TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
በትራፊክ አደጋ 7 ሰዎች ህይወት ወድያውኑ ተቀጠፈ።

ከሟቾች በተጨማሪ ስድስት ተጓዦች በከባድ ተጎድተዋል።

አደጋው ዛሬ ጥዋት ትግራይ ከመቐለ 50 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ወቕሮ ክልተ አውላዕሎ ዓደቀሳንድድ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ነው የደረሰው።

አደጋው የደረሰው ሚኒባስ መኪና ከቅጥቅጥ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ጋር ተጋጭተው እንደሆነ የክልተ ኣውላዕሎ ወረዳ ፖሊስ ገልጿል።

አሰቃቂ ግጭቱ የህዝብ ማመላለሻ ቅጥቅጥ አውቶቡሱ ከመቐለ ወደ ሓውዜን ሲጓዝ ሚኒባሱ ደግሞ ከሓውዜን ወደ መቐለ ሲጓዝ በጠመዝማዛ ቦታ ላይ ነው የተከሰተው።

በዚህም ሹፌሩ ጨምሮ 7 ሰዎች ወዲያው ህይወታቸው ሲያልፍ 6 ሰዎች በከባድ ሁኔታ ተጎድተዋል።

የአደጋው መነሻ እየተጣራ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

መረጃው የድምጺ ወያነ ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#USA ዶናልድ ትራምፕ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ቃለመሀላ ፈጸሙ።

ፕሬዚዳንቱ ወደ ቢሮ እንደገቡ 200 ገደማ ትዕዛዞች ላይ ፊርማቸውን እንደሚያኖሩ ተናግረዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፊርማቸውን ከሚያኖሩባቸው ትዕዛዞች መካከል ፦
- በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰነድ አልባ ስደተኞችን ከአሜሪካ ማባረር ፤
- ጾታቸውን የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት ላይ እንዳይሳተፉ ማድረግ ፤
- ብዝሀነት፣ እኩልነትና አካታችነት የሚባሉ ፖሊሲዎችን ከጦር ሠራዊቱ ማስወገድ ዋነኞቹ ናቸው።

ትዕዛዞቻቸው በፍ/ቤት ሙግት ሊቀርብባቸው ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia
እንኳን ለብርሃን ባንክ 15ኛ አመት አደረስዎ!
ያለፉትን አስራ አምስት አመታት አብራችሁን ለነበራችሁ ደንበኞቻችን በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን!


15 ዓመታት በታማኝነትና በትጋት!
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ሥራችን!
#15thanniversary #berhanbank #bank #Stressfreebanking #bankinethiopia #finance
ከዚህ በታች የተቀመጡትን ትክክለኛ የባንኩን ገፆች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ፡፡
👇👇👇
➡️ Facebook
➡️ Telegram
➡️ Instagram
➡️ Twitter
➡️ LinkedIn
#SafaricomEthiopia

🍋 እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን ! ድሮም ጥምቀት የሚያምረው በጋራ ሲያከብሩት እኮ ነው! የዕለታዊ ዳታ ጥቅሎችን ስንገዛ ለ24 የሚቆይ የ100% ጉርሻ: የድምፅ ጥቅል ስንገዛ 100% ጉርሻ እናግኝ። የበዓሉን ልዩ ድባብ ለሌሎች እናካፍል!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#MPESASafaricom
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
TIKVAH-ETHIOPIA
መታወቂያ መስጠት መቼ ይጀመራል ? " አሁን ማጣራት ጀምረናል የገቡትን መረጃዎች፣ አሰራሮችና ማኑዋሎች ጭምር ተዘጋጅቷል " - CRRSA የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከክልል ከተሞች መሸኛ ለሚያመጡ ዜጎች የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት መታወቂያ መስጠት መቼ እንደሚጀምር ጠይቀነው የሰጠንን ምላሽ በተደጋጋሚ አድርሰናችሁ ነበር። ኤጀንሲውን ከዚህ ቀደም…
#አዲስአበባ #መታወቂያ

“ ወደ 33 ሺሕ የሚሆን መረጃ ለሰላምና ጸጥታ ልከናል በየክልሉ ተጠርቶ እንዲመጣ በአንድ ወር ውስጥ ” - CRSSA

ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው ለሚመጡ ተቋርጦ የቆየው የአዲስ አበባ መታወቂያ የመስጠት አገልግሎት መቼ እንደሚጀመር ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲን በተደጋጋሚ መጠየቁ ይታወሳል።

ከዚህ ቀደም አገልግሎቱ መቼ ይጀመራል? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቀው ኤጀንሲው፣ “ በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ እንጀምራለን ” የሚል መስጠቱ አይዘነጋም።

አገልግሎቱ ባለመጀመሩ በድጋሚ መቼ እንደሚጀመር ስንጠይቀውም፣ “ ነሐሴ አጋማሽ 2016 ዓ/ም የትምህርት ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኃላ እንሰጣለን ” ነበር ያለው።

ይሁን እንጂ ከዚያ በኋላም አገልግሎቱን የመስጠት ተግባሩ ሲጓተት ቆይቷል።  

አሁንስ አገልግሎቱ ተጀመረ ?

አሁንስ ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው ለሚመጡ ተገልጋዮች የመታወቂያ አገልግሎት የመስጠት ስራው ተጀመረ ? ተብሎ የተጠየቀው ኤጀንሲው አገልግሎቱ እንደተጀመረ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የኤጀንሲው ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዮናስ አለማየሁ ምን አሉ ?

“ አገልግሎቱ ከተጀመረ ወር ሆኖታል። በሁለት መልኩ ነው ሥራውን እየሰራን ያለነው።

አንደኛው ቀርበው ሪፓርት እንዲያደርጉ፣ የፋይዳ ቅድመ ሁኔታ አደረግን። ከተጠሩት ውስጥ ቀድመው ሪፓርት ያደረጉት በጣም ጥቂት ናቸው።

ከዚያ ባሻገር ደግሞ ለሚዲያ በተደጋጋሚ እንደገለጽነው ክልል የመጡ መሸኛዎችን መልሰን ለክልል እንልካለን ማንነታቸውን ለማረጋገጥ ብለን ነበር። 

በዚህም በዛም መልኩ እንግዲህ እኛ ጋ ሪፓርት ያደረጉ ሰዎች ቁጥር ካመለከቱት ቁጥር ጋር ሲያያዝ በጣም አንሷል መጥተው ሪፓርት ያደረጉ ማለት ነው።

እናጣራለን ስንልም ሀሰተኛ ሰነድ ላይ ያለው ሁኔታ ትንሽ ፍርሃት ፈጥሯል መሰለኝ። ወደ 33 ሺሕ የሚሆን መረጃ ለሰላምና ጸጥታ ልከናል በየክልሉ ተጠርቶ እንዲመጣ በአንድ ወር ውስጥ።

ያ ማለት ሀሰተኛ መሸኛ ይዞ መጥቶ እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ያደረገውን፣ ሀሰተኛ መሸኛ ያስገባውንም ሰው ወደ ወንጀል ተጠያቂነት እናመጣለን የማይቀር ነው።

ዞሮ ዞሮ አገልግሎቱ ክፍት ነው ”
ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ኤጀንሲው ከ42 ሺሕ በላይ ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው ወረፋ እየጠበቁ ያሉ አገልግሎት ፈላጊዎችን መረጃ አጣርቶ አገልግሎት እንደሚሰጥ ከዚህ ቀደም አስታውቆ ነበር።

(በቀጣይ ተጨማሪ መረጃ እናቀርባለን)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🧕" የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ በመጣስ አሁንም ሴት ሙስሊም ተማሪዎች / ልጆቻችን ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ ከልክሏል "  - የተማሪዎች ቤተሰቦች 👉 " የተጣሰ የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ የለም ፤ የትምህርት ህግ እና ደንብ ያከበሩ ተማሪዎች ወደ ክፍል ገብተው መማር ጀምረዋል ፤ ቀሪዎቹ እንዲመለሱ ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ላይ ነን " -  የአክሱም…
#ሂጃብ #ሰልፍ

በሂጃብ ጉዳይ ነገ መቐለ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ሊደረግ ነው።

የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከሂጃብ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ የፍርድ ቤት እና የትምህርት ቢሮ ወሳኔና ትእዛዝ እንዲተገበር የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሄድ አስታውቋል።

ምክር ቤቱ ፥ የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ መደረጋቸውና ከትምህርት ገበታ መራቃቸው መግለጹ ይታወሳል።

በአክሱም የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከሂጃብ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ባለፉት ሁለት ወራት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለሦሥት ጊዜ ደብዳቤ የፃፈው እንዲሁም የፍርድ ቤት ትእዛዝ አልቀበልም በማለታቸው ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ መገደዱን ገልጿል።

በዚህም ነገ ጥዋት 1 ሰዓት በመቐለ ከተማ ሮማናት አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደረግ አሳውቋል።

ሁሉም ፍትህ ፈላጊ የሰልፉ ተሳታፊ እንዲሆንም ጥሪ አቅርቧል።

ሰልፉ ከቀናት በፊት ዓርብ ጥር 9 ሊደረግ የነበረ ቢሆንም የጥምቀት በዓል ዋዜማ በመሆኑ ምክንያት ነው ለነገ የተዘዋወረው።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ከአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ ተከታታይ መረጃዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል ፤ ነገ ማክሰኞ ጥር 13/2017 በመቐለ ከተማ የሚካሄደውን ስልፍም ተከታትሎ ያቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA ዶናልድ ትራምፕ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ቃለመሀላ ፈጸሙ። ፕሬዚዳንቱ ወደ ቢሮ እንደገቡ 200 ገደማ ትዕዛዞች ላይ ፊርማቸውን እንደሚያኖሩ ተናግረዋል። ፕሬዜዳንቱ ፊርማቸውን ከሚያኖሩባቸው ትዕዛዞች መካከል ፦ - በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰነድ አልባ ስደተኞችን ከአሜሪካ ማባረር ፤ - ጾታቸውን የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት ላይ እንዳይሳተፉ ማድረግ ፤ - ብዝሀነት፣ እኩልነትና…
" ሁለት ፆታዎች ብቻ ነው ያሉት እነሱም #ወንድ እና #ሴት ናቸው " - ፕሬዝዳንት ትራምፕ

47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሮ እንደገቡ ከሚሰሯቸው ዋነኛ ስራዎች አንዱ በሀገሪቱ ለወንድ እና ሴት ፆታ ብቻ እውቅና መስጠት ነው።

ይህም በቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ስልጣን የመልቀቂያ ጊዜ ለትራንስጀንደር / ፆታቸውን ለሚቀይሩ ሰዎች የሚሰጠውን ከለላና ጥበቃ የሚሽር ነው።

ለወንድ እና ለሴት ብቻ እውቅና መስጠት ትራፕም ከሚያስተላልፏቸው ትዕዛዛት አንዱና ዋነኛው እንደሆነ ታውቋል።

ትራምፕ ቃለ መሀላ ሲፈጽሙ ፥ " ከዛሬ ጀምሮ / ከእንግዲህ ወዲህ / የአሜሪካ መንግሥት ፖሊሲ እውቅና የሚሰጠው ለሁለት ፆታ ብቻ ነው እነሱም ወንድ እና ሴት " ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።

የአሜሪካ መንግሥት ከአሁን በኃላ እውቅና የሚሰጠው ለወንድ እና ሴት ፆታ ብቻ እንዳሆነ የገለጹት ትራፕም ፤ ስልጣናቸውን ተጠቅመው ብዝሀነት፣ እኩልነትና አካታችነት የሚባሉ ፖሊሲዎችን ለማስወገድ የአፈጻሚ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፉ ተነግሯል።

ከዚህ ባለፈ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ፤ ፆታቸውን የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት ላይ እንዳይሳተፉ የሚያደርግ ትዕዛዝም ያስተላልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ትራምፕ " ሰዎች ተፈጥሯዊ ፃታቸውን መቀየር የለባቸውም " ብለው የሚያምኑ ሲሆን ከዚህ ቀደም ፆታቸውን የቀየሩ የሀገሪቱ ጦር አባላት ወታደሮችን ከስራ እንደሚያግዱ መነገሩ ይታወሳል።

15 ሺህ ፆታቸውን የቀየሩ ወታደሮችን የማባረር እቅድ አላቸው።

ከዚህ በተጨማሪም ተፈጥሯዊ ጾታቸውን የቀየሩ አሜሪካዊያን የሀገሪቱን ጦር መቀላቀል እንዳይችሉ እገዳ እንደሚጥሉ መገለጹ የሚዘነጋ አይደለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቪድዮው የፎክስ ኒውስ መሆኑን ይገልጻል።

#USA #PresidentDonaldTrump

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በአቢሲንያ የቨርቹዋል ባንኪንግ ማዕከሎች የATM ካርድ በቆማችሁበት በሰከንዶች ውስጥ ማግኘት ትችላላችሁ።

#Banking #BanksinEthiopia  #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሂጃብ #ሰልፍ በሂጃብ ጉዳይ ነገ መቐለ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ሊደረግ ነው። የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከሂጃብ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ የፍርድ ቤት እና የትምህርት ቢሮ ወሳኔና ትእዛዝ እንዲተገበር የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሄድ አስታውቋል። ምክር ቤቱ ፥ የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ መደረጋቸውና ከትምህርት ገበታ መራቃቸው መግለጹ ይታወሳል።…
" ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች  "  - ሰልፈኞች

የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የፍርድ ቤት እና የትምህርት ቢሮ ወሳኔና ትእዛዝ እንዲተገበር የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ምክር ቤቱ ዛሬ ጥር 13/2017 ዓ.ም "ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " በሚል መሪ ቃል በመቐለ ከተማ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገኝተዋል።

ሰልፈኞቹ ፦

- ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ትምህርት መአድ ይመለሱ !

- ህገ-መንግስት ይከበር !

- የፍርድ ቤት ትእዛዝ ይከበር !

- ሰላም እና ፍትህ ለትግራይ !

የሚሉና እና ሌሎች መፈክሮች በማስማት ላይ ናቸው።

በስፍራው የሚገኘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ዝርዝሩ ያቀርባል። 

Photo Credit - Tigrai TV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች ! " - ሰልፈኞች

በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የፍርድ ቤት እና የትምህርት ቢሮ ወሳኔና ትእዛዝ እንዲተገበር የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በመቐለ ተካሂደዋል።

ሰልፉ የተዘጋጀው በትግራይ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት አማካኝነት ነው።

ምክር ቤቱ ዛሬ " ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " በሚል መሪ ቃል በመቐለ ከተማ ሮማናት አደባባይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ተገኝተው ነበር።

ሰልፈኞቹ ፦

- ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ይመለሱ !
- ህገ-መንግስት ይከበር !
- ፍትህ ለእህቶቻችን ነፃነት ለሁሉ !
- ሂጃብ መልበስ ሃይማኖታዊ መብትና ግዴታ ነው !
- ሂጃቤ መልኬ ነው !
- የፍርድ ቤት ትእዛዝ ይከበር !
- ሰላም እና ፍትህ ለትግራይ !
- መብታችን ይጠበቅልን !
- ከተበዳዮች ጎን እንቁም !
- ፍትህን እንጠይቃለን !
- ከሂጃባችን ጋር ታግለናል፤ ሂጃባችን ለብሰን እንማራለን !
- ሂጃባችን ምርጫችን እና መብታችን ነው !

... የሚሉና እና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።

በመቐለ ሮማናት አደባባይ ለተሰባሰቡት ሰልፈኞች መልእክት ያስተላለፉት የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዜዳንት ሸኽ አደም ዓብደልቃድር  ፥ " ትግራይ የሃይማኖቶች የመቻቻል የነፃነት ተምሳሌት ነች፤ ይሁን እንጂ ይህንኑ ስልጡንነት ወደ ኋላ በሚመልስ መልኩ ልጆቻችን ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ ከዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና እንዲቀሩ ተደርገዋል "  ብለዋል።

ችግሩ ሳይባባስ እንዲፈታ ለሁለት ወራት በላይ የተለያየ ጥረቱ መደረጉ ያወሱት ፕሬዜዳንቱ  " ትምህርት ቤቶቹ የክልሉ እና የአገሪቱን ህግ በማክበር የሂጃብ ክልከላውን በአጭር ጊዜ ማንሳት አለባቸው ፤ ጥያቄያችን በአጭር ጊዜ ካልተመለሰ ግን ጥያቄያችን እስከ መጨረሻው ድረስ በሰላማዊ መንገድ እንቀጥላለን " ሲሉ ተናግረዋል።

" የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲሁም ክርስትያን ወንድሞቻችን ችግሩ ክጅምሩ እንዲፈታ ብዙ ጥረት  አድርጋችሃል " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ችግሩ በዘላቂነት እስኪፈታ ድረስም የጀመራችሁት ትግል ተጠናክሮ ይቀጥል " በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል።

ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች በመዘዋወር የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ሁሉም የሚመለከታቸው መንግስታዊ አካላት ጉዳዩ ወደ ሃይማኖታዊ ግጭት እንዳያመራ የሚያስገነዝብ ፣ መንግስታዊ ያልሆኑ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ከትምህርት ገበታቸው የተስተጓጎሉ ሴት ተማሪዎች መካካሻ ትምህርት እንዲያገኙ ያለሙ የሚያወሱ 12  ጥሪዎች እና ልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ መልእክቶች ለክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር በማቅረብ እና  በማስተላለፍ ከረፋዱ 4:30 ሰልፉ ተጠናቋል።

ሰላማዊ ሰልፉ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ የከተማዋ የፀጥታ ሃይሎች የተቀናጀ ጥበቃ ያደረጉ ሲሆን በሰላም ተጀምሮ በሰላም መጠናቀቁ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

በሌላ በኩል ፥ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ ክልከላ አድርገዋል የተባሉት በአክሱም ከተማ የሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የጋራ የፅሁፍ ምላሽ ሰጥተዋል።

ት/ቤቶቹ ምን አሉ ?

" 1. የሴት ሙስሊም ተማሪዎች የሂጃብ አጠቃቀም አስመልክቶ በትግራይ ያለው ህግ እና አተገባበሩ ምን ይመስላል ?

ትምህር ቤቶቻችን የትግራይ ትምህርት ቢሮ በ1995 ዓ.ም ያወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ነው እየተጠቀሙ ያሉት ። አዲስ ፖሊሲ ወይም መመሪያ እና ደንብ በትምህርት ሚንስቴር ከወጣ ደግሞ ከትምህርት ቢሮ ጋር ተነጋግሮ ይህንን መመሪያ እና ደንብ ተጠቀሙ ብሎ ይልክልናል ። እኛም ተግባራዊ እናደርጋለን። ይህን ባለልሆነበት ' እህያውን ፈርቶ ዳውላውን ' የሆነ ጥያቄ እና ጫና ግን ግራ የሚያጋባ ነው።

በ1995 ዓ.ም የወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ደግሞ ተማሪዎች መምህራን ወላጆች ተወያይተው ያፀዱቁት ላለፉት 22 ዓመታት እየተጠቀሙት ያለ መመሪያ ደንብ ነው።

በ1995 ዓ.ም የወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ደንብ ደግሞ እንዲታይ በያዝነው ዓመት መጀመሪያ ከወላጅ ተማሪዎች ጥያቄ ተነስቶ ነበር ። የተነሳው ጥያቄ መሰረት በማድረግ በመመሪያ እና ደንቡ ውይይት ተካሂዶ ታህሳስ 6/2017 ዓ.ም በአንድ ተቃውሞ በሙሉ ድምፅ ፀድቀዋል።

በውይይት እና ድምፅ አሰጣጡ የሙስሊም እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ተሳትፈውበት በሙሉ መግባባት መተማመን የተደረሰበት ነው። ታድያ ከአሁን በፊት ታይቶ የማይታወቅ የሂጃብ ክልከላ ጥያቄ ከየት ? እንዴት መጣ ? ትምህርት ቤቶታቻችን ግራ ገብቶዋቸዋል።

2. የትምህርት ቤት ዩኒፎርም አለባበስ ደንብ እና ስነ-ሰርዓት ምን ይመስላል ?

በ1995 ዓ.ም በፀደቀው የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መምሪያ እና ደንብ መሰረት ትምህርት ቤቶቻችን የሚከተለውን የአለባበስ ስርዓት እንዲተገብሩ ያስገድዳል።

የቤተክርስትያን ካህናት እና ዲያቆናት ተማሪዎች ሻሽ መጠምጠምያ ፣ ነጠላ ማድረግ አይፈቀድም። ወንድ ተማሪዎች ባንከር ፣ ፍሪዝ የፀጉር አቆራረጥ አይፈቀድም።

ሴት ተማሪዎችም ነጠላ ፣ መሃረብ ፣ ሻሽ መጠምጠምያ ፣ ጥቁር የሃዘን ሻርፕ ፣ ሂል ጫማ ፣ ሱሪ ፣ የማንኛውም ሃይማኖት አለባበስ የሚያንፀባርቅ ልብስ እንዲለብሱ አይፈቀድም። ይህ የሆነበት ደግሞ በመካከላቸው የሃብት የሃይማኖት ልዩነት ፈጥሮ የመማር የማስተማር ሂደቱ እንዳይታወክ ለማድረግ ያለመ ነው።

ይህ ህግ ደግሞ ክርስትያን ፣ ሙስሊም መምህር የተማሪ ወላጅ ተወያይተው ያፀደቁት እና የሚተዳሩበት ነው። አሁን ታድያ ምን አዲስ ነገር ተፈጥሮ ነው በትምህርት ቤቶቻችን ላይ የሚዘመተው ? 

 3. ስለ ዘንድሮ 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች መሬት ላይ ያለው መረጃ ምንድነው ?

በአክሱም አራት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሉ።  በአራቱ ትምህርት ቤቶች ዘንድሮ ለ12ኛ ክፍል አገር  አቀፍ ፈተና የሚቀርቡት  ተማሪዎች 1044 ናቸው።

ከነዚህ 1044 ተማሪዎች 17 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ናቸው። ከነዚህ 17 ሴት ተማሪዎች ለ22 ዓመታት በቆየው የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መመሪያ እና ደንብ በመቀበል 7 ሴት ተማሪዎች ፈተናው ለመውሰድ ፎርም ሞልተዋል።

10 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ደግሞ ከአክሱም ከተማ እስከ ሳውዲ ዓረብያ በተዘረጋ የውጭ ተፅእኖ ፈተና ለመውሰድ የሚያስችላቸው ፎርም አልሞሉም። ሃቁ ይህ ሆኖ እያለ ' 159 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ እንዲስተጓጎሉ ተደረገ ' እየተባለ ነው የሚወራው። 142 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በትምህርት ቤቶቻችን የሌሉ የፈጠራ ድርሰቶች ናቸው።

የተቀሩት 10 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ቢሆኑ ፎርም መልተው ለመፈተን ፍላጎት አላቸው ፤ ከትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፣ ከመቐለ ፣ ከአዲስ አበባ እስከ ሳውዲ ዓረብያ በየቀኑ እየተደወለ ማስፈራርያ ይደርሳቸዋል። ይህ አካሄድ ደግሞ የቆየውን አብሮነት እና መቻቻል የሚጎዳ ለህዝብ እና አገር የማይጠቅም መወገዝ ያለበት ተግባር ነው። "

... ሲሉ ትምህርት ቤቶቹ በጥምር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በላኩት የፅሁፍ ምላሽ ገልጸዋል።

#UPDATE ትምህርት ቤቶቹ ዘግይተው በላኩት መልዕክት ደግሞ " ሁሉም ተፈታኞች ፎርም ሞልተዋል ለፈተናም ብቁ ናቸው " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle
#ቲክቫህኢትዮጵያመቐለ

@tikvahethiopia