#አክሱም
🧕" እኛ የምንፈልገው ፍትህ ነው። ሂጃባችንን አድርገን ነው መማር የምንፈልገው። ያለ ሂጃብ ሸሪዓም አይፈቅድም አስቸኳይ እና ዘላቂ መፍትሄ ይሰጠን " - ተማሪዎች
➡️ " የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በአጠቃላይ ሁሉም የሉም ከትምህርት ገበታ ላይ ወጥተዋል " - የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት
👉 " ማንም ተማሪ በትምህርት ቤት ሃይማኖትን የሚያንጸባርቅ ነገር ማድረግ የለበትም " - የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
በትግራይ ፣ አክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ላለፉት 2 ሳምንታት የራስ መሸፈኛ ሂጃብ ለብሰው ወደ ትምህርት ቤት መግባት እንደተከለከሉና በዚህም ከትምህርት ገበታ መውጣታቸውን የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አሳውቋል።
በዚህ ዓመት ከሂጃብ መልበስ ጋር በተያያዘ በአክሱም በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውዝግቡ የጀመረው ጥቅምት ወር ነው።
ተቋሙ ለክልል ትምህርት ቢሮ አሳውቆ አውንታዊ ምላሽ ቢሰጠውም በተግባር የተቀየረ ነገር ግን የለም።
የምክር ቤቱ ፀሀፊ ሓጂ መሓመድ ካሕሳይ ምን አሉ ?
" ፀጉራቸውን ሸፍነው ትምህር ቤት እንዲሄዱ ማየት ያልተፈቀደበት መታየት የለበትም ፀጉሯ የአንድ ሴት ይሄ ሃይማኖታዊ ግዴታ ነው።
ሃይማኖት ውስጥ ፖለቲካ አይገባም፣ ፖለቲካ በሃይማኖት አይገባም እየተባለ በአንቀጽ ተቀምጦ እያለ አሁን ፖለቲካ በሃይማኖት እየገባ ነው።
ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት ቤት ዩኒፎርም ጋር የሚመሳሰል የፀጉር መሸፈኛ ሂጃብ መጠቀም እንደሚችሉ በ2000 ዓ/ም የወጣ ሀገር አቀፍ መመሪያ አለ።
ስለዚህ ዝም ብለን የምናየው ነገር አይሆንም።
በአሁኑ ጊዜ በአራት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ወጥተዋል።
ዋናው ደግሞ 3 ወር ሲማሩ የነበሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለብሔራዊ ፈተና የኦንላይ ምዝገባ የሚደረግበት ወቅት ነው በዚህ ሳምንት ያልቃል የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች እስካሁን አልተመዘገቡም።
የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በአጠቃላይ ሁሉም የሉም ትምህርት ገበታ ላይ ወጥተዋል፤ አልገቡም እስካሁን።
ችግሩ እንዲፈታ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ እና ከአክሱም ከተማ አስተዳደር ትምህርይ ፅ/ቤት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው " ብለዋል።
ተማሪዎች ምን ይላሉ ?
" በጦርነት ምክንያት ለ2 ዓመታት ከሌሎች ተማሪዎች ወደኃላ ቀርተናል አሁን ደግሞ በሂጃብ ምክንያት ፈተና ሊያመልጠን ነው።
ፎርሙ እያመለጠን ነው። ሌሎች ተማሪዎች በሂጀብ ፎርም እንደሞሉ ነው የምናውቀው። እኛ የምንፈልገው ፍትህ ነው። ሂጃባችንን አድርገን ነው መማር የምንፈልገው።
ያለ ሂጃብ ሸሪዓም አይፈቅድም ፤ መፍትሄው ደግሞ በጣም አስቸኳይ እና ዘላቂ መሆን አለበት። እስካሁን መብታችን እየተከበረ አይደለም " ብለዋል።
NB. የክልል ትምህርት ቢሮ እና የአክሱም ከተማ አስተዳደር ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆኑም።
የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምን አለ ?
ምክትል ርዕሰ መምህር ገ/መስቀል ገ/እግዚአብሔር ፦
" ' ትምህርት ቤቶች ከሃይማኖት እና ከፖለቲካ ነጻ መሆን አለባቸው ' ይላል የትግራይ ክልል የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መመሪያ ማንም ተማሪ በትምህርት ቤት ሃይማኖትን የሚያንጸባርቅ ነገር ማድረግ የለበትም።
ክርስቲያኑ መስቀል ወይም መጠምጠሚያ ፤ ሙስሊሙም ሂጀብ ወይም ኮፍያ ማድረግ አይፈቀድም። የትምህርት ቤቱ መለያ ዩኒፎርም ብቻ ነው መልበስ የሚገባው።
የተወሰኑ ተማሪዎች ሂጃባቸውን አናውልቅም ብለው ነበር አሁን ግን ተማሪዎች የትምህት ቤቱን መመሪያ ተከትለው እየገቡ ናቸው።
አሰራሩ ለዓመታት የቆየ ነው " ብለዋል።
አንድ በጉዳዩ ላይ ቃላቸው የሰጡ የክልል ትምህርት ቢሮ ሰራተኛ ፤ " በክልሉ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ እየሆነ ያለው በ1995 የወጣ መመሪያ ነው በዚያ መመሪያ ትምህርት ቤቶች የራሳቸውን መተዳደሪያ ማውጣት እንደሚችሉ ይደነግጋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ትግርኛ አገልግሎት መሆኑን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
🧕" እኛ የምንፈልገው ፍትህ ነው። ሂጃባችንን አድርገን ነው መማር የምንፈልገው። ያለ ሂጃብ ሸሪዓም አይፈቅድም አስቸኳይ እና ዘላቂ መፍትሄ ይሰጠን " - ተማሪዎች
➡️ " የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በአጠቃላይ ሁሉም የሉም ከትምህርት ገበታ ላይ ወጥተዋል " - የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት
👉 " ማንም ተማሪ በትምህርት ቤት ሃይማኖትን የሚያንጸባርቅ ነገር ማድረግ የለበትም " - የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
በትግራይ ፣ አክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ላለፉት 2 ሳምንታት የራስ መሸፈኛ ሂጃብ ለብሰው ወደ ትምህርት ቤት መግባት እንደተከለከሉና በዚህም ከትምህርት ገበታ መውጣታቸውን የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አሳውቋል።
በዚህ ዓመት ከሂጃብ መልበስ ጋር በተያያዘ በአክሱም በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውዝግቡ የጀመረው ጥቅምት ወር ነው።
ተቋሙ ለክልል ትምህርት ቢሮ አሳውቆ አውንታዊ ምላሽ ቢሰጠውም በተግባር የተቀየረ ነገር ግን የለም።
የምክር ቤቱ ፀሀፊ ሓጂ መሓመድ ካሕሳይ ምን አሉ ?
" ፀጉራቸውን ሸፍነው ትምህር ቤት እንዲሄዱ ማየት ያልተፈቀደበት መታየት የለበትም ፀጉሯ የአንድ ሴት ይሄ ሃይማኖታዊ ግዴታ ነው።
ሃይማኖት ውስጥ ፖለቲካ አይገባም፣ ፖለቲካ በሃይማኖት አይገባም እየተባለ በአንቀጽ ተቀምጦ እያለ አሁን ፖለቲካ በሃይማኖት እየገባ ነው።
ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት ቤት ዩኒፎርም ጋር የሚመሳሰል የፀጉር መሸፈኛ ሂጃብ መጠቀም እንደሚችሉ በ2000 ዓ/ም የወጣ ሀገር አቀፍ መመሪያ አለ።
ስለዚህ ዝም ብለን የምናየው ነገር አይሆንም።
በአሁኑ ጊዜ በአራት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ወጥተዋል።
ዋናው ደግሞ 3 ወር ሲማሩ የነበሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለብሔራዊ ፈተና የኦንላይ ምዝገባ የሚደረግበት ወቅት ነው በዚህ ሳምንት ያልቃል የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች እስካሁን አልተመዘገቡም።
የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በአጠቃላይ ሁሉም የሉም ትምህርት ገበታ ላይ ወጥተዋል፤ አልገቡም እስካሁን።
ችግሩ እንዲፈታ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ እና ከአክሱም ከተማ አስተዳደር ትምህርይ ፅ/ቤት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው " ብለዋል።
ተማሪዎች ምን ይላሉ ?
" በጦርነት ምክንያት ለ2 ዓመታት ከሌሎች ተማሪዎች ወደኃላ ቀርተናል አሁን ደግሞ በሂጃብ ምክንያት ፈተና ሊያመልጠን ነው።
ፎርሙ እያመለጠን ነው። ሌሎች ተማሪዎች በሂጀብ ፎርም እንደሞሉ ነው የምናውቀው። እኛ የምንፈልገው ፍትህ ነው። ሂጃባችንን አድርገን ነው መማር የምንፈልገው።
ያለ ሂጃብ ሸሪዓም አይፈቅድም ፤ መፍትሄው ደግሞ በጣም አስቸኳይ እና ዘላቂ መሆን አለበት። እስካሁን መብታችን እየተከበረ አይደለም " ብለዋል።
NB. የክልል ትምህርት ቢሮ እና የአክሱም ከተማ አስተዳደር ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆኑም።
የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምን አለ ?
ምክትል ርዕሰ መምህር ገ/መስቀል ገ/እግዚአብሔር ፦
" ' ትምህርት ቤቶች ከሃይማኖት እና ከፖለቲካ ነጻ መሆን አለባቸው ' ይላል የትግራይ ክልል የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መመሪያ ማንም ተማሪ በትምህርት ቤት ሃይማኖትን የሚያንጸባርቅ ነገር ማድረግ የለበትም።
ክርስቲያኑ መስቀል ወይም መጠምጠሚያ ፤ ሙስሊሙም ሂጀብ ወይም ኮፍያ ማድረግ አይፈቀድም። የትምህርት ቤቱ መለያ ዩኒፎርም ብቻ ነው መልበስ የሚገባው።
የተወሰኑ ተማሪዎች ሂጃባቸውን አናውልቅም ብለው ነበር አሁን ግን ተማሪዎች የትምህት ቤቱን መመሪያ ተከትለው እየገቡ ናቸው።
አሰራሩ ለዓመታት የቆየ ነው " ብለዋል።
አንድ በጉዳዩ ላይ ቃላቸው የሰጡ የክልል ትምህርት ቢሮ ሰራተኛ ፤ " በክልሉ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ እየሆነ ያለው በ1995 የወጣ መመሪያ ነው በዚያ መመሪያ ትምህርት ቤቶች የራሳቸውን መተዳደሪያ ማውጣት እንደሚችሉ ይደነግጋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ትግርኛ አገልግሎት መሆኑን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ ዓመታዊው የታኅሣሥ 19 የሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የንግሥ በዓል በሐዋሳ ከተማ ተከብሯል።
የንግሥ በዓሉ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኦርቶዶክሳውያን በተገኙበት ነው የተከበረው።
የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በዓሉ ያለ አንዳች ኮሽታ በሰላም በከፍተኛ ድምቀት ተከብሯል ብሏል።
የፎቶ ባለቤት ፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር
@tikvahethiopia
የንግሥ በዓሉ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኦርቶዶክሳውያን በተገኙበት ነው የተከበረው።
የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በዓሉ ያለ አንዳች ኮሽታ በሰላም በከፍተኛ ድምቀት ተከብሯል ብሏል።
የፎቶ ባለቤት ፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ ዓመታዊው የታኅሣሥ 19 የሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የንግሥ በዓል በሐዋሳ ከተማ ተከብሯል። የንግሥ በዓሉ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኦርቶዶክሳውያን በተገኙበት ነው የተከበረው። የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በዓሉ ያለ አንዳች ኮሽታ በሰላም በከፍተኛ ድምቀት ተከብሯል ብሏል። የፎቶ ባለቤት ፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር @tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የታኅሣሥ 19 የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በሰላም በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
በበዓሉ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተገኝተው ነበር።
በክብረ በዓሉ ላይ ቅዱስነታቸው ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ሰጥተዋል።
በቁልቢ የቅዱስ ገብርኤል ንግሥ በዓል ላይ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምእመን ተገኝቶ ነበር።
ዓመታዊው የታሥሣ 19 የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በተለያዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አህጉረ ስብከቶችም ተከብሮ ውሏል።
የፎቶ ባለቤት ፦ የኢ/ኦ/ተ/ዋ/ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
@tikvahethiopia
በበዓሉ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተገኝተው ነበር።
በክብረ በዓሉ ላይ ቅዱስነታቸው ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ሰጥተዋል።
በቁልቢ የቅዱስ ገብርኤል ንግሥ በዓል ላይ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምእመን ተገኝቶ ነበር።
ዓመታዊው የታሥሣ 19 የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በተለያዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አህጉረ ስብከቶችም ተከብሮ ውሏል።
የፎቶ ባለቤት ፦ የኢ/ኦ/ተ/ዋ/ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
🚨 " የመብት ጥየቄ በማንሳታችን ከስራ ታግደናል " - የመስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ሰራተኞች
🔴 " ባልተገባ አመፅ ድርጅቱን በማክሰራቸው ምክንያት ለ30 ቀናት ከስራ እንዲታገዱ ተወሰኗል " - ድርጅቱ
በመቐለ ከተማ የሚገኘው የትእምት (EFORT) ድርጅቶች አህት ኩባንያ በሆነው መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ እና ሰራተኞቹ መካከል የተፈጠረው ሰጣ ገባ ከጀመረ ቆይቷል።
ሰራተኞች ያሉባቸው የመብት እና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄዎች እንዲፈቱላቸው በወርሃ ጥቅምት 2017 ዓ.ም ሰላማዊ ስልፈው አድርገው ነበር።
ያነሱዋቸው ጥያቄዎች ሳይመለሱ በመቅረታቸው ለሁለተኛ ጊዜ በያዝነው ወር ሁለተኛ ሳምንት መጀመሪያ ካለፈው የቀጠለ ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።
ሰራተኞቹ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ ፦
- በድርጅቱ የሰራተኞች አስተዳደር መመሪያ መሰረት በውድድር የተሰጠን የእድገት እርከን የሚመጥን ደመወዝ እንዲሰጠን ብንጠይቅም ' በጀት የለም ' በሚል ጥየቄያችን ጀሮ ዳባ ልበስ ተብሏል።
- ለድካም እና ልፋታችን የሚመጥን ደመወዝ ስለማይከፈለን ኑሮሯችንን ለመምራት ተቸግረናል።
- አንድ የሙያ እና የጉልበት ሰራተኛ በቀን ከ50 አስከ 200 ብር ነው የሚከፈለው በዚህ አነስተኛ ክፍያ ቤተሰብ ይቅር እና ራስን ማስተዳደር አቅቶናል ስለሆነም አስፈላጊ የደመወዝ ጭማሪ ይደረግልን።
- ለ10 አመታት የቆየው ጥያቄያችን " ስትራክቸር እየተሰራ ነው " በሚል ሽፋን ምክንያት እየተንከባለለ ቆይቶ በአሁኑ ወቅት " የፈለገ ይስራ ፤ ያልፈለገ ይሂድ " ወደ ማለት ተገብቷል ይህ ልክ አይደለም።
- አቅማችን አሟጠን እየሰራን የልፋታችን እያገኘን አይደለምን ... ሲሉ ድምፃቸው አሰምተዋል።
የድርጅቱ የገበያ ልማት እና የሰው ሃይል አስተዳደደር ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቅያ ፤ ሰራተኞቹ ከታህሳስ 11 እስከ 16/2017 ዓ.ም የስራ ማቆም አድማ በማድረግ ድርጅቱን ላልተገባ ኪሳራ በመጣላቸእ ከታህሳስ 17/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ1 ወር ከስራ እንዲታገዱ መወሰኑን አስታውቋል።
ለአንድ ወር ከስራ የታገዱት ሰራተኞች ቁጥራቸው 250 መሆኑን ደርጅቱ ስማቸው ጠቅሶ ይፋ አድርጓል።
" የድርጅቱ ማኔጅመንት መብታችሁ እና የሚገባችሁ ለምን ትጠይቃላችሁ ? ለምን አጋላጥችሁን ? ስማችንን ጥላሸት ቀብታችሁታል ብሎ የወሰደው እርምጃ ተቀባይነት የለውም " ሲሉ ሰራተኞቹ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል።
መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጅነሪነንግ በብረታ ብረትና ሞደፊክ ስራዎች የተሰማራ ከትእምት (EFORT) ግዙፍ ካምፓኒዎች አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
🚨 " የመብት ጥየቄ በማንሳታችን ከስራ ታግደናል " - የመስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ሰራተኞች
🔴 " ባልተገባ አመፅ ድርጅቱን በማክሰራቸው ምክንያት ለ30 ቀናት ከስራ እንዲታገዱ ተወሰኗል " - ድርጅቱ
በመቐለ ከተማ የሚገኘው የትእምት (EFORT) ድርጅቶች አህት ኩባንያ በሆነው መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ እና ሰራተኞቹ መካከል የተፈጠረው ሰጣ ገባ ከጀመረ ቆይቷል።
ሰራተኞች ያሉባቸው የመብት እና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄዎች እንዲፈቱላቸው በወርሃ ጥቅምት 2017 ዓ.ም ሰላማዊ ስልፈው አድርገው ነበር።
ያነሱዋቸው ጥያቄዎች ሳይመለሱ በመቅረታቸው ለሁለተኛ ጊዜ በያዝነው ወር ሁለተኛ ሳምንት መጀመሪያ ካለፈው የቀጠለ ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።
ሰራተኞቹ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ ፦
- በድርጅቱ የሰራተኞች አስተዳደር መመሪያ መሰረት በውድድር የተሰጠን የእድገት እርከን የሚመጥን ደመወዝ እንዲሰጠን ብንጠይቅም ' በጀት የለም ' በሚል ጥየቄያችን ጀሮ ዳባ ልበስ ተብሏል።
- ለድካም እና ልፋታችን የሚመጥን ደመወዝ ስለማይከፈለን ኑሮሯችንን ለመምራት ተቸግረናል።
- አንድ የሙያ እና የጉልበት ሰራተኛ በቀን ከ50 አስከ 200 ብር ነው የሚከፈለው በዚህ አነስተኛ ክፍያ ቤተሰብ ይቅር እና ራስን ማስተዳደር አቅቶናል ስለሆነም አስፈላጊ የደመወዝ ጭማሪ ይደረግልን።
- ለ10 አመታት የቆየው ጥያቄያችን " ስትራክቸር እየተሰራ ነው " በሚል ሽፋን ምክንያት እየተንከባለለ ቆይቶ በአሁኑ ወቅት " የፈለገ ይስራ ፤ ያልፈለገ ይሂድ " ወደ ማለት ተገብቷል ይህ ልክ አይደለም።
- አቅማችን አሟጠን እየሰራን የልፋታችን እያገኘን አይደለምን ... ሲሉ ድምፃቸው አሰምተዋል።
የድርጅቱ የገበያ ልማት እና የሰው ሃይል አስተዳደደር ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቅያ ፤ ሰራተኞቹ ከታህሳስ 11 እስከ 16/2017 ዓ.ም የስራ ማቆም አድማ በማድረግ ድርጅቱን ላልተገባ ኪሳራ በመጣላቸእ ከታህሳስ 17/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ1 ወር ከስራ እንዲታገዱ መወሰኑን አስታውቋል።
ለአንድ ወር ከስራ የታገዱት ሰራተኞች ቁጥራቸው 250 መሆኑን ደርጅቱ ስማቸው ጠቅሶ ይፋ አድርጓል።
" የድርጅቱ ማኔጅመንት መብታችሁ እና የሚገባችሁ ለምን ትጠይቃላችሁ ? ለምን አጋላጥችሁን ? ስማችንን ጥላሸት ቀብታችሁታል ብሎ የወሰደው እርምጃ ተቀባይነት የለውም " ሲሉ ሰራተኞቹ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል።
መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጅነሪነንግ በብረታ ብረትና ሞደፊክ ስራዎች የተሰማራ ከትእምት (EFORT) ግዙፍ ካምፓኒዎች አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia