TIKVAH-ETHIOPIA
" አስደናቂ ድል ተቀዳጅቻለሁ " - ትራምፕ ዶናልድ ትራምፕ " አስደናቂ ድል ተቀዳጀሁ " አሉ። የሪፐብሊካኑ ዕጩ ትራምፕ ድላቸውን ለደጋፊዎቻቸው የተናገሩት በፍሎሪዳ በተካሄደ መድረክ ነው። ትራምፕ ይህ የአሜሪካ ወርቃማ ዘመን እንደሚሆን ተናግረዋል። " ይህ ለአሜሪካ ህዝብ ታላቅ ድል ነው፤ አሜሪካን እንደገና ታላቅ ለማድረግ ያስችለናል " ብለዋል። በድንበሮች ያሉ ጉዳዮችን እልባት እንደሚሰጡ ቃል…
#USA
ስደተኞች በትራምፕ የስልጣን ዘመን ምን ይገጥማቸው ይሆን ?
ከዚህ ቀደም በምርጫ ዘመቻ ወቅት ዶላንድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉ በስደተኞች ጉዳይ ጠንካራ እርምጃዎችን እንደሚወስዱ ቃል ገብተው ነበር።
ትራምፕ " በአስቸኳይ የስደተኞችን ወረራ አስቆማለሁ፣ ማንኛውም አይነት የህገወጥ ስደተኞችን በረራ እንዲቆም እንዲሁም በማንኛውም መንገድ ወደ አሜሪካ ምድር እንዳይገቡ አደርጋለሁ " ነበር ያሉት።
ከዚህ ባለፈ በስልጣን ዘመናቸው በአሜሪካ ታሪክ ትልቅ የተባለ ዲፖርቴሽን (ከሀገር የማስወጣት) ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
" ከአሜሪካ ምድር ጓዛቸውን አስይዘን ወደ መጡበት እንልካቸዋለን " ያሏቸው ዶክመንት አልባ ህገወጥ ስደተኞችን ነው።
በስድተኞች ጉዳይ ላይ ያላቸው አቋም ከዚህ ቀደምም የሚታወቀው ትራምፕ አሁንም ፕሬዜዳንት ሲሆኑ እንደሚያጠናክሩት ነው በዘመቻ ወቅት ለደጋፊዎቻቸው ቃል የገቡት።
ትራምፕ ቢያንስ ቢያንስ ከ15 እስከ 20 ሚሊዮን ህገወጥ ስደተኞችን ከአሜሪካ ለማስወጣት እቅድ አላቸው ነው የሚባለው።
ይሄን ሁሉ የሰው ቁጥር ግን እንዴት ከአሜሪካ ዲፖርት እንደሚያደርጉ በዝርዝር የሚታወቅ ነገር የለም።
ከዚህ በተጨማሪም በዘመቻቸው ወቅት ፥ ለ4 አመት በስልጣን ሲቆዩ ህገወጥ ስደትን ከማስቆም ባለፈ በህጋዊ ስደተኞች ላይ ደግሞ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።
ትራምፕ ፥ " ስደተኞች ከደቡብ አሜሪካ ፣ #ከአፍሪካ፣ ከእስያ እየመጡ ነው ፤ ከሁሉም የዓለም ክፍል ወደ ሀገራችን የፈሰሱ ነው " ሲሉ ነበር የተናገሩት።
ስደተኞችን " #የሀገራችንን_ደም_እየበከሉ_ነው " በማለት ተናግረውም ብዙዎችን አስቆጥተው ነበር።
በስደተኞች ላይ ጠንካራ አቋም ያላቸው ዶናልድ ትራምፕ አሁን ላይ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዜዳንት መሆናቸው እርግጥ ሆኗል።
#TikvahEthiopia
#USA #deport
@tikvahethiopia
ስደተኞች በትራምፕ የስልጣን ዘመን ምን ይገጥማቸው ይሆን ?
ከዚህ ቀደም በምርጫ ዘመቻ ወቅት ዶላንድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉ በስደተኞች ጉዳይ ጠንካራ እርምጃዎችን እንደሚወስዱ ቃል ገብተው ነበር።
ትራምፕ " በአስቸኳይ የስደተኞችን ወረራ አስቆማለሁ፣ ማንኛውም አይነት የህገወጥ ስደተኞችን በረራ እንዲቆም እንዲሁም በማንኛውም መንገድ ወደ አሜሪካ ምድር እንዳይገቡ አደርጋለሁ " ነበር ያሉት።
ከዚህ ባለፈ በስልጣን ዘመናቸው በአሜሪካ ታሪክ ትልቅ የተባለ ዲፖርቴሽን (ከሀገር የማስወጣት) ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
" ከአሜሪካ ምድር ጓዛቸውን አስይዘን ወደ መጡበት እንልካቸዋለን " ያሏቸው ዶክመንት አልባ ህገወጥ ስደተኞችን ነው።
በስድተኞች ጉዳይ ላይ ያላቸው አቋም ከዚህ ቀደምም የሚታወቀው ትራምፕ አሁንም ፕሬዜዳንት ሲሆኑ እንደሚያጠናክሩት ነው በዘመቻ ወቅት ለደጋፊዎቻቸው ቃል የገቡት።
ትራምፕ ቢያንስ ቢያንስ ከ15 እስከ 20 ሚሊዮን ህገወጥ ስደተኞችን ከአሜሪካ ለማስወጣት እቅድ አላቸው ነው የሚባለው።
ይሄን ሁሉ የሰው ቁጥር ግን እንዴት ከአሜሪካ ዲፖርት እንደሚያደርጉ በዝርዝር የሚታወቅ ነገር የለም።
ከዚህ በተጨማሪም በዘመቻቸው ወቅት ፥ ለ4 አመት በስልጣን ሲቆዩ ህገወጥ ስደትን ከማስቆም ባለፈ በህጋዊ ስደተኞች ላይ ደግሞ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።
ትራምፕ ፥ " ስደተኞች ከደቡብ አሜሪካ ፣ #ከአፍሪካ፣ ከእስያ እየመጡ ነው ፤ ከሁሉም የዓለም ክፍል ወደ ሀገራችን የፈሰሱ ነው " ሲሉ ነበር የተናገሩት።
ስደተኞችን " #የሀገራችንን_ደም_እየበከሉ_ነው " በማለት ተናግረውም ብዙዎችን አስቆጥተው ነበር።
በስደተኞች ላይ ጠንካራ አቋም ያላቸው ዶናልድ ትራምፕ አሁን ላይ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዜዳንት መሆናቸው እርግጥ ሆኗል።
#TikvahEthiopia
#USA #deport
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
⚡️ በዕለታዊ የዳታ ጥቅሎች ቀኑን ሙሉ በየሄድንበት ፈታ እንበል! 🥳
M-PESA ላይ ስንገዛ ሁሉም ቅናሽ አላቸው!
በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በአስተማማኙ ኔትወርክ ዳታ እንንበሽበሽ!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቦታችንን https://yangx.top/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
⚡️ በዕለታዊ የዳታ ጥቅሎች ቀኑን ሙሉ በየሄድንበት ፈታ እንበል! 🥳
M-PESA ላይ ስንገዛ ሁሉም ቅናሽ አላቸው!
በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በአስተማማኙ ኔትወርክ ዳታ እንንበሽበሽ!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቦታችንን https://yangx.top/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቐለ መቐለ ከተማ ውስጥ በጭካኔ የተገደለች እንስት አስከሬንዋ ከ2 ቀን በኋላ መገኘቱን ፓሊስ አስታውቋል። የጭካኔ ተግባሩ የት ፣ መቼ ፣ እንዴት ተፈፀመ ? የጭካኔ ተግባሩ በትግራይ ፣ መቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ዓዲሓ ተብሎ በሚጠራው ልዩ ሰፈር በሚገኝ የአንድ ሆቴል ክፍል ነው የተፈፀመው። ሓበን የማነ የ19 ዓመት ወጣት ስትሆን በሆቴል ክፍል #በቢላዋ ተገድላ መገኘትዋና ጥቅምት 20 /2017…
#መቐለ
" ተጠርጣሪው ተይዞ ለክልሉ ፖሊስ ተላለልፎ ተሰጥቷል " - ፖሊስ
የ19 ዓመትዋን ወጣት በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ በፓሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል።
የመቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጸው ፥ ጥቅምት 19 /2017 ዓ.ም ሓበን የማነ የተባለች ፍቅረኛውን በተከራዩት የሆቴል ክፍል በጬቤ በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ ከቀናት ፍለጋ በኃላ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
በአሰቃቂ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ዳዊት ዘርኡ ተወልደ የተባለው ግለሰብ አሰቃቂ ተግባሩን ፈፅሞ በመሰወሩ ሲፈለግ ቆይቷል።
የሟች ቤተሰብ ጨምሮ በርካታ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች በከባድ ግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ግለሰብ ከትግራይ ክልል ወጥቶ በአማራ ክልል በኩል ሊያመልጥ ሲል በደሴ ከተማ መያዙን ፅፈዋል።
የመረጃው ትክክለኝነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያረጋገጡት የሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሲስ አዛዥ ሞገስ ወርቁ ፥ ተጠርጣሪው በዛሬው ቀን ጥቅምት 27/2017 ዓ.ም ለክልሉ ፓሊስ ተላለልፎ መሰጠቱን ገልፀዋል።
ግለሰቡ ደሴ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ ለፖሊስ ጥቆማ በመድረሱ ነው ሊያዝ የቻለው።
ከክልል ፖሊስ በተገኘው መረጃ ደግሞ ግለሰቡ በአላማጣ አድርጎ ነው ወደ ደሴ የተጓዘው። ወደዛ የሄደውም በረዳት ሹፌርነት ነው።
አንድ ለሊትም በደሴ ከተማ ካሳለፈ በኃላ ሰውነቱ ላይ ያለውን ንቅሳት የሚሸፍን ልብስ ገዝቶ ወደ ያዘው መኝታ ክፍል ሲገባ በደረሰ ጥቆማ ሊያዝ ችሏል። ከዛም መቐለ ፖሊስ አባላቱን በመላክ ተጠርጣሪው ወደ መቐለ እንዲመጣ አድርጓል።
የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም የደሴ ህዝብ ላደረገው ትብብር ምስጋና አቅርቧል።
በከባድ የግድያ ተግባር የተጠረጠረው ግለሰብ አስመልክቶ በማህበራዊ የትስስር ገፆች የተሰራጨው አጭር ቪድዮ እንደሚያመለክተው ፥ ተጠርጣሪው ፍቅረኛውን በጬቤ ከገደላት በኋላ ተፀፅቶ ራሱ ለመግደል ሞኩሮ ሳይሳካለት መቅረቱ በአንደበቱ ይገልፃል።
የሟች ወጣት ሓበን የማነ አባት አቶ የማነ ንጉስ ልጃቸው በጭካኔ በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ በአጭር ጊዜ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ለተባበሩ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
የፎቶ ባለቤት ፦ የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን
@tikvahethiopia
" ተጠርጣሪው ተይዞ ለክልሉ ፖሊስ ተላለልፎ ተሰጥቷል " - ፖሊስ
የ19 ዓመትዋን ወጣት በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ በፓሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል።
የመቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጸው ፥ ጥቅምት 19 /2017 ዓ.ም ሓበን የማነ የተባለች ፍቅረኛውን በተከራዩት የሆቴል ክፍል በጬቤ በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ ከቀናት ፍለጋ በኃላ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
በአሰቃቂ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ዳዊት ዘርኡ ተወልደ የተባለው ግለሰብ አሰቃቂ ተግባሩን ፈፅሞ በመሰወሩ ሲፈለግ ቆይቷል።
የሟች ቤተሰብ ጨምሮ በርካታ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች በከባድ ግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ግለሰብ ከትግራይ ክልል ወጥቶ በአማራ ክልል በኩል ሊያመልጥ ሲል በደሴ ከተማ መያዙን ፅፈዋል።
የመረጃው ትክክለኝነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያረጋገጡት የሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሲስ አዛዥ ሞገስ ወርቁ ፥ ተጠርጣሪው በዛሬው ቀን ጥቅምት 27/2017 ዓ.ም ለክልሉ ፓሊስ ተላለልፎ መሰጠቱን ገልፀዋል።
ግለሰቡ ደሴ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ ለፖሊስ ጥቆማ በመድረሱ ነው ሊያዝ የቻለው።
ከክልል ፖሊስ በተገኘው መረጃ ደግሞ ግለሰቡ በአላማጣ አድርጎ ነው ወደ ደሴ የተጓዘው። ወደዛ የሄደውም በረዳት ሹፌርነት ነው።
አንድ ለሊትም በደሴ ከተማ ካሳለፈ በኃላ ሰውነቱ ላይ ያለውን ንቅሳት የሚሸፍን ልብስ ገዝቶ ወደ ያዘው መኝታ ክፍል ሲገባ በደረሰ ጥቆማ ሊያዝ ችሏል። ከዛም መቐለ ፖሊስ አባላቱን በመላክ ተጠርጣሪው ወደ መቐለ እንዲመጣ አድርጓል።
የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም የደሴ ህዝብ ላደረገው ትብብር ምስጋና አቅርቧል።
በከባድ የግድያ ተግባር የተጠረጠረው ግለሰብ አስመልክቶ በማህበራዊ የትስስር ገፆች የተሰራጨው አጭር ቪድዮ እንደሚያመለክተው ፥ ተጠርጣሪው ፍቅረኛውን በጬቤ ከገደላት በኋላ ተፀፅቶ ራሱ ለመግደል ሞኩሮ ሳይሳካለት መቅረቱ በአንደበቱ ይገልፃል።
የሟች ወጣት ሓበን የማነ አባት አቶ የማነ ንጉስ ልጃቸው በጭካኔ በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ በአጭር ጊዜ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ለተባበሩ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
የፎቶ ባለቤት ፦ የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን
@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ🚨
ቴግሬቶል የተሰኘ በአፍ የሚወሰድ ፈሳሽ (Oral Suspension) መድኃኒት የጨቅላ ህፃናት እንዳይጠቀሙት የኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን አሳስቧል፡፡
ቴግሬቶል የተሰኘ በአፍ የሚወሰድ ፈሳሽ (Oral Suspension) መድኃኒት ኖቫርቲስ ፋርማ ሽዌይዝ AG/ Novartis Pharma Schweiz AG በተባለ የገበያ ፍቃድ ባለው የመድኃኒት አምራች ፋብሪካ የሚመረት ነው።
ቴግሬቶል (ካርባማዜፔይን) 100 mg/5ml Oral Suspension (OS) የተሰኘው መድኃኒት አብዛኛውን ጊዜ አጠቃላይ ለሚጥልና ከፊል መንቀጥቀጥ/ management of generalized tonic clonic and partial seizures ለማከም የሚያገለግል ነው።
ይሁን እንጂ የተጠቀሰው መድኃኒት በውስጡ በሚይዘው ፕሮፓይሊን ግላይኮል (propylene glycol) የሚባል ንጥረ-ነገር መጠን ምክንያት ለጨቅላ ሕፃናት ማለትም ከ4 ሳምንታት በታች ለሆኑ ሕፃናት ወይም በሶስት ወራት የመወለድ ጊዜያቸው ሳይደርስ ለተወለዱ ሕፃናት ሊወስዱት እንደማይመከር ባለስልጣን መ/ቤቱ ገልጿል።
ተቋሙ ፥ በዚህ ምርት ውስጥ ከሚገኙት ተጨማሪ ንጥረ ነገሮች አንዱ የሆነው ፕሮፓይሊን ግላይኮል ለምግብ እና ትንባሆ ምርቶች እንዲሁም ለፋርማሲዩቲካል እና መዋቢያዎች በአጠቃላይ በአሜሪካ የምግብ እና የመድኃኒት አስተዳደር (FDA) ደህንነቱ የተጠበቀ እንደሆነ ይታወቃል ብሏል።
ይሁንና በዚህ ምርት ውስጥ ያለው መጠን በዚህ የማሳወቂያ መልዕከት ላይ ከተጠቀሱት ለጨቅላ ሕፃናት እና ጊዜያቸው ሳይደርስ ለተወለዱ ሕፃናት እስከ ሦስት ወር ድረስ ከደህንነት ገደብ በላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ነው ያለው።
ስለሆነም ይህንን መድኃኒት በጨቅላ ሕፃናት ጊዜያቸው ሳይደርስ ለተወለዱ ሕፃናት እስከ ሦስት ወር ድረስ መጠቀም ጉዳቱ ከጥቅሙ የሚያመዝን በመሆኑ ሁሉም የጤና ባለሙያዎች መድኃኒቱን ለተጠቀሱት የእድሜ ክልል ከማዘዝ እና ከማከፋፈል እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
ህብረተሰቡም መድኃኒቱን እንዳይጠቀም መልዕክት አስተለልፏል።
@tikvahethiopia
ቴግሬቶል የተሰኘ በአፍ የሚወሰድ ፈሳሽ (Oral Suspension) መድኃኒት የጨቅላ ህፃናት እንዳይጠቀሙት የኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን አሳስቧል፡፡
ቴግሬቶል የተሰኘ በአፍ የሚወሰድ ፈሳሽ (Oral Suspension) መድኃኒት ኖቫርቲስ ፋርማ ሽዌይዝ AG/ Novartis Pharma Schweiz AG በተባለ የገበያ ፍቃድ ባለው የመድኃኒት አምራች ፋብሪካ የሚመረት ነው።
ቴግሬቶል (ካርባማዜፔይን) 100 mg/5ml Oral Suspension (OS) የተሰኘው መድኃኒት አብዛኛውን ጊዜ አጠቃላይ ለሚጥልና ከፊል መንቀጥቀጥ/ management of generalized tonic clonic and partial seizures ለማከም የሚያገለግል ነው።
ይሁን እንጂ የተጠቀሰው መድኃኒት በውስጡ በሚይዘው ፕሮፓይሊን ግላይኮል (propylene glycol) የሚባል ንጥረ-ነገር መጠን ምክንያት ለጨቅላ ሕፃናት ማለትም ከ4 ሳምንታት በታች ለሆኑ ሕፃናት ወይም በሶስት ወራት የመወለድ ጊዜያቸው ሳይደርስ ለተወለዱ ሕፃናት ሊወስዱት እንደማይመከር ባለስልጣን መ/ቤቱ ገልጿል።
ተቋሙ ፥ በዚህ ምርት ውስጥ ከሚገኙት ተጨማሪ ንጥረ ነገሮች አንዱ የሆነው ፕሮፓይሊን ግላይኮል ለምግብ እና ትንባሆ ምርቶች እንዲሁም ለፋርማሲዩቲካል እና መዋቢያዎች በአጠቃላይ በአሜሪካ የምግብ እና የመድኃኒት አስተዳደር (FDA) ደህንነቱ የተጠበቀ እንደሆነ ይታወቃል ብሏል።
ይሁንና በዚህ ምርት ውስጥ ያለው መጠን በዚህ የማሳወቂያ መልዕከት ላይ ከተጠቀሱት ለጨቅላ ሕፃናት እና ጊዜያቸው ሳይደርስ ለተወለዱ ሕፃናት እስከ ሦስት ወር ድረስ ከደህንነት ገደብ በላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ነው ያለው።
ስለሆነም ይህንን መድኃኒት በጨቅላ ሕፃናት ጊዜያቸው ሳይደርስ ለተወለዱ ሕፃናት እስከ ሦስት ወር ድረስ መጠቀም ጉዳቱ ከጥቅሙ የሚያመዝን በመሆኑ ሁሉም የጤና ባለሙያዎች መድኃኒቱን ለተጠቀሱት የእድሜ ክልል ከማዘዝ እና ከማከፋፈል እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
ህብረተሰቡም መድኃኒቱን እንዳይጠቀም መልዕክት አስተለልፏል።
@tikvahethiopia
የኬንያው ፕሬዝዳንት ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ቦሌ ኤርፖርት ሲደርሱ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ናቸው የተቀበሏቸዋል።
ሩቶ በአዲስ አበባ ቆይታቸው የሁለትዮሽ ውይይት ያደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በተጨማሪም በ ' World Without Hunger ' ጉባኤ ላይ ይካፈላሉ።
የሀገራቸው ልጅ እና በሀገራቸው ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ወቅት ብርቱ ተፎካካሪያቸው የነበሩት ራይላ ኦዲንጋ ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ዕጩ ሆነው ይፋ በሚደረጉበት ስነስርዓት ላይ እንደሚገኙ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ናቸው።
ሩቶ አዲስ አበባ ከመምጣታቸው በፊት ደቡብ ሱዳን ጁባ ነበሩ። ጁባ ሄደው የነበረው በሀገሪቱ የሰላም ሂደት ላይ ከፕሬዜዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ለመነጋገር ነው።
ሩቶ ከጁባው ቆያታቸው በኃላ በይፋ የወጣ መረጃ ሳይኖር ምሽት ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል።
@tikvahethiopia
ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ቦሌ ኤርፖርት ሲደርሱ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ናቸው የተቀበሏቸዋል።
ሩቶ በአዲስ አበባ ቆይታቸው የሁለትዮሽ ውይይት ያደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በተጨማሪም በ ' World Without Hunger ' ጉባኤ ላይ ይካፈላሉ።
የሀገራቸው ልጅ እና በሀገራቸው ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ወቅት ብርቱ ተፎካካሪያቸው የነበሩት ራይላ ኦዲንጋ ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ዕጩ ሆነው ይፋ በሚደረጉበት ስነስርዓት ላይ እንደሚገኙ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ናቸው።
ሩቶ አዲስ አበባ ከመምጣታቸው በፊት ደቡብ ሱዳን ጁባ ነበሩ። ጁባ ሄደው የነበረው በሀገሪቱ የሰላም ሂደት ላይ ከፕሬዜዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ለመነጋገር ነው።
ሩቶ ከጁባው ቆያታቸው በኃላ በይፋ የወጣ መረጃ ሳይኖር ምሽት ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA
ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀዳሚ ስራቸው ዶክመንት የሌላቸውን / ሰነድ አልባ ስደተኞችን በብዛት ከሀገር ማስወጣት ነው ተብሏል።
የትራምፕ ዘመቻ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሌቪት እንደገለፁት ትራምፕ በፕሬዚዳንትነት ስልጣናቸው ከሚወስዷቸው የመጀመሪያ እርምጃዎች መካከል አንዱ ዶክመንት የሌላቸው / ሰነድ አልባ ስደተኞችን በብዛት ለማስወጣት የገቡትን ቃል መፈጸም ነው።
ሌቪት ፥ ትራምፕ በአሜሪካ ህዝብ ዘንድ አስደናቂ የተባለ ድል ማስመዝገባቸውን ገልጸው " ይህ ድል ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው የገቡትን ቃል እንዲፈጽሙ ' ትዕዛዝ ' እንዲሰጡ ያስችላቸዋል " ብለዋል።
ይህም ሰነድ አልባ ስደተኞችን በብዛት / በገፍ ወደ መጡበት ሀገር መመለስ (ማስ ዲፖርቴሽን) እንደሆነ ጠቁመዋል።
አንዳንድ ሚዲያዎች ይህ ሰነድ አልባዎችን በብዛት ከአሜሪካ የማስወጣቱ /ማስ ዲፖርቴሽን/ ተግባር የትራምፕ የመጀመሪያው ቀን ስራ ይሆናል ብለዋል።
ትራምፕ በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት ሰነድ የሌላቸውን ሰዎችን በሚመለከት " ከአሜሪካ ምድር ጓዛቸውን አስይዘን ወደ መጡበት እንልካቸዋለን " ሲሉ ቃል ገብተው ነበር።
አንዳንድ ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙት ትራምፕ በስልጣን ዘመናቸው ቢያንስ ቢያንስ ከ15 እስከ 20 ሚሊዮን ሰነድ የሌላቸው ስደተኞችን ከአሜሪካ ለማስወጣት እቅድ አላቸው።
#TikvahEthiopia
#USA #massdeportation
@tikvahethiopia
ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀዳሚ ስራቸው ዶክመንት የሌላቸውን / ሰነድ አልባ ስደተኞችን በብዛት ከሀገር ማስወጣት ነው ተብሏል።
የትራምፕ ዘመቻ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሌቪት እንደገለፁት ትራምፕ በፕሬዚዳንትነት ስልጣናቸው ከሚወስዷቸው የመጀመሪያ እርምጃዎች መካከል አንዱ ዶክመንት የሌላቸው / ሰነድ አልባ ስደተኞችን በብዛት ለማስወጣት የገቡትን ቃል መፈጸም ነው።
ሌቪት ፥ ትራምፕ በአሜሪካ ህዝብ ዘንድ አስደናቂ የተባለ ድል ማስመዝገባቸውን ገልጸው " ይህ ድል ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው የገቡትን ቃል እንዲፈጽሙ ' ትዕዛዝ ' እንዲሰጡ ያስችላቸዋል " ብለዋል።
ይህም ሰነድ አልባ ስደተኞችን በብዛት / በገፍ ወደ መጡበት ሀገር መመለስ (ማስ ዲፖርቴሽን) እንደሆነ ጠቁመዋል።
አንዳንድ ሚዲያዎች ይህ ሰነድ አልባዎችን በብዛት ከአሜሪካ የማስወጣቱ /ማስ ዲፖርቴሽን/ ተግባር የትራምፕ የመጀመሪያው ቀን ስራ ይሆናል ብለዋል።
ትራምፕ በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት ሰነድ የሌላቸውን ሰዎችን በሚመለከት " ከአሜሪካ ምድር ጓዛቸውን አስይዘን ወደ መጡበት እንልካቸዋለን " ሲሉ ቃል ገብተው ነበር።
አንዳንድ ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙት ትራምፕ በስልጣን ዘመናቸው ቢያንስ ቢያንስ ከ15 እስከ 20 ሚሊዮን ሰነድ የሌላቸው ስደተኞችን ከአሜሪካ ለማስወጣት እቅድ አላቸው።
#TikvahEthiopia
#USA #massdeportation
@tikvahethiopia
ነጻ ትምህርት ☑️
#LG_KOICA_Hope
LG-KOICA Hope የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቲቪቲ መግቢያ መስፈርቱን ለሚያሟሉ ተማሪዎች በICT እና Electronics የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን #በነጻ ማስተማር ይፈልጋል።
ኮሌጁ በዚህ ዙር እስከ 150 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የተዘጋጀ ሲሆን የሀገር ዉስጥና የዉጭ ሀገር የሥራ ዕድል አማራጮችም አካቷል።
ከዚህ በተጨማሪ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸውና መስፈርቱን ለሚያማሉ የተመረጡ ተማሪዎች የምግብ፣ የትራንስፖርት እና ሌሎች ወጪዎችን የሚሸፍን ይሆናል።
የማመልከቻ ጊዜና ቦታ : ከጥቅምት 11 - ህዳር 06 2017 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡00 - 11፡00 ሰዓት ሰሚት ኮንዶሚኒየም 3ኛ በር
ለተጨማሪ መረጃ - 011-6-67-75-64 011-6-66-18-29
#LG_KOICA_Hope
LG-KOICA Hope የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቲቪቲ መግቢያ መስፈርቱን ለሚያሟሉ ተማሪዎች በICT እና Electronics የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን #በነጻ ማስተማር ይፈልጋል።
ኮሌጁ በዚህ ዙር እስከ 150 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የተዘጋጀ ሲሆን የሀገር ዉስጥና የዉጭ ሀገር የሥራ ዕድል አማራጮችም አካቷል።
ከዚህ በተጨማሪ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸውና መስፈርቱን ለሚያማሉ የተመረጡ ተማሪዎች የምግብ፣ የትራንስፖርት እና ሌሎች ወጪዎችን የሚሸፍን ይሆናል።
የማመልከቻ ጊዜና ቦታ : ከጥቅምት 11 - ህዳር 06 2017 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡00 - 11፡00 ሰዓት ሰሚት ኮንዶሚኒየም 3ኛ በር
ለተጨማሪ መረጃ - 011-6-67-75-64 011-6-66-18-29
ሞኤንኮ ፥ በኢትዮጵያ የቢዋይዲ (BYD) ኤሌክትሪክ እና ሃይብሪድ ተሸከርካሪዎች ይፋዊ አከፋፋይ መሆኑን ገለጸ።
በኢንችኬፕ ኩባንያ ስር የሚተዳደረው ሞኤንኮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መረጃ ፥ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቴክኖሎጂ ዓለም አቀፍ መሪ ከሆነው ቢዋይዲ (BYD) ጋር በኢትዮጵያ የቢዋይዲ የኤሌክትሪክ እና ሃይብሪድ ተሸከርካሪዎች ዋና አከፋፋይ ለመሆን የሚያስችለውን ስምምነት መፈራረሙን ገልጿክ።
በስምምነቱ ሞኤንኮ በኢትዮጵያ በዋናነት የቢዋይዲ (BYD) ተሽከርካሪዎችን የሚያከፋፍል ይሆናል።
ሞኤንኮ ከታህሳስ 2017 ጀምሮ ለአካባቢ አየር ተሰማሚ እና በቴክኖሎጂ የተራቀቁ የቢዋይዲ ተሸከርካሪዎችን ከአስተማማኝ ጥገና ፣ መለዋወጫ እና ዋስትና ጋር እንደሚያቀርብም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
" ይህ ስምምነት ዘላቂና አዳዲስ ቴክኖሎጅዎችን የማስተዋወቅ እና ለማቅረብ ያለንን ቁርጠኝነት ያሳያል ' ብሏል።
የኢንችኬፕ አፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፍራንሲስ አግቦንላሆር ፥ " ይህ አጋርነት ለኢትዮጵያ የተሸከርካሪ ኢንዱስትሪ ወሳኝ አስተዋጽዖ ያበረክታል ፤ ይህም የአዳዲስ ፈጠራ መስፋፋት እና ታዳሽ ሀይልን በመጠቀም ዘላቂ የሆነ የትራንስፖርት አገልግሎትን ያፋጥናል " ብለዋል።
@tikvahethiopia
በኢንችኬፕ ኩባንያ ስር የሚተዳደረው ሞኤንኮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መረጃ ፥ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቴክኖሎጂ ዓለም አቀፍ መሪ ከሆነው ቢዋይዲ (BYD) ጋር በኢትዮጵያ የቢዋይዲ የኤሌክትሪክ እና ሃይብሪድ ተሸከርካሪዎች ዋና አከፋፋይ ለመሆን የሚያስችለውን ስምምነት መፈራረሙን ገልጿክ።
በስምምነቱ ሞኤንኮ በኢትዮጵያ በዋናነት የቢዋይዲ (BYD) ተሽከርካሪዎችን የሚያከፋፍል ይሆናል።
ሞኤንኮ ከታህሳስ 2017 ጀምሮ ለአካባቢ አየር ተሰማሚ እና በቴክኖሎጂ የተራቀቁ የቢዋይዲ ተሸከርካሪዎችን ከአስተማማኝ ጥገና ፣ መለዋወጫ እና ዋስትና ጋር እንደሚያቀርብም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
" ይህ ስምምነት ዘላቂና አዳዲስ ቴክኖሎጅዎችን የማስተዋወቅ እና ለማቅረብ ያለንን ቁርጠኝነት ያሳያል ' ብሏል።
የኢንችኬፕ አፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፍራንሲስ አግቦንላሆር ፥ " ይህ አጋርነት ለኢትዮጵያ የተሸከርካሪ ኢንዱስትሪ ወሳኝ አስተዋጽዖ ያበረክታል ፤ ይህም የአዳዲስ ፈጠራ መስፋፋት እና ታዳሽ ሀይልን በመጠቀም ዘላቂ የሆነ የትራንስፖርት አገልግሎትን ያፋጥናል " ብለዋል።
@tikvahethiopia