TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የስልጣን ሽምሹር አደረጉ። ፕሬዜዳንቱ በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ ሾመዋል። በአቶ ጌታቸው ረዳ ተፈርሞ ነሃሴ 14/2016 ዓ.ም የወጣው ደብዳቤ ፤ ፀጋይ ገብረተኽለ የዞኑ አስተዳዳሪ በመሆን የሚገባቸው ጥቅም ተጠብቆላቸው ሃላፊነቱን በአግባቡ…
#TPLF #Tigray
በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ማንኛውም አይነት የስልጣን ሹምሽር አልቀበልም አለ።
በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " በማንኛው የሃላፊነት እርከን በራስ ፍላጎት የሚደረግ የስራ ምደባና ሹምሽር ተቀባይነት የለውም " ብሏል።
የእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ለሁሉም የዞንና የወረዳ የድርጅቱ ፅህፈት ጠቅሶ ባሰራጨው ደብዳቤ ፥ " ከሰርዓታዊና ተቋማዊ አሰራር ውጪ የሚካሄዱ የስራ ምደባዎች ኢህጋዊ ብቻ ሳይሆኑ ተጠያቂነትን ያስከትላሉ " ሲል አስጠንቅቋል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ መሾማቸው ዘግበናል።
ነሃሴ 18/2016 ዓ.ም የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ደግሞ በሰሜናዊ ምዕራብ ዋና አስተዳዳሪና በቅርቡ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት ተክላይ ገ/መድህን ምትክ የክልሉ የስፓርት ኮሚሽን ኮምሽነር የነበሩት ተኽላይ ፍቓዱ ተሹመዋል።
ትግራይ ካሉዋት ሰባት የዞን አስተዳደሮች በአሁኑ ጊዜ ስድስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ የመቐለ ከተማ ብቻ በቅርቡ በተካሄደ ጉባኤ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይመራል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ማንኛውም አይነት የስልጣን ሹምሽር አልቀበልም አለ።
በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " በማንኛው የሃላፊነት እርከን በራስ ፍላጎት የሚደረግ የስራ ምደባና ሹምሽር ተቀባይነት የለውም " ብሏል።
የእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ለሁሉም የዞንና የወረዳ የድርጅቱ ፅህፈት ጠቅሶ ባሰራጨው ደብዳቤ ፥ " ከሰርዓታዊና ተቋማዊ አሰራር ውጪ የሚካሄዱ የስራ ምደባዎች ኢህጋዊ ብቻ ሳይሆኑ ተጠያቂነትን ያስከትላሉ " ሲል አስጠንቅቋል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ መሾማቸው ዘግበናል።
ነሃሴ 18/2016 ዓ.ም የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ደግሞ በሰሜናዊ ምዕራብ ዋና አስተዳዳሪና በቅርቡ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት ተክላይ ገ/መድህን ምትክ የክልሉ የስፓርት ኮሚሽን ኮምሽነር የነበሩት ተኽላይ ፍቓዱ ተሹመዋል።
ትግራይ ካሉዋት ሰባት የዞን አስተዳደሮች በአሁኑ ጊዜ ስድስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ የመቐለ ከተማ ብቻ በቅርቡ በተካሄደ ጉባኤ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይመራል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Telegram የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፈረንሳይ ውስጥ ታሰረ። ➡ በፈረንሳይ የሩስያ ኤምባሲ የዱሮቭን ሁኔታ በቅርብ እየተከታተለ ነው። ➡ ዱሮቭ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል። ➡ ብሎገሮች በፈረንሳይ ኤምባሲዎች የተቃውሞ ሰልፍ እየጠሩ ናቸው። የቴሌግራም መተግበሪያ መስራቹና ዋና ስራ አስኪያጁ ፓቨል ዱሮቭ ትላንት ቅዳሜ ምሽት ፈረንሳይ ፣ በፈረንሳይ ከፓሪስ ወጣ ብሎ…
" እንዲለቀቅ ይጠይቃሉ ወይስ ምላሳቸውን ውጠው ጸጥ ይላሉ ? " - ዛራኮቫ
የምዕራባውያኑ ለሰብዓዊነትና ነጻነት ቆመናል የሚሉ ድርጅቶች የቴሌግራም መስራች ፓቨል ዱሮቭ እንዲለቀቅ ይጠይቃሉ ?
የዱሮቭን ፈረንሳይ ውስጥ መታሰረን በመለተከተ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች " ምላሳቸውን ውጠው ዝም ይላሉ ? ወይስ እንዲፈታ ይጠይቃሉ ? " ብለዋል።
እ.ኤ.አ. በ2018 ፦
- ሂዩማን ራይትስ ዎች ፣
- አምነስቲ ኢንተርናሽናል ፣
- ፍሪደም ሃውስ ፣
- ድንበር የለሽ ሪፖርተሮች እና ሌሎችን ጨምሮ 26 መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ቡድን የሩስያ ፍርድ ቤት ቴሌግራምን ለማገድ የሰጠውን ውሳኔ አውግዘው ነበር ሲሉ አስታውሰዋል።
ዲፕሎማቷ ፤ " አሁን ፓሪስ ደውለው የዱሮቭን መፈታት የሚጠይቁ ይመስላችኋል ? ወይስ ምላሳቸውን ውጠው ዝም ይላሉ ? " ሲሉ በቴሌግራም ቻናላቸው ላይ ፅፈዋል።
ዛራኮቫ ፤ በ2018 ቴሌግራም ላይ የሕግ አውጭ ቅሬታዎች ነበሩ፣ ይህም በብዙ የኢንክሪፕሽን ሥርዓቱ ቴክኒካል መለኪያዎች ምክንያት ነው ሲሉ አስታውሰው ፤ ዱሮቭ ግን ነፃ ሆኖ መቆየቱን መተግበሪያውን ማሳገዱን ገልጸዋል።
የዱሮቭ በተያዘበት ቅፅበት በፈረንሳይ የሩስያ ኤምባሲ ጉዳዩን መከታተል እንደጀመረ ጠቁመዋል።
" የእኛን ዲፕሎማቶች ስለ ስራቸው ማስታወስ አያስፈልግም " ሲሉም ዛካሮቫ አክለዋል።
ቴሌግራም ሩስያ እንዲሁም በዩክሬን አካባቢ እጅግ ከፍተኛ ተጠቃሚ ያለው ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባለስልጣናትም ተመራጭ መልዕክት መለዋወጫ አድርገውታል።
ዱሮቭ የሩስያ እና የፈረንሳይ ዜግነት አለው።
@tikvahethiopia
የምዕራባውያኑ ለሰብዓዊነትና ነጻነት ቆመናል የሚሉ ድርጅቶች የቴሌግራም መስራች ፓቨል ዱሮቭ እንዲለቀቅ ይጠይቃሉ ?
የዱሮቭን ፈረንሳይ ውስጥ መታሰረን በመለተከተ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች " ምላሳቸውን ውጠው ዝም ይላሉ ? ወይስ እንዲፈታ ይጠይቃሉ ? " ብለዋል።
እ.ኤ.አ. በ2018 ፦
- ሂዩማን ራይትስ ዎች ፣
- አምነስቲ ኢንተርናሽናል ፣
- ፍሪደም ሃውስ ፣
- ድንበር የለሽ ሪፖርተሮች እና ሌሎችን ጨምሮ 26 መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ቡድን የሩስያ ፍርድ ቤት ቴሌግራምን ለማገድ የሰጠውን ውሳኔ አውግዘው ነበር ሲሉ አስታውሰዋል።
ዲፕሎማቷ ፤ " አሁን ፓሪስ ደውለው የዱሮቭን መፈታት የሚጠይቁ ይመስላችኋል ? ወይስ ምላሳቸውን ውጠው ዝም ይላሉ ? " ሲሉ በቴሌግራም ቻናላቸው ላይ ፅፈዋል።
ዛራኮቫ ፤ በ2018 ቴሌግራም ላይ የሕግ አውጭ ቅሬታዎች ነበሩ፣ ይህም በብዙ የኢንክሪፕሽን ሥርዓቱ ቴክኒካል መለኪያዎች ምክንያት ነው ሲሉ አስታውሰው ፤ ዱሮቭ ግን ነፃ ሆኖ መቆየቱን መተግበሪያውን ማሳገዱን ገልጸዋል።
የዱሮቭ በተያዘበት ቅፅበት በፈረንሳይ የሩስያ ኤምባሲ ጉዳዩን መከታተል እንደጀመረ ጠቁመዋል።
" የእኛን ዲፕሎማቶች ስለ ስራቸው ማስታወስ አያስፈልግም " ሲሉም ዛካሮቫ አክለዋል።
ቴሌግራም ሩስያ እንዲሁም በዩክሬን አካባቢ እጅግ ከፍተኛ ተጠቃሚ ያለው ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባለስልጣናትም ተመራጭ መልዕክት መለዋወጫ አድርገውታል።
ዱሮቭ የሩስያ እና የፈረንሳይ ዜግነት አለው።
@tikvahethiopia
" የሽብር ወንጀል ምርመራ ጀምሪያለሁ " - ፌዴራል ፖሊስ
ሰሞኑን ከአዲስ አበባ መቐለ ለጉዞ በተዘጋጀ አውሮፕላን ውስጥ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ በፈጠሩ 6 ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ መጀመሩን የፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ ፦
👉 ዮሀንስ ዳንኤል
👉 አማኑኤል መውጫ
👉 ናትናኤል ወንድወሰን
👉 ኤልያስ ድሪባ
👉 ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው።
የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ መዝገብ እንደሚያሳየው፥ " እነዚህ ተጠርጣሪዎች ተፈጥሮ በፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት አውሮፕላኑ መብረር አይችልም እየተባለ፣ አስገድዶ ለማስኬድ የፈጠሩት አምባጓሮ በወንጀል ሕጉ ተጠያቂ ያደርጋቸዋል " ብሏል።
" የፖሊስ የምርመራ ቡድን ተጠርጣሪዎች ላይ በወንጀል ተጠያቂ ለማድረግ ከተጀመረው ምርመራ ባሻገር፣ ከጸረሰላም ሃይሎች ተልእኮ ተቀብለው የተንቀሳቀሱ በመሆናቸው በሽብር ወንጀልም መጠርጠራቸውን ነው " የገለጸው።
የምርመራ መዝገቡ ፥ " በወቅቱ የአየር መንገዱ ከደህንነት ኃይሎች ጋር በመሆን በትዕግስት ቢማጸናቸውም፣ ድብቅ አጀንዳቸውን እያራመዱ በመሆናቸው አሻፈረን ብለዋል " ሲል ገልጿል።
" ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ ተግባር መጠቀም ሲገባቸው፣ የሀገር ኩራት እና የራሳቸው ንብረት የሆነውን አየር መንገድ ማንቋሸሻቸው አሳዛኝ ተግባር ነው " ብሏል
" እነዚህ በቁጥጥር ስር የሚገኙ 6 ተጠርጣሪዎች በተላለፉት የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የበረራ አሰራር ጥሰት ብሎም በሽብር ወንጀሎች የምርመራ መዝገብ ነገ ነሀሴ 20/2016 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ " ሲል ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia
ሰሞኑን ከአዲስ አበባ መቐለ ለጉዞ በተዘጋጀ አውሮፕላን ውስጥ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ በፈጠሩ 6 ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ መጀመሩን የፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ ፦
👉 ዮሀንስ ዳንኤል
👉 አማኑኤል መውጫ
👉 ናትናኤል ወንድወሰን
👉 ኤልያስ ድሪባ
👉 ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው።
የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ መዝገብ እንደሚያሳየው፥ " እነዚህ ተጠርጣሪዎች ተፈጥሮ በፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት አውሮፕላኑ መብረር አይችልም እየተባለ፣ አስገድዶ ለማስኬድ የፈጠሩት አምባጓሮ በወንጀል ሕጉ ተጠያቂ ያደርጋቸዋል " ብሏል።
" የፖሊስ የምርመራ ቡድን ተጠርጣሪዎች ላይ በወንጀል ተጠያቂ ለማድረግ ከተጀመረው ምርመራ ባሻገር፣ ከጸረሰላም ሃይሎች ተልእኮ ተቀብለው የተንቀሳቀሱ በመሆናቸው በሽብር ወንጀልም መጠርጠራቸውን ነው " የገለጸው።
የምርመራ መዝገቡ ፥ " በወቅቱ የአየር መንገዱ ከደህንነት ኃይሎች ጋር በመሆን በትዕግስት ቢማጸናቸውም፣ ድብቅ አጀንዳቸውን እያራመዱ በመሆናቸው አሻፈረን ብለዋል " ሲል ገልጿል።
" ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ ተግባር መጠቀም ሲገባቸው፣ የሀገር ኩራት እና የራሳቸው ንብረት የሆነውን አየር መንገድ ማንቋሸሻቸው አሳዛኝ ተግባር ነው " ብሏል
" እነዚህ በቁጥጥር ስር የሚገኙ 6 ተጠርጣሪዎች በተላለፉት የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የበረራ አሰራር ጥሰት ብሎም በሽብር ወንጀሎች የምርመራ መዝገብ ነገ ነሀሴ 20/2016 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ " ሲል ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሽብር ወንጀል ምርመራ ጀምሪያለሁ " - ፌዴራል ፖሊስ ሰሞኑን ከአዲስ አበባ መቐለ ለጉዞ በተዘጋጀ አውሮፕላን ውስጥ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ በፈጠሩ 6 ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ መጀመሩን የፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል። ተጠርጣሪዎቹ ፦ 👉 ዮሀንስ ዳንኤል 👉 አማኑኤል መውጫ 👉 ናትናኤል ወንድወሰን 👉 ኤልያስ ድሪባ 👉 ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው።…
#Ethiopia
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል በማለት በቁጥጥር ስር አውሎ የሽብር ወንጀል ምርመራ የከፈተባቸውን 6 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ማንነት የሚያሳይ ፎቶ ይፋ አድርጓል።
ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋልኳቸው በሀገራችን ካለው የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ አውሮፕላን መብረር አይችልም " ያሉ የበረራ ባለሙያዎችን በማስገደድ በረራውን ለማስቀጠል በፈጠሩት አምባጓሮ እና ግርግር ወንጀል ተጠርጥረው ነው ሲል አስረድቷል።
ነገ ፍርድ ቤት አቀርባቸዋለሁ ብሏል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል በማለት በቁጥጥር ስር አውሎ የሽብር ወንጀል ምርመራ የከፈተባቸውን 6 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ማንነት የሚያሳይ ፎቶ ይፋ አድርጓል።
ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋልኳቸው በሀገራችን ካለው የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ አውሮፕላን መብረር አይችልም " ያሉ የበረራ ባለሙያዎችን በማስገደድ በረራውን ለማስቀጠል በፈጠሩት አምባጓሮ እና ግርግር ወንጀል ተጠርጥረው ነው ሲል አስረድቷል።
ነገ ፍርድ ቤት አቀርባቸዋለሁ ብሏል።
@tikvahethiopia
📣 Jasiri's Fully-Funded Talent Investor Program, Cohort 7 Application, is open!
Requirements:
✅ Must be a citizen of Ethiopia, Kenya, or Rwanda, whether living in their home country or abroad.
✅ Ready to fully dedicate themselves to entrepreneurship, including a three-month Residential Intensive in Rwanda.
✅ Skilled and knowledgeable in their professional field, able to spot opportunities in their sector.
✅ Committed to starting a new, innovative venture with rapid growth potential.
✅ Has a history of being an achiever, problem solver, and value creator.
✅ Collaborative and eager to connect with other ambitious peers to co-found new ventures.
To join the 7th cohort, Apply here 👉🏾 https://bit.ly/3A8rxtV
For more information, Join our telegram channel 👉🏾 @Jasiri4africa
Requirements:
✅ Must be a citizen of Ethiopia, Kenya, or Rwanda, whether living in their home country or abroad.
✅ Ready to fully dedicate themselves to entrepreneurship, including a three-month Residential Intensive in Rwanda.
✅ Skilled and knowledgeable in their professional field, able to spot opportunities in their sector.
✅ Committed to starting a new, innovative venture with rapid growth potential.
✅ Has a history of being an achiever, problem solver, and value creator.
✅ Collaborative and eager to connect with other ambitious peers to co-found new ventures.
To join the 7th cohort, Apply here 👉🏾 https://bit.ly/3A8rxtV
For more information, Join our telegram channel 👉🏾 @Jasiri4africa
#Ethiopia
በሁለት ቀናት ውስጥ ሁለት የሀገራችን ኢትዮጵያ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ህይወታቸው አልፏል።
የመጀመሪያው ተዋናይ ጌታቸው እጅጉ (ባቡጂ) ሲሆን ተዋናዩ እጅግ በርካታ ፊልሞች ላይ ተውኗል።
አርቲስቱ በአንድ ወቅት በሰጠው ቃል ከ60 በላይ ፊልሞች ላይ ተውኗል።
ቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመቅረብ በወቅታዊና ማህበራዊ፣ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ሃሳቡን ሲያካፍል ፤ ጠንካራ ትችቶች በድፍረት በመናገር ይታወቃል።
የአርቲስቱ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ከቀኑ 8:00 ሰዓት በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ይፈጸማል።
በሌላ በኩል ፤ አንጋፋው አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።
አርቲስቱ በበርካታ ቴአትሮች፣ ፊልሞች እንዲሁም የሬዲዮ እና የቴሌቭዥን ተከታታይ ድራማዎች ላይ በተዋናይነት እና በአዘጋጅነት ተሳትፏል፡፡
በተለይም በቅርቡ " እረኛዬ " በተሰኘው ድራማ በተጨማሪ በ " ገመና አንድ " እና በ " ገመና ሁለት " ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች በድንቅ የትወና ብቃቱ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት እንዲያገኝ አድርጎታል።
የአርቲስቱ የአስክሬን ሽኝት ነገ ነሐሴ 21/ 2016 ዓ.ም ከረፋድ 3 ሰዓት ጀምሮ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሚካሄድ ሲሆን የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ከ5 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት ድረስ በቀጨኔ መድሃኒዓለም ቤተክርስቲያን ይፈጸማል።
ነፍስ ይማር🕯
@tikvahethiopia
በሁለት ቀናት ውስጥ ሁለት የሀገራችን ኢትዮጵያ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ህይወታቸው አልፏል።
የመጀመሪያው ተዋናይ ጌታቸው እጅጉ (ባቡጂ) ሲሆን ተዋናዩ እጅግ በርካታ ፊልሞች ላይ ተውኗል።
አርቲስቱ በአንድ ወቅት በሰጠው ቃል ከ60 በላይ ፊልሞች ላይ ተውኗል።
ቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመቅረብ በወቅታዊና ማህበራዊ፣ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ሃሳቡን ሲያካፍል ፤ ጠንካራ ትችቶች በድፍረት በመናገር ይታወቃል።
የአርቲስቱ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ከቀኑ 8:00 ሰዓት በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ይፈጸማል።
በሌላ በኩል ፤ አንጋፋው አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።
አርቲስቱ በበርካታ ቴአትሮች፣ ፊልሞች እንዲሁም የሬዲዮ እና የቴሌቭዥን ተከታታይ ድራማዎች ላይ በተዋናይነት እና በአዘጋጅነት ተሳትፏል፡፡
በተለይም በቅርቡ " እረኛዬ " በተሰኘው ድራማ በተጨማሪ በ " ገመና አንድ " እና በ " ገመና ሁለት " ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች በድንቅ የትወና ብቃቱ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት እንዲያገኝ አድርጎታል።
የአርቲስቱ የአስክሬን ሽኝት ነገ ነሐሴ 21/ 2016 ዓ.ም ከረፋድ 3 ሰዓት ጀምሮ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሚካሄድ ሲሆን የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ከ5 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት ድረስ በቀጨኔ መድሃኒዓለም ቤተክርስቲያን ይፈጸማል።
ነፍስ ይማር🕯
@tikvahethiopia
#Ethiopia
ጥሬ ዕቃዎች በዱቤ ወይም በወጪ ንግድ ማበረታቻ ሥርዓት ተጠቅመው ያስገቡ ላኪዎች፣ በአንድ ዓመት ውስጥ አምርተው ወደ ውጭ መላክ ካልቻሉና ለአገር ውስጥ ለመሸጥ #ሳይፈቀድላቸው ለሽያጭ ካቀረቡ 25 በመቶ ቅጣት እንደሚጣልባቸው ተገልጿል።
በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ.ም. ታትሞ የወጣው የወጪ ንግድ ማበረታቻ ሥርዓት ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1342/2016 በ " ቫውንቸር " ሥርዓት፣ እንዲሁም በ ' ቦንድ ኤክስፖርት ፋብሪካ " ሥርዓት ወደ አገር ውስጥ የገባ የጥሬ ዕቃ ለተጠቃሚ [ለአምራቹ] ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርቱ ተመርቶ ለውጭ ገበያ መቅረብ እንደሚኖርበት ይደነግጋል።
በተቀመጠ ጊዜ ገደብ ምርቱን ለውጭ ገበያ ማቅረብ ካልተቻለ የጉምሩክ ኮሚሽን ምክንያቱ በቂ መሆኑን ሲያምንበት ብቻ ሊራዘም የሚችል ሲሆን የማራዘሚያ ገደቡ ከመጠናቅቁ በፊት ለኮሚሽኑ መቅረብ እንዳለበት ተገልጿል።
በአገር ውስጥ እንዲሸጥ ያልተፈቀደለት የ " ቫውንቸር " ሥርዓት ተጠቃሚ ጥቅም ላይ ባልዋለው ጥሬ ዕቃ ላይ ሊከፍል ከሚገባው ቀረጥና ታክስ ተጨማሪ 25 በመቶ እንዲከፍል እንደሚደረግ ተደንግጓል።
በቦንድ ግብዓት አቅርቦት መጋዘን ሥርዓት ወደ አገር የገባ ግብዓት ወደ መጋዘን ከገባበት ጊዜ ጀምሮ በ1 ዓመት ጊዜ ውስጥ ለአምራቾች ካልተላለፈ መከፈል ካለበት ቀረጥና ታክስ በተጨማሪ የቀረጡንና የታክሱን 10 በመቶ ሊከፍል እንደሚገባ ይህንን ማድረግ ካልተቻለም የጉምሩክ ኮሚሽን ሲያምንበት ጊዜው ሊራዘም እንደሚችል ተመላክቷል።
አቅራቢዎች በሚሰጡት ዱቤ ወይም በፍራንኮ ቫሉታ ዕቃዎችን ወደ አገር ውስጥ የሚያስገባ አስመጪ ተፈላጊውን ምርት በአገር ውስጥ ከተመረተ በኋላ ፣ የምርቱ ተቀባይነት መኖሩን የሚያረጋግጥ ከገዥው የተላከ ትዕዛዝ ወይም የተደረገ ውል ማቅረብ መቻል እንዳለበት በአዋጁ ተደንግጓል።
ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Ethiopia-Reporter-08-26
Credit - Ethiopia Reporter
@tikvahethiopia
ጥሬ ዕቃዎች በዱቤ ወይም በወጪ ንግድ ማበረታቻ ሥርዓት ተጠቅመው ያስገቡ ላኪዎች፣ በአንድ ዓመት ውስጥ አምርተው ወደ ውጭ መላክ ካልቻሉና ለአገር ውስጥ ለመሸጥ #ሳይፈቀድላቸው ለሽያጭ ካቀረቡ 25 በመቶ ቅጣት እንደሚጣልባቸው ተገልጿል።
በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ.ም. ታትሞ የወጣው የወጪ ንግድ ማበረታቻ ሥርዓት ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1342/2016 በ " ቫውንቸር " ሥርዓት፣ እንዲሁም በ ' ቦንድ ኤክስፖርት ፋብሪካ " ሥርዓት ወደ አገር ውስጥ የገባ የጥሬ ዕቃ ለተጠቃሚ [ለአምራቹ] ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርቱ ተመርቶ ለውጭ ገበያ መቅረብ እንደሚኖርበት ይደነግጋል።
በተቀመጠ ጊዜ ገደብ ምርቱን ለውጭ ገበያ ማቅረብ ካልተቻለ የጉምሩክ ኮሚሽን ምክንያቱ በቂ መሆኑን ሲያምንበት ብቻ ሊራዘም የሚችል ሲሆን የማራዘሚያ ገደቡ ከመጠናቅቁ በፊት ለኮሚሽኑ መቅረብ እንዳለበት ተገልጿል።
በአገር ውስጥ እንዲሸጥ ያልተፈቀደለት የ " ቫውንቸር " ሥርዓት ተጠቃሚ ጥቅም ላይ ባልዋለው ጥሬ ዕቃ ላይ ሊከፍል ከሚገባው ቀረጥና ታክስ ተጨማሪ 25 በመቶ እንዲከፍል እንደሚደረግ ተደንግጓል።
በቦንድ ግብዓት አቅርቦት መጋዘን ሥርዓት ወደ አገር የገባ ግብዓት ወደ መጋዘን ከገባበት ጊዜ ጀምሮ በ1 ዓመት ጊዜ ውስጥ ለአምራቾች ካልተላለፈ መከፈል ካለበት ቀረጥና ታክስ በተጨማሪ የቀረጡንና የታክሱን 10 በመቶ ሊከፍል እንደሚገባ ይህንን ማድረግ ካልተቻለም የጉምሩክ ኮሚሽን ሲያምንበት ጊዜው ሊራዘም እንደሚችል ተመላክቷል።
አቅራቢዎች በሚሰጡት ዱቤ ወይም በፍራንኮ ቫሉታ ዕቃዎችን ወደ አገር ውስጥ የሚያስገባ አስመጪ ተፈላጊውን ምርት በአገር ውስጥ ከተመረተ በኋላ ፣ የምርቱ ተቀባይነት መኖሩን የሚያረጋግጥ ከገዥው የተላከ ትዕዛዝ ወይም የተደረገ ውል ማቅረብ መቻል እንዳለበት በአዋጁ ተደንግጓል።
ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Ethiopia-Reporter-08-26
Credit - Ethiopia Reporter
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Omo የኦሞ ወንዝ ሙላት ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው አርሶአደር በ4ቱም አቅጣጫ ንብረቱን ጥሎ መሸሽ ላይ ነው። ችግሩ እንደሚከሰት ታውቆ በርካታ ስራ ሲሰራ ቢቆይም የኦሞ ወንዝ መጠን ከተለመደውና ከታሰበው ውጭ መሆኑን ተከትሎ ግን ለዞኑ መንግስትም ሆነ ለግብረሰናይ ድርጅቶች ሁኔታው ከባድ ሆኖባቸዋል። የወንዙ ሙላት ከባድ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ አርብቶ አደሩን በአራት ጊዜያዊ…
#ALERT🚨
⚠️ " በውሀ ተውጠን ከማለቃችን በፊት ድረሱልን " - የኦሞራቴ ከተማ ነዋሪዎች
🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር
የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል ስንል ከቀናት በፊት መዘገባችን ይታወሳል።
ይሁንና አሁን ላይ የኦሞ ወንዝ ከአቅም በላይ በመሙላቱና የአካባቢዉ መሬት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መተኛቱን ተከትሎ የወረዳዉ ዋና ከተማ የሆነችዉን ኦሞራቴን ደሴት ሲያደርጋት ህዝቡም መዉጫ በማጣት ጭንቀት ውስጦ መግባቱን ሰምተናል።
የድረሱልን ጥሪያቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያደረሱት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚገልጹት ለአመታት በወንዙ ሙላት ሲቸገሩ መቆየታቸውንና አሁን ግን ከርቀት ወደምትገኘው ኦሞራቴ ከተማ በእጅጉ መጠጋቱ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ ከመዋጣቸው በፊት የሚመለከተዉ አካል እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።
በአካባቢው የነበሩት አርብቶ አደሮች በበኩላቸው ሙሉ በሙሉ የግጦሽ መሬቶች በወንዙ ተቆርሶ መወሰዱንና ከብቶቻቸው ማለቃቸውን ገልጸዉ አሁን ላይ የተጠለሉባቸው ጊዜያዊ መጠለያዎች በውሀው እየተጥለቀለቁ በመሆኑ ህይወታቸዉ አደጋ ላይ መውደቁን አስተድተዋል።
ስለሁኔታዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ " የዉሀዉ አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው " ብለዋል።
ማህበረሰቡ አፈር በማዳበሪያ እየቋጠረ ግድብ መስራቱ ውሀውን ስላላስቆመው የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ብለዋል።
" አሁን ላይ የኦሞራቴ ከተማ ከጊዜያዊ መጠለያዎችም ሆነ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ለመገናኘትም ሆነ ለመሸሽ ቱርሚን የሚያገናኘዉ ድልድይ በመሰበሩና ወደኬኒያ የሚወስደዉ ዋና መንገድ በውሀው ክራክ በማድረጉ ደሴት ሆናል " ሲሉ ገልጸዋል።
በመሆኑም " የኦሞራቴ ህዝብ የከፋ ችግር ላይ በመሆኑ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ " ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር
የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል ስንል ከቀናት በፊት መዘገባችን ይታወሳል።
ይሁንና አሁን ላይ የኦሞ ወንዝ ከአቅም በላይ በመሙላቱና የአካባቢዉ መሬት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መተኛቱን ተከትሎ የወረዳዉ ዋና ከተማ የሆነችዉን ኦሞራቴን ደሴት ሲያደርጋት ህዝቡም መዉጫ በማጣት ጭንቀት ውስጦ መግባቱን ሰምተናል።
የድረሱልን ጥሪያቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያደረሱት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚገልጹት ለአመታት በወንዙ ሙላት ሲቸገሩ መቆየታቸውንና አሁን ግን ከርቀት ወደምትገኘው ኦሞራቴ ከተማ በእጅጉ መጠጋቱ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ ከመዋጣቸው በፊት የሚመለከተዉ አካል እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።
በአካባቢው የነበሩት አርብቶ አደሮች በበኩላቸው ሙሉ በሙሉ የግጦሽ መሬቶች በወንዙ ተቆርሶ መወሰዱንና ከብቶቻቸው ማለቃቸውን ገልጸዉ አሁን ላይ የተጠለሉባቸው ጊዜያዊ መጠለያዎች በውሀው እየተጥለቀለቁ በመሆኑ ህይወታቸዉ አደጋ ላይ መውደቁን አስተድተዋል።
ስለሁኔታዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ " የዉሀዉ አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው " ብለዋል።
ማህበረሰቡ አፈር በማዳበሪያ እየቋጠረ ግድብ መስራቱ ውሀውን ስላላስቆመው የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ብለዋል።
" አሁን ላይ የኦሞራቴ ከተማ ከጊዜያዊ መጠለያዎችም ሆነ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ለመገናኘትም ሆነ ለመሸሽ ቱርሚን የሚያገናኘዉ ድልድይ በመሰበሩና ወደኬኒያ የሚወስደዉ ዋና መንገድ በውሀው ክራክ በማድረጉ ደሴት ሆናል " ሲሉ ገልጸዋል።
በመሆኑም " የኦሞራቴ ህዝብ የከፋ ችግር ላይ በመሆኑ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ " ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#ALERT🚨 ⚠️ " በውሀ ተውጠን ከማለቃችን በፊት ድረሱልን " - የኦሞራቴ ከተማ ነዋሪዎች 🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Alert🚨
ኦሞ ወንዝ በከፍተኛ ሁኔታ በመሙላቱ የወንዙ ውሃ እና የቱርካና ሀይቅ ይዞታውን እያሰፋ በመሆኑ በኦሞራቴ ከተማ በ1.9 ኪ/ሜ ርቀት አከባቢ በተለያዩ ቦታዎች የመሬት መሰንጠቅ እዲሁም ውሃው ውስጥ ለውስጥ እየሄደ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
ኦሞ ወንዝ በከፍተኛ ሁኔታ በመሙላቱ የወንዙ ውሃ እና የቱርካና ሀይቅ ይዞታውን እያሰፋ በመሆኑ በኦሞራቴ ከተማ በ1.9 ኪ/ሜ ርቀት አከባቢ በተለያዩ ቦታዎች የመሬት መሰንጠቅ እዲሁም ውሃው ውስጥ ለውስጥ እየሄደ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል በማለት በቁጥጥር ስር አውሎ የሽብር ወንጀል ምርመራ የከፈተባቸውን 6 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ማንነት የሚያሳይ ፎቶ ይፋ አድርጓል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋልኳቸው በሀገራችን ካለው የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ አውሮፕላን…
#Update
የአቪዬሽን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ ፈጥረዋል የተባሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል።
ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia
የአቪዬሽን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ ፈጥረዋል የተባሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል።
ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia