በሲዳማ ክልል በደረሰ አሰቃቂ የመኪና አደጋ ከ70 በላይ ሰዎች ህይወታቸው አለፈ።
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በቦና ዙሪያ ወረዳ ጋላና ወንዝ ተብሎ በሚጠራዉ ድልድይ ላይ ከ70 በላይ ሰርገኞችን ይዞ ወደ በንሳ ወረዳ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ ክፍት መኪና ድልድዩን ስቶ ወንዝ ዉስጥ መግባቱን የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉን የሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ቢሮው " እስካሁን ቁጥሩ ያልታወቀ ሰዉ ሕይወት አልፏል " ሲል ገልጿል።
የክልሉ ፖሊስ በሰጠን ቃል 71 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን አሳውቋል።
የአደጋ መንስኤ እየተጣራ ሲሆን አጠቃላይ የተጠቃለለ መረጃ ይገለጻል።
ነፍስ ይማር !
@tikvahethiopia
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በቦና ዙሪያ ወረዳ ጋላና ወንዝ ተብሎ በሚጠራዉ ድልድይ ላይ ከ70 በላይ ሰርገኞችን ይዞ ወደ በንሳ ወረዳ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ ክፍት መኪና ድልድዩን ስቶ ወንዝ ዉስጥ መግባቱን የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉን የሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ቢሮው " እስካሁን ቁጥሩ ያልታወቀ ሰዉ ሕይወት አልፏል " ሲል ገልጿል።
የክልሉ ፖሊስ በሰጠን ቃል 71 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን አሳውቋል።
የአደጋ መንስኤ እየተጣራ ሲሆን አጠቃላይ የተጠቃለለ መረጃ ይገለጻል።
ነፍስ ይማር !
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በሲዳማ ክልል በደረሰ አሰቃቂ የመኪና አደጋ ከ70 በላይ ሰዎች ህይወታቸው አለፈ። በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በቦና ዙሪያ ወረዳ ጋላና ወንዝ ተብሎ በሚጠራዉ ድልድይ ላይ ከ70 በላይ ሰርገኞችን ይዞ ወደ በንሳ ወረዳ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ ክፍት መኪና ድልድዩን ስቶ ወንዝ ዉስጥ መግባቱን የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉን የሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ…
" የ71 ሰዎች ሕይወት አልፏል " - ፖሊስ
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በቦና ዙሪያ ወረዳ ጋላና ወንዝ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ 74 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ መኪና ድልድዩን ስቶ ወንዝ ዉስጥ በመግባቱ የ71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ አደጋዉን አስመልክቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት " በመኪናው ላይ የነበሩት የቡና ሳይት ስራ ላይ ቆይተዉ ወደ ከተማ ሲመለሱ የነበሩ ሰዎች ናቸዉ " ብለዋል።
የአደጋዉ መንስኤ የተጣራ ሲሆን 68 ወንዶችና 3 ሴት በድምሩ 71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አረጋግጠዋል።
የተረፉት 3 ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዉ በሕክምና እየተረዱ መሆኑን የገለፁት ኮሚሽነሩ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል።
ነፍስ ይማር !
@tikvahethiopia
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በቦና ዙሪያ ወረዳ ጋላና ወንዝ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ 74 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ መኪና ድልድዩን ስቶ ወንዝ ዉስጥ በመግባቱ የ71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ አደጋዉን አስመልክቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት " በመኪናው ላይ የነበሩት የቡና ሳይት ስራ ላይ ቆይተዉ ወደ ከተማ ሲመለሱ የነበሩ ሰዎች ናቸዉ " ብለዋል።
የአደጋዉ መንስኤ የተጣራ ሲሆን 68 ወንዶችና 3 ሴት በድምሩ 71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አረጋግጠዋል።
የተረፉት 3 ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዉ በሕክምና እየተረዱ መሆኑን የገለፁት ኮሚሽነሩ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል።
ነፍስ ይማር !
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake አዋሽ አካባቢ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ መቀጠሉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እየገለጹ ናቸው። ትላንት ምሽት እንዲሁም ዛሬ ጥዋት አካባቢ ጠንከር ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደነበር ጠቁመዋል። እንደ ' አሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ' መረጃ ዛሬ እሁድ ከአዋሽ 33 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሬክተር ስኬል 4.8 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ…
#Earthquake አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አሁንም ቀጥሏል።
ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ በሬክተር ስኬል 5 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በድጋሚ ተከስቷል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ የጂኦፊዚክስ እና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር የሆኑት ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) ፤ ዛሬ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በሬክተር ስኬል 5 ሆኖ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበባ በተደጋጋሚ መሰማቱን ተናግረዋል።
" በአካባቢው ያለው የቅልጥ ዓለት ድንጋይ (ማግማ) እንቅስቃሴ አሁንም ቀጥሏል " ያሉት ኤልያስ (ዶ/ር) " የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ እንዲከሰት እያደረገ ያለውም ይኸው ነው " ሲሉ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ በሬክተር ስኬል 5 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በድጋሚ ተከስቷል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ የጂኦፊዚክስ እና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር የሆኑት ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) ፤ ዛሬ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በሬክተር ስኬል 5 ሆኖ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበባ በተደጋጋሚ መሰማቱን ተናግረዋል።
" በአካባቢው ያለው የቅልጥ ዓለት ድንጋይ (ማግማ) እንቅስቃሴ አሁንም ቀጥሏል " ያሉት ኤልያስ (ዶ/ር) " የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ እንዲከሰት እያደረገ ያለውም ይኸው ነው " ሲሉ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" በአደጋዉ ሙሽራዉን ጨምሮ የ71 ሰዎች ሕይወት አልፏል " - ማቴ መንገሻ (ዶ/ር)
🚨 " አደጋዉ ' ከቡና ሳይት በሚመለሱ ሰዎች ላይ የተከሰተ ነዉ ' ተብሎ የተገለፀት አግባብ ሙሽራዉን ጨምሮ አብዛኞቹ ሟቾች የቡና ሳይት የሚሰሩ በመሆናቸዉ ነው ! "
ዛሬ በሲዳማ ክልል፣ ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ቦና ወረዳ ልዩ ስሙ ጋላና ድልድይ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ ሰርገኞችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ መኪና ተገልብጦ ሙሽራውን ጨምሮ የ71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ ማቴ መንገሻ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" አይሱዙው 11 ሰዓት አካባቢ መነሻዉን ቦና ወረዳ ሚሪዴ ገጠር ቀበሌ አድርጎ ወራንቻ ወደተባለ አጎራበች ቀበሌ የወንድ ወገን የሆኑ ከ70 በላይ ሰርገኞችን ጭኖ ወደ ሴቷ ቤት ጉዞ ላይ ነበር " ብለዋል።
ገላና ድልድይ ላይ ሲደርስ ግን ድልድዩን ስቶ ወደ ወንዝ ዉስጥ በመግባቱ እስካሁን በተጣራዉ መረጃ አስክሬናቸው ቦና አጠቃላይ ሆስፒታል የደረሰ 66 እንዲሁም ከአደጋዉ ቦታ በቀጥታ ቤተሰቦቻቼዉ የወሰዷቸዉን ጨምሮ በአጠቃላይ ወንድ 68 ሴት 3 በድምሩ 71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አረጋግጠዋል።
በ4 ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንና አንዲት ሴት ወደ ሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል መላኳንም ማቴ (ዶ/ር) ጨምረው ገልፀዋል
የአደጋው ትክክለኛ መንስኤ እየተጣራ ነዉ ያሉት ማቴ (ዶ/ር) ፤ " በገጠር አከባቢ በሰርግ እና ደስታ ወቅት በክፍት መኪኖች ላይ ከመጠን በላይ መጫንና አልፎ አልፎም መጠጥ የመቀማመስ ሁኔታዎች ስለሚኖሩ፤ ይህ ለአደጋው አንዱ መንስዔ ተደርጎ ይገመታል " ብለዋል።
" አደጋዉ ' ከቡና ሳይት በሚመለሱ ሰዎች ላይ የተከሰተ ነዉ ' ተብሎ የተገለፀት አግባብ ሙሽራዉን ጨምሮ አብዛኞቹ ሟቾች የቡና ሳይት የሚሰሩ በመሆናቸዉና ተሽከሪካሪዉም የቡና ሳይት በመሆኑ ነዉ " ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
የክልሉ ፖሊስ ቀደም ብሎ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል መኪናው ላይ የነበሩት ወገኖች የቡና ሳይት ስራ ላይ ቆይተው ሲመለሱ የነበሩ እንደሆኑ ገልጾ ነበር።
እንደ ዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ማብራሪያ ግን ምንም እንኳን መኪናው ላይ የነበሩት አብዛኛዎቹ ወገኖች (ሙሽራውን ጨምሮ) የቡና ሳይት ስራ ላይ ተሰማርተው የሚሰሩና መኪናውም የቡና ሳይት ቢሆንም በሰዓቱ ሲጓዙ የነበረውና አደጋው የደረሰው ለሰርግ ወደ ሴቷ ቤት ማለትም ሙሽራው ሙሽሪትን ለመውሰድ ሲሄዱ ነው።
በአደጋዉ ከአንድ ቤተሰብ እስከ 4 ሰዉ የሞተበት ሁኔታ ስለመኖሩ የገለጹት ማቴ ማንገሻ (ዶ/ር) የአደጋው ሰለባ የሆኑት ሁሉም ሟቾች ከ40 ዓመት በታች የሆኑ ወጣቶች ስለመሆናቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
" በአደጋዉ ሙሽራዉን ጨምሮ የ71 ሰዎች ሕይወት አልፏል " - ማቴ መንገሻ (ዶ/ር)
🚨 " አደጋዉ ' ከቡና ሳይት በሚመለሱ ሰዎች ላይ የተከሰተ ነዉ ' ተብሎ የተገለፀት አግባብ ሙሽራዉን ጨምሮ አብዛኞቹ ሟቾች የቡና ሳይት የሚሰሩ በመሆናቸዉ ነው ! "
ዛሬ በሲዳማ ክልል፣ ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ቦና ወረዳ ልዩ ስሙ ጋላና ድልድይ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ ሰርገኞችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ መኪና ተገልብጦ ሙሽራውን ጨምሮ የ71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ ማቴ መንገሻ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" አይሱዙው 11 ሰዓት አካባቢ መነሻዉን ቦና ወረዳ ሚሪዴ ገጠር ቀበሌ አድርጎ ወራንቻ ወደተባለ አጎራበች ቀበሌ የወንድ ወገን የሆኑ ከ70 በላይ ሰርገኞችን ጭኖ ወደ ሴቷ ቤት ጉዞ ላይ ነበር " ብለዋል።
ገላና ድልድይ ላይ ሲደርስ ግን ድልድዩን ስቶ ወደ ወንዝ ዉስጥ በመግባቱ እስካሁን በተጣራዉ መረጃ አስክሬናቸው ቦና አጠቃላይ ሆስፒታል የደረሰ 66 እንዲሁም ከአደጋዉ ቦታ በቀጥታ ቤተሰቦቻቼዉ የወሰዷቸዉን ጨምሮ በአጠቃላይ ወንድ 68 ሴት 3 በድምሩ 71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አረጋግጠዋል።
በ4 ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንና አንዲት ሴት ወደ ሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል መላኳንም ማቴ (ዶ/ር) ጨምረው ገልፀዋል
የአደጋው ትክክለኛ መንስኤ እየተጣራ ነዉ ያሉት ማቴ (ዶ/ር) ፤ " በገጠር አከባቢ በሰርግ እና ደስታ ወቅት በክፍት መኪኖች ላይ ከመጠን በላይ መጫንና አልፎ አልፎም መጠጥ የመቀማመስ ሁኔታዎች ስለሚኖሩ፤ ይህ ለአደጋው አንዱ መንስዔ ተደርጎ ይገመታል " ብለዋል።
" አደጋዉ ' ከቡና ሳይት በሚመለሱ ሰዎች ላይ የተከሰተ ነዉ ' ተብሎ የተገለፀት አግባብ ሙሽራዉን ጨምሮ አብዛኞቹ ሟቾች የቡና ሳይት የሚሰሩ በመሆናቸዉና ተሽከሪካሪዉም የቡና ሳይት በመሆኑ ነዉ " ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
የክልሉ ፖሊስ ቀደም ብሎ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል መኪናው ላይ የነበሩት ወገኖች የቡና ሳይት ስራ ላይ ቆይተው ሲመለሱ የነበሩ እንደሆኑ ገልጾ ነበር።
እንደ ዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ማብራሪያ ግን ምንም እንኳን መኪናው ላይ የነበሩት አብዛኛዎቹ ወገኖች (ሙሽራውን ጨምሮ) የቡና ሳይት ስራ ላይ ተሰማርተው የሚሰሩና መኪናውም የቡና ሳይት ቢሆንም በሰዓቱ ሲጓዙ የነበረውና አደጋው የደረሰው ለሰርግ ወደ ሴቷ ቤት ማለትም ሙሽራው ሙሽሪትን ለመውሰድ ሲሄዱ ነው።
በአደጋዉ ከአንድ ቤተሰብ እስከ 4 ሰዉ የሞተበት ሁኔታ ስለመኖሩ የገለጹት ማቴ ማንገሻ (ዶ/ር) የአደጋው ሰለባ የሆኑት ሁሉም ሟቾች ከ40 ዓመት በታች የሆኑ ወጣቶች ስለመሆናቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ
#ይቀበሉ_ይመንዝሩ_ተጨማሪ_2%_ #እና_ልዩ_የበአል_ስጦታዎን_ይውሰዱ
ከውጪ ሃገራት የሚላክልዎትን ገንዘብ ከብርሃን ባንክ ጋር ከሚሰሩ አለምአቀፍ የገንዘብ አስተላላፊዎች #ሪያ #ዳሃብሽል #ዌስተርን_ዩኒየን #መኒግራም #ትራንስ_ፋስትና #ወርልድ_ረሚት በኩል ሲቀበሉ ወይም በእጅዎ ያለውን የውጭ ሃገር ገንዘብ በባንካችን ሲመነዝሩ ከእለቱ የምንዛሪ ተመን በተጨማሪ 2% እና ልዩ የበዓል ስጦታ ያገኛሉ!
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
#moneytransfer #Stressfreebanking #berhanbank #bank #finance #bankinethiopia
ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ!
➡️ Facebook
➡️ Telegram
➡️ Instagram
➡️ Twitter
➡️ LinkedIn
➡️ YouTube
#ይቀበሉ_ይመንዝሩ_ተጨማሪ_2%_ #እና_ልዩ_የበአል_ስጦታዎን_ይውሰዱ
ከውጪ ሃገራት የሚላክልዎትን ገንዘብ ከብርሃን ባንክ ጋር ከሚሰሩ አለምአቀፍ የገንዘብ አስተላላፊዎች #ሪያ #ዳሃብሽል #ዌስተርን_ዩኒየን #መኒግራም #ትራንስ_ፋስትና #ወርልድ_ረሚት በኩል ሲቀበሉ ወይም በእጅዎ ያለውን የውጭ ሃገር ገንዘብ በባንካችን ሲመነዝሩ ከእለቱ የምንዛሪ ተመን በተጨማሪ 2% እና ልዩ የበዓል ስጦታ ያገኛሉ!
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
#moneytransfer #Stressfreebanking #berhanbank #bank #finance #bankinethiopia
ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ!
➡️ Telegram
➡️ YouTube
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አሁንም ቀጥሏል። ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ በሬክተር ስኬል 5 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በድጋሚ ተከስቷል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ የጂኦፊዚክስ እና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር የሆኑት ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) ፤ ዛሬ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በሬክተር ስኬል 5 ሆኖ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ…
" ከ2 ሺሕ 500 በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል " - አቶ አደም ባሂ
በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ አከባቢ በሚከሰት ተደጋጋሚ ርዕደ መሬት ከ100 በላይ ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸዉ ሲሆን 2 ሺሕ 560 ሰዎች መፈናቀላቸውን እና እንሰሳት መሞታቸውን የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ አስተዳደር አቶ አደም ባሂ አሳውቀዋል።
ለአሐዱ በሰጡት ቃል ፤ " ይህ ክስተት በሚድያ እንደሚባለዉ በቀን ሦስቴ እና ሁለቴ የሚከሰት ሳይሆን ከዚያም በላይ አስጊ እየሆነ ይገኛል " ብለዋል።
በአካባቢዉ ያለዉ የከሰም ግድብን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችስ ጉዳት ደርሶባቸዋል ወይ ? ለሚለው ጥያቄ " ግድቡን በተመለከተ ራሱን የቻለ አደረጃጀት ተደራጅቶ እየተጠበቀ ይገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።
" እስካሁን በተፈጠረዉ ርዕደ መሬት ምክንያት ምንም ጉዳት ባይደርስበትም፤ በተደጋጋሚ በአቅራቢያው እየተከሰተ በመሆኑ በጥብቅ እየተከታተሉ ነው " ሲሉ አክለዋል።
በተጨማሪም በአካባቢዉ ያለዉ ተፈናቃይ ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ መሆኑን አንስተው ፤ መጠለያ፣ ምግብ እና መሰረታዊ ግብአቶች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል።
የክልሉ የአደጋ ስጋት ድጋፍ እንዲያደርግም እንደጠየቁ ገልጸዋል።
በተደጋጋሚ ጊዜ በተከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦች ምክንያት፤ እስከ አሁን በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ሳቡሬ እና ዶኾ ቀበሌዎች ከ30 በላይ የመኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱም ተነግሯል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የአሐዱ ነው።
@tikvahethiopia
በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ አከባቢ በሚከሰት ተደጋጋሚ ርዕደ መሬት ከ100 በላይ ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸዉ ሲሆን 2 ሺሕ 560 ሰዎች መፈናቀላቸውን እና እንሰሳት መሞታቸውን የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ አስተዳደር አቶ አደም ባሂ አሳውቀዋል።
ለአሐዱ በሰጡት ቃል ፤ " ይህ ክስተት በሚድያ እንደሚባለዉ በቀን ሦስቴ እና ሁለቴ የሚከሰት ሳይሆን ከዚያም በላይ አስጊ እየሆነ ይገኛል " ብለዋል።
በአካባቢዉ ያለዉ የከሰም ግድብን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችስ ጉዳት ደርሶባቸዋል ወይ ? ለሚለው ጥያቄ " ግድቡን በተመለከተ ራሱን የቻለ አደረጃጀት ተደራጅቶ እየተጠበቀ ይገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።
" እስካሁን በተፈጠረዉ ርዕደ መሬት ምክንያት ምንም ጉዳት ባይደርስበትም፤ በተደጋጋሚ በአቅራቢያው እየተከሰተ በመሆኑ በጥብቅ እየተከታተሉ ነው " ሲሉ አክለዋል።
በተጨማሪም በአካባቢዉ ያለዉ ተፈናቃይ ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ መሆኑን አንስተው ፤ መጠለያ፣ ምግብ እና መሰረታዊ ግብአቶች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል።
የክልሉ የአደጋ ስጋት ድጋፍ እንዲያደርግም እንደጠየቁ ገልጸዋል።
በተደጋጋሚ ጊዜ በተከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦች ምክንያት፤ እስከ አሁን በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ሳቡሬ እና ዶኾ ቀበሌዎች ከ30 በላይ የመኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱም ተነግሯል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የአሐዱ ነው።
@tikvahethiopia
#NGAT
ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች ምዝገባ ከታህሳስ 21 እስከ 25/2017 ዓ.ም ይከናወናል፡፡
ለመመዝገብ 👇
HTTPS://NGAT.ETHERNET.EDU.ET
ከምዝገባው ጋር ለተያያዘ ማንኛውም ጥያቄ በሥራ ሰዓት በኢሜል አድራሻ [email protected] ወይም በስልክ ቁጥር 0920157474 (Enatnesh Gebeyehu) እና 0911335683 (Fasil Tsegaye) ማብራሪያ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን ተገልጿል።
የመፈተኛ ' USER NAME ' እና " PASSWORD ' በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ሲሆን፤ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈጸም ይጠበቅባችኋል ተብሏል፡፡
ፈተናው የሚሰጥበትን ጊዜ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
#MoE
Via @tikvahuniversity
ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች ምዝገባ ከታህሳስ 21 እስከ 25/2017 ዓ.ም ይከናወናል፡፡
ለመመዝገብ 👇
HTTPS://NGAT.ETHERNET.EDU.ET
ከምዝገባው ጋር ለተያያዘ ማንኛውም ጥያቄ በሥራ ሰዓት በኢሜል አድራሻ [email protected] ወይም በስልክ ቁጥር 0920157474 (Enatnesh Gebeyehu) እና 0911335683 (Fasil Tsegaye) ማብራሪያ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን ተገልጿል።
የመፈተኛ ' USER NAME ' እና " PASSWORD ' በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ሲሆን፤ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈጸም ይጠበቅባችኋል ተብሏል፡፡
ፈተናው የሚሰጥበትን ጊዜ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
#MoE
Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የመሬት መንቀጥቀጡ የቦታ ለውጥ አድርጓል ?
" በአንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም " - ፕ/ር አታላይ አየለ
በትላንትናው ዕለት በቀን፣ በምሽትና በለሊቱ ክፍለ ጊዜ ተደጋጋሚ የሆነ የመሬት መንቀጥቀጦች መከሰታቸው ዓለም አቀፍ ጁኦሎጂካል ተቋማት ዘግበዋል።
ትላንት ምሽት 2:10 የተከሰተው እና ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ ከተሰማው በሬክተር ስኬል 5.0 ሆኖ ከተመዘገበው መንቀጥቀጥ በተጨማሪ ለሊት 7:20 ላይ 5.1 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ አስታውቋል።
የመሬት መንቀጥቀጡ በተጠቀሰው መጠን መከሰቱን እና ዛሬ ጠዋት 2:11 ላይም ሌላ መንቀጥቀጥ በመታየቱ የመተንተን ስራ እየተሰራ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ህዋ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም፤ የሴስሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕ/ር አታላይ አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ትላንት ለሊት 7:20 ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ከደብረ ሲና 52 ኪሜ ርቀት ላይ ምሽት ላይ የተከሰተው ደግሞ ከአዋሽ 14 ኪሜ ርቀት ላይ የተከሰተ ነው መባሉ ከዚህ ቀደም ይከሰት ከነበረበት የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የቦታ ለውጥ አለ ማለት አለመሆኑን አስረድተዋል።
ተመራማሪው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?
" ትላንትና ከሰዓት ጀምሮ በጣም የተደጋጋመ ከፍተኛ መጠን ያለው ከ4.6 ጀምሮ እስከ 5.0 የተመዘገበ መንቀጥቀጥ ተከስቷል ፤ ነገር ግን ደብረ ሲና ሲል ከፈንታሌ በወፍ በረር ሲለካ ነው ከተለያየ አቅጣጫ በማየት ነው እንጂ መነሻው ስለተቀየረ አይደለም።
አንድ አካባቢ ላይ መሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት በአቅራቢያው ያለው ከተማ የትኛው ነው ? የሚለው ይታያል ከዛ የተለያዩ ከተሞችን እንደ ሪፈረንስ ይጠቅስና ከዛ ከተማ ምን ያህል ነው የሚርቀው የሚለውን ሪፈር ያደርጋል፤ እንደዛ ሲሆን ሌላ ሰው መንቀጥቀጡ ለዛ ከተማ ቀርቧል ማለት ነው የሚል ስጋት ሊያድርበት ይችላል ነገር ግን እስካሁን የተቀየረ ነገር የለም፤ ፈንታሌ ዙሪያ ነው እንቅስቃሴው እየተታየ ያለው።
የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ እና የጀርመኑ የጂኦ ሳይንስ ተቋማት የሚጠቀሙት ዳታ አውቶማቲክ ነው ሲስተሙ ቶሎ አናላይዝ አድርጎ የተከሰተበትን መጠን እና አካባቢ ከርቀት ጋር ይናገራል ነገር ግን ይህ አይነቱን አዘጋገብ የሚከተሉት ለማህበረሰቡ በምን ያህል ርቀት ላይ ነው የተከሰተው የሚለውን ለማስረዳት ነው።
ለምሳሌ፦ አንድ ብቻ አይደለም የተለያዩ ቦታዎች ይጠቅሳሉ ከመተሃራ፣ከደብረሲና ፣ከደብረ ብርሃን እና ከአዲስ አበባስ ምን ያህል ርቀት ላይ ይገኛል ሊል ይችላል በአንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም።
አዲስ ነገር አይደለም ስንመዘግብ የኖርነው ነገር ነው ነገር ግን መሃንዲስም፣ ኢንቨስተርም ሆነ የሚመለከተው አካል ጆሮ ሰጥቶ ጥንቃቄ አድርጎ አያውቅም አሁን የሚከሰተውንም መአት እንደተከሰተ አድርጎ የሚያወራ አለ እንደዛ አይደለም በተለያየ ጊዜ ይመዘገባል።
በ1997 በአፋር ታይቶ የማይታወቅ የቅልጥ አለት እንቅስቃሴ ነበር ብዙ አለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ሁሉ መጥተው አብረን የሰራናቸው ስራዎች አሉ፣ ፈንታሌም በፈረንጂዎቹ 1981 እንደ አሁኑ 3 እና 4 ወር የቆየ የቅልጥ አለት እንቅስቃሴ ነበር።
የመረጃ ውንዥብር እየተፈጠረ ነው ሳይንቲስት የምንለው ማነው ? ታማኝነቱስ ምን ያህል ነው ?የሚለው አስቸጋሪ ሆኗል ያልሆነውን ሆኗል እያሉ የሚያወናብደውም ብዝቷል ተማረ የምንለውም መሬት ላይ ያለውም ህብረተሰብ።
መሬት በራሷ ጉዞ እየሄደች የምታስተነፍሰው ሃይል ነው ምንም የሚያስደንቅ ነገር አይደለም ቦታውም፣ በምን ያህል ርቀት ላይ እንደሆነ ይታወቃል በተለይ አዲስ አበባ ያለ ሰው ምንም ሊደነግጥ አይገባም።
ከትላንት እኩለ ቀን ጀምሮ ጎላ ጎላ ያሉት መንቀጥቀጦች የመደጋገም ፍጥነታቸው ጨምሯል ቀጣይነትም ያለው ሊሆን ይችላል እየተከታተልን እየመዘገብን እንገኛለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AAU
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
" በአንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም " - ፕ/ር አታላይ አየለ
በትላንትናው ዕለት በቀን፣ በምሽትና በለሊቱ ክፍለ ጊዜ ተደጋጋሚ የሆነ የመሬት መንቀጥቀጦች መከሰታቸው ዓለም አቀፍ ጁኦሎጂካል ተቋማት ዘግበዋል።
ትላንት ምሽት 2:10 የተከሰተው እና ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ ከተሰማው በሬክተር ስኬል 5.0 ሆኖ ከተመዘገበው መንቀጥቀጥ በተጨማሪ ለሊት 7:20 ላይ 5.1 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ አስታውቋል።
የመሬት መንቀጥቀጡ በተጠቀሰው መጠን መከሰቱን እና ዛሬ ጠዋት 2:11 ላይም ሌላ መንቀጥቀጥ በመታየቱ የመተንተን ስራ እየተሰራ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ህዋ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም፤ የሴስሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕ/ር አታላይ አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ትላንት ለሊት 7:20 ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ከደብረ ሲና 52 ኪሜ ርቀት ላይ ምሽት ላይ የተከሰተው ደግሞ ከአዋሽ 14 ኪሜ ርቀት ላይ የተከሰተ ነው መባሉ ከዚህ ቀደም ይከሰት ከነበረበት የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የቦታ ለውጥ አለ ማለት አለመሆኑን አስረድተዋል።
ተመራማሪው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?
" ትላንትና ከሰዓት ጀምሮ በጣም የተደጋጋመ ከፍተኛ መጠን ያለው ከ4.6 ጀምሮ እስከ 5.0 የተመዘገበ መንቀጥቀጥ ተከስቷል ፤ ነገር ግን ደብረ ሲና ሲል ከፈንታሌ በወፍ በረር ሲለካ ነው ከተለያየ አቅጣጫ በማየት ነው እንጂ መነሻው ስለተቀየረ አይደለም።
አንድ አካባቢ ላይ መሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት በአቅራቢያው ያለው ከተማ የትኛው ነው ? የሚለው ይታያል ከዛ የተለያዩ ከተሞችን እንደ ሪፈረንስ ይጠቅስና ከዛ ከተማ ምን ያህል ነው የሚርቀው የሚለውን ሪፈር ያደርጋል፤ እንደዛ ሲሆን ሌላ ሰው መንቀጥቀጡ ለዛ ከተማ ቀርቧል ማለት ነው የሚል ስጋት ሊያድርበት ይችላል ነገር ግን እስካሁን የተቀየረ ነገር የለም፤ ፈንታሌ ዙሪያ ነው እንቅስቃሴው እየተታየ ያለው።
የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ እና የጀርመኑ የጂኦ ሳይንስ ተቋማት የሚጠቀሙት ዳታ አውቶማቲክ ነው ሲስተሙ ቶሎ አናላይዝ አድርጎ የተከሰተበትን መጠን እና አካባቢ ከርቀት ጋር ይናገራል ነገር ግን ይህ አይነቱን አዘጋገብ የሚከተሉት ለማህበረሰቡ በምን ያህል ርቀት ላይ ነው የተከሰተው የሚለውን ለማስረዳት ነው።
ለምሳሌ፦ አንድ ብቻ አይደለም የተለያዩ ቦታዎች ይጠቅሳሉ ከመተሃራ፣ከደብረሲና ፣ከደብረ ብርሃን እና ከአዲስ አበባስ ምን ያህል ርቀት ላይ ይገኛል ሊል ይችላል በአንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም።
አዲስ ነገር አይደለም ስንመዘግብ የኖርነው ነገር ነው ነገር ግን መሃንዲስም፣ ኢንቨስተርም ሆነ የሚመለከተው አካል ጆሮ ሰጥቶ ጥንቃቄ አድርጎ አያውቅም አሁን የሚከሰተውንም መአት እንደተከሰተ አድርጎ የሚያወራ አለ እንደዛ አይደለም በተለያየ ጊዜ ይመዘገባል።
በ1997 በአፋር ታይቶ የማይታወቅ የቅልጥ አለት እንቅስቃሴ ነበር ብዙ አለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ሁሉ መጥተው አብረን የሰራናቸው ስራዎች አሉ፣ ፈንታሌም በፈረንጂዎቹ 1981 እንደ አሁኑ 3 እና 4 ወር የቆየ የቅልጥ አለት እንቅስቃሴ ነበር።
የመረጃ ውንዥብር እየተፈጠረ ነው ሳይንቲስት የምንለው ማነው ? ታማኝነቱስ ምን ያህል ነው ?የሚለው አስቸጋሪ ሆኗል ያልሆነውን ሆኗል እያሉ የሚያወናብደውም ብዝቷል ተማረ የምንለውም መሬት ላይ ያለውም ህብረተሰብ።
መሬት በራሷ ጉዞ እየሄደች የምታስተነፍሰው ሃይል ነው ምንም የሚያስደንቅ ነገር አይደለም ቦታውም፣ በምን ያህል ርቀት ላይ እንደሆነ ይታወቃል በተለይ አዲስ አበባ ያለ ሰው ምንም ሊደነግጥ አይገባም።
ከትላንት እኩለ ቀን ጀምሮ ጎላ ጎላ ያሉት መንቀጥቀጦች የመደጋገም ፍጥነታቸው ጨምሯል ቀጣይነትም ያለው ሊሆን ይችላል እየተከታተልን እየመዘገብን እንገኛለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AAU
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
#AwashBank
ሽልማትዎን ይውሰዱ!
=========
አዋሽ ባንክ ‘ባንክዎ በእጅዎ’ በሚል መሪ ቃል ለአንድ ወር የሚቆይ የዲጂታል ባንኪንግ ንቅናቄ እያካሄደ ይገኛል። በመሆኑም የአዋሽ ብር ፕሮ ሞባይል ባንኪንግ አገልግሎትን ሲጠቀሙ፡
- ለነጋዴዎች 52 ስማርት ስልክ ስጦታዎች
- ለድርጅት ገንዘብ ተቀባዮች በጋራ እስከ 15 ሺህ ብር የጉርሻ ስጦታ
- ለደንበኞች አዋሽ ብር ፕሮን ሲመዘገቡና መጠቀም ሲጀምሩ የ15 ብር የጉርሻ ስጦታ
- ከዚህ በፊት ተመዝግበው ነገር ግን ሳያንቀሳቅሱት ቆይተው አሁን መጠቀም ሲጀምሩ የ15 ብር የጉርሻ ስጦታ ይበረከትልዎታል!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ።
ለበለጠ መረጃ https://yangx.top/awash_bank_official ወይም www.awashbank.com ይጎብኙ!
አዋሽ ባንክ!
ሽልማትዎን ይውሰዱ!
=========
አዋሽ ባንክ ‘ባንክዎ በእጅዎ’ በሚል መሪ ቃል ለአንድ ወር የሚቆይ የዲጂታል ባንኪንግ ንቅናቄ እያካሄደ ይገኛል። በመሆኑም የአዋሽ ብር ፕሮ ሞባይል ባንኪንግ አገልግሎትን ሲጠቀሙ፡
- ለነጋዴዎች 52 ስማርት ስልክ ስጦታዎች
- ለድርጅት ገንዘብ ተቀባዮች በጋራ እስከ 15 ሺህ ብር የጉርሻ ስጦታ
- ለደንበኞች አዋሽ ብር ፕሮን ሲመዘገቡና መጠቀም ሲጀምሩ የ15 ብር የጉርሻ ስጦታ
- ከዚህ በፊት ተመዝግበው ነገር ግን ሳያንቀሳቅሱት ቆይተው አሁን መጠቀም ሲጀምሩ የ15 ብር የጉርሻ ስጦታ ይበረከትልዎታል!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ።
ለበለጠ መረጃ https://yangx.top/awash_bank_official ወይም www.awashbank.com ይጎብኙ!
አዋሽ ባንክ!
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቃዎች ታግተዋል " የተባሉት 3 የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች ሜይሊ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በሚገኝ እስር ቤት እንደሚገኙ የትግራይ ቴሌቪዥን ከደቂቃዎች በፊት ማረጋገጡ ይታወሳል። አሁን ከስፍራው በተገኘው መረጃ ሦስቱ ጋዜጠኞች ከእስር ተለቀዋል። የጋዜጠኞቹ መፈታት በማስመልከት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ፥ ጋዜጠኞቹ መረጃ…
#Tigray
የትግራይ የፀጥታና የሰላም ቢሮ " ትግራይ ቴሌቪዥን " ይቅርታ ይጠይቅ አለ።
ቢሮው ይህን ያለድ ለአንድ ቀን ያህል በእገታና አስር ቆይተው ተለቀቁ በተባሉት ሦስት የትግራይ ቴሌቪዥን ባለሙያዎች ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ነው።
የቢሮው መግለጫ የሚድያ ባለሙያዎቹ እገታ እና እስር አስመልክቶ የተሰራጨውን መረጃ የሚቃወም እንድምታ አለው።
ተስፋዝጊ ዓስበይ ፣ ኢሳያስ በየነ እና ኣታኽልቲ የተባሉ የትግራይ ቴሌቪዥን የሚድያ ባለሙያዎች ታግተውበታል ወደ ተባለው ቦታ መሄዳቸው የወረዳ ፣ የቀበሌ እና የመንደር አመራሮች መረጃ አልነበራቸውም ብሏል።
ይህ ባልሆነበት ሁኔታ ' ታግተናል ታስረናል ' ማለታቸው ልክ እንዳልሆነ አመላክቷል።
" ጋዜጠኞቹ ወደ ቦታው እንዲንቀሳቀሱ የቀበሌ እና የመንደር አመራሮች መረጃ እንዲኖራቸው የግድ ነው ወይ ? " የሚል ጥያቄን ግን የቢሮው መግለጫ አለመለሰም።
" ሊበሉዋት የፈለጓትን አሞራ ቆቅ ናት ይሉዋታል " ብሎ የተረተው የሰላምና የፀጥታ ቢሮ መግለጫ ፤ ተገቢ ማጣራት ሳይደረግ የሚድያ ባለሙያዎቹ ' ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ታግተዋል ፤ ታፍነዋል ' ተብሎ የተሰራጨው መረጃ መስተካከል እና የትግራይ ቴሌቪዥን ይቅርታ ሊጠየቅበት እንደሚገባ አስገንዝቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጋዜጠኞች እና የሚድያ ባለሙያዎች የሙያ ነፃነታቸው ተከብሮ በማንኛውም ጊዜ በማንኛውም ቦታ ተዘዋውረው መረጃ በማሰባሰብ ለህዝብ የማድረስ መብት እንዳላቸው የገለጸው የትግራይ ጋዜጠኞች ማህበር ፤ በትግራይ ቴሌቪዥን የሚድያ ባለሙያዎች ላይ የተደረገው ወከባ አፈና ፣ እስር እና እንግልት በፅኑ ኮንነዋል።
ጋዜጠኞቹ ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወር ለህዝብ እና ለአገር መረጃ ለማቅረብ ሲንቀሳቀሱ ተገቢ የፀጥታ ጥብቃ ሊድረግላቸው እንደሚገባ ያሳሰበው የማህበሩ መግለጫ ፤ ህግ እና ስርዓት አክብረው ተገቢ የሙያ ተግባራቸው በሚከውኑ የሚድያ ባለሙያዎች ላይ የሚድረግ ማንኛውም ዓይነት አፈና ፣ በደል ፣ ክልከላ እና ወከባ በጥብቅ እንቃወማለን ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ የፀጥታና የሰላም ቢሮ " ትግራይ ቴሌቪዥን " ይቅርታ ይጠይቅ አለ።
ቢሮው ይህን ያለድ ለአንድ ቀን ያህል በእገታና አስር ቆይተው ተለቀቁ በተባሉት ሦስት የትግራይ ቴሌቪዥን ባለሙያዎች ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ነው።
የቢሮው መግለጫ የሚድያ ባለሙያዎቹ እገታ እና እስር አስመልክቶ የተሰራጨውን መረጃ የሚቃወም እንድምታ አለው።
ተስፋዝጊ ዓስበይ ፣ ኢሳያስ በየነ እና ኣታኽልቲ የተባሉ የትግራይ ቴሌቪዥን የሚድያ ባለሙያዎች ታግተውበታል ወደ ተባለው ቦታ መሄዳቸው የወረዳ ፣ የቀበሌ እና የመንደር አመራሮች መረጃ አልነበራቸውም ብሏል።
ይህ ባልሆነበት ሁኔታ ' ታግተናል ታስረናል ' ማለታቸው ልክ እንዳልሆነ አመላክቷል።
" ጋዜጠኞቹ ወደ ቦታው እንዲንቀሳቀሱ የቀበሌ እና የመንደር አመራሮች መረጃ እንዲኖራቸው የግድ ነው ወይ ? " የሚል ጥያቄን ግን የቢሮው መግለጫ አለመለሰም።
" ሊበሉዋት የፈለጓትን አሞራ ቆቅ ናት ይሉዋታል " ብሎ የተረተው የሰላምና የፀጥታ ቢሮ መግለጫ ፤ ተገቢ ማጣራት ሳይደረግ የሚድያ ባለሙያዎቹ ' ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ታግተዋል ፤ ታፍነዋል ' ተብሎ የተሰራጨው መረጃ መስተካከል እና የትግራይ ቴሌቪዥን ይቅርታ ሊጠየቅበት እንደሚገባ አስገንዝቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጋዜጠኞች እና የሚድያ ባለሙያዎች የሙያ ነፃነታቸው ተከብሮ በማንኛውም ጊዜ በማንኛውም ቦታ ተዘዋውረው መረጃ በማሰባሰብ ለህዝብ የማድረስ መብት እንዳላቸው የገለጸው የትግራይ ጋዜጠኞች ማህበር ፤ በትግራይ ቴሌቪዥን የሚድያ ባለሙያዎች ላይ የተደረገው ወከባ አፈና ፣ እስር እና እንግልት በፅኑ ኮንነዋል።
ጋዜጠኞቹ ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወር ለህዝብ እና ለአገር መረጃ ለማቅረብ ሲንቀሳቀሱ ተገቢ የፀጥታ ጥብቃ ሊድረግላቸው እንደሚገባ ያሳሰበው የማህበሩ መግለጫ ፤ ህግ እና ስርዓት አክብረው ተገቢ የሙያ ተግባራቸው በሚከውኑ የሚድያ ባለሙያዎች ላይ የሚድረግ ማንኛውም ዓይነት አፈና ፣ በደል ፣ ክልከላ እና ወከባ በጥብቅ እንቃወማለን ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ወደ ኖርዌይ ለልምድ ልውውጥ የሄዱ የሁለት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ወደ ሀገር ሳይመለሱ ቀሩ።
የኢዜማ እና የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አባላት ለልምድ ልውውጥ ከሃገር በወጡበት አለመመለሳቸው ተሰምቷል።
የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦሮ) የሴቶች ጉዳይ ሃላፊ ወ/ሮ አበበች ደቻሳ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የሴቶች ጉዳይ ተጠሪ የነበሩት ወ/ሮ ቅድስት ግርማ በመስከረም አጋማሽ ለልምድ ልውውጥ ወደ #ኖርዌይ ባቀኑበት ወቅት አለመመለሳቸው ተነግሯል።
ሁለቱ አባላት ወደ ኖርዌይ ያቀኑትና ያልተመለሱት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የልምምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ በተላኩበት ወቅት መሆኑን የም/ ቤቱ ጸሃፊ አቶ ደስታ ዲንቃ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አባላቱ በጋራ ምክር ቤቱ የሴቶች ክንፍ ሰብሳቢነት እና ስራ አስፈጻሚነት ሲያገለግሉ ነበር።
አቶ ደስታ ፥ " የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ለማጠናከር በሃገር ደረጃ ከፓርላማ አባላት ጋር እና የሲቪክ ተቋማት ጋር እየተገናኙ ብዙ ስራዎችን ሲሰሩ ነበር " ብለዋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የኢዜማ አባል ፤ አባሏ በስራ ገበታቸው ላይ አለመኖራቸው በማስረዳት " ለምን እንዳልተመለሱ የምናውቀው ነገር የለም " ብሏል።
የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በበኩሉ ከልጆቿና ከባለቤቷ ጋር በፖለቲካ ምክንያት ለእስር ተዳርገው እንደነበር የገለጸ ሲሆን ለመቅረቷም ምክንያት ይህ ሳይሆን እንዳልቀረ ገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢዜማ እና የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አባላት ለልምድ ልውውጥ ከሃገር በወጡበት አለመመለሳቸው ተሰምቷል።
የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦሮ) የሴቶች ጉዳይ ሃላፊ ወ/ሮ አበበች ደቻሳ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የሴቶች ጉዳይ ተጠሪ የነበሩት ወ/ሮ ቅድስት ግርማ በመስከረም አጋማሽ ለልምድ ልውውጥ ወደ #ኖርዌይ ባቀኑበት ወቅት አለመመለሳቸው ተነግሯል።
ሁለቱ አባላት ወደ ኖርዌይ ያቀኑትና ያልተመለሱት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የልምምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ በተላኩበት ወቅት መሆኑን የም/ ቤቱ ጸሃፊ አቶ ደስታ ዲንቃ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አባላቱ በጋራ ምክር ቤቱ የሴቶች ክንፍ ሰብሳቢነት እና ስራ አስፈጻሚነት ሲያገለግሉ ነበር።
አቶ ደስታ ፥ " የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ለማጠናከር በሃገር ደረጃ ከፓርላማ አባላት ጋር እና የሲቪክ ተቋማት ጋር እየተገናኙ ብዙ ስራዎችን ሲሰሩ ነበር " ብለዋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የኢዜማ አባል ፤ አባሏ በስራ ገበታቸው ላይ አለመኖራቸው በማስረዳት " ለምን እንዳልተመለሱ የምናውቀው ነገር የለም " ብሏል።
የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በበኩሉ ከልጆቿና ከባለቤቷ ጋር በፖለቲካ ምክንያት ለእስር ተዳርገው እንደነበር የገለጸ ሲሆን ለመቅረቷም ምክንያት ይህ ሳይሆን እንዳልቀረ ገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ በተመሳሳይ ሰዓት እንደሚካሄድ ተገለጸ።
ይህንን የገለጸው አዘጋጁ የኢትዮጵያ ጃንደረባ ትውልድ / ኢጃት ማኅበር ነው።
የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት ምክንያት በማድረግ የሚዘጋጀው ይህ የዝማሬ መርሐግብር በበዓሉ ዋዜማ ታኅሣሥ 28/ 2017 ዓ/ም ይካሄዳል።
በአዲስ አበባ ከተማ የዝማሬ መርሐግብሩ አምና በተካሄደበት በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል (ቦሌ መድኃኔዓለም) እንደሚካሄድ ነው አዘጋጆቹ ያሳወቁት።
" የጌታችንን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት በዝማሬ እናክብር " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የልደት በዓልን ዋዜማ በቤተክርስቲያን ተገኝተው በዝማሬ እንዲያከብሩ ተብሏል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ አዘጋጆቹ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ካዘጋጁት " የአእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads " መርሐግብር ውጭ ሌላ እንዳላዘጋጁ እንዲሁም ለዚህ መርሐግብር ተብሎ የሚደረግ ምዝገባም እንደሌለና ምዕመኑ ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል።
ባለፈው ዓመት በአዲስ አበባ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል በተካሄደው " የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኦርቶዶክሳዊ ወጣት የልደት ዋዜማን በዝማሬና በፀሎት ተቀብሎ ነበር።
መርሐግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትና ብፁአን አባቶች ተገኝተው እንደነበር አይዘነጋም።
ከመርሐግብሩ ቀደም ብሎ ምዕመናን በተለይም ወጣቶች የተዘጋጁ መዝሙሮችን አጥንተው እንዲመጡ መዝሙሮቹ በኦንላይን ሲሰራጩ ነበር።
ዘንድሮም በተመሳሳይ ለመርሃግብሩ የተዘጋጁ መዝሙሮች በማኅበሩ የማህበራዊ ሚዲያዎች (Janderbaw Media Youtube) ተጭነው ምዕመኑ ጋር እንዲዳረሱ እየተደረገ ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ይህንን የገለጸው አዘጋጁ የኢትዮጵያ ጃንደረባ ትውልድ / ኢጃት ማኅበር ነው።
የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት ምክንያት በማድረግ የሚዘጋጀው ይህ የዝማሬ መርሐግብር በበዓሉ ዋዜማ ታኅሣሥ 28/ 2017 ዓ/ም ይካሄዳል።
በአዲስ አበባ ከተማ የዝማሬ መርሐግብሩ አምና በተካሄደበት በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል (ቦሌ መድኃኔዓለም) እንደሚካሄድ ነው አዘጋጆቹ ያሳወቁት።
" የጌታችንን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት በዝማሬ እናክብር " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የልደት በዓልን ዋዜማ በቤተክርስቲያን ተገኝተው በዝማሬ እንዲያከብሩ ተብሏል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ አዘጋጆቹ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ካዘጋጁት " የአእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads " መርሐግብር ውጭ ሌላ እንዳላዘጋጁ እንዲሁም ለዚህ መርሐግብር ተብሎ የሚደረግ ምዝገባም እንደሌለና ምዕመኑ ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል።
ባለፈው ዓመት በአዲስ አበባ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል በተካሄደው " የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኦርቶዶክሳዊ ወጣት የልደት ዋዜማን በዝማሬና በፀሎት ተቀብሎ ነበር።
መርሐግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትና ብፁአን አባቶች ተገኝተው እንደነበር አይዘነጋም።
ከመርሐግብሩ ቀደም ብሎ ምዕመናን በተለይም ወጣቶች የተዘጋጁ መዝሙሮችን አጥንተው እንዲመጡ መዝሙሮቹ በኦንላይን ሲሰራጩ ነበር።
ዘንድሮም በተመሳሳይ ለመርሃግብሩ የተዘጋጁ መዝሙሮች በማኅበሩ የማህበራዊ ሚዲያዎች (Janderbaw Media Youtube) ተጭነው ምዕመኑ ጋር እንዲዳረሱ እየተደረገ ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia