TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ ህንጻ ቤቶች ባለቤቶች ኃ/የተ/ህብረት ስራ ማህበር የነዋሪዎች ይዞታ መሆኑ እየታወቀ ለሶስተኛ ወገን ተላልፏል ያለው ይዞታ ጉዳይ ፍርድ ቤት ድረስ የደረሰ ነው።
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው ጉዳዩን የተከታተለው።
ከሳሽ ሆኖ የቀረበው ደግሞ ታሌሮ ኃ/የተ/የግል ማህበር ነው። ክስ ያቀረበው በሰንጋ ተራ የጋራ ህንጻ ነዋሪዎች ኃ/የተ/ የህብረት ስራ ማህበር ላይ ነው።
ከሳሽ ያቀረበው ክስ ፥ ተከሳሾች በኃይል ገብተው የተሰጠኝን ከ600 ካ.ሜ በላይ የሆነ ቦታ ለመንጠቅ የብረት አጥር በማጠር ሁከትም ፈጥረዋል የሚል ነው።
" በሁከቱ ምክንያት ለደረሰብኝ ጉዳትና ኪሳራ ከነወለዱ ተከሳሾች እንዲተኩ ይወስንልኝ " የሚል ነው።
ከዚህ ጋር የሰነድ ማስረጃ አቅርቧል።
የሰንጋ ተራ የጋራ ህንጻ ነዋሪዎች ኃ/የተ/ የህብረት ስራ ማህበር በበኩሉ ፦
- ከሳሽ የሁከት ይወገድልኝ ክስ ያቀረበበት ይዞታ በእጃ አደርጎ ወይም በይዞታው ስር አድርጎ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ ሲያዝበት የነበረ ይዞታ አይደለም።
- ከሳሽ ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ይዞታ ይዞት አያውቅም።
- ከሳሽ ባያያዙት ካርታ ላይ ከተረጋገጠው ይዞታ ውጭ የሆነ ይዞታ ነው። ይዞታው በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በክ/ከተማው መሬት ልማት ማኔጅመንት በኩል ካሳ ተከፍሎብት የሰንጋ ተራ የጋራ ህንፃ ነዋሪዎች ማህበር ይዞታነት የተካለለ ነው፡፡
ስለሆነም ከሳሽ በእጁ በማይገኝ ይዞታ የራሱ ባልሆነና በይዞታው ስር ባልነበረ ይዞታ ላይ ያቀረበው ክስ ተቀባይነት እንደሌለው ገልጿል።
ሌላው ከሳሽ የፕላን ስምምነት የተሰጠው አሁን ክርክር በተነሳበት ይዞታ ላይ ሳይሆን አስቀድሞ በነበረው ይዞታ ላይ እንደሆነ አመልክተዋል።
በከሳሽ ይዞታ በማስረጃነት ከተያያዘው ካርታ ላይ መረዳት እንደሚቻለው ባለ 7 ፎቅ ህንጻ የሰራው በ1685 ካ/ሜ ይዞታ ላይ ነው እንጂ በክሱ ላይ እንደተገለጸው በካርታ ከተያያዘው ይዞታ ውጭ ባለው 600 ካ/ሜ በላይ በሆነው ይዞታ ላይ አይደለም ብለዋል።
ክሳሽ የሁከት ይወገድ ክስ ያቀረበው በህጋዊ መንገድ ከያዘው ይዞታ ውጪ በሆነው በ600 ካ/ሜ ይዞታ ላይ ነው ይህም በእጁ አድርጎ የማያዝበት በመሆኑ ክሱ ተገቢነት የለውም ብለው ተከራክረዋል።
የሰንጋ ተራ የጋራ ህንጻ ነዋሪዎች ኃ/የተ/ የህብረት ስራ ማህበር ፦
° በከሳሽ ይዞታ ወስጥ በመግባት የሰራነው አጥር የለም፤
° ይዞታው የከሽ ስለመሆኑም የሚያረጋግጥ ምንም አይነት ማስረጃም የለም።
° አጥር የሰራነውም በይዞታችን ስር አድርገን እየተጠቀምንበት ባለው ይዞታ እና ስልጣን ካው አካል የተሰጠንን የግንባታ ቦታ ፕላን እና የአጥር ግንባታ ፈቃድ በመያዝ በህጋዊ መንገድ ነው።
° በከሳሽ በኩል የቀረቡት ሰነዶች ለክርክሩ መነሻ በሆነው ይዞታ በ600 ካ.ሜ በላይ የሆነው ይዞታ ላይ ባለይዞታነቱን የሚያስረዱ ማስረጃዎች አይደሉም።
° ' ማስፋፊያ ጠይቄ ተስጥቶኛል ' ካለም አግባብ ባለው አካል የተሰጠው ለመሆኑ ሊያረጋግጥ የሚችል ማስረጃ ማቅረብ ሲገባው አላቀረበም።
ክሱ ውድቅ ይሁን ፤ በቂ ወጪና ኪሳራ እንዲከፈለን ሲሉ ጠይቀዋል።
የልደታ ክ/ከተማ መሬት ልማት ማኔጅመንት ጽ/ቤት ጣልታ ገብቶ እንዲከራከር ይታዘዝልን በማለትም ለፍርድ ቤት አመልክተው ነበር።
ማህበሩ በማስረጃነት የሰነድ ማስረጃ እና የሰው ምስክር አቅርቧል።
ፍርድቤቱ የልደታ ክ/ከተማ መሬት ልማት ማኔጅመንት ጽ/ቤት ጣልቃ ገብቶ እንዲከራክር በ29/10/13 ዓ.ም ላይ ትእዛዝ የሰጠ ቢሆንም ጣልቃገብ የሰጡት መልስ ባለመኖሩ መልስ የመስጠት መብታቸው ታልፎ ክስ በሌሉበት ተሰምቷል።
ፍርድ ቤት በሁለቱም በኩል የቀረቡ ዶክመንቶችን ከተመላከተ በኃላ ጉዳዩ በገለልተኛ አካል መጣራት አለበት በማለት የአዲስ አበባ የመሬት ይዞታ አስተዳደር ፅ/ቤት ከልደታ ክ/ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ፅ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን ግራ ቀኙ በተገኙበት ይዞታው በከሳሽ ስራ መሆን አለመሆኑን በማጣራት ምላሽ እንዲልክ አዟል።
በኃላም የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ፥
" የቅየሳ መሳሪያ ይዘን በቦታው ላይ በአካል ተገኝተን ልኬት ልንወስድ ዝግጅት እያደረግን እያለ ከሳሽ ጥያቄያቸው በይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በያዙት 1685 ካ.ሜ ይዞታቸው ላይ ሳይሆን በካርታ ከያዙት ውጭ ተጨማሪ የቦታ ማስፋፋት ጥያቄ መሆኑን በቃል ያስረዱን ሲሆን በዚህም ልኬት ሳናከናውን ተመልሰናል። ጥያቄያቸው አስተዳደራዊ ውሳኔ የሚሻ በመሆኑ ለሚመለከተው አካል አመልክተናል። " የሚል ምላሽ ነው የሰጠው።
ፍ/ቤቱም በምላሽ የቀረበው የስነድ ማስረጃ ለክርክሩ መነሻ የሆነው ይዞታ ከሳሽ በይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በያዙት 1685 ካ.ሜ ይዞታቸው ላይ ሳይሆን በካርታ ከያዙት ውጭ ተጨማሪ የቦታ ማስፋፋት ጥያቄ መሆኑን እና አስተዳደራዊ ውሳኔ የሚሻ መሆኑን ያሳያል ብሏል።
በዚህም ምላሽ የሚያስረዳው ለክርክሩ መነሻ የሆነው ይዞታ የከሳሽ ይዞታ አለመሆኑን እንደሆነ በግልጽ አስቀምጧል።
ከሳሽ ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ይዞታ በእጁ አድርጎ በእዉነት እያዘዘበት መሆኑ እና ይዞታዉን በህግ አግባብ ያገኘዉ መሆኑ በማስረጃ ያልተረጋገጠ በመሆኑ የከሳሽን ክስ ፍ/ቤቱ አልተቀበለውም።
ውድቅም በማድረግ ወስኗል፡፡
ይህ ውሳኔ በተሰጠበት ሁኔታ ቆይቶ እና አረሳስቶ በሚመስል ሁኔታ ቦታው በፖሊስ ኃይል ታግዞ ታጥሯል።
የሰንጋ ተራ የጋራ ህንጻ ነዋሪዎች ኃ/የተ/ የህብረት ስራ ማህበር የማጠር ተግባሩና እየተፈጸመ ያለው ከህግ ውጭ የሚደረግ ድርጊት ይቁም በሚል ይመለከታቸው ያላቸው ቢሮችን ለማነጋገር ቢጥርም ሰሚ አላገኘም።
አሁንም ቦታው ታጥሮ ይገኛል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰው የፍርድ ቤት ውሳኔና ሌሎች ዶክመንቶች ከላይ ተያይዘዋል)
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በንጉስ ማልት ሁልጊዜ ደስስስስስስስስስስስስስስስስስታ! ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://yangx.top/Negus_Malt
#ከአልኮልነፃ #ደስደስበንጉስ #የጣዕምልኬት_የደስታስሜት #ንጉስማልት
#ከአልኮልነፃ #ደስደስበንጉስ #የጣዕምልኬት_የደስታስሜት #ንጉስማልት
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " በድጋሚ ቢሮ ሂደን ጠየቅናቸው ግን የተስፋ ቃል ከመስጠት ውጪ መሬት ላይ ምንም ተጨባጭ ነገር አይሰሩም " - ቤት ገዢዎች ከ600 በላይ የሚሆኑ የአያት ግሪን ኖህ ሪልስቴት ቤት ገዢዎች፣ በውላቸው መሠረት ድርጅቱ የመብራት፣ የውሃ፣ የታንከር መሠረተ ልማቶችን ባለሟማላቱ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከፍለው ከገዙት ቤታቸው መግባት እንዳልቻሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡…
#AddisAbaba
“ ከቆጣሪ ጋ የመገጣጠም ሥራው ግፋ ቢል ከዚህ በኋላ አንድ ወር ቢፈጅ ነው ” - ኖህ ሪልስቴት
ኖህ ሪልስቴት ሰሚነት አካባቢ “ ኤርፓርት ድራይቭ ” በተሰኘ ሳይቱ የገነባቸውን ሱቆችና ቤቶች ዛሬ ለገዢዎቹ ማስረከቡን ገልጿል።
የድርጅቱ የሕግ ክፍል ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ደስታ፣ “ ዛሬ ሰሚት አካባቢ በሚገኘው 'ኤርፓርት ድራይቭ' የተሰኘ ሳይት ቤቶችን ስላጠናቀቅን የምረቃት ሥነ ስርዓት አካሂደናል ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በዚህ ፕሮጀክት በአጠቃላይ ሱቅን ጨምሮ ወደ 750 ቤቶች እንዳስረከቡ ገልጸዋል።
በመርሃ ግብሩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ ባደረጉት ንግግር፣ “ በዛሬው እለት እያስመረቅናቸው ያሉ 750 ቤቶቾና 43 ሱቆች ከተማችንን የሚመጥኑ ሆነው ለምተዋል ” ብለዋል።
እስከዛሬ ባስረክባችኋቸው ቤቶች የመሠረተ ልማት ቅሬታ ይነሳል (ለምሳሌ አያት ግሪን ሰይት ተጠቃሽ ነው) በአሁኑ ሳይትስ ተመሳሳይ ቅሬታ እንዳይኖር መሠረተ ልማቱ ተሟልቷል ? ሲል ቲክቫህ ለአቶ ዮሴፍ ጥያቄ አቅርቧል።
ምን አሉ ?
“ ከአያት ግሪን ፓርክ ልምድ ወስደናል። ሁሉም ፕሮጀክቶቻችን ላይ መዘግዬት የተፈጠረው ከኮቪድ ጀምሮ ባለው ችግር ነው። ነገር ግን ከዚያ በኋላ ያለውን ነገር እንዴት እንፍታ ? በሚል ግሪን ፓርኩ ላይ ልምድ ወስደናል።
ከወሰድነው ልምድ አንጻር ለዚህኛው ፕሬጀክት አስፈላጊው ጀነሬተር ገብቷል ፤ ትራንስፎርመር ገብቷል። የመብራት ፓሎችም ተተክለዋል። ከህንጻዎቹ ጋር የማገናኘት ሥራ ብቻ ነው የሚቀረን።
ውሃን በተመለከተ ፤ ቦታው ላይ የከርሰ ምድር ውሃ ቆፍረን ለነዋሪው አዘጋጅተናል። ስለዚህ የውሃ ችግር አይኖርም።
መብራትን በተመለከተም ከመንግስት የፓወር ችግር የለም። በኛ በኩል የሚያስፈልገውን ትራንስፎርመር፣ ጀነሬተር፣ ሌሎቹን ኢንፍራስትራክቸሮች በሙሉ አዘጋጅተናል። ስለዚህ እሱን የማገናኘት ሥራ እንሰራለን ” ብለዋል።
በአጠቃላይ በገዢዎች የሚነሱ የመሠረተ ልማት ቅሬታዎችን ለመቅረፍ ኖህ ምን እየሰራ ነው ? ዛሬ ያስረከባችኋቸው ቤቶች መሠረተ ልማቶች መቼ ይጠናቀቃሉ ? የሚጠናቀቁበትን ጊዜስ ከገዥዎቹ ጋር ተነጋግራችኋል ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ማብራሪያቸው ምንድን ነው?
“ ትልቅ እንቅፋት የነበረው የትራንስፎርመር ችግር ነው። ከመንግስት (ከኤሌፓ) ነው የሚገዛ የነበረው። ከዚያ ብቻ በሚገዛበት ጊዜ ወረፋ እንጠብቅ ነበር። አሁን ግን ተፈቅዶልናል ከገበያ እንድንገዛ። ያ እንቅፋት የለም።
ውሃን በተመለከተ ፤ የከተማውን የውሃ እጥረት ስለምናውቅ ትኩረት ሰጥተን የምንሰራው በከርሰ ምድር ላይ ነው። ውሃም ቶሎ የሚገኝበትን መንገድ እንሰራለን።
ህንጻዎቹ ያልቃሉ ከዛ የመሠረተ ልማት ጥያቄ አለ። ይሄ ጥያቄ የኛ ብቻ አይደለም። ዋናው ሆኖ እያለ በመንግስት ፕሮጀክቶች ላይም የውሃ እጥረት አለ። ለመቅረፍ እየሰራን ነው።
መሠረተ ልማቱ በምን ያክል ጊዜ ውስጥ ያልቃል ? ሁሉም እቃ ቀርቧል። የቀረው ነገር መብራት በሚሰራው ኮንትራክተር መገጣጠም ነው። ከቆጣሪ ጋ የመገጣጠም ሥራው ግፋ ቢል ከዚህ በኋላ አንድ ወር ቢፈጅ ነው ” ሲሉ መልሰዋል።
የአያት ግሪን ፓርክ የገዢዎች የመሠረተ ልማት ከምን እንደደረሰ ጠይቀናቸው በሰጡን ቃል አቶ ዮሴፍ ፤ “ ተመሳሳይ እምጃዎችን ወስደን የመብራት አገልግሎቱ አሁን በዬቤቱ ቆጣሪ የማስገባት ሥራ ተጀምሯል” ነው ያሉት።
“ ስለዚህ እዛም ያለውን ችግር አቃለናል። ውሃን በተመለከተ ለውሃ የሚያስፉፍገው የታንከር ማስቀመጫ ቦታ ችግር ነበረብን እሱን ፈትተን ውሃውን ግቢ ውስጥ አስቀምጠን ወደ ፊት እየተራመድን ነው ያለነው ” ሲሉ አክለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ ከቆጣሪ ጋ የመገጣጠም ሥራው ግፋ ቢል ከዚህ በኋላ አንድ ወር ቢፈጅ ነው ” - ኖህ ሪልስቴት
ኖህ ሪልስቴት ሰሚነት አካባቢ “ ኤርፓርት ድራይቭ ” በተሰኘ ሳይቱ የገነባቸውን ሱቆችና ቤቶች ዛሬ ለገዢዎቹ ማስረከቡን ገልጿል።
የድርጅቱ የሕግ ክፍል ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ደስታ፣ “ ዛሬ ሰሚት አካባቢ በሚገኘው 'ኤርፓርት ድራይቭ' የተሰኘ ሳይት ቤቶችን ስላጠናቀቅን የምረቃት ሥነ ስርዓት አካሂደናል ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በዚህ ፕሮጀክት በአጠቃላይ ሱቅን ጨምሮ ወደ 750 ቤቶች እንዳስረከቡ ገልጸዋል።
በመርሃ ግብሩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ ባደረጉት ንግግር፣ “ በዛሬው እለት እያስመረቅናቸው ያሉ 750 ቤቶቾና 43 ሱቆች ከተማችንን የሚመጥኑ ሆነው ለምተዋል ” ብለዋል።
እስከዛሬ ባስረክባችኋቸው ቤቶች የመሠረተ ልማት ቅሬታ ይነሳል (ለምሳሌ አያት ግሪን ሰይት ተጠቃሽ ነው) በአሁኑ ሳይትስ ተመሳሳይ ቅሬታ እንዳይኖር መሠረተ ልማቱ ተሟልቷል ? ሲል ቲክቫህ ለአቶ ዮሴፍ ጥያቄ አቅርቧል።
ምን አሉ ?
“ ከአያት ግሪን ፓርክ ልምድ ወስደናል። ሁሉም ፕሮጀክቶቻችን ላይ መዘግዬት የተፈጠረው ከኮቪድ ጀምሮ ባለው ችግር ነው። ነገር ግን ከዚያ በኋላ ያለውን ነገር እንዴት እንፍታ ? በሚል ግሪን ፓርኩ ላይ ልምድ ወስደናል።
ከወሰድነው ልምድ አንጻር ለዚህኛው ፕሬጀክት አስፈላጊው ጀነሬተር ገብቷል ፤ ትራንስፎርመር ገብቷል። የመብራት ፓሎችም ተተክለዋል። ከህንጻዎቹ ጋር የማገናኘት ሥራ ብቻ ነው የሚቀረን።
ውሃን በተመለከተ ፤ ቦታው ላይ የከርሰ ምድር ውሃ ቆፍረን ለነዋሪው አዘጋጅተናል። ስለዚህ የውሃ ችግር አይኖርም።
መብራትን በተመለከተም ከመንግስት የፓወር ችግር የለም። በኛ በኩል የሚያስፈልገውን ትራንስፎርመር፣ ጀነሬተር፣ ሌሎቹን ኢንፍራስትራክቸሮች በሙሉ አዘጋጅተናል። ስለዚህ እሱን የማገናኘት ሥራ እንሰራለን ” ብለዋል።
በአጠቃላይ በገዢዎች የሚነሱ የመሠረተ ልማት ቅሬታዎችን ለመቅረፍ ኖህ ምን እየሰራ ነው ? ዛሬ ያስረከባችኋቸው ቤቶች መሠረተ ልማቶች መቼ ይጠናቀቃሉ ? የሚጠናቀቁበትን ጊዜስ ከገዥዎቹ ጋር ተነጋግራችኋል ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ማብራሪያቸው ምንድን ነው?
“ ትልቅ እንቅፋት የነበረው የትራንስፎርመር ችግር ነው። ከመንግስት (ከኤሌፓ) ነው የሚገዛ የነበረው። ከዚያ ብቻ በሚገዛበት ጊዜ ወረፋ እንጠብቅ ነበር። አሁን ግን ተፈቅዶልናል ከገበያ እንድንገዛ። ያ እንቅፋት የለም።
ውሃን በተመለከተ ፤ የከተማውን የውሃ እጥረት ስለምናውቅ ትኩረት ሰጥተን የምንሰራው በከርሰ ምድር ላይ ነው። ውሃም ቶሎ የሚገኝበትን መንገድ እንሰራለን።
ህንጻዎቹ ያልቃሉ ከዛ የመሠረተ ልማት ጥያቄ አለ። ይሄ ጥያቄ የኛ ብቻ አይደለም። ዋናው ሆኖ እያለ በመንግስት ፕሮጀክቶች ላይም የውሃ እጥረት አለ። ለመቅረፍ እየሰራን ነው።
መሠረተ ልማቱ በምን ያክል ጊዜ ውስጥ ያልቃል ? ሁሉም እቃ ቀርቧል። የቀረው ነገር መብራት በሚሰራው ኮንትራክተር መገጣጠም ነው። ከቆጣሪ ጋ የመገጣጠም ሥራው ግፋ ቢል ከዚህ በኋላ አንድ ወር ቢፈጅ ነው ” ሲሉ መልሰዋል።
የአያት ግሪን ፓርክ የገዢዎች የመሠረተ ልማት ከምን እንደደረሰ ጠይቀናቸው በሰጡን ቃል አቶ ዮሴፍ ፤ “ ተመሳሳይ እምጃዎችን ወስደን የመብራት አገልግሎቱ አሁን በዬቤቱ ቆጣሪ የማስገባት ሥራ ተጀምሯል” ነው ያሉት።
“ ስለዚህ እዛም ያለውን ችግር አቃለናል። ውሃን በተመለከተ ለውሃ የሚያስፉፍገው የታንከር ማስቀመጫ ቦታ ችግር ነበረብን እሱን ፈትተን ውሃውን ግቢ ውስጥ አስቀምጠን ወደ ፊት እየተራመድን ነው ያለነው ” ሲሉ አክለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
መቐለ ? የመቐለ ከተማ ም/ቤት ዛሬ አካሂዶታል በተባለ ሰብሰባ ፥ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመራው ህወሓት ውስጥ የስራ አስፈፃሚ አባል ሆነው የተመረጡትን ዶ/ር ረዳኢ በርሀ የከተማዋ ከንቲባ ሆኖው እንዲያገለግሉ በ1 የተቃውሞ በ5 ድምፀ ተአቅቦ እንደመረጣቸው ተሰምቷል። የከተማዋ ም/ቤት ከተማዋ በከንቲባነት ሲመሩ የቆዩት በዶ/ር ደብረፅዮን በሚመራው ህወሓት የማእከላዊ ኮሚቴ አባል የሆኑትን አቶ…
#መቐለ
" የጊዚያዊ አስተዳደሩን የሚፃረር አቋም በመያዝ በጊዚያዊ አስተዳደሩ ስር ያለን መዋቅር መምራት አትችሉም " - አቶ ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አዲሱን የመቐለ ከንቲባ ከስራ አገዱ።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ " ለዶ/ር ረዳኢ በርሀ " በማለት ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ ፤ አዲሱ የመቐለ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ረዳኢ በርሀ ህጋዊ ያልሆነ ተግባራቸውን እንዲያቆሙ አሳስበዋል።
" የመቐለ ከተማ ምክር ቤት መጠቀምያ በማድረግ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ የሚፃረር ተግባር መፈፀም አይቻልም " ያለው የፕሬዜዳንቱ ደብዳቤ የአዲሱ ከንቲባ ሹመት በጊዚያዊ አስተዳደሩ ተቀባይነት እንደሌለው አስረድቷል።
አቶ ጌታቸው " የጊዚያዊ አስተዳደሩን የሚፃረር አቋም በመያዝ በጊዚያዊ አስተዳደሩ ስር ያለን መዋቅር መምራት አትችሉም ፤ ጊዚያዊ አስተዳደሩም ከእርስዎ ጋር መሰራት አይችልም " ብለዋል።
በመቐለ ከተማ የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች " ህጋዊ አይደሉም " የተባሉት ከንቲባ የሚሰጡዋቸው አመራሮች እና ትእዛዞች ተቀብለው እንዳይፈፅሙ ፕሬዜዳንቱ አስጠንቅቀዋል።
አዲሱ የመቐለ ከንቲባ ዶ/ር ረዳኢ በርሀ ፤ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመሩት ህወሓት የስራ አስፈፃሚ ሆነው የተመረጡ ናቸው።
በያዝነው ወር መጀመሪያ ሳምንት ደግሞ የቀድሞውን ከንቲባ አቶ ይትባረክ አምሃ በመተካት ከንቲባ ሆነው እንዲመሩ በመቐለ ከተማ ምክር ቤት መሾማቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መዘገቡ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" የጊዚያዊ አስተዳደሩን የሚፃረር አቋም በመያዝ በጊዚያዊ አስተዳደሩ ስር ያለን መዋቅር መምራት አትችሉም " - አቶ ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አዲሱን የመቐለ ከንቲባ ከስራ አገዱ።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ " ለዶ/ር ረዳኢ በርሀ " በማለት ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ ፤ አዲሱ የመቐለ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ረዳኢ በርሀ ህጋዊ ያልሆነ ተግባራቸውን እንዲያቆሙ አሳስበዋል።
" የመቐለ ከተማ ምክር ቤት መጠቀምያ በማድረግ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ የሚፃረር ተግባር መፈፀም አይቻልም " ያለው የፕሬዜዳንቱ ደብዳቤ የአዲሱ ከንቲባ ሹመት በጊዚያዊ አስተዳደሩ ተቀባይነት እንደሌለው አስረድቷል።
አቶ ጌታቸው " የጊዚያዊ አስተዳደሩን የሚፃረር አቋም በመያዝ በጊዚያዊ አስተዳደሩ ስር ያለን መዋቅር መምራት አትችሉም ፤ ጊዚያዊ አስተዳደሩም ከእርስዎ ጋር መሰራት አይችልም " ብለዋል።
በመቐለ ከተማ የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች " ህጋዊ አይደሉም " የተባሉት ከንቲባ የሚሰጡዋቸው አመራሮች እና ትእዛዞች ተቀብለው እንዳይፈፅሙ ፕሬዜዳንቱ አስጠንቅቀዋል።
አዲሱ የመቐለ ከንቲባ ዶ/ር ረዳኢ በርሀ ፤ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመሩት ህወሓት የስራ አስፈፃሚ ሆነው የተመረጡ ናቸው።
በያዝነው ወር መጀመሪያ ሳምንት ደግሞ የቀድሞውን ከንቲባ አቶ ይትባረክ አምሃ በመተካት ከንቲባ ሆነው እንዲመሩ በመቐለ ከተማ ምክር ቤት መሾማቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መዘገቡ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" በሰው ላይ ጨዋታ ነው እንዴ የያዙት ? " - ነዋሪዎች
በአዲስ አበባ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ' ጨፌ ሜዳ ' ነዋሪዎች በመብራት መቆራረጥ እንዲሁም ጠፍቶ እስከወዲያኛው መቅረት እጅግ በጣም ተማረዋል።
በተደጋጋሚ ቅሬታ ቢያቀርቡም መፍትሄ አላገኙም።
ነዋሪዎች ለኤ ኤም ኤን በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
➡️ ከአምትና ከሁለት ዓመት በፊት እንዲሁ ይጠፋል ይቃጠላል መጥተው ይቀይራሉ ፤ የሚቀይሩት ኃይሉ የተመጣጠነ አይደለም ወዲያ ይጠፋል።
➡️ ሰው ላይ ጨዋታ ነው እንዴ የያዙት ? ለምንድነው እንዲህ የሚደረገው ? ሰራን ብለው እንደሄዱ ወዲያው ይጠፋል። እነሱ ደመወዛቸውን እየበሉ ነው ፤ እንጀራ ጋግሮ መብያ ይጠፋል እንዴ ?
➡️ ከ30 እና 40 ዓመት በፊት ስንገለገልበት በነበረበት መጠን እንድንገለገል እየተደረገ ሰው ጭለማ ውስጥ ነው ያለው።
➡️ ፍሪጅ ተበላሽቷል አይሰራም ፤ ቴሌቪዥን ተበላሽቷል ለሰራተኛ ብር እየሰጠን ነው የምናሰራው። ለፍተን ደክመን አጠራቅመን በእርጅና ጾም እንፈታበታለን ያለው ነገር ሁላ እየተበላሸብን ነው። ባለፈው ብዙ ነገር ተበላሽቶ ጥለናል።
➡️ ፍሪጅ የሚፈልግ መድሃኒት አለ ያ ሁሉ ከንቱ ቀረ ሰው ይሙት እያሉ ነው ?
➡️ ህጻናት ፣ ልጆች ፣ አቅመ ደካማ አለ ስንት ጣጣ ነው ያለው። ቤት ውስጥ ብዙ ነገር ነው ያለው። ቢደወልላቸው አይመጡ ፤ መጣን መጣን እያሉ ያሾፋሉ። ሲመጡ ደግሞ ምኑን ነክተውት እንደሚሄዱ አይታወቅም ኬላ እንኳን ሳያልፉ ወዲያው ይጠፋል።
➡️ የተቦካ እህል እየተበላሸ ነው የት ይጋገር ?
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ኃላፊ ዳይሬክተር ይሄይስ ስዩም ለኤ ኤም ኤን በሰጡት ቃል ፤ ቅሬታው እውነትነት እንዳለው ገልጸዋል።
" ለፈጠርንባቸው ችግር ደንበኞቻችንን ይቅርታ ጠይቃለሁ። በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁለት ሳምንት ሳይሞላ ወይም ከዛም ባነሰ ጊዜ መፍትሄ እንሰጣቸዋለን " ብለዋል።
#ፈረንሳይለጋሲዮን #ጨፌሜዳ
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#MPESASafaricom
ጉዞው ሰላም ነው ፤ እዚህ የሃገር ዉስጥ የበረራ ጉዞ ላይ 5% ተመላሽ ሲጨመርበት ደግሞ ፤ በጣም ሰላም ነው ፤ የሃገር ዉስጥ በረራ ትኬታችንን በM-PESA ከፍለን 5% ተመላሽ አሁኑኑ እናግኝ !
የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#FurtherAheadTogether
ጉዞው ሰላም ነው ፤ እዚህ የሃገር ዉስጥ የበረራ ጉዞ ላይ 5% ተመላሽ ሲጨመርበት ደግሞ ፤ በጣም ሰላም ነው ፤ የሃገር ዉስጥ በረራ ትኬታችንን በM-PESA ከፍለን 5% ተመላሽ አሁኑኑ እናግኝ !
የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#FurtherAheadTogether
" የአንድ አመት ከሁለት ወራት በላይ እልቂት ቀላል እልቂት አይደለም !! "
በአማራ ክልል ከአንድ አመት በላይ የሆነውን ጦርነት ዛሬም መቋጫ አላገኘም።
በየጊዜው በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች በሚካሄዱ ውጊያዎች የበርካታ ሰዎች ህይወት እያለፈ ነው።
ንጸሃን የጦርነቱ ሰለባ መሆናቸው ቀጥሏል።
የሰብዓዊ መብት ተቋማት በሚያወጧቸው ሪፖርቶች በድሮን ጭምር በሚፈጸም ጥቃት ንጹሃን ሰለባ እየሆኑ ነው።
ሴቶችና ህጻናት ፣ በእድሜም የገፉ ዜጎች ከፍተኛ ጉዳትና ዋጋ እየከፈሉ ናቸው።
በክልሉ እና ከክልሉ ውጭ በተለያዩ ከተሞች ' የፋኖ ' ደጋፊ ናችሁ በሚል ለእስር ለእንግልት የተዳረጉ ዜጎች በርካቶች ናቸው።
ጤና ተቋማት ስራ መስራት አልቻሉም።
የጤና ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ነው። የመድሃኒት ችግር በስፋት አለ። በተለይ ግጭት ሲኖር ከከተማ በወጡ አካባቢዎች ፤ ከተማ ውስጥ ሳይቀር መድሃኒት እና የጤና አገልግሎት ማግኘት ፈተና ሆኗል።
ተማሪዎች ተረጋግተው ትምህርታቸውን ለመከታተል አልቻሉም። ላለፉት ተከታታይ አመታት የአማራ ተማሪዎች እጅግ በስቃይ ውስጥ እያለፉ ናቸው።
ዘንድሮ ለ2017 የትምህርት ዘመን ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪ ይመዘገባል ተብሎ የነበረ ቢሆንም እስካለፈው መስከረም 8 የተመዘገበው 2 ሚሊዮን 295 ሺህ 150 ተማሪ ብቻ ነው።
በክልሉ ያሉ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም የግቢ ጥሪ ተራዝሞባቸው ያለ ትምህርት ቤታቸው ቀጭ ብለው ይገኛሉ።
በሰሜኑ ጦርነት ክፉኛ የተዳከመው የክልሉ ኢኮኖሚ አሁን ላይ ያለበት ሁኔታ አሳሳቢ ሆኗል።
ገንዘብ ያላቸው ስራ መስራት አልቻልም በሚል ወደ አዲስ አበባ እየገቡ እንደሆነ ከዚህ ቀደም ብዙ ተነግሯል።
ከቱሪስቶች ብዙ ገቢ ያስገባ የነበረው የአማራ ክልል አሁን ላይ ለጉብኝት ብሎ ወደ ክልሉ የሚጓዝ ተጓዥ አጥቷል።
የክልሉ አሁናዊ ፀጥታ ሁኔታ ሰዎች በማገት ገንዘብ ለሚቀበሉ አካላት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮ በርካቶች ታግተው ከፍለው ወጥተዋል። አንዳንዶች ከፍለው ሁሉ ተገድለዋል። ህጻናት ሳይቀሩ እየታገቱ ገንዘብ ይጠየቃል።
በክልሉ በተለይ በገጠራማ አካባቢዎች ተጠያቂነት እና ስርዓት የሚባለው ነገር ከጠፋ ሰነባብቷል።
በአጠቃላይ ክልሉ ያለበት ሁኔታ አሳሳቢ ነው።
ለመሆኑን በአማራ ክልል ያለውን ጦርነት በሰላማዊ መንገድና በድርድር እንዲፈታ ያመቻቻል ተብሎ የተሰየመው የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል እስካሁን ምን አደረገ ? ይህ የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ሰሞኑን የሰላም ካውንስሉን አግኘትን ምን እየሰራችሁ ነው ? ህዝቡ ከዚህ መከራ የሚወጣበት ተስፋስ አለው ወይ ? ችግሩ በሰላም ይፈታ ይሆን ? ስንል ጠይቀናል።
ካውንስሉ ምን አለ ?
➡️ችግሮቹ በአንድ ጀንበር የሚያልቁ ስላልሆኑ ጊዜ እየወሰደ ነው የመጣው። የፋኖ ታጣቂዎችም አንድ አመራር ፈጥረው የክልሉን ህዝብ ጥያቄ ማስመለስ የሚችሉት በድርድር ነው። ' ለአማራ ህዝብ ጥያቄ ነው የቆምነው ' ካሉ ጥያቄው ሊመለስ የሚችለው በጦርነት አይደለም። በድርድሩ በፋኖም በኩል ፍላጎት ያላቸው እንዳሉ ሁሉ ፍላጎት የሌላቸው ወገኖችም አሉ። ከመንግስት ጋር ለመደራደር ፍላጎት የሌላቸው ወገኖች ‘ በጦርነት እንገፋለን ’ የሚሉ ናቸው። ፍላጎት ያላቸው ወገኖች ደግሞ ‘ አንድ ሆነን ለመምጣት ሁኔታዎችን እያመቻቸን ነው ’ የሚሉ፣ የመንግስትን ቁርጠኝነትም የሚጠይቁ ናቸው።
➡️ ለድርድሩ መንግስት ምን ያህል ቁርጠኛ ነው ? የሚሉ ወገኖች አሉ። መንግስት ቁርጠኛ ነው ብለን ለማለት ፈቃደኝነቱ በክልል ደረጃ የታዬ ቢሆንም፣ በፌደራል ደረጃም እንድምታ በመግለጽ ረገድ የሚገለጽ ነው። ነገር ግን በመግለጫ ደረጃ በፌደራል መንግስት አለመሰጠቱን ግምት ውስጥ አስገብተን ችግሮቹ በሂደት ይፈታሉ። ሁለቱንም ወገኖች ለውይይቱ ዝግጁ ሆናችሁ በፈለጋችሁት ቦታ፣ በመረጣችሁት አደራዳሪ፣ በራሳችሁ ማኒፌስቶ ጥያቄያችሁን አቅርባችሁ ችግሩ ይፈታ ብለን አሳስበናል።
➡️ ችግሩ በድርድር እንዲፈታ ተፅዕኖ እንዲፈጥሩ ከኢንተርናሽናል ኮሚዩኒቲ ጋር (ከአሜሪካ፣ ከኢጋድ ከካናዳ መንግስት) ግንኙነት አድርገናል። ‘ሁለቱም ኃይሎች ላይ ተፅዕኖ ለማሳደር የበኩላችን እገዛ እናደርጋለን’ ብለዋል።
ካለፉት ጥቂት ሳምንታት ወዲህ አማራ ክልል ያለው የተኩስ ልውውጥ ጠንከር ብሎ ታይቷል። ሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች ወደ ድርድር በመምጣት ፋንታ ወደ ጠንካራ ጦርነት ያስገባቸው ያልተስማሙበት ጉዳይ ምንድን ነው ? በሚል ለካውንስሉ ጥያቄ ቀርቧል።
ካውንስሉ ምን ምላሽ ሰጠ ?
" ድርድር በየትኛውም መንገድ ሊከናወን ይችላል። እየተዋጉ መደራደር፣ ተኩስ እያቆሙ መደራደር፣ የበላይነትን ይዞ መደራደር የድርድሩ አንድ ፕሪንሲፕል ነው።
ምናልባት እየተዋጉም ቢደራደሩ ፣ ተኩስ አቁመውም ቢደራደሩ ይሄ ድርድርን በውስጥ ያዘለ ድርድር ማድረግ የሚያስችላቸው ሁኔታ ሊኖረው ይችላል።
አሁን ላይም እየተዋጉም ቢሆን ' እንደራደር ' ሊሉ ይችላሉ። ተስፋ የሚያስቆርጥ ነገር የለም። ሁሌም ይዋጋሉ። 14 ወራት ሆናቸው። ይሄ ውጊያ ምንም አዲስ ነገር አይደለም። ከዚህ በፊት የነበረ ነው።
እኛ አሁን ይሄ እንዳይቀጥል ነው እየነገርን ያለነው። ሁለቱም ወገኖች በየጊዜው ውጊያ ያውጃሉ በሚዲያቸው እንሰማለን። ፋኖዎቹም ያውጃሉ፤ በመንግስትም አዲስ ነገር አይደለም። "
ድርድር ለማድረግ 2ቱም አካላት በሙሉ ሥምምነት ያልቀረቡባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች ምንድን ናቸው ? በሚል ለቀረበው ጥያቄ ካውንስሉ ተከታዩን መልሷል።
“ በህዝብ ዘንድ ያለውን የከፋ ስቃይ እንዲያዩ ነው የምንመክረው። ሁለቱም ወገኖች ደግሞ ማዬት ያልቻሉት ነገር ህዝብ አሁን ያለበትን ስቃይ ነው።
እኛ ደግሞ ህዝቡ በየቀኑ እየሞተ ፣ እየደቀቀ ፣ ህልውናውን ጭምር ፈተና ውስጥ የከተተበት ጊዜ መሆኑን እናያለን።
ህዝቡን አብረነው ስለምንኖር በስሚ ስሚ አይደለም የምንሰማው በዓይናችን የምናየው መጥፎ ተግባር ከአጠገባችን ነው ያለው።
ስለዚህ ህዝቡ ችግር ላይ መውደቁን ሁለቱም ማዬት አለባቸው። " ብሏል።
ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ መንግስት እና በታጠቁ ኃይሎች ለአብነት ከ " ኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት / ሸኔ " ጋር ድርድር ተሞክሮ ያለ ውጤት ተቋጭቷል ፤ በአማራ ክልል ድርድር ቢደረግ ተመሳሳይ የሆነ እጣ ፈንታ እንዳያጋጥመው ምን ይሰራል በሚል ለቀረበው ጥያቄም ካውንስሉ ምላሹን ሰጥቷል።
ካውንስሉ ፦
“ አንዳንዶቹ ችግሮቹን በውይይት ለመፍታት ቶሎ ብለው ወደ ድርድር ይመጣሉ። መንግስት የኃይል የበላይነትን ባገኘ ጊዜ የዓለም ኃያላን የመጡበትና ትብብር የተደረገበት፣ ፈጥነው የመጡበት ሁኔታ ነበር።
ምክንያቱም መንግስት የኃይል የበላይነት ስላገኘ ነው።
‘ ህዝብ የሚፈልገው ጦርነት ነው ’ ብሎ ካመነ ‘ ድርድርም አልፈልግም ’ ይልና ሲዋጋ ይቆያል። ይሄ የስልጣኔ አካሄድ አይደለም።
ካለፈው ድርድር መማር፣ ከዚህ በላይ ህዝቡ ሳያልቅ ወደ ውይይት መምጣት ያስፈልጋል። የአንድ ዓመት ከሁለት ወራት በላይ እልቂት ቀላል እልቂት አይደለም። የደረሰብን ፈተናም ቀላል አይደለም።
አለመታደል ነው እኮ። መማር አለብን። ሕዝብ እየተመታ፣ ህዝብ እየወደመ፣ ህዝብ ልጁን እያጣ፣ ትምህርት ቤት እየተዘጋ…‘ህዝብ ይደግፈኛል’ ማለት ካለመረዳት የሚመነጭ እንጂ መፍትሄው በእጃቸው ነው። ሁለቱም ኃይሎች ለድርድር ይቅረቡ "
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል ከአንድ አመት በላይ የሆነውን ጦርነት ዛሬም መቋጫ አላገኘም።
በየጊዜው በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች በሚካሄዱ ውጊያዎች የበርካታ ሰዎች ህይወት እያለፈ ነው።
ንጸሃን የጦርነቱ ሰለባ መሆናቸው ቀጥሏል።
የሰብዓዊ መብት ተቋማት በሚያወጧቸው ሪፖርቶች በድሮን ጭምር በሚፈጸም ጥቃት ንጹሃን ሰለባ እየሆኑ ነው።
ሴቶችና ህጻናት ፣ በእድሜም የገፉ ዜጎች ከፍተኛ ጉዳትና ዋጋ እየከፈሉ ናቸው።
በክልሉ እና ከክልሉ ውጭ በተለያዩ ከተሞች ' የፋኖ ' ደጋፊ ናችሁ በሚል ለእስር ለእንግልት የተዳረጉ ዜጎች በርካቶች ናቸው።
ጤና ተቋማት ስራ መስራት አልቻሉም።
የጤና ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ነው። የመድሃኒት ችግር በስፋት አለ። በተለይ ግጭት ሲኖር ከከተማ በወጡ አካባቢዎች ፤ ከተማ ውስጥ ሳይቀር መድሃኒት እና የጤና አገልግሎት ማግኘት ፈተና ሆኗል።
ተማሪዎች ተረጋግተው ትምህርታቸውን ለመከታተል አልቻሉም። ላለፉት ተከታታይ አመታት የአማራ ተማሪዎች እጅግ በስቃይ ውስጥ እያለፉ ናቸው።
ዘንድሮ ለ2017 የትምህርት ዘመን ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪ ይመዘገባል ተብሎ የነበረ ቢሆንም እስካለፈው መስከረም 8 የተመዘገበው 2 ሚሊዮን 295 ሺህ 150 ተማሪ ብቻ ነው።
በክልሉ ያሉ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም የግቢ ጥሪ ተራዝሞባቸው ያለ ትምህርት ቤታቸው ቀጭ ብለው ይገኛሉ።
በሰሜኑ ጦርነት ክፉኛ የተዳከመው የክልሉ ኢኮኖሚ አሁን ላይ ያለበት ሁኔታ አሳሳቢ ሆኗል።
ገንዘብ ያላቸው ስራ መስራት አልቻልም በሚል ወደ አዲስ አበባ እየገቡ እንደሆነ ከዚህ ቀደም ብዙ ተነግሯል።
ከቱሪስቶች ብዙ ገቢ ያስገባ የነበረው የአማራ ክልል አሁን ላይ ለጉብኝት ብሎ ወደ ክልሉ የሚጓዝ ተጓዥ አጥቷል።
የክልሉ አሁናዊ ፀጥታ ሁኔታ ሰዎች በማገት ገንዘብ ለሚቀበሉ አካላት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮ በርካቶች ታግተው ከፍለው ወጥተዋል። አንዳንዶች ከፍለው ሁሉ ተገድለዋል። ህጻናት ሳይቀሩ እየታገቱ ገንዘብ ይጠየቃል።
በክልሉ በተለይ በገጠራማ አካባቢዎች ተጠያቂነት እና ስርዓት የሚባለው ነገር ከጠፋ ሰነባብቷል።
በአጠቃላይ ክልሉ ያለበት ሁኔታ አሳሳቢ ነው።
ለመሆኑን በአማራ ክልል ያለውን ጦርነት በሰላማዊ መንገድና በድርድር እንዲፈታ ያመቻቻል ተብሎ የተሰየመው የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል እስካሁን ምን አደረገ ? ይህ የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ሰሞኑን የሰላም ካውንስሉን አግኘትን ምን እየሰራችሁ ነው ? ህዝቡ ከዚህ መከራ የሚወጣበት ተስፋስ አለው ወይ ? ችግሩ በሰላም ይፈታ ይሆን ? ስንል ጠይቀናል።
ካውንስሉ ምን አለ ?
➡️ችግሮቹ በአንድ ጀንበር የሚያልቁ ስላልሆኑ ጊዜ እየወሰደ ነው የመጣው። የፋኖ ታጣቂዎችም አንድ አመራር ፈጥረው የክልሉን ህዝብ ጥያቄ ማስመለስ የሚችሉት በድርድር ነው። ' ለአማራ ህዝብ ጥያቄ ነው የቆምነው ' ካሉ ጥያቄው ሊመለስ የሚችለው በጦርነት አይደለም። በድርድሩ በፋኖም በኩል ፍላጎት ያላቸው እንዳሉ ሁሉ ፍላጎት የሌላቸው ወገኖችም አሉ። ከመንግስት ጋር ለመደራደር ፍላጎት የሌላቸው ወገኖች ‘ በጦርነት እንገፋለን ’ የሚሉ ናቸው። ፍላጎት ያላቸው ወገኖች ደግሞ ‘ አንድ ሆነን ለመምጣት ሁኔታዎችን እያመቻቸን ነው ’ የሚሉ፣ የመንግስትን ቁርጠኝነትም የሚጠይቁ ናቸው።
➡️ ለድርድሩ መንግስት ምን ያህል ቁርጠኛ ነው ? የሚሉ ወገኖች አሉ። መንግስት ቁርጠኛ ነው ብለን ለማለት ፈቃደኝነቱ በክልል ደረጃ የታዬ ቢሆንም፣ በፌደራል ደረጃም እንድምታ በመግለጽ ረገድ የሚገለጽ ነው። ነገር ግን በመግለጫ ደረጃ በፌደራል መንግስት አለመሰጠቱን ግምት ውስጥ አስገብተን ችግሮቹ በሂደት ይፈታሉ። ሁለቱንም ወገኖች ለውይይቱ ዝግጁ ሆናችሁ በፈለጋችሁት ቦታ፣ በመረጣችሁት አደራዳሪ፣ በራሳችሁ ማኒፌስቶ ጥያቄያችሁን አቅርባችሁ ችግሩ ይፈታ ብለን አሳስበናል።
➡️ ችግሩ በድርድር እንዲፈታ ተፅዕኖ እንዲፈጥሩ ከኢንተርናሽናል ኮሚዩኒቲ ጋር (ከአሜሪካ፣ ከኢጋድ ከካናዳ መንግስት) ግንኙነት አድርገናል። ‘ሁለቱም ኃይሎች ላይ ተፅዕኖ ለማሳደር የበኩላችን እገዛ እናደርጋለን’ ብለዋል።
ካለፉት ጥቂት ሳምንታት ወዲህ አማራ ክልል ያለው የተኩስ ልውውጥ ጠንከር ብሎ ታይቷል። ሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች ወደ ድርድር በመምጣት ፋንታ ወደ ጠንካራ ጦርነት ያስገባቸው ያልተስማሙበት ጉዳይ ምንድን ነው ? በሚል ለካውንስሉ ጥያቄ ቀርቧል።
ካውንስሉ ምን ምላሽ ሰጠ ?
" ድርድር በየትኛውም መንገድ ሊከናወን ይችላል። እየተዋጉ መደራደር፣ ተኩስ እያቆሙ መደራደር፣ የበላይነትን ይዞ መደራደር የድርድሩ አንድ ፕሪንሲፕል ነው።
ምናልባት እየተዋጉም ቢደራደሩ ፣ ተኩስ አቁመውም ቢደራደሩ ይሄ ድርድርን በውስጥ ያዘለ ድርድር ማድረግ የሚያስችላቸው ሁኔታ ሊኖረው ይችላል።
አሁን ላይም እየተዋጉም ቢሆን ' እንደራደር ' ሊሉ ይችላሉ። ተስፋ የሚያስቆርጥ ነገር የለም። ሁሌም ይዋጋሉ። 14 ወራት ሆናቸው። ይሄ ውጊያ ምንም አዲስ ነገር አይደለም። ከዚህ በፊት የነበረ ነው።
እኛ አሁን ይሄ እንዳይቀጥል ነው እየነገርን ያለነው። ሁለቱም ወገኖች በየጊዜው ውጊያ ያውጃሉ በሚዲያቸው እንሰማለን። ፋኖዎቹም ያውጃሉ፤ በመንግስትም አዲስ ነገር አይደለም። "
ድርድር ለማድረግ 2ቱም አካላት በሙሉ ሥምምነት ያልቀረቡባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች ምንድን ናቸው ? በሚል ለቀረበው ጥያቄ ካውንስሉ ተከታዩን መልሷል።
“ በህዝብ ዘንድ ያለውን የከፋ ስቃይ እንዲያዩ ነው የምንመክረው። ሁለቱም ወገኖች ደግሞ ማዬት ያልቻሉት ነገር ህዝብ አሁን ያለበትን ስቃይ ነው።
እኛ ደግሞ ህዝቡ በየቀኑ እየሞተ ፣ እየደቀቀ ፣ ህልውናውን ጭምር ፈተና ውስጥ የከተተበት ጊዜ መሆኑን እናያለን።
ህዝቡን አብረነው ስለምንኖር በስሚ ስሚ አይደለም የምንሰማው በዓይናችን የምናየው መጥፎ ተግባር ከአጠገባችን ነው ያለው።
ስለዚህ ህዝቡ ችግር ላይ መውደቁን ሁለቱም ማዬት አለባቸው። " ብሏል።
ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ መንግስት እና በታጠቁ ኃይሎች ለአብነት ከ " ኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት / ሸኔ " ጋር ድርድር ተሞክሮ ያለ ውጤት ተቋጭቷል ፤ በአማራ ክልል ድርድር ቢደረግ ተመሳሳይ የሆነ እጣ ፈንታ እንዳያጋጥመው ምን ይሰራል በሚል ለቀረበው ጥያቄም ካውንስሉ ምላሹን ሰጥቷል።
ካውንስሉ ፦
“ አንዳንዶቹ ችግሮቹን በውይይት ለመፍታት ቶሎ ብለው ወደ ድርድር ይመጣሉ። መንግስት የኃይል የበላይነትን ባገኘ ጊዜ የዓለም ኃያላን የመጡበትና ትብብር የተደረገበት፣ ፈጥነው የመጡበት ሁኔታ ነበር።
ምክንያቱም መንግስት የኃይል የበላይነት ስላገኘ ነው።
‘ ህዝብ የሚፈልገው ጦርነት ነው ’ ብሎ ካመነ ‘ ድርድርም አልፈልግም ’ ይልና ሲዋጋ ይቆያል። ይሄ የስልጣኔ አካሄድ አይደለም።
ካለፈው ድርድር መማር፣ ከዚህ በላይ ህዝቡ ሳያልቅ ወደ ውይይት መምጣት ያስፈልጋል። የአንድ ዓመት ከሁለት ወራት በላይ እልቂት ቀላል እልቂት አይደለም። የደረሰብን ፈተናም ቀላል አይደለም።
አለመታደል ነው እኮ። መማር አለብን። ሕዝብ እየተመታ፣ ህዝብ እየወደመ፣ ህዝብ ልጁን እያጣ፣ ትምህርት ቤት እየተዘጋ…‘ህዝብ ይደግፈኛል’ ማለት ካለመረዳት የሚመነጭ እንጂ መፍትሄው በእጃቸው ነው። ሁለቱም ኃይሎች ለድርድር ይቅረቡ "
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት መዘዙ ለአጎራባች ሃገራትም ተርፏል " - ካተሪን ፓቲሎ
የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት በሱዳን ላይ ካስተለው ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ባሻገር ኢትዮጵያን ጨምሮ በአጎራባች ሃገራት ላይ ብርቱ ኤኮኖሚያዊ ጉዳት ማድረሱን የዓለም የገንዘብ ድርጅት አስታወቀ።
በድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ካተሪን ፓቲሎ " የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት መዘዙ ለአጎራባች ሃገራትም ተርፏል " ብለዋል።
" ቀድሞውኑ በራሳቸው የውስጥ ጉዳዮቻቸው ተይዘው የነበሩ የሱዳን ተጎራባቾች በስደተኞች መጥለቅለቅን ጨምሮ ሌሎች የደህንነት እና የንግድ ተግዳሮቶች አስከትሎባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
የዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም የትንበያ ሪፖርት እንደሚያመለክተው በጦርነቱ በተለይ በማዕከላዊ አፍሪቃ ፣ ቻድ ፣ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ላይ ከፍተኛ ኤኮኖሚያዊ ጉዳት ሊደርስ ይችላል።
በተለይ ከገቢዋ አብዛኛውን ከነዳጅ ዘይት ሽያጭ የምታገኘው ደቡብ ሱዳን ባለፈው የካቲት ወር ሱዳን ውስጥ ከዋነኞቹ የነዳጅ ዘይት ማስተላለፊያዎች ቱቦዎች በአንዱ ላይ ጉዳት ከደረሰባት በኋላ ነገሮች አሳሳቢ መሆናቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
በተመሳሳይ በመካከለኛው ምስራቅ እና በዩክሬን እየተካሄዱ ያሉ ሌሎች " ውጫዊ ግጭቶች " እንደ የምግብ ዋጋ ፣ ማዳበሪያ እና የኃይል ወጪዎች ላይ ተጽዕኖ ማሳደራቸውን የዓለም የገንዘብ ድርጅት ገልጿል። #ዶቼቨለሬድዮ
@tikvahethiopia
የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት በሱዳን ላይ ካስተለው ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ባሻገር ኢትዮጵያን ጨምሮ በአጎራባች ሃገራት ላይ ብርቱ ኤኮኖሚያዊ ጉዳት ማድረሱን የዓለም የገንዘብ ድርጅት አስታወቀ።
በድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ካተሪን ፓቲሎ " የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት መዘዙ ለአጎራባች ሃገራትም ተርፏል " ብለዋል።
" ቀድሞውኑ በራሳቸው የውስጥ ጉዳዮቻቸው ተይዘው የነበሩ የሱዳን ተጎራባቾች በስደተኞች መጥለቅለቅን ጨምሮ ሌሎች የደህንነት እና የንግድ ተግዳሮቶች አስከትሎባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
የዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም የትንበያ ሪፖርት እንደሚያመለክተው በጦርነቱ በተለይ በማዕከላዊ አፍሪቃ ፣ ቻድ ፣ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ላይ ከፍተኛ ኤኮኖሚያዊ ጉዳት ሊደርስ ይችላል።
በተለይ ከገቢዋ አብዛኛውን ከነዳጅ ዘይት ሽያጭ የምታገኘው ደቡብ ሱዳን ባለፈው የካቲት ወር ሱዳን ውስጥ ከዋነኞቹ የነዳጅ ዘይት ማስተላለፊያዎች ቱቦዎች በአንዱ ላይ ጉዳት ከደረሰባት በኋላ ነገሮች አሳሳቢ መሆናቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
በተመሳሳይ በመካከለኛው ምስራቅ እና በዩክሬን እየተካሄዱ ያሉ ሌሎች " ውጫዊ ግጭቶች " እንደ የምግብ ዋጋ ፣ ማዳበሪያ እና የኃይል ወጪዎች ላይ ተጽዕኖ ማሳደራቸውን የዓለም የገንዘብ ድርጅት ገልጿል። #ዶቼቨለሬድዮ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት መዘዙ ለአጎራባች ሃገራትም ተርፏል " - ካተሪን ፓቲሎ የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት በሱዳን ላይ ካስተለው ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ባሻገር ኢትዮጵያን ጨምሮ በአጎራባች ሃገራት ላይ ብርቱ ኤኮኖሚያዊ ጉዳት ማድረሱን የዓለም የገንዘብ ድርጅት አስታወቀ። በድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ካተሪን ፓቲሎ " የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት መዘዙ ለአጎራባች…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Sudan
ዛሬም ድረስ አሸናፊ ያልተገኘለትና ዳፋው ለጎረቤቶች ሀገራት ጭምር የተረፈው የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት የብዙ ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል።
በርካቶችም ጦርነትን ሽሽት ሀገር ጥለው ወደ ጎረቤት ሀገራት ተሰደዋል።
የሱዳን ከተሞች ወደ ፍርስራሽነት ተቀይረዋል።
ሀገሪቱ ያሏት መሰረተ ልማቶች እንዳልነበሩ ሆነዋል።
ኢኮኖሚው ደቋል፤ ሞቷል።
የሚበላ የሚላስ የሚቀመስ ያጣው ሱዳናዊ እጅግ ብዙ ነው።
ተፋላሚዎቹ ቁጭ ብለው እንዲነጋገሩ ብዙ ቢሞከረም እምቢኝ እንዳሉ ናቸው። ጦርነቱንም አፋፍመው ቀጥለዋል።
ከዓመት ባለፈው የእርስ በርስ ጦርነት አንድም አሸናፊ አልተገኘም። ይልቁንም ሱዳን እንዳልነበረች ሆናለች። ዳግም ለማንሰራራት በርካታ አመታት ይወስድባታል።
ከላይ የተያያዘው ቪድዮ በአንድ ከተማ ያለውን አስከፊ ገጽታ የሚያሳይ ነው።
@tikvahethiopia
ዛሬም ድረስ አሸናፊ ያልተገኘለትና ዳፋው ለጎረቤቶች ሀገራት ጭምር የተረፈው የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት የብዙ ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል።
በርካቶችም ጦርነትን ሽሽት ሀገር ጥለው ወደ ጎረቤት ሀገራት ተሰደዋል።
የሱዳን ከተሞች ወደ ፍርስራሽነት ተቀይረዋል።
ሀገሪቱ ያሏት መሰረተ ልማቶች እንዳልነበሩ ሆነዋል።
ኢኮኖሚው ደቋል፤ ሞቷል።
የሚበላ የሚላስ የሚቀመስ ያጣው ሱዳናዊ እጅግ ብዙ ነው።
ተፋላሚዎቹ ቁጭ ብለው እንዲነጋገሩ ብዙ ቢሞከረም እምቢኝ እንዳሉ ናቸው። ጦርነቱንም አፋፍመው ቀጥለዋል።
ከዓመት ባለፈው የእርስ በርስ ጦርነት አንድም አሸናፊ አልተገኘም። ይልቁንም ሱዳን እንዳልነበረች ሆናለች። ዳግም ለማንሰራራት በርካታ አመታት ይወስድባታል።
ከላይ የተያያዘው ቪድዮ በአንድ ከተማ ያለውን አስከፊ ገጽታ የሚያሳይ ነው።
@tikvahethiopia