጋል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
" ደረቃማ ሳር ስላለ በትንሹ ነው የሚቀጣጠለውና በሰው ኃይል ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎት፣ በሰው ኃይል ከመቆጣጠር በላይ ሆኖ ነው በግሬደርና፣ ከእሳቱ ርቆ በሎደር የማስራብ ሥራ የተሰራው” ሲሉ አስታውሰዋል።
ፖርኩ ወደ 244 የአእዋፍ ዝርያዎች፣ 42 አጥቢዎችና ሌሎች እንስሳት እንዳሉበት አስረድተው፣ “የተመሰረተው በኬንያና በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን ትልቁ የሜዳ አህያ ለመጠበቅ ነው” ብለዋል።
ኮቪድ ከመከሰቱ በፊት እስከ 200 ሺሕ፣ ኮቪድ ተከስቶ ከቆዬ በኋላ የቱሪስት ቁጥር በመቀነሱ ከ50 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ገቢ የሚገኝበት እጩ ፓርክ መሆኑ ተነግሯል።
ፓርኩ ከአዲስ አበባ በ27ዐ ርቀት ላይ ያለ፣ ኤሪያው 1099 ስኩየር ኪሎሜትር የሆነ፣ ወይራ፣ የሀበሻ ጽድ፣ ዝንባ የመሳሰሉ እፅዋቶች ያሉበት፣ 40 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሜዳ ላይ ያረፈ ሳር ያለበት ነውም ተብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
የየእለቱን ዜናዎችን በSMS እናግኝ! 🗞📲
ከሳፋሪኮም ቁጥራችን 'A’ ብለን ወደ 30000 SMS አሁኑኑ በመላክ ወይም ወደ *779# በመደወል የቲክቫህ ትኩስ መረጃዎችን እናግኝ! በቀን 1ብር ብቻ! ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት ⚡️
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
#MPESASafaricom
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
የየእለቱን ዜናዎችን በSMS እናግኝ! 🗞📲
ከሳፋሪኮም ቁጥራችን 'A’ ብለን ወደ 30000 SMS አሁኑኑ በመላክ ወይም ወደ *779# በመደወል የቲክቫህ ትኩስ መረጃዎችን እናግኝ! በቀን 1ብር ብቻ! ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት ⚡️
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
#MPESASafaricom
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
" ከጦርነቱ በፊት ነጋዴዎች ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር አድጓል " - ከትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት
የትግራይ ክልል ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ማደጉን የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አሳውቋል።
ም/ቤቱ ይህን ያሳወቀው ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።
የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዘዳንት አቶ በሪሁን ሃፍቱ ምን አሉ ?
➡️ ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ከባንክ ወስደውት ነበረው የባንክ እዳ በ5 አመት ወስጥ ከ32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
➡️ ተከስቶ የነበረው ጦርነት ብዙ ሀብት አውድሟል የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን አጥፍቷል፣ ቀሪዎችንም ከንግድ እንቅስቃሴ ውጭ አድርጎ የገበያ ትስስራቸውን እንዲያጡ አድርጓል።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የጠፉት የባንክ ብድር ይዘው ነው።
➡️ የባንክ እዳ ይዘው የወደሙ የንግድ ተቋማትን ወደ መደበኛ ሥርዓት ለመመለስ ከባድ ነው ፤ ምክንያቱም ባለሀብቱ ፈልጎ ባላመጣው ጦርነት ተዳክሟል።
➡️ በክልሉ ያሉ ባለሀብቶች ንብረታቸው መውደሙ እና ሀብታቸው መጥፋቱ ሳያንስ እዳቸውን ከነወለዱ እና ከነቅጣቱ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ነው። ይህም አግባባብ አደለም። ምክኒያቱም ባለሃብቶች ጦርነቱን ፈልገውት አይደለም ያመጡት።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ተቋማት ተመልስው ወደስራ የሚገቡበት ሁኔታ ሳይፈጠር ባለሃብቶች ባልሰሩበት የተበደሩትን እዳ ከነወለዱ እንዲከፍሉ መደረጉ ተገቢ አይደለም። መከፈል ግዴታም ከሆነም ደግሞ ቢያንስ እየሰሩ እንዲከፍሉ ልዩ ማበረታቻ ያሰፈልጋቸዋል።
➡️ የወደሙትን በአዲስ ለመተካት የተዳከሙትን ደግሞ ለማነቃቃት ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። ያን ማድረግ የሚቻል ከሆነ ነጋዴው ነግዶ አትርፎ አዲስ ግብር ከፋይ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት የነበረበትን እዳም የመክፈል አቅም ይኖረዋል።
➡️ አሁን ያለብን ትልቁ ችግር ተጨማሪ ድጋፍ አለማግኘት ነው። ባንኮች ተጨማሪ ብድር ለመስጠትም እየተቸገሩ ነው።
➡️ ባለሃብቶች ከጦርነቱ በፊት የተበደሩት እዳ ወለዱም ከዛሬ ነገ እየጨመረ ነው ያለው ፤ አይደለም ሰርቶ ማትረፍ ይቅርና ስራ በቆመበት እና ንብረት በወደመበት ወቅትም ወለዱ እየታሰበ ነው ያ ወለድ ደግሞ የወለድ ወለድ ቅጣት እየታሰበበት ነው።
➡️ ያለው ችግር የተለየ የብደር ጥቅል ካልተዘየደለት አሁን ባለው አሰራር የሚፈታ አይደለም።
➡️ የወደመው ንብረት በቢሊዮን የሚገመት ነው በዚህ ላይ ደግሞ የኢኮኖሚው ማሻሽያ ሲጨመር ችግሩን የከፋ አድርጎታል።
➡️ ጦርነቱ ከቆመ ወዲህ ባለፉት ሁለት አመታት ለክልሉ ባለሃብቶች የቀረበው ብድር 2 ቢሊዮን ብር የማይሞላ ነው ይህም ከችግሩ ስፋት ጋር አብሮ የሚሄድ አይደለም።
➡️ በቅረቡ ከብሄራዊ ባንክ ጋር ውይይት ተደርጎ ነበር በዚህም ነጋዴዎች በሐራጅ ለመሸጥ ጊዜውን ለአንድ አመት እንዲራዝም ተደርጓል ግን ይህ በቂ አይደለም።
የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ማደጉን የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አሳውቋል።
ም/ቤቱ ይህን ያሳወቀው ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።
የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዘዳንት አቶ በሪሁን ሃፍቱ ምን አሉ ?
➡️ ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ከባንክ ወስደውት ነበረው የባንክ እዳ በ5 አመት ወስጥ ከ32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
➡️ ተከስቶ የነበረው ጦርነት ብዙ ሀብት አውድሟል የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን አጥፍቷል፣ ቀሪዎችንም ከንግድ እንቅስቃሴ ውጭ አድርጎ የገበያ ትስስራቸውን እንዲያጡ አድርጓል።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የጠፉት የባንክ ብድር ይዘው ነው።
➡️ የባንክ እዳ ይዘው የወደሙ የንግድ ተቋማትን ወደ መደበኛ ሥርዓት ለመመለስ ከባድ ነው ፤ ምክንያቱም ባለሀብቱ ፈልጎ ባላመጣው ጦርነት ተዳክሟል።
➡️ በክልሉ ያሉ ባለሀብቶች ንብረታቸው መውደሙ እና ሀብታቸው መጥፋቱ ሳያንስ እዳቸውን ከነወለዱ እና ከነቅጣቱ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ነው። ይህም አግባባብ አደለም። ምክኒያቱም ባለሃብቶች ጦርነቱን ፈልገውት አይደለም ያመጡት።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ተቋማት ተመልስው ወደስራ የሚገቡበት ሁኔታ ሳይፈጠር ባለሃብቶች ባልሰሩበት የተበደሩትን እዳ ከነወለዱ እንዲከፍሉ መደረጉ ተገቢ አይደለም። መከፈል ግዴታም ከሆነም ደግሞ ቢያንስ እየሰሩ እንዲከፍሉ ልዩ ማበረታቻ ያሰፈልጋቸዋል።
➡️ የወደሙትን በአዲስ ለመተካት የተዳከሙትን ደግሞ ለማነቃቃት ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። ያን ማድረግ የሚቻል ከሆነ ነጋዴው ነግዶ አትርፎ አዲስ ግብር ከፋይ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት የነበረበትን እዳም የመክፈል አቅም ይኖረዋል።
➡️ አሁን ያለብን ትልቁ ችግር ተጨማሪ ድጋፍ አለማግኘት ነው። ባንኮች ተጨማሪ ብድር ለመስጠትም እየተቸገሩ ነው።
➡️ ባለሃብቶች ከጦርነቱ በፊት የተበደሩት እዳ ወለዱም ከዛሬ ነገ እየጨመረ ነው ያለው ፤ አይደለም ሰርቶ ማትረፍ ይቅርና ስራ በቆመበት እና ንብረት በወደመበት ወቅትም ወለዱ እየታሰበ ነው ያ ወለድ ደግሞ የወለድ ወለድ ቅጣት እየታሰበበት ነው።
➡️ ያለው ችግር የተለየ የብደር ጥቅል ካልተዘየደለት አሁን ባለው አሰራር የሚፈታ አይደለም።
➡️ የወደመው ንብረት በቢሊዮን የሚገመት ነው በዚህ ላይ ደግሞ የኢኮኖሚው ማሻሽያ ሲጨመር ችግሩን የከፋ አድርጎታል።
➡️ ጦርነቱ ከቆመ ወዲህ ባለፉት ሁለት አመታት ለክልሉ ባለሃብቶች የቀረበው ብድር 2 ቢሊዮን ብር የማይሞላ ነው ይህም ከችግሩ ስፋት ጋር አብሮ የሚሄድ አይደለም።
➡️ በቅረቡ ከብሄራዊ ባንክ ጋር ውይይት ተደርጎ ነበር በዚህም ነጋዴዎች በሐራጅ ለመሸጥ ጊዜውን ለአንድ አመት እንዲራዝም ተደርጓል ግን ይህ በቂ አይደለም።
የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
#AU #Ethiopia
46ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ የአስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ዛሬ ተጀምሯል።
በዚህም ዛሬ በተካሄደው ምርጫ #ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣለች።
@tikvahethiopia
46ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ የአስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ዛሬ ተጀምሯል።
በዚህም ዛሬ በተካሄደው ምርጫ #ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣለች።
@tikvahethiopia
" ከታክስ በፊት 34.4 ቢሊዮን ብር አትርፊያለሁ " - ኢትዮ ቴሌኮም
ኢትዮ ቴሌኮም 3.24 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞች በማፍራት አጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቹን ብዛት 80.5 ሚሊዮን ማድረሱን አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ መንፈቅ ሪፖርት ያቀረቡት የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ምን አሉ ?
➡️ 3.24 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞች አፍርተናል።
➡️ 9.3 ሚሊዮን የአዳዲስ ሲም ካርድ ሽያጭ የተከናወነ ሲሆን ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ8% ጭማሪ እንዲሁም ከእቅድ ጋር ሲነጻጸር የ113% አፈጻጸም አለው።
➡️ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 7.5 % እድገት በማሳየት የተጠቃሚዎች ቁጥር 43.5 ሚሊዮን ደርሷል።
➡️ የሞባይል ኢንተርኔት ትራፊክ ማለትም (በሞባይል ኔትወርክ የተላከ እና የተቀበለው የዲጂታል መረጃ መጠን) በተመለከተ በበጀት አመቱ እስከ ህዳር ወር ድረስ 642.2 ቢሊዮን ሜጋ ባይት ትራፊክ ተመዝግቧል። ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ48.8 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
➡️ የብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት 5% ጭማሪ በማሳየት የተጠቃሚዎቹ ቁጥር 784.1 ሺ ደርሷል።
➡️ በአጠቃላይ ከባለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የደንበኞች እድገቱ በ7.9 በመቶ አድጓል።
ኩባንያው ምን ያህል አተረፈ ?
➡️ በመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት 61.9 ቢሊዮን ገቢ አግኝተናል። ይህም የዕቅዳችን 90.7 በመቶ ያሳካ ነው።
➡️ ከታክስ መሰል ወጪዎች በፊት ያለው ምጣኔ (EBITDA) 55.5 በመቶ ነው። ከታክስ በፊት 34.4 ቢሊዮን ትርፍ ተመዝግቧል።
➡️ ከአጠቃላይ ከገቢ ውስጥ 72.61 ሚሊዮን ዶላር የሚሆነውን በውጭ ምንዛሬ የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
ኢትዮ ቴሌኮም 3.24 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞች በማፍራት አጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቹን ብዛት 80.5 ሚሊዮን ማድረሱን አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ መንፈቅ ሪፖርት ያቀረቡት የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ምን አሉ ?
➡️ 3.24 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞች አፍርተናል።
➡️ 9.3 ሚሊዮን የአዳዲስ ሲም ካርድ ሽያጭ የተከናወነ ሲሆን ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ8% ጭማሪ እንዲሁም ከእቅድ ጋር ሲነጻጸር የ113% አፈጻጸም አለው።
➡️ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 7.5 % እድገት በማሳየት የተጠቃሚዎች ቁጥር 43.5 ሚሊዮን ደርሷል።
➡️ የሞባይል ኢንተርኔት ትራፊክ ማለትም (በሞባይል ኔትወርክ የተላከ እና የተቀበለው የዲጂታል መረጃ መጠን) በተመለከተ በበጀት አመቱ እስከ ህዳር ወር ድረስ 642.2 ቢሊዮን ሜጋ ባይት ትራፊክ ተመዝግቧል። ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ48.8 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
➡️ የብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት 5% ጭማሪ በማሳየት የተጠቃሚዎቹ ቁጥር 784.1 ሺ ደርሷል።
➡️ በአጠቃላይ ከባለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የደንበኞች እድገቱ በ7.9 በመቶ አድጓል።
ኩባንያው ምን ያህል አተረፈ ?
➡️ በመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት 61.9 ቢሊዮን ገቢ አግኝተናል። ይህም የዕቅዳችን 90.7 በመቶ ያሳካ ነው።
➡️ ከታክስ መሰል ወጪዎች በፊት ያለው ምጣኔ (EBITDA) 55.5 በመቶ ነው። ከታክስ በፊት 34.4 ቢሊዮን ትርፍ ተመዝግቧል።
➡️ ከአጠቃላይ ከገቢ ውስጥ 72.61 ሚሊዮን ዶላር የሚሆነውን በውጭ ምንዛሬ የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
🔊 #የሠራተኞችድምፅ
“ ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው። ወዴት እንጩህ ? ” - ሠራተኞች
በምዕራብ አርሲ ዞን ዝዋይ ዱግዳ ወረዳ ያሉ ጤና ባለሙያዎችና ሠራተኞች “አመራሮች ደመወዛችንን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ለምን? ብሎ መጠየቅም አይቻልም” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ምሬታቸውን አሰምተዋል።
“‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ በሚል ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው" ያሉት ስሞታ አቅራቢዎቹ፣ "ወዴት እንጩህ?” ሲሉ ጠይቀዋል።
“ለቀበሌ ቤት መስሪያ" እንዲሁም "ለቡሳ ጎኖፋ” በሚል ደመወዛቸው ያለፈቃዳቸው እንደሚቆረጥ፣ የዲቲ ክፍያ በወቅቱ እንደማይከፈላቸው፣ አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ ክፍያም እንዳልተፈጸመላቸው አስረድተዋል።
“ዝም ብለው ነው የሚቆርጡብን ፈቃዳችንንም እንኳ አይጠይቁንም” ያሉ ሲሆን፣ የኑሮ ውድነቱን ተቋቁመው ቤተሰብ ማስዳደር ስላልቻሉ መፍትሄ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል።
ሠራተኞች ስላማረራቸው ጉዳይ ምን አሉ?
“ ከደመወዛችን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ያለ ማንም ፍላጎት ሰሞኑን 100% ከደመወዛችን ቆርጠዋል። ደመወዙ የሚቆረጠው ለፈረሙትም ላልፈረሙትም ነው።
በአመት 100% በደመወዝ ስኬል ነው የሚቆረጠው። ይህ በወር ከ500 እስከ 800 ሊሆን ይችላል። እንደዬ ስኬሉ መጠኑ ይለያያል። በዚህ ወር ደመወዛችን ተቆርጧል።
የዱዩቲ ክፍያም የአሁኑ ዘግይቷል። ሌላው የሦስት ወራት የዱቲ ክፍያ አልተፈጸመልንም ገና እየጠበቅን ነው። ፋይናንስ ነው ያልከፈለን። ፎርሙ ፋይናንስ ጋ ደርሷል።
የሁለት ወራት አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ አልተከፈለንም። ደመወዛችንን አናውቅም የማይቆረጥ የለም። ዝም ብለው ነው የሚቆርጡት ያለምንም ፈቃድ። እኛን አይጠይቁንም። እንደፈለጉ ነው የሚያደርጉን። ሠራተኛም አይጠይቅም።
ገንዘባችን በብዛት እየተቆረጠ ያለው ‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ ተብሎ ነው። ከዚህም በፊት ያለፍላጎታችን ይቆርጡ ነበር። የትም አቤት ቢባል መልስ አይገኝም።
ይህ ድርጊት የሚፈጸመው እኛ ወረዳ ብቻ እንጂ ሌላ ወረዳ ላይ አልሰማንም ደመወዝ እየቆረጡ ያሉት ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቅሬታው ምላሽ ለማካተት ከክልል፣ ዞን እንዲሁም ወረዳ ባለስልጣናት ለቀናት ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜው ምላሽ አልተገኘም። ሆኖም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኞች ከሆኑ በድጋሚ ጥረት ያደርጋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው። ወዴት እንጩህ ? ” - ሠራተኞች
በምዕራብ አርሲ ዞን ዝዋይ ዱግዳ ወረዳ ያሉ ጤና ባለሙያዎችና ሠራተኞች “አመራሮች ደመወዛችንን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ለምን? ብሎ መጠየቅም አይቻልም” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ምሬታቸውን አሰምተዋል።
“‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ በሚል ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው" ያሉት ስሞታ አቅራቢዎቹ፣ "ወዴት እንጩህ?” ሲሉ ጠይቀዋል።
“ለቀበሌ ቤት መስሪያ" እንዲሁም "ለቡሳ ጎኖፋ” በሚል ደመወዛቸው ያለፈቃዳቸው እንደሚቆረጥ፣ የዲቲ ክፍያ በወቅቱ እንደማይከፈላቸው፣ አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ ክፍያም እንዳልተፈጸመላቸው አስረድተዋል።
“ዝም ብለው ነው የሚቆርጡብን ፈቃዳችንንም እንኳ አይጠይቁንም” ያሉ ሲሆን፣ የኑሮ ውድነቱን ተቋቁመው ቤተሰብ ማስዳደር ስላልቻሉ መፍትሄ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል።
ሠራተኞች ስላማረራቸው ጉዳይ ምን አሉ?
“ ከደመወዛችን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ያለ ማንም ፍላጎት ሰሞኑን 100% ከደመወዛችን ቆርጠዋል። ደመወዙ የሚቆረጠው ለፈረሙትም ላልፈረሙትም ነው።
በአመት 100% በደመወዝ ስኬል ነው የሚቆረጠው። ይህ በወር ከ500 እስከ 800 ሊሆን ይችላል። እንደዬ ስኬሉ መጠኑ ይለያያል። በዚህ ወር ደመወዛችን ተቆርጧል።
የዱዩቲ ክፍያም የአሁኑ ዘግይቷል። ሌላው የሦስት ወራት የዱቲ ክፍያ አልተፈጸመልንም ገና እየጠበቅን ነው። ፋይናንስ ነው ያልከፈለን። ፎርሙ ፋይናንስ ጋ ደርሷል።
የሁለት ወራት አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ አልተከፈለንም። ደመወዛችንን አናውቅም የማይቆረጥ የለም። ዝም ብለው ነው የሚቆርጡት ያለምንም ፈቃድ። እኛን አይጠይቁንም። እንደፈለጉ ነው የሚያደርጉን። ሠራተኛም አይጠይቅም።
ገንዘባችን በብዛት እየተቆረጠ ያለው ‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ ተብሎ ነው። ከዚህም በፊት ያለፍላጎታችን ይቆርጡ ነበር። የትም አቤት ቢባል መልስ አይገኝም።
ይህ ድርጊት የሚፈጸመው እኛ ወረዳ ብቻ እንጂ ሌላ ወረዳ ላይ አልሰማንም ደመወዝ እየቆረጡ ያሉት ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቅሬታው ምላሽ ለማካተት ከክልል፣ ዞን እንዲሁም ወረዳ ባለስልጣናት ለቀናት ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜው ምላሽ አልተገኘም። ሆኖም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኞች ከሆኑ በድጋሚ ጥረት ያደርጋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#ፋይዳ #NationalID
" ከፍርድ ቤት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጥያቄው ከዛ እስካልመጣ [የግል መረጃ] ለመንግስት የሥራ አስፈጻሚ አይሰጥም " - አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ
ኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራምን በይፋ ካስተዋወቀችበት ጀምሮ እስከ አሁን 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበዋል፤ እስካሁንም ይህንን አገልግሎት ከ50 በላይ ከሆኑ አገልግሎቶች ጋር የማስተሳሰር ሥራም ተሰርቷል።
ይህ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ መንግስት ከሚበጅተው በጀት በተጨማሪ ለተግባራዊነቱ ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ 300 ሚሊዮን ዶላር ብድር እንዲሁም 50 ሚሊዮን የሚሆን ድጋፍ አግኝታለች።
የፋይዳ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ትግበራን ዘግይታ መጀመሯ ላይ ቢስማሙም በአንጻሩ ግን የተሻለ ቴክኖሎጂ እና ልዩ ልዩ እሳቤዎችን እንድታካትት ረድቷቷል ይላሉ።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በወሳኝ አገልግሎቶች ላይ በአስገዳጅነት ጭምር መቅረቡ የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ከፍ እንዳደረገው ይታመናል። አሁን ላይ በቀን ከ60ሺ ሰዎች በላይ የመመዝገብ አቅም መፈጠሩን ከፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ያገኘነው መረጃም ያመለክታል።
አሁን ካሉት የመመዝገቢያ ሳጥኖች ተጨማሪ በቅርቡ 3000 የሚያህል እንደሚጨመር ዋና ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ይህም የተመዝጋቢዎችን ቁጥር በዚህ ዓመት መጨረሻ ወደ 30 ሚሊዮን ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የጣት አሻራ የሰጡ ዜጎች ብዛት 33 ሚሊዮን፤ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN Number) ያገኙ ዜጎች 5.6 ሚሊዮን በላይ እንደዮኑ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የባዮሜትሪክ ዳታን መሰረት ያደረገ የዲጂታል መታወቂያ ተግባራዊ ያደረጉ ሲሆን ለአብነትም ናይጄሪያ በዓለም ባንክ ድጋፍ ከ10 ዓመታት በላይ በፈጀው ጉዞዋ ከ107 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን መዝግባለች።
ሀገራት የባዮሜትሪክ መረጃዎችን ያካተተ ምዝገባ በሚያከናውኑበት ወቅት በመሰረታዊነት ሦስት ተግዳሮቶች ይገጥሟቸዋል። እነዚህም ከዜጎች ጋር ያለ የተግባቦት ክፍተት፤ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና የደኅንነት ጥያቄዎች ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከቤተሰቦቹ የተነሱ ጥያቄዎችን ሰብስቦ ምላሽ እንዲሰጥባቸው ለጽ/ቤቱ አቅርቧል።
በተለይም ከመሰረታዊ ዓላማ እና ከግል መረጃ ደኅንነት ጋር የተያያዙ፤ ከቤተሰቡ የተሰበሰቡ ጥያቄዎችን ለፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ምላሽ እንዲሰጥባቸው አድርጓል።
የፋይዳ ዋና ዓላማው ምንድን ነው?
"ፋይዳ" ከሌሎች መታወቂያዎች ጋር ለንጽጽር የሚቀርብ እንዳልሆነ ዋና ሥራ አስኪያጁ ያስረዳሉ። ይህም ፋይዳ የተናበበ የዜጎች መረጃ በብሔራዊ ደረጃ እንዲኖር የሚያስችል መሰረተ ልማት እንደሆነ ነው የሚገልጹት።
አቶ ዮዳሄ፥ "ፋይዳ እንደ Social Security ቁጥር ነው" በማለትም አሁን ላይ ከሌሎች መታወቂያዎች ጋር የሚደረጉ ንጽጽሮች ይህን ካለመረዳት እንደሆነ ይጠቅሳሉ።
ሌሎች መታወቂያዎችንስ ይተካል ?
ፋይዳ፤ የነዋሪነት መታወቂያ ላይ ያለው መረጃ ከፖስፖርት መረጃ ጋር እንዲሁም ከጤና፤ ከፋይናንስ መሰል አገልገሎቶች ጋር ትስስር እንዲፈጠር የሚያስችል እንጂ ሌሎቹን የመተካት ዓላማ እንደሌለው ገልጸዋል። "ሲስተሞቹ እየተናበቡ ሲሄዱ ነው ብዙ ጥቅም ማግኘት የሚቻለው" ሲሉ ዋና ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል።
ለምን የደም አይነት አልተካተተም ?
የደም አይነትም ሆነ የእናት ስም በፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ የማይሰበሰቡት ለሚሰጠው መረጃ ማረጋገጫ ማቅረብ አስቸጋሪ በመሆኑና ለሲስተሙ የተመጠነ መረጃ መውሰድ (Data Minimization) እንደ ስትራቴጂ በመያዙ መሆኑን ዋና ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል።
የሚሰበሰበው መረጃ የት ይቀመጣል ?
የዜጎች የግል መረጃ ከተሰበሰበ በኋላ ደኅንነቱ በተጠበቀ በብሔራዊ መረጃ ቋት እንደሚቀመጥ የገለጹት አቶ ዮዳሄ፥ የተቋማቸው ዋና ተልዕኮም ይሄንን ብዙ ሀብት የወጣበት መረጃ በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ እንዲሁም ከተጠቃሚ አካላት ጋር ማስተሳሰር እንደሆነ አስረድተዋል።
የዜጎች የግል መረጃ ለሦስተኛ ወገን ተላልፎ ይሰጣል ?
በርካቶች በስጋት የሚጠቅሱት አንዱ ዋነኛ ጉዳይ መረጃቸው ለሦስተኛ ወገን ተላልፎ ስለመሰጠቱ ነው። ለዚህ ጥያቄ አቶ ዮዳሄ ሲመልሱ "ከፍርድ ቤት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጥያቄው ከዛ እስካልመጣ [የግል መረጃ] ለመንግስት የሥራ አስፈጻሚ አይሰጥም" ብለዋል።
ከዚህ በላይ በአግባቡ ዲዛይን ካልተደረገ የግል መረጃን አደጋ ላይ የሚጥለው ብለው ያነሱት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከባለቤቱ ፈቃድ ውጪ እርስ በእርስ የሚያወሩ ከሆነ እንደሆነ አስረድተዋል።
ለዚህም በቅርቡ ላይ "Verify Fayda 2" የተሰኘ ሲስተም ማበልጸጋቸውን በመጥቀስ ለሁሉም የተለየ Token እንዲኖራቸውና የሚያስፈልጋቸውንና የተፈቀደላቸውን መረጃ ብቻ እንዲወስዱ የሚያስችልና ያለ መረጃ ባለቤቱ ፈቃድ ሁለት ተቋማት እርስ በእርስ መረጃ እንዳይቀያየሩ የሚያስችል እንደሆነ ጠቅሰዋል።
ፋይዳ ለምን አስገዳጅ ሆነ ?
አንዳንድ ተቋማት ፋይዳን ግዳጅ ሲያደርጉት አንዳንድ ተቋማት ደግሞ ሳይቀበሉ ሲቀሩ ይስተዋላል። ይህንን አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስኪያጁ "ፋይዳ ስላለኝ መኪና ልንዳ ማለት አትችልም፤ እንዲሁ ፖስፖርት ለማውጣት ሌሎች የሚያስፈልጉ ነገሮች አሉ" ሲሉ ፋይዳን አስገዳጅ የማድረግ እና ያለማድረግ ጉዳይ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ እንደሚወሰን ገልጸዋል።
ከሁሉም ነገር ጋር እንዲተሳሰር እንደማይጠበቅ የገለጹት አቶ ዮዳሄ ለዲጂታል ኢኮኖሚው ከሚጠቅሙ አገልግሎት ጋር በዋነኛነት እንደሚያያዝ አንስተዋል።
ለአብነትም በቅርቡ ሲም ካርድ ለማውጣት ፋይዳ በግዳጅነት እንደሚቀመጥ እንዲሁም በፖስፖርት እና በአዲስ አበባ ነዋሪነት መታወቂዎች ላይ የፋይዳ ቁጥር እንደሚካተት አንስተዋል።
ፋይዳ በቀጣዩ ምርጫ ላይ አገልግሎት ላይ ይውላል ?
አቶ ዮዳሄ ምርጫ ቦርድ ሲስተም ቢኖራቸውና ትስስር መፍጠር ከተቻለ ተቋማቸው ዝግጁ መሆኑን ገልጸው " ለዩኒክነስ ያስፈልገናል ካሉ ቢያስተሳስሩት ደስ ይለናል . . . እንኳን እንደ ምርጫ ቦርድ አይነት ትልቅ የዲሞክራሲ ተቋም ጋር ቀርቶ ከፊንቴኮች ጋርም ትስስር ፈጥረናል" ሲሉ ምላሻቸውን አስቀምጠዋል።
📱 አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሰጡትን ምላሾች ይመልከቱ https://youtu.be/b_X_LnM4cTA?feature=shared
@tikvahethiopia
" ከፍርድ ቤት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጥያቄው ከዛ እስካልመጣ [የግል መረጃ] ለመንግስት የሥራ አስፈጻሚ አይሰጥም " - አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ
ኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራምን በይፋ ካስተዋወቀችበት ጀምሮ እስከ አሁን 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበዋል፤ እስካሁንም ይህንን አገልግሎት ከ50 በላይ ከሆኑ አገልግሎቶች ጋር የማስተሳሰር ሥራም ተሰርቷል።
ይህ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ መንግስት ከሚበጅተው በጀት በተጨማሪ ለተግባራዊነቱ ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ 300 ሚሊዮን ዶላር ብድር እንዲሁም 50 ሚሊዮን የሚሆን ድጋፍ አግኝታለች።
የፋይዳ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ትግበራን ዘግይታ መጀመሯ ላይ ቢስማሙም በአንጻሩ ግን የተሻለ ቴክኖሎጂ እና ልዩ ልዩ እሳቤዎችን እንድታካትት ረድቷቷል ይላሉ።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በወሳኝ አገልግሎቶች ላይ በአስገዳጅነት ጭምር መቅረቡ የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ከፍ እንዳደረገው ይታመናል። አሁን ላይ በቀን ከ60ሺ ሰዎች በላይ የመመዝገብ አቅም መፈጠሩን ከፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ያገኘነው መረጃም ያመለክታል።
አሁን ካሉት የመመዝገቢያ ሳጥኖች ተጨማሪ በቅርቡ 3000 የሚያህል እንደሚጨመር ዋና ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ይህም የተመዝጋቢዎችን ቁጥር በዚህ ዓመት መጨረሻ ወደ 30 ሚሊዮን ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የጣት አሻራ የሰጡ ዜጎች ብዛት 33 ሚሊዮን፤ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN Number) ያገኙ ዜጎች 5.6 ሚሊዮን በላይ እንደዮኑ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የባዮሜትሪክ ዳታን መሰረት ያደረገ የዲጂታል መታወቂያ ተግባራዊ ያደረጉ ሲሆን ለአብነትም ናይጄሪያ በዓለም ባንክ ድጋፍ ከ10 ዓመታት በላይ በፈጀው ጉዞዋ ከ107 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን መዝግባለች።
ሀገራት የባዮሜትሪክ መረጃዎችን ያካተተ ምዝገባ በሚያከናውኑበት ወቅት በመሰረታዊነት ሦስት ተግዳሮቶች ይገጥሟቸዋል። እነዚህም ከዜጎች ጋር ያለ የተግባቦት ክፍተት፤ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና የደኅንነት ጥያቄዎች ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከቤተሰቦቹ የተነሱ ጥያቄዎችን ሰብስቦ ምላሽ እንዲሰጥባቸው ለጽ/ቤቱ አቅርቧል።
በተለይም ከመሰረታዊ ዓላማ እና ከግል መረጃ ደኅንነት ጋር የተያያዙ፤ ከቤተሰቡ የተሰበሰቡ ጥያቄዎችን ለፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ምላሽ እንዲሰጥባቸው አድርጓል።
የፋይዳ ዋና ዓላማው ምንድን ነው?
"ፋይዳ" ከሌሎች መታወቂያዎች ጋር ለንጽጽር የሚቀርብ እንዳልሆነ ዋና ሥራ አስኪያጁ ያስረዳሉ። ይህም ፋይዳ የተናበበ የዜጎች መረጃ በብሔራዊ ደረጃ እንዲኖር የሚያስችል መሰረተ ልማት እንደሆነ ነው የሚገልጹት።
አቶ ዮዳሄ፥ "ፋይዳ እንደ Social Security ቁጥር ነው" በማለትም አሁን ላይ ከሌሎች መታወቂያዎች ጋር የሚደረጉ ንጽጽሮች ይህን ካለመረዳት እንደሆነ ይጠቅሳሉ።
ሌሎች መታወቂያዎችንስ ይተካል ?
ፋይዳ፤ የነዋሪነት መታወቂያ ላይ ያለው መረጃ ከፖስፖርት መረጃ ጋር እንዲሁም ከጤና፤ ከፋይናንስ መሰል አገልገሎቶች ጋር ትስስር እንዲፈጠር የሚያስችል እንጂ ሌሎቹን የመተካት ዓላማ እንደሌለው ገልጸዋል። "ሲስተሞቹ እየተናበቡ ሲሄዱ ነው ብዙ ጥቅም ማግኘት የሚቻለው" ሲሉ ዋና ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል።
ለምን የደም አይነት አልተካተተም ?
የደም አይነትም ሆነ የእናት ስም በፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ የማይሰበሰቡት ለሚሰጠው መረጃ ማረጋገጫ ማቅረብ አስቸጋሪ በመሆኑና ለሲስተሙ የተመጠነ መረጃ መውሰድ (Data Minimization) እንደ ስትራቴጂ በመያዙ መሆኑን ዋና ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል።
የሚሰበሰበው መረጃ የት ይቀመጣል ?
የዜጎች የግል መረጃ ከተሰበሰበ በኋላ ደኅንነቱ በተጠበቀ በብሔራዊ መረጃ ቋት እንደሚቀመጥ የገለጹት አቶ ዮዳሄ፥ የተቋማቸው ዋና ተልዕኮም ይሄንን ብዙ ሀብት የወጣበት መረጃ በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ እንዲሁም ከተጠቃሚ አካላት ጋር ማስተሳሰር እንደሆነ አስረድተዋል።
የዜጎች የግል መረጃ ለሦስተኛ ወገን ተላልፎ ይሰጣል ?
በርካቶች በስጋት የሚጠቅሱት አንዱ ዋነኛ ጉዳይ መረጃቸው ለሦስተኛ ወገን ተላልፎ ስለመሰጠቱ ነው። ለዚህ ጥያቄ አቶ ዮዳሄ ሲመልሱ "ከፍርድ ቤት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጥያቄው ከዛ እስካልመጣ [የግል መረጃ] ለመንግስት የሥራ አስፈጻሚ አይሰጥም" ብለዋል።
ከዚህ በላይ በአግባቡ ዲዛይን ካልተደረገ የግል መረጃን አደጋ ላይ የሚጥለው ብለው ያነሱት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከባለቤቱ ፈቃድ ውጪ እርስ በእርስ የሚያወሩ ከሆነ እንደሆነ አስረድተዋል።
ለዚህም በቅርቡ ላይ "Verify Fayda 2" የተሰኘ ሲስተም ማበልጸጋቸውን በመጥቀስ ለሁሉም የተለየ Token እንዲኖራቸውና የሚያስፈልጋቸውንና የተፈቀደላቸውን መረጃ ብቻ እንዲወስዱ የሚያስችልና ያለ መረጃ ባለቤቱ ፈቃድ ሁለት ተቋማት እርስ በእርስ መረጃ እንዳይቀያየሩ የሚያስችል እንደሆነ ጠቅሰዋል።
ፋይዳ ለምን አስገዳጅ ሆነ ?
አንዳንድ ተቋማት ፋይዳን ግዳጅ ሲያደርጉት አንዳንድ ተቋማት ደግሞ ሳይቀበሉ ሲቀሩ ይስተዋላል። ይህንን አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስኪያጁ "ፋይዳ ስላለኝ መኪና ልንዳ ማለት አትችልም፤ እንዲሁ ፖስፖርት ለማውጣት ሌሎች የሚያስፈልጉ ነገሮች አሉ" ሲሉ ፋይዳን አስገዳጅ የማድረግ እና ያለማድረግ ጉዳይ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ እንደሚወሰን ገልጸዋል።
ከሁሉም ነገር ጋር እንዲተሳሰር እንደማይጠበቅ የገለጹት አቶ ዮዳሄ ለዲጂታል ኢኮኖሚው ከሚጠቅሙ አገልግሎት ጋር በዋነኛነት እንደሚያያዝ አንስተዋል።
ለአብነትም በቅርቡ ሲም ካርድ ለማውጣት ፋይዳ በግዳጅነት እንደሚቀመጥ እንዲሁም በፖስፖርት እና በአዲስ አበባ ነዋሪነት መታወቂዎች ላይ የፋይዳ ቁጥር እንደሚካተት አንስተዋል።
ፋይዳ በቀጣዩ ምርጫ ላይ አገልግሎት ላይ ይውላል ?
አቶ ዮዳሄ ምርጫ ቦርድ ሲስተም ቢኖራቸውና ትስስር መፍጠር ከተቻለ ተቋማቸው ዝግጁ መሆኑን ገልጸው " ለዩኒክነስ ያስፈልገናል ካሉ ቢያስተሳስሩት ደስ ይለናል . . . እንኳን እንደ ምርጫ ቦርድ አይነት ትልቅ የዲሞክራሲ ተቋም ጋር ቀርቶ ከፊንቴኮች ጋርም ትስስር ፈጥረናል" ሲሉ ምላሻቸውን አስቀምጠዋል።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM