አቢሲንያ ባንክ
ባንካችን ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በካፌ የሚሰጠውን ማዕከል በድምቀት አስመረቀ!
ባንካችን አቢሲንያ በዋናው መስሪያ ቤት በሚገኘውና ከጫካ ቡና ጋር በመተባበር የከፈተውን ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በካፌ የሚሰጠውን ማዕከል በትላንትናው ዕለት ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም የባንካችን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ በቃሉ ዘለቀ፣ የጫካ ቡና ባለቤት አቶ ብስራት በላይ እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል፡፡
ይህ ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በካፌ በውስጡ በሚገኙ የኢንተርአክቲቨ ቴለር ማሽኖችና (ITM) የራስ አገዝ አገልግሎት መስጠት በሚችሉ ታብሌቶች አማካኝነት ደንበኞች ከቅርንጫፎች ማግኘት የሚችሉትን የባንክ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡
በተጨማሪም በማዕከሉ ውስጥ በሚሰጠው የካፌና የሬስቶራንት አገልግሎት ከጥሬ ገንዘብና ከወረቀት ንክኪ ነጻ (Cashless and Paperless) መልኩ በተለያዩ የዲጅታል አማራጮች የአገልግሎት ክፍያ የሚስተናገድ ይሆናል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ሊንኩን ይጠቀሙ፡-https://surl.li/ypzbwf
ባንካችን ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በካፌ የሚሰጠውን ማዕከል በድምቀት አስመረቀ!
ባንካችን አቢሲንያ በዋናው መስሪያ ቤት በሚገኘውና ከጫካ ቡና ጋር በመተባበር የከፈተውን ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በካፌ የሚሰጠውን ማዕከል በትላንትናው ዕለት ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም የባንካችን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ በቃሉ ዘለቀ፣ የጫካ ቡና ባለቤት አቶ ብስራት በላይ እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል፡፡
ይህ ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በካፌ በውስጡ በሚገኙ የኢንተርአክቲቨ ቴለር ማሽኖችና (ITM) የራስ አገዝ አገልግሎት መስጠት በሚችሉ ታብሌቶች አማካኝነት ደንበኞች ከቅርንጫፎች ማግኘት የሚችሉትን የባንክ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡
በተጨማሪም በማዕከሉ ውስጥ በሚሰጠው የካፌና የሬስቶራንት አገልግሎት ከጥሬ ገንዘብና ከወረቀት ንክኪ ነጻ (Cashless and Paperless) መልኩ በተለያዩ የዲጅታል አማራጮች የአገልግሎት ክፍያ የሚስተናገድ ይሆናል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ሊንኩን ይጠቀሙ፡-https://surl.li/ypzbwf
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " እስካሁን በህይወት የተገኘ የለም " በአሜሪካ ፤ ዋሽንግቶን ዲሲ የመንገደኞች አውሮፕላን ከጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ በ " ፖቶማክ ወንዝ " ውስጥ ከተከሰከሰበት አደጋ የነፍስ አድን ሰራተኞች እስካሁን አንድም ሰው በህይወት አላገኙም። የነፍስ አድን ስራው ግን መቀጠሉ ተነግሯል። አውሮፕላኑ 60 መንገደኞችን እና 4 የበረራ ሰራተኞችን ይዞ ነው 3 ሰው ከያዘው የጦር ሂሊኮፕተር ጋር…
#USA
" ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " - ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ
በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ በፊላደልፊያ ከተማ ሰሜን ምሥራቅ ክፍል አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከሰከሰ።
የሕክምና አውሮፕላኑ ድርጅት-ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ በሰጠው መግለጫ ፤ ጄቱ አርብ ምሽት አንድ ታማሚ ሕፃንና አስታማሚዋን እናቷን እንዲሁም 4 የበረራ አስተናጋጆችን አሳፍሮ እየተጓዘ ነበር ።
በአውሮፕላኑ ላይ ተሳፍራ የነበረችው ሕፃን ሕይወቷን አደጋ ላይ በሚጥል የጤና እክል የነበረባት ሲሆን በአሜሪካ ሕክምና አድርጋ ወደ ሜክሲኮ ቲጁዋና እየተጓዘች እንደነበር የአየር አምቡላንስ ድርጅቱ ለኤንቢሲ ኒውስ ተናግረዋል።
ከእናት እና ልጅ በተጨማሪም አብራሪው ፣ረዳት አብራሪው ፣ ዶክተር እና የመድሃኒት ባለሙያ በአውሮፕላኑ ውስጥ ነበሩ።
ድርጅቱ " ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " ብሏል።
አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት አካባቢም ቤቶች እና ተሽከርካሪዎች በእሳት የተያያዙ ሲሆን መሬት ላይ የነበሩ ሰዎችም ለጉዳት መዳረጋቸው ተገልጿል።
የግዛቷ አስተዳዳር " የሕይወት መጥፋት እንደሚኖር እናውቃለን፤ አደጋው አሳዛኝ ነው " ብሏል።
የፊላደልፊያ ከንቲባ ቺርል ፓርከር የከተማዋ ባለስልጣናት በአደጋው የደረሰው ጉዳት መጠን ምን ያህል እንደሆነ አለማወቃቸውን ገልጸው ፤ በአደጋው የተጎዱ ወገኖችን በፀሎት እንዲታሰቡ ጠይቀዋል።
እስካሁን በህይወት ያለ ሰው ስለመኖሩ ማረጋገጥ አልተቻለም።
ከቀናት በፊት በዋሽንግቶን ዲሲ የመንገደኞች አውሮፕላን ከጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ ወንዝ ላይ ከተከሰከሰ በኃላ በህይወት የተረፈ ሰው አልተገኘም።
መረጃው ከቢቢሲ እና ኤንቢሲ ኒውስ የተውጣጣ ነው።
ቪድዮ ፦ ፌርበክ
@tikvahethiopia
" ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " - ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ
በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ በፊላደልፊያ ከተማ ሰሜን ምሥራቅ ክፍል አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከሰከሰ።
የሕክምና አውሮፕላኑ ድርጅት-ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ በሰጠው መግለጫ ፤ ጄቱ አርብ ምሽት አንድ ታማሚ ሕፃንና አስታማሚዋን እናቷን እንዲሁም 4 የበረራ አስተናጋጆችን አሳፍሮ እየተጓዘ ነበር ።
በአውሮፕላኑ ላይ ተሳፍራ የነበረችው ሕፃን ሕይወቷን አደጋ ላይ በሚጥል የጤና እክል የነበረባት ሲሆን በአሜሪካ ሕክምና አድርጋ ወደ ሜክሲኮ ቲጁዋና እየተጓዘች እንደነበር የአየር አምቡላንስ ድርጅቱ ለኤንቢሲ ኒውስ ተናግረዋል።
ከእናት እና ልጅ በተጨማሪም አብራሪው ፣ረዳት አብራሪው ፣ ዶክተር እና የመድሃኒት ባለሙያ በአውሮፕላኑ ውስጥ ነበሩ።
ድርጅቱ " ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " ብሏል።
አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት አካባቢም ቤቶች እና ተሽከርካሪዎች በእሳት የተያያዙ ሲሆን መሬት ላይ የነበሩ ሰዎችም ለጉዳት መዳረጋቸው ተገልጿል።
የግዛቷ አስተዳዳር " የሕይወት መጥፋት እንደሚኖር እናውቃለን፤ አደጋው አሳዛኝ ነው " ብሏል።
የፊላደልፊያ ከንቲባ ቺርል ፓርከር የከተማዋ ባለስልጣናት በአደጋው የደረሰው ጉዳት መጠን ምን ያህል እንደሆነ አለማወቃቸውን ገልጸው ፤ በአደጋው የተጎዱ ወገኖችን በፀሎት እንዲታሰቡ ጠይቀዋል።
እስካሁን በህይወት ያለ ሰው ስለመኖሩ ማረጋገጥ አልተቻለም።
ከቀናት በፊት በዋሽንግቶን ዲሲ የመንገደኞች አውሮፕላን ከጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ ወንዝ ላይ ከተከሰከሰ በኃላ በህይወት የተረፈ ሰው አልተገኘም።
መረጃው ከቢቢሲ እና ኤንቢሲ ኒውስ የተውጣጣ ነው።
ቪድዮ ፦ ፌርበክ
@tikvahethiopia
" ላለፉት አምስት አመታት ከሳሽ እንጂ አማራጭ ሃሳብ ይዞ የሚመጣ ግለሰብ፣ቡድን እና ፓርቲ አላየንም " - ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር)
ከትላንትና በስቲያ የተጀመረው የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ቅዳሜ ሲካሄድ የዋለ ሲሆን ዛሬ እሁድ ማጠቃለያውን ያገኝቷል።
ጠቅላላ ጉባኤው በፓርቲው ፕሬዜዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመክፈቻ ንግግር የተከፈተ ሲሆን በጉባኤው የሃገር ውስጥ እንዲሁም የውጭ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ተገኝተውበት ነበር።
" ከቃል እስከ ባህል " በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኘው የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በርካታ ውሳኔዎች ይወሰኑበታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን እስከሚቀጥለው ጉባኤ ድረስ ፓርቲውን የሚመሩ ከፍተኛ አመራሮች በጉባኤው ላይ እንደሚመረጡ ይጠበቃል።
በጉባኤው መክፈቻ ላይ የፓርቲው ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ዘለግ ያለ ንግግር አሰምተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለግማሽ ሰዓት በሚጠጋ የመክፈቻ ንግግራቸው " ላለፉት አምስት አመታት ከሳሽ እንጂ አማራጭ ሃሳብ ይዞ የመጣ ግለሰብ፣ ቡድን እና ፓርቲ አላየንም " ሲሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የተቹ ሲሆን ሃገር በቀል እሳቤዎችን ይዞ ለሚመጣ ፓርቲ አብረን ለመስራት ዝግጁ ነን ሲሉ ተደምጠዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ እየታዩ ላሉ ግጭቶች እና አለመግባባቶችም " ትላንት ፖለቲካ ሲያንቦጫርቁ የነበሩ " ያሏቸውን አካላት ተጠያቂ አድርገዋል።
ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው በዝርዝር ምን አሉ ?
" የኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ ታሪክ በጣም አጭር ነው 60 ዓመት ያልሞላው ታሪክ ነው ያለው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት 50 ዓመታት የነበረን የፓርቲ ፖለቲካ ልምምድ የምንጠላውን አብዝተን መውቀስ ፣ልናፈርስ ልንንድ ያሰብነውን አብዝተን በብዙ ማስረጃ መክሰስ እንጂ ልንገነባ የምናስበውን ፣ልናመጣ የምንፈልገውን ለውጥ ማመላከት ላይ ውስንነት ነበረብን።
ብልጽግና ሊያፈርስ የሚፈልገው በርካታ ኋላ ቀር አሰራሮች እና ልምምዶች ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ።
ብልጽግና ለኢትዮጵያ ፍቱን መድኃኒት መደመር ነው ብሎ ሃሳብ ይዞ ሲመጣ ላለፉት አምስት አመታት ከሳሽ እንጂ አማራጭ ሃሳብ ይዞ የሚመጣ ግለሰብ፣ ቡድን እና ፓርቲ አላየንም።
ሃሳብ የለሽ ፖለቲከኞች፣ ሃሳብ የለሽ ፓርቲዎች ለአጭር ጊዜ ድል የረጅም ጊዜ መከራን ያመጡብናል ።
ቶርቸር በኢትዮጵያ ይቁም ብለን ላለፉት ስድስት ዓመታት ብታምኑም ባታምኑም አንድ ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ ቶርች አይደረግም በዚህም እኛ እንኮራለን።
አባቶቻችን ፖለቲካን በቅጡ አልተለማመዱም ሃገርኛ ሃሳብ አላፈለቁም በተዋሱት ሃሳብ ሲጨቃጨቁ እና ሲጋደሉ የኖሩ ስለሆነ አሁንም ያን ማስቀጠል ይፈልጋሉ።
በኦሮሚያ ግጭት አለ ፣በአማራ ግጭት አለ፣በትግራይ ግጭት አለ በተለያየ ቦታ ግጭት አለ የዚህ ግጭት ጠንሳሽ ጨማቂዎች ትላንት ፖለቲካ ሲያንቦጫርቁ የነበሩ ሰዎች ናቸው " ብለዋል።
ዛሬ እሁድ በጠቅላላ ጉባኤ የመሳተፍ ዕድል የሚያገኙት 225 የብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መሆናቸውን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ከጉባኤው ቀደም ብሎ በሰጡት መግለጫ ማሳወቃቸው ይታወሳል።
@tikvahethiopia
ከትላንትና በስቲያ የተጀመረው የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ቅዳሜ ሲካሄድ የዋለ ሲሆን ዛሬ እሁድ ማጠቃለያውን ያገኝቷል።
ጠቅላላ ጉባኤው በፓርቲው ፕሬዜዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመክፈቻ ንግግር የተከፈተ ሲሆን በጉባኤው የሃገር ውስጥ እንዲሁም የውጭ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ተገኝተውበት ነበር።
" ከቃል እስከ ባህል " በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኘው የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በርካታ ውሳኔዎች ይወሰኑበታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን እስከሚቀጥለው ጉባኤ ድረስ ፓርቲውን የሚመሩ ከፍተኛ አመራሮች በጉባኤው ላይ እንደሚመረጡ ይጠበቃል።
በጉባኤው መክፈቻ ላይ የፓርቲው ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ዘለግ ያለ ንግግር አሰምተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለግማሽ ሰዓት በሚጠጋ የመክፈቻ ንግግራቸው " ላለፉት አምስት አመታት ከሳሽ እንጂ አማራጭ ሃሳብ ይዞ የመጣ ግለሰብ፣ ቡድን እና ፓርቲ አላየንም " ሲሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የተቹ ሲሆን ሃገር በቀል እሳቤዎችን ይዞ ለሚመጣ ፓርቲ አብረን ለመስራት ዝግጁ ነን ሲሉ ተደምጠዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ እየታዩ ላሉ ግጭቶች እና አለመግባባቶችም " ትላንት ፖለቲካ ሲያንቦጫርቁ የነበሩ " ያሏቸውን አካላት ተጠያቂ አድርገዋል።
ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው በዝርዝር ምን አሉ ?
" የኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ ታሪክ በጣም አጭር ነው 60 ዓመት ያልሞላው ታሪክ ነው ያለው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት 50 ዓመታት የነበረን የፓርቲ ፖለቲካ ልምምድ የምንጠላውን አብዝተን መውቀስ ፣ልናፈርስ ልንንድ ያሰብነውን አብዝተን በብዙ ማስረጃ መክሰስ እንጂ ልንገነባ የምናስበውን ፣ልናመጣ የምንፈልገውን ለውጥ ማመላከት ላይ ውስንነት ነበረብን።
ብልጽግና ሊያፈርስ የሚፈልገው በርካታ ኋላ ቀር አሰራሮች እና ልምምዶች ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ።
ብልጽግና ለኢትዮጵያ ፍቱን መድኃኒት መደመር ነው ብሎ ሃሳብ ይዞ ሲመጣ ላለፉት አምስት አመታት ከሳሽ እንጂ አማራጭ ሃሳብ ይዞ የሚመጣ ግለሰብ፣ ቡድን እና ፓርቲ አላየንም።
ሃሳብ የለሽ ፖለቲከኞች፣ ሃሳብ የለሽ ፓርቲዎች ለአጭር ጊዜ ድል የረጅም ጊዜ መከራን ያመጡብናል ።
ቶርቸር በኢትዮጵያ ይቁም ብለን ላለፉት ስድስት ዓመታት ብታምኑም ባታምኑም አንድ ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ ቶርች አይደረግም በዚህም እኛ እንኮራለን።
አባቶቻችን ፖለቲካን በቅጡ አልተለማመዱም ሃገርኛ ሃሳብ አላፈለቁም በተዋሱት ሃሳብ ሲጨቃጨቁ እና ሲጋደሉ የኖሩ ስለሆነ አሁንም ያን ማስቀጠል ይፈልጋሉ።
በኦሮሚያ ግጭት አለ ፣በአማራ ግጭት አለ፣በትግራይ ግጭት አለ በተለያየ ቦታ ግጭት አለ የዚህ ግጭት ጠንሳሽ ጨማቂዎች ትላንት ፖለቲካ ሲያንቦጫርቁ የነበሩ ሰዎች ናቸው " ብለዋል።
ዛሬ እሁድ በጠቅላላ ጉባኤ የመሳተፍ ዕድል የሚያገኙት 225 የብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መሆናቸውን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ከጉባኤው ቀደም ብሎ በሰጡት መግለጫ ማሳወቃቸው ይታወሳል።
@tikvahethiopia
" ከ10 ሄክታር በላይ የፓርኩ ክፍል በቃጠሎ ወድሟል " - የማዜ ብሔራዊ ፓርክ
ከትናትና በስቲያ ማምሻውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ አከባቢ የተነሳዉ እሳት ሌሊቱን ሙሉ ሳይጠፋ ማደሩንና በፓርኩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዜ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ጬማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በአከባቢው ከፓርኩ አቅራቢያ ከሚገኝ ሞርካ ቀበሌ አንድ አርሶ አደር የማሳ ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት እያካሄደ ከነበረዉ ቃጠሎ የወጣ እሳት ምሽት 12 ሰዓት አከባቢ በፓርኩ ዙሪያ የሚገኝን 5 ሄክታር ቦታ ካወደመ በኋላ ከሌሊቱ 8 ሰዓት ገደማ የፓርኩን ክፍል ማዉደም መጀመሩን የገለፁት አቶ መስፍን ከወቅቱ ነፋሻማነትና የሰዓቱ ምቹ አለመሆን የእሳት ማጥፋትን ስራ ፈትኖት እንደነበር አስታዉቀዋል።
የእሳት ማጥፋት ስራዉ ከዛሬ ማለዳ ከ12 ሰዓት ጀምሮ በተደራጀ መልኩ በአከባቢው ነዋሪዎች፣ በፀጥታ መዋቅርና በእሳት አደጋ ብርጌድ ርብርብ ሲደረግበት ቆይቶ ከፓርኩ ዉጪ 5 ሄክታር ከፓርኩ ክፍል ደግም 10 ሄክታር በላይ ካወደመ በኋላ ረፋዱ አራት አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አቶ መስፍን አስታዉቀዋል።
አቶ መስፍን አክለዉም እስካሁን በተደረገዉ ማጣራት ከፓርኩ ስነ ምህደር ዉድመት ባሻገር በአራዊቱ ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልፀዋል።
በእሳት ማጥፋቱ ስራ ከተሳተፉት የአከባቢዉ ነዋሪዎች ፣የፀጥታ መዋቅር አባላትና በሃይለማርያምና ሮማን ፋዉንዴሽን የተቋቋመው የእሳት አደጋ ብርጌድ በተጨማሪ ከወላይታ ወደ ሳዉላ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የግልና ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ሕዝቡን በማጓጓዝ ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ምስጋና አቅርበዋል።
የማዜ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ እና ጎፋ ዞኖች መካከል ቁጫ ወረዳ አከባቢ የሚገኝ ሲሆን ከአዲስ አበባ 460 ፣ከሐዋሳ 235 እንዲሁም ከጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ 196 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።
የፓርኩ አጠቃላይ ስፋት 220 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆንበሀገራችን በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘዉ የስዋይኔ ቆርኬ ጨምሮ አንበሳ፣አቦሸማኔ፣የቆላና ትልልቆቹ አጋዘኖች፣አምባራይሌና ከርከሮን ጨምሮ 39 የተለያዩ አጥቢ እንስሳቶች፣196 የአዕዋፋት ዝርያዎች እና ከ80 በላይ የእፅዋት አይነቶ እንደሚገኙበት ከማዜ ብሔራዊ ፓርክ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
ከትናትና በስቲያ ማምሻውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ አከባቢ የተነሳዉ እሳት ሌሊቱን ሙሉ ሳይጠፋ ማደሩንና በፓርኩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዜ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ጬማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በአከባቢው ከፓርኩ አቅራቢያ ከሚገኝ ሞርካ ቀበሌ አንድ አርሶ አደር የማሳ ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት እያካሄደ ከነበረዉ ቃጠሎ የወጣ እሳት ምሽት 12 ሰዓት አከባቢ በፓርኩ ዙሪያ የሚገኝን 5 ሄክታር ቦታ ካወደመ በኋላ ከሌሊቱ 8 ሰዓት ገደማ የፓርኩን ክፍል ማዉደም መጀመሩን የገለፁት አቶ መስፍን ከወቅቱ ነፋሻማነትና የሰዓቱ ምቹ አለመሆን የእሳት ማጥፋትን ስራ ፈትኖት እንደነበር አስታዉቀዋል።
የእሳት ማጥፋት ስራዉ ከዛሬ ማለዳ ከ12 ሰዓት ጀምሮ በተደራጀ መልኩ በአከባቢው ነዋሪዎች፣ በፀጥታ መዋቅርና በእሳት አደጋ ብርጌድ ርብርብ ሲደረግበት ቆይቶ ከፓርኩ ዉጪ 5 ሄክታር ከፓርኩ ክፍል ደግም 10 ሄክታር በላይ ካወደመ በኋላ ረፋዱ አራት አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አቶ መስፍን አስታዉቀዋል።
አቶ መስፍን አክለዉም እስካሁን በተደረገዉ ማጣራት ከፓርኩ ስነ ምህደር ዉድመት ባሻገር በአራዊቱ ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልፀዋል።
በእሳት ማጥፋቱ ስራ ከተሳተፉት የአከባቢዉ ነዋሪዎች ፣የፀጥታ መዋቅር አባላትና በሃይለማርያምና ሮማን ፋዉንዴሽን የተቋቋመው የእሳት አደጋ ብርጌድ በተጨማሪ ከወላይታ ወደ ሳዉላ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የግልና ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ሕዝቡን በማጓጓዝ ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ምስጋና አቅርበዋል።
የማዜ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ እና ጎፋ ዞኖች መካከል ቁጫ ወረዳ አከባቢ የሚገኝ ሲሆን ከአዲስ አበባ 460 ፣ከሐዋሳ 235 እንዲሁም ከጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ 196 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።
የፓርኩ አጠቃላይ ስፋት 220 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆንበሀገራችን በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘዉ የስዋይኔ ቆርኬ ጨምሮ አንበሳ፣አቦሸማኔ፣የቆላና ትልልቆቹ አጋዘኖች፣አምባራይሌና ከርከሮን ጨምሮ 39 የተለያዩ አጥቢ እንስሳቶች፣196 የአዕዋፋት ዝርያዎች እና ከ80 በላይ የእፅዋት አይነቶ እንደሚገኙበት ከማዜ ብሔራዊ ፓርክ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በትራፊክ አደጋ የ6 ወጣቶች ሕይወት አለፈ።
በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ " ሽቆ " ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ቡና ጭኖ ከሳይት ሲወጣ የነበረ የሠሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- 18766 ኦሮ የሆነ የጭነት መኪና ተገልብጦ የ6 ወጣቶች ሕይወት አለፈ።
ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱም ታእላውቋል።
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ደህንነት ቁጥጥር ዳይሬክቶረት ዳይሬክተር ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል ሽንኩራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፥ በመኪናዉ ላይ ሹፌርና ረዳቱን ጨምሮ አስር ሰዎች ነበሩ።
ስምንቱ ገዳ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ የቡና ሳይት የሚሰሩ ታዳጊ ወጣቶች እንደነበሩና በአደጋው ወቅት መኪናዉ ሲገለበጥ ቡናዉ በላያቸዉ ላይ በመጫኑ 6ቱ ወዲያዉኑ ሲሞቱ ሁለቱ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዉ የመጀመሪያ ሕክምና በአለታ ወንዶ ሆስፒታል ከተደረገላቸው በኋላ ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ሀዋሳ መላካቸውን ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል አስታዉቀዋል።
ዋና ኢንስፐክተሩ ሹፌሩና ረዳቱ በአሁኑ ሰዓት በአለታ ወንዶ ወረዳ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መሆናቸዉን አረጋግጠዋል።
በክልሉ በቡና ምርት ወቅት የሚኖሩ እንቅስቃሴዎች ለትራፊክ አደጋዎች የመጋለጥ ዕድልን ከፍ እንደሚያደርጉ በትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዙሪያ በሁሉም መዋቅሮች ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ ቢሆንም በቸልተኝነትና ከልክ ባለፈ በራስ መተማመን በገጠሪቱ አከባቢዎች አደጋዎች እንደሚከሰቱ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ " ሽቆ " ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ቡና ጭኖ ከሳይት ሲወጣ የነበረ የሠሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- 18766 ኦሮ የሆነ የጭነት መኪና ተገልብጦ የ6 ወጣቶች ሕይወት አለፈ።
ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱም ታእላውቋል።
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ደህንነት ቁጥጥር ዳይሬክቶረት ዳይሬክተር ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል ሽንኩራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፥ በመኪናዉ ላይ ሹፌርና ረዳቱን ጨምሮ አስር ሰዎች ነበሩ።
ስምንቱ ገዳ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ የቡና ሳይት የሚሰሩ ታዳጊ ወጣቶች እንደነበሩና በአደጋው ወቅት መኪናዉ ሲገለበጥ ቡናዉ በላያቸዉ ላይ በመጫኑ 6ቱ ወዲያዉኑ ሲሞቱ ሁለቱ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዉ የመጀመሪያ ሕክምና በአለታ ወንዶ ሆስፒታል ከተደረገላቸው በኋላ ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ሀዋሳ መላካቸውን ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል አስታዉቀዋል።
ዋና ኢንስፐክተሩ ሹፌሩና ረዳቱ በአሁኑ ሰዓት በአለታ ወንዶ ወረዳ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መሆናቸዉን አረጋግጠዋል።
በክልሉ በቡና ምርት ወቅት የሚኖሩ እንቅስቃሴዎች ለትራፊክ አደጋዎች የመጋለጥ ዕድልን ከፍ እንደሚያደርጉ በትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዙሪያ በሁሉም መዋቅሮች ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ ቢሆንም በቸልተኝነትና ከልክ ባለፈ በራስ መተማመን በገጠሪቱ አከባቢዎች አደጋዎች እንደሚከሰቱ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" ፍትህ እንሻለን ! " - ቤተሰቦች
በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ወልቂጤ ወረዳ አንዲት ህጻን ከቤት ተወስዳ ከተደፈረች በኋላ ተገድላ መገኘቷ ቁጣ ቀስቅሷል።
" በኛ የደረሰ በማንም አይድረስ " የሚሉት የተጎጂ ቤተሰብ በልጃቸው ላይ ለደረሰው ቀሰቃቂ ወንጀል " ፍትህ እንሻለለን " ብለዋል።
ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች፡፡ የ8 ዓመት ልጅ ስትሆን ገና የአንደኛ ክፍል ተማሪ ነበረች።
ባሳለፍነው ሳምንት ባለፈ ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ከትምህርት ቤት ተመልሳ ምሳ እንደበላች ከመኖሪያ ቤቷ የደረሰችበት ሳይታወቅ ቀርቷል።
በዕለቱ ፍለጋ የወጣው ቤተሰብ ታዳጊዋን ከነሙሉ ጤንነትና በህይወት ለማግኘት ግን አልታደሉም፡፡
ሮጣ ያልጠገበች ፤ ክፉ ከደጉን እንኳን የማትለይ ህፃን ለአዕምሮ በሚከብድ ሁኔታ ከተደፈረች በኋላ " እንዳትናገር በሚል " ከመኖሪያ ቤታቸው ጀርባ በቅርብ ርቀት ላይ ህይወቷ አልፎ መገኘቱን አንድ የቤተሰቧ አባል ለዶቼ ቬለ ሬድዮ ተናግረዋል።
ህፃኗ ከተገደለች በኋላ ተሰቅላ መገኘቷን የገለጹት የቤተሰብ አባሉ " ጫማዋን ያወለቁባትና የሰቀሏት ቦታ አንድ አይደለም የ50 ሜትር ገደማ ርቀት አለው " ብለዋል።
በወረዳው ኤላ ከተማ በ8 ዓመቷ ልጅ ሲምቦ ላይ የተፈጸመው ጥቃት አባት የመንግስት ሰራተኛ መሆናቸው እና በስራ ቦታ መሆናቸው እንዲሁም እናት የ2 ወር እመጫት በመሆናቸው አጋጣሚውን በመጠቀም እንደነበር የቤተሰቡ አባል ተናግረዋል።
የተጎጂ ቤተሰብ አባል የሆኑት አስተያየት ሰጪ " የህፃኗ ቤተሰብ ቤት በፊት ለፊት በኩል ሆቴል በመሆኑ የሚገባውና የሚወጣው ብዙ ነው፡፡ በጓሮ በኩል ፑል መጫወቻም አለ፡፡ ደፋሪዎችም በዚያው በጀርባ በር እንደወሰዷት ነው የቤተሰብ ስጋት " ብለዋል።
2009 ዓ.ም. የተወለደችው ትንሿ ሲምቦ ገና በ8 ዓመቷ ለዚህ እጅግ ለአሰቃቂ ድርጊት ሰለባ መሆኗ ቤተሰቦቿን ቁጭት ውስጥ ከቷል።
" ባለሙያዎች በሰውነቷ ላይ የታየውን ፈሳሽ በመውሰድ ምርመራ እያደረጉ ነው " ያሉት የቤተሰብ አባል እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋለ ተጠርጣሪ አለመኖሩንም ገልጸዋል፡፡
ባለፈው ረቡዕ ከሰዓት በኋላ 9 ሰዓት ተኩል የተገኘው የህፃኗ ሲምቦ አስክሬን በትናንትናው እለት ስርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ወልቂጤ ወረዳ አንዲት ህጻን ከቤት ተወስዳ ከተደፈረች በኋላ ተገድላ መገኘቷ ቁጣ ቀስቅሷል።
" በኛ የደረሰ በማንም አይድረስ " የሚሉት የተጎጂ ቤተሰብ በልጃቸው ላይ ለደረሰው ቀሰቃቂ ወንጀል " ፍትህ እንሻለለን " ብለዋል።
ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች፡፡ የ8 ዓመት ልጅ ስትሆን ገና የአንደኛ ክፍል ተማሪ ነበረች።
ባሳለፍነው ሳምንት ባለፈ ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ከትምህርት ቤት ተመልሳ ምሳ እንደበላች ከመኖሪያ ቤቷ የደረሰችበት ሳይታወቅ ቀርቷል።
በዕለቱ ፍለጋ የወጣው ቤተሰብ ታዳጊዋን ከነሙሉ ጤንነትና በህይወት ለማግኘት ግን አልታደሉም፡፡
ሮጣ ያልጠገበች ፤ ክፉ ከደጉን እንኳን የማትለይ ህፃን ለአዕምሮ በሚከብድ ሁኔታ ከተደፈረች በኋላ " እንዳትናገር በሚል " ከመኖሪያ ቤታቸው ጀርባ በቅርብ ርቀት ላይ ህይወቷ አልፎ መገኘቱን አንድ የቤተሰቧ አባል ለዶቼ ቬለ ሬድዮ ተናግረዋል።
ህፃኗ ከተገደለች በኋላ ተሰቅላ መገኘቷን የገለጹት የቤተሰብ አባሉ " ጫማዋን ያወለቁባትና የሰቀሏት ቦታ አንድ አይደለም የ50 ሜትር ገደማ ርቀት አለው " ብለዋል።
በወረዳው ኤላ ከተማ በ8 ዓመቷ ልጅ ሲምቦ ላይ የተፈጸመው ጥቃት አባት የመንግስት ሰራተኛ መሆናቸው እና በስራ ቦታ መሆናቸው እንዲሁም እናት የ2 ወር እመጫት በመሆናቸው አጋጣሚውን በመጠቀም እንደነበር የቤተሰቡ አባል ተናግረዋል።
የተጎጂ ቤተሰብ አባል የሆኑት አስተያየት ሰጪ " የህፃኗ ቤተሰብ ቤት በፊት ለፊት በኩል ሆቴል በመሆኑ የሚገባውና የሚወጣው ብዙ ነው፡፡ በጓሮ በኩል ፑል መጫወቻም አለ፡፡ ደፋሪዎችም በዚያው በጀርባ በር እንደወሰዷት ነው የቤተሰብ ስጋት " ብለዋል።
2009 ዓ.ም. የተወለደችው ትንሿ ሲምቦ ገና በ8 ዓመቷ ለዚህ እጅግ ለአሰቃቂ ድርጊት ሰለባ መሆኗ ቤተሰቦቿን ቁጭት ውስጥ ከቷል።
" ባለሙያዎች በሰውነቷ ላይ የታየውን ፈሳሽ በመውሰድ ምርመራ እያደረጉ ነው " ያሉት የቤተሰብ አባል እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋለ ተጠርጣሪ አለመኖሩንም ገልጸዋል፡፡
ባለፈው ረቡዕ ከሰዓት በኋላ 9 ሰዓት ተኩል የተገኘው የህፃኗ ሲምቦ አስክሬን በትናንትናው እለት ስርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ላለፉት አምስት አመታት ከሳሽ እንጂ አማራጭ ሃሳብ ይዞ የሚመጣ ግለሰብ፣ቡድን እና ፓርቲ አላየንም " - ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ከትላንትና በስቲያ የተጀመረው የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ቅዳሜ ሲካሄድ የዋለ ሲሆን ዛሬ እሁድ ማጠቃለያውን ያገኝቷል። ጠቅላላ ጉባኤው በፓርቲው ፕሬዜዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመክፈቻ ንግግር የተከፈተ ሲሆን በጉባኤው የሃገር ውስጥ…
ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።
የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) የፓርቲው ፕሬዜዳንት አድርጎ በከፍተኛ ድምጽ እንደመረጣቸው ፓርቲው አሳውቋል።
ተመራጩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ እንደፈጸሙ ተገልጿል።
በተያያዘ ዜና ጉባኤው አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚደንቶች አድርጎ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መምረጡ ተነግሯል።
ሁለቱ ምክትል ፕሬዚደንቶች በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።
@tikvahethiopia
የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) የፓርቲው ፕሬዜዳንት አድርጎ በከፍተኛ ድምጽ እንደመረጣቸው ፓርቲው አሳውቋል።
ተመራጩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ እንደፈጸሙ ተገልጿል።
በተያያዘ ዜና ጉባኤው አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚደንቶች አድርጎ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መምረጡ ተነግሯል።
ሁለቱ ምክትል ፕሬዚደንቶች በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።
@tikvahethiopia