TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#HaileResortJimma

“ ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል" - ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ

የሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ ሆቴልና ሪዞርት 10ኛ መዳረሻ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ዛሬ (ሐሙስ ታኀሳስ 24 ቀን 2017 ዓ/ም) ተመርቋል።

ሆቴሉ 3 የመመገቢያ አደራሾች፣ የልጆች መጫወቻ፣ ሞሮኮ ባዝ እንዳሉት፣ ለ210 ሰዎች ቋሚ የሥራ እድል እንደፈጠረ፣ ለወደፊት ደግሞ ወደ 400 ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ እድል እንደሚፈጥር ተነግሮለታል።

ሆቴሉ አሁን የተጠናቀቁ ወደ 106 ክፍሎች እንዳሉት፣ ሁሉም ሰጠናቀቁ ደግሞ ወደ 114 ክፍሎች እንደሚኖሩት ተመልክቷል።

በመርሀ ግብሩ የተገኙት ሻለቃ ኃይሌ ባደረጉት ንግግር፣ በአንድ ዓመት ከስምንት ወራት የሆቴሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ላጠናቀቁት ሠራተኞች በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።

ጅማ ላይ የኮንስትራክሽን እቃ ውድ መሆኑን የገለጹት ሻለቃ ኃይሌ፣ “ብሎኬት ከአዲስ አበባ እየተጓጓዘ ነው የተሰራው” ሲሉ ተናግረዋል።

“ኮንስትራክሽኑን ውድ ያደረገው የመንገዱ መበላሸት ነው” ያሉት ኃይሌ፣ “ብሎኬቶች እየተሰባበሩ ነበር። ሁሉ ሰው በአውሮፕላን መጓጓዝ አይችልም” ነው ያሉት።

የሆቴሉን ወጪ በተመለከተ በገለጹበት አውድ ደግሞ፣ “ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል” ብለዋል።

የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በመርሀ ግብሩ ተገኝተው ባደረጉት ገለጻ ደግሞ፣ “ጅማ አባጅፋር ሁሉንም የምታቅፍ ከተማ ናት። ባለሃብቶች ጅማን ለመቀየር ከኅይሌ እንዲማሩ ማሳያ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትጃኒ ናስር ፥ “ኃይሌ ሲጠራ እንስቃለን፣ ኃይሌ ሲጠራ እንባችን ይመጣል፣ ኃይሌ እንኳን አገኘንህ” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል።

“ሱልልታ ላይ የኃይሌን ሆቴል ሳይ እንዲህ አይነት ሆቴል ጅማ ላይ ቢገነባ ብዬ ተመኝቼ ነበር። አሁን እንደዚህ ተሰርቶ አየሁትና እንባዬ ነው የመጣው። የተመረቀው ለኃይሌ ሳይሆን ለጅማ ህዝብ ነው” ሲሉ አመስግነዋል።

በ10ሩም የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች 900  ሩሞች እንዳሉ፣ ለ2500 ሠራተኞች የሥራ እድል እንደተፈጠረ ተመልክቷል።

ፎቶ ፦ በግዛቱ አማረ

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake : እየተከሰተ ያለው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ዛሬም ቀጥሏል። ዛሬ ረቡዕ ከጥዋት አንስቶ እስከ ምሽት በተለያየ ጊዜ በሬክተር ስኬል ከ4.5 እስከ 4.9 ድረስ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በአዋሽ ፈንታሌና አካባቢው ተከስቷል። ሰሞኑን ጠንከር ያለውና ተደጋግሞም እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አፋር ላይ የንብረት ጉዳት አድርሷል። ወገኖቻችን የመሬት መንቀጥቀጡ ካየለባቸው ቦታዎች…
#Earthquake

ዛሬ በሬክተር ስኬል 5.1 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ገልጿል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በሰሜን 36 ኪ/ሜ በኩል ነው የተመዝገበው።

የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት አዲስ አበባ እና ቦታዎችም የተሰማ ሲሆን በተለይ በአዲስ አበባ ንዝረቱ በደንብ ይሰማ ነበር።

አንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፥ " የመሬት ንዝረት እየተሰማ ነው ፤ ያለሁት ቦሌ አካባቢ መኪና ውስጥ ነው ፤ በደቂቃዎች ልዩነት ሁለቴ አጋጥሟል " ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ሌላ አንድ የቤተሰባችን አባል  " መኪናዬ ውስጥ ሆኜ ትንሽ ንቅንቅ ስል ተሰምቶኛል ወደ አያት አካባቢ ቆሜ ባለሁበት " ሲል ገልጿል።

ከሰሞኑን የተለያየ መጠን ያላቸው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች እየተመዘገቡ ሲሆን የዛሬው 5.1 ከፍ ካሉት አንዱ ነው።

በሬክተር ስኬል 5.1 ከተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ በኃላ በሬክተር ስኬል 4.5 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥም ነበር።

አፋር ላይ በተለይ የመሬት መንቀጥቀጡ አይሎ በሚሰማባቸው ቦታዎች ንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በርካቶችም ከቤታቸው ሸሽተው ሄደዋል።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
ከ600 በላይ ተሳታፊዎች የሚኖሩት የምልክት ቋንቋ ጉባዔ በቅርቡ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

የራሷን የምልክት ቋንቋ የምትጠቀመው ኢትዮጵያ 15ኛውን የምልክት ቋንቋ ዓለም-አቀፍ የምርምር ጉባዔን (TISLR) ከመጪው ጥር 6 እስከ 9 በአዲስ አበባ ታስተናግዳለች።

ከዚህ ቀደም በነበሩት ጉባኤዎች ተሳታፊ የነበረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወዳድሮ የዘንድሮውን ጉባዔ እንዲያዘገጋጅ መመረጡን ተከትሎ ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ጉባዔውን አዘጋጅቷል።

ይህ በየ 3 ዓመቱ የሚካሄደው የምርምር ጉባኤ በአፍሪካ ሲዘጋጅ የመጀመሪያው መሆኑንና ዓለም አቀፍ የዘርፉ ምሁራንን ጨምሮ ከ600 በላይ ተሳታፊዎች የሚሳተፉበት እንደሚሆን ዛሬ በነበረው የቅድመ ጉባኤ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል።

ኢትዮጵያ የምልከት ቋንቋን የብሔራዊ ቋንቋ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር ምን እየሰራች ትገኛለች ?

የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚ/ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ "የቋንቋ ፖሊሲው ለምልክት ቋንቋ እውቅና ይሰጣል ይህንን ሥራ ማድነቅ ያስፈልጋል፤ የብሔራዊ ቋንቋ ለማድረግ ግን ሰፊ ጥናቶች መስራት ይጠበቅብናል።" ብለዋል።

ይሄም ጉባዔም የምልክት ቋንቋዎችን እንደ ህጋዊና አስፈላጊ ቋንቋዎች እውቅና ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ ይሆናል ነው ያሉት።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕረዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በመግለጫው ወቅት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምልክት ቋንቋ በማስተማር 15 ዓመታትን ማስቆጠሩን ጠቅሰው በጉባዔው በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታዎች ላይ የተሰሩ ሥራዎች የሚቀርቡበት ነው ብለዋል።

አክለውም፥ የዩኒቨርስቲው ተመራማሪዎች፣ መምህራን፤ ተማሪዎች ተሳታፊ እንዲሆኑ እና ከዓለም አቀፍ አቻዎቻቸው እንዲማማሩ እድል ይሰጣል ያሉት ዶ/ር ሳሙኤል "የምልክት ቋንቋ እውቅና እንዲኖረው የበኩላችንን አስተዋጽኦ የምናበረክትበት ይሆናል" ሲሉ ገልጸዋል።

በዚህ ጉባዔ ኢትዮጵያ ምን የምታቀርበው ነገር አዘጋጅታለች ?

ዶ/ር ኤርጎጌ በዚህ ጉባኤ ከሚቀርቡ የጥናትና ምርምር ሥራዎች በተጨማሪ የተሰሩ ሥራዎችን እንድናቀርብ እድል ይሰጠናል ያሉ ሲሆን፤ በተለይም የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፍ ላይ የሚገኘውን የአካል ጉዳተኞች መብቶች የተጠቃለለ አዋጅን ጠቅሰዋል።

የአካል ጉዳተኞች መብቶች የተጠቃለለ አዋጅ ምን ይዟል?

በዚህ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ አሳልፈው አመዲን፥ አዋጁ ተበታትኖ የነበሩትን መብቶች ወደ አንድ በማሰባሰብ በተለይም ተጠያቂነትን የሚያሰፍን እንደሆነ ገልጸውልናል።

ከ90 ያላነሱ አንቀጾችን ይዟል በተባለው በዚህ የተጠቃለለ አዋጅ፥ የምልክት ቋንቋን በተመለከተ መጠቀሱን ያነሱት ዳይሬክተሩ፥ "የምልክት ቋንቋ እንደ አንድ ኢትዮጵያ ውስጥ እውቅና እንደተሰጣቸው ቋንቋዎች ታስቦ ተግባራዊ መደረግ አለበት የሚል ተካቶበታል" ብለዋል።

የምልክት ቋንቋን መጠቀም በኢትዮጵያ አስገዳጅ ነው ?

ይህንን ጥያቄ ያቀረብንላቸው የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማኅበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ አሊ "በተለይም የመስማት የተሳናቸው ተሳታፊዎች ባሉባቸው መድረኮች እንዲሁም በሚዲያ አዋጁ በግልጽ እንደተቀመጠው የመገናኛ ብዙኃን የምልክት ቋንቋ የመጠቀም ግዴታ ተጥሎባቸዋል" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

የጉባዔው አዘጋጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉባዔው መሳተፍ የሚፈልጉ በዚህ http://tislrethiopia.org/registration/ ሊንክ ተጨማሪ መረጃዎችን መውሰድና መመዝገብ እንደሚችሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopia
#SignLanguage
#EthSL

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Haile " ሙሉን አፍርሰን እየገነባን ነው። ከመንግሥት ምንም ማካካሻ አልተደረገልኝም " - ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ከዚህ በፊት በሻሸመኔ በጸጥታ ችግር ስለወደመው ሆቴል ሁኔታ እና በጎንደር  ከተማ በሚገኘው ሪዞርት በኩል በጸጥታ ችግር የገጠማቸውን የገቢ መቀዛቀዝን በተመለከተ ዛሬ በወላይታ ሶዶ ከተማ የሆቴል ምረቃ መርሀ ግብር በተገኙበት ወቅት ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከዚህ…
“የካሳዋን ጉዳይ አሁንም እየጠበኳት ነው። ግን የለችም” - ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ

የሻሸመኔ ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ውድመት እንደደረሰበት የሚታወቅ ሲሆን ፣ አፍርሰው እየሰሩ እንደነበር ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ ገልጸው ነበር።

ከ10 ወራት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ሙሉውን አፍርሰን እየሰራን ነው። ከመንግስት ምንም አይነት ማካካሻ አልተሰጠኝም ” ነበር ያሉት።

“ እኔ አላቃጠልኩትም። መንግስት እንደ መንግስት መወጣት ነበረበት ” ብለው፣ “  እኛ ለብዙ አመታት እንግዲህ በኢንቨስትመንት ተሰማርተን እየሰራን ነው ” ማለታቸው አይዘነጋም።

አሁንስ ከመንግሰት ካሳ ተከፈላቸው ?

የሻሸመኔው ሆቴልና ሪዞርት ለደረሰው ውድመት መንግስት ከሳ እንዳልከፈለዎት ገልጸው ነበር፣ ተከፈለዎት ? ተብሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ጥያቄ ያቀረበላቸው ሻለቃ ኃይሌ አሁንም ካሳ እንዳልተከፈላቸው ተናግረዋል።

“ የካሳዋን ጉዳይ እየጠበኳት ነው ግን የለችም። እሷን ነገር እብቃለሁ ” ነው ያሉት።

የውጪ ኢንቨስተሮች እንዲመጡ እንዲህ አይነት አደጋዎች ሲደርሱ ካሳ ቢከፈል መልካም መሆኑን አስረድተው፣ “ ዞሮ ዞሮ ግን አልሆነም። አልተቀበልኩም ” ብለዋል።

ሆቴሉን ከባለሦስት ወደ ባለአራት ኮከብ አድርገው እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ “ ህንፃ እያፈረሱ መስሪት ሁለት ሥራ ነው አንደኛ ማፍረስ፣ ሁለተኛ ደግሞ መገንባት አለ ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ በአጠቃላይ ግን ስለሆቴልና ሪዞርት ሲወራ እከሌ ሆቴል ከፈተ፣ እከሌ ሪዞርት ከፈተ የሚለው ምንም ፋይዳ የለውም። ማነው የሚተባበረው ? ማነው አብሮት ያለው? ከአዲስ አበባ ከ300 ኪሎ ሜትር ሲመጣ ሴፍ ነው ወይ? የሚሉት ምላሽ የሚፈልጉ ናቸው ” ሲሉም አስገንዝበዋል።

በተያያዘ ዜና በአማራ ክልል በመንግስትና በፋኖ ታጣቂዎች እየተካሄደ ያለውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በጎንደር ከተማ ያለው ሆቴላቸው ገቢው እየተቀዛቀዘ መሆኑንም ከዚህ ቀደም መግለጻቸው ይታወሳል።

የጎንደሩ ሆቴል ገቢው በምን ያህል ቀንሷል ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ላቀረበላቸው ጥያቄ ሻለቃ ኃይሌ፣ “ አለ እንዴ ለመሆኑ ቢዝነሱ? 56፣ 57 ሩም ተይዞ 5 ሰዎች ስላሳደርክ ምንድን ነው ገቢው? ” የሚል ጥያቄ አዘል ምላሽ ሰጥተውም ነበር።

አሁንስ የጎንደሩ ሆቴል ገቢ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? በሚል ዛሬ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ደግሞ፣ “ በጎንደሩ ሆቴል የሚፈለገውን ያህል እየተሰራ አይደለም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

የቀጣይ የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርቶች መዳረሻ የት እንደሚሆን በዛሬ የጅማ ሪዞርት ምረቃ መርሀ ግብር ላይ ማብራሪያ የሰጡት ሻለቃ ኃይሌ፣ የሻሸመኔውንና የደብረ ብርሃኑን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ “ ድሬዳዋና ሀረርም ቀጣይ መዳረሻችን ይሆናል” ሲሉ ጠቁመዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
🔈 #የነዋሪዎችድምጽ

⚫️ " ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ነው ያለብን መኖር አልቻልንም በሳምንት ሶስት እና አራት ቀን መብራት የለንም " - ቅሬታ አቅራቢ

🔴 " ከክረምት በፊት ችግሩ ይቀረፋል ታገሱ " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት


በአዲስ አበባ ከተማ ሰሚት ፍርድ ቤት፣ ሰሚት ሳፋሪ፣ ሰሚት ፔፕሲ ፋብሪካ ፣ ፍየል ቤት ፣ ወጂ ሰፈር፣ ሰንራይዝ ሪል ስቴት፣ ፊሊንት ስቶን ሆምስ እና ጎሮ ሚካኤል አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች በአካባቢው በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የሃይል መቆራረጥ ከፍተኛ የሆነ ምሬት ውስጥ እንደከተታቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በአካባቢው የሚገኙ በተለይም የፍሊንት ስቶን ትዊን የጋራ መኖሪያ መንደር ነዋሪዎች " ከህዳር 02/03/17 ዓ/ም ጀምሮ የመብራት አገልግሎት ቀንም ለሊትም ሳናገኝ በችግር ላይ እንገኛለን " ሲሉ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን በደብዳቤ ጭምር ቢያሳውቁም " መፍትሄ የሚሰጠን አጥተናል " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበኩሉ በአካባቢው ለሃይል መቆራረጥ መንስኤ የሆነው በመሬት ውስጥ በሚቀበሩ የሃይል መስመሮች ላይ የሚያጋጥም የመሰረት ልማት ጉዳት እና ስርቆት ምክንያት መሆኑን በመግለጽ ደንበኞቹ የሃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የሚጠይቅ ጽሁፍ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አስፍሯል።

ነዋሪዎች በዝርዝር ምን አሉ ?

" ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ነው ያለብን መኖር አልቻልንም በሳምንት ሶስት እና አራት ቀን መብራት የለንም መብራት አይመጣም ከመጣም ለሊት ነው ከዛ ተመልሶ ይጠፋል መኖር ከብዶናል።

ህመምተኞች አሉ ፤ ፍሪጅ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች አሉ ከዚህም በላይ በዚህ ኑሮ ውድነት ምግብ ለመድፋት ተገደናል።

ከህዳር 18 እስከ ታህሳስ 9 ባለው ጊዜ አምስት ጊዜ በተደጋጋሚ በመንገድ ስራ ምክንያት በመሬት ውስጥ ያለ መስመር በኤክስካቫተር እየተመታ ሃይል ተቋርጧል።

መፈጠር አልነበረበትም ቅድመ መከላከል ስራዎች ሊሰሩ ይገባ ነበር ከሆነ በኋላ ግን በተደጋጋሚ መፈጠር አልነበረበትም ተጠያቂነትም ሊኖር ይገባ ነበር።

ከታህሳስ 10 በኋላ ግን አንድ ጊዜ ሲመታ ከ18 ሰዓት እስከ 3 ቀን መብራት ይጠፋ ጀምሯል ከዛ በኋላ መቆራረጡ በከፍተኛ ሁኔታ ባሰ በ24 ሰዓት ጊዜ ውስጥ ለ25 ደቂቃ ብቻ ሃይል የምናገኝበት ጊዜ ሁሉ አለ።

ትልቁ ቆየ ከተባለ 4 ሰዓት ነው ይህም ከእኩለ ለሊት እስከ ንጋት ባለው ጊዜ ውስጥ ነው ሰው ከተኛ በኋላ ለምንም አገልግሎት መዋል በማይችልበት ሰዓት ነው ከሚመጣው።

የመልሶ ግንባታ ስራ ለማከናወን በሚል በወጣው ዝርዝር ውስጥ አካባቢያችን የሃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ የሚገልጸው ከ 3 ሰዓት እስከ 10 ሰዓት ቢሆንም እኛ ከንጋት ጀምሮ እስከ እኩለ ለሊት መብራት አናገኝም።

ችግሩን ማስቆም ሲችሉ ማህበረሰቡ በመሃል እየተቀጣ ነው ልጆች ከትምህርት ቤት መጥተው ማጥናት አልቻሉም ፣በተደጋጋሚ በመጥፋቱም ምክንያት ነዋሪው ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እየተዳረገ ነው " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢ/ር ሺፈራው ተሊላ ምን ምላሽ ሰጡ ?

" ቀን ቀን የፕሮጀክት ስራ አለ በስራው ምክንያት ይቋረጣል ማታ ማታ ይለቁላቸዋል ሙሉ ቀን የማይበራላቸው ብልሽት ሲኖር ነው እንደዛ የሚሆነው ሁሌ አይደለም።

ከሰሚት ጀምሮ እስከ ወረገኑ ድረስ እዛ መስመር ላይ መሰረተ ልማት ስራ እየተሰራ ነው ስራዎች በቅንጅት ነው የሚሰሩት አንዳንዴ ብዙ ስራ ስለሆነ እየተሰራ ያለው ከአቅም በላይ በሆኑ ምክንያቶች ችግሮች ይከሰታሉ።

ለዘለቄታው ለመገልገያ (Utility) የሚሆን ኮሪደር አብሮ እየተሰራ ነው ለተወሰነ ጊዜ ነው የተጠቀሰው አይነት ችግር የሚኖረው በቀጣይ በጣም አስተማማኝ የሆነ መሰረተ ልማት እየተሰራ ነው።

መንገድ በሚሰራበት ጊዜ ከእግረኛና ከአስፋልት መንገድ ጎን የውሃ ፣ የቴሌኮም እና የኤሌክትሪክ መስመር (Utility Corridor) አብሮ እየተገነባ ነው።

ቀደም ሲል የነበረው አካሄድ ብልሽት በሚኖርበት ጊዜ አስባልት ተቆፍሮ ነበር የሚሰራው በአሁኑ አሰራር ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ብልሽት ሲኖር መቆፈር እና ማፍረስ ሳያስፈልግ ገብቶ ለመስራት ያስችላል ፣ የመቀየር እና የማሻሻል ስራ ሲያስፈልግ ማሟላት የሚችል የአቅም ማሳደግ ስራ እየተሰራ ነው።

ይህ አይነት ቅንጅት ባለመኖሩ ብዙ ችግሮች ሲከሰቱ ነበር አሁንም የምናየው ችግር የተከሰተው ቀደም ሲል ይህ አይነት ቅንጅት እና የUtility corridor ባለመኖሩ ምክንያት የተከሰተ ነው ።

ይሄንን ችግር ለአንዴ እና ለመጨረሻ ችግሩን ለመፍታት እና ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት እየሰራን ነው።

የተወሰነ ጊዜ መታገስ ነው ለዘመናት የሚያገለግል ስራ ነው የሚሰራው ስራው እስከ 6 ወር ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ ነው ከክረምቱ በፊት ያልቃል" ብለዋል።

እስከዛ አሁን ባሉበት አይነት የመብራት ችግር ውስጥ ይቆያሉ ወይ ? ስንል ለዋና ስራ አስፈጻሚው ጥያቄ አንስተናል።

ኢ/ር ሺፈራው ተሊላ

" ሲሪየስ በሆነ ነገር ውስጥ ላይቆዩ ይችላሉ ብዙ ነገር እየተሻሻለ ነው የሚሄደው ብዙ ቁፋሮ አለ ቁፋሮ ካለቀም በኋላ መሰረተ ልማቱ ቦታውን ይይዛል ለስራ ሲባል ሃይል መቆራረጥ ይኖራል ነገር ግን እየተሻሻለ ይሄዳል።

ከመገናኛ ሰሚትም ሲሰራ እንደዚህ አይነት ችግሮች ነበሩ አሁን CMC አካባቢ እንደዚህ አይነት ችግር የለም ከዚህ በኋላ እንደዚህ አይነት ችግሮች አይኖሩም የሁሉም ስራ ያልቃል ከክረምት በፊት ችግሩ ይቀረፋል ታገሱ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ችግሩን በማቃለል እስከዛ በተሻለ መንገድ ሃይል የሚያገኙበት እድል ይኖራል ወይ ? የሚል ጥያቄም ያነሳንላቸው ሲሆን በምላሻቸውም " እንደዛ እናደርጋለን ከባድ ችግር ስለነበር አንድ ጊዜ ነው እስካሁን ለቀናት በሚባል ደረጃ የተቋረጠው ከዚህ በኋላ እንደዚህ አይነት ነገር እንዳይኖር ጥረት እናደርጋለን " ሲሉ መልሰዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake ዛሬ በሬክተር ስኬል 5.1 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ገልጿል። የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በሰሜን 36 ኪ/ሜ በኩል ነው የተመዝገበው። የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት አዲስ አበባ እና ቦታዎችም የተሰማ ሲሆን በተለይ በአዲስ አበባ ንዝረቱ በደንብ ይሰማ ነበር። አንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፥ " የመሬት ንዝረት እየተሰማ ነው…
#Earthquake

ዛሬ ሀሙስ ቀን ላይ ከተመዘገበው በሬክተር ስኬል 5.1 በኃላም 4.5 የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት በኃላ በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት ተመዝግቧል።

እንደ አሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጀ ከቀድሙ በኃላ በሬክተር ስኬል 4.5 ፣ በድጋሚ 4.5 ከዛ 4.6 ከዛም 4.9 ተመዝግቧል።

ከ5.1 በኃላ የተመዘገበው ከፍተኛው የመሬት መንቀጥቀጥ 4.9 ነው።

ሁሉም ቦታቸው ከአዋሽ የተወሰኑ ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ነው።

ንዝረቱ በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞችም ተሰምቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake ዛሬ ሀሙስ ቀን ላይ ከተመዘገበው በሬክተር ስኬል 5.1 በኃላም 4.5 የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት በኃላ በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት ተመዝግቧል። እንደ አሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጀ ከቀድሙ በኃላ በሬክተር ስኬል 4.5 ፣ በድጋሚ 4.5 ከዛ 4.6 ከዛም 4.9 ተመዝግቧል። ከ5.1 በኃላ የተመዘገበው ከፍተኛው የመሬት መንቀጥቀጥ 4.9 ነው። ሁሉም ቦታቸው ከአዋሽ የተወሰኑ…
ለመሆኑን በሀገራችን የመሬት መንቀጥቀጥ ስጋት ያለባቸው ቦታዎች የትኞቹ ናቸው ?

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ህዋ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም፤ የሴስሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕ/ር አታላይ አየለ ፦

" ... ከላይ ከነ መቐለ ጀምሮ ወልዲያ፣ ደሴን እያካተተ የሚመጣው በአዲስ አበባ አድርጎ እስከ አርባ ምንጭ የሚዘልቀው ደጋማው የሀገሪቱ ክፍል ነው። ስምጥ ሸለቆ መሃሉ ላይ አለ።

ከዛ ወደ ማዶ ስንሻገር ከድሬዳዋ ጀምሮ ጎባን ባሌን፣ አካባቢ አድርጎ አሰላን ጨምሮ አሰላም በስምጥ ሸለቆ ጫፍ ላይ ነው።

በጣም ትልቅ የሆነ ቆላማ ክፍል ከአፋር ጀምሮ ከዳሎልና ከኤርታሌ አካባቢ አንስቶ ድሬዳዋን እያካለለ ሰመራን መሃል አድርጎ በአዳማ ፣ ቢሾፍቱ አድርጎ ሀዋሳ፣ አርባ ምንጭ ድረስ የሚዘልቀውን ስምጥ ሸለቆ እየነካካ ነው የሚሄደው።

በተገለጹት ቆላማ አካባቢ በተባሉት / ስምጥ ሸለቆ ውስጥ ባሉት ወይም ለነሱ አዋሳኝ በሆኑት ቦታዎች ለመሬት መንቀጥቀጥ ተጋላጭ ናቸው አዲስ አበባን ጨምሮ።

አዲስ አበባን ሰው ላይገነዘብ ይችላል የሰላሌን ሜዳ ጨርሰን እንጦጦ ቁልቁለቱን ወደዚህ ስንይዝ ስምጥ ሸለቆን ያዝን ማለት ነው። ስለዚህ አዲስ አበባ ያለችው ከስምጥ ሸለቆ ኮርቻ ላይ ናት።

እነዚህ ከተሞች የመሬት መንቀጥቀጥ ሊፈጠር በሚችልበት አካባቢ የተገነቡ ናቸው።

ለምሳሌ ፥ ህዳሴ ግድብ ያለበት በቅርብ ርቀት የመሬት መንቀጥቀጥ የሚያሰጋው አይደለም። ምናልባት ከ60 ከ70 ፐርሰንት በላይ የሚያሰጋው አይደለም።

ቁም ነገሩ እሱ አይደለም። ምን ያክሉ የኢትዮጵያን ወሳኝ የተባለ ኢኮኖሚ የያዙ ናቸው በየት አካባቢ ይገኛሉ ከተሞችስ ስንት ናቸው ? ከተባለ ከስምጥ ሸለቆ ተፅእኖ ውጭ ያሉት ከተሞች በጣም ጥቂት ናቸው።

በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ወይም አዋሳኝ ውስጥ ያሉትን ከደመርን ከ80 እስከ 90 ፐርሰንት ሁሉም በሚባል ደረጃ አንድም በስምጥ ሸለቆ ውስጥ አልያም ጫፍ ላይ ናቸው። ስለዚህ ከመሬት መንቀጥቀጥ ተፅእኖ ውጭ ናቸው ማለት አይቻልም። "

@tikvahethiopia