TIKVAH-ETHIOPIA
" ... ኢትዮጵያ ጎረቤታችን ናት፤ ከእነሱ ጋር ቢዝነስ መስራት እንፈልጋለን " - ሰኢድ ሀሰን አቡዱለሂ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች / #UAE / ንብረት የሆነው ' ዲፒ ወርልድ ኩባንያ ' የሚያስተዳድረው የበርበራ ወደብ የኢትዮጵያን 30 በመቶ ጭነት እንዲያስተናግድ የሶማሌላንድ ባለስልጣናት ማቀዳቸው ተሰምቷል። ለዚህ የወደብ አጠቃቀምና የጉምሩክ ሥርዓቶችን የተመለከተ ስምምነት በኢትዮጵያና ሶማሌላንድ…
" ወደቡ ዝግጁ ነው፤ መንገዱም ከሞላ ጎደል ዝግጁ ነው " - ሰዓድ አሊ ሽሬ
ሶማሌላንድ የበርበራ ወደብ #የኢትዮጵያን 30% ጭነት እንዲያስተናግድ ትፈልጋለች።
ለዚህ ደግሞ አስፈላጊ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ገልጸለች።
አሁን ላይ ስምምነት እንዲፈረም እየተሰራ ነው ተብሏል።
የሶማሌላንድ የፋይናንስ ሚኒስትር ሰዓድ አሊ ሽሬ ምን አሉ ?
" አካላዊ መሰረተ ልማትን በተመለከተ ወደቡን ገንበተናል።
☑ አንድ ኪሎሜትር የሚሰፋ የመርከብ ማቆሚያ፤
☑ ኮንቴነሮችን መጫንና ማውረድ የሚችሉ ክሬኖች ያሉት ዓለም አቀፍ ወደብ አለ፤
☑ ከበርበራ ወደብ ድንበር ላይ እስከምትገኘው #ውጫሌ ያለውን መንገድ ገንብተናል፤
ስለዚህ ወደቡ ዝግጁ ነው። መንገዱም ከሞላ ጎደል ዝግጁ ነው። ከዚህ በተጨማሪ በበርበራ ነጻ የኢኮኖሚ ዞኖች አሉን።
የነዳጅ ማጠራቀሚያ ጋኖች ከነዳጅ ጫኝ መርከቦች ማራገፊያ አዘጋጅተናል። አካላዊ ክፍል ከሞላ ጎደል አልቋል።
ለምሳሌ በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል የወደብ አጠቃቀም ስምምነት (Transit Agreement) ሊኖረን ይገባል። የጉምሩክ ስርዓቶቻችን ማገናኘት ወይም ማስተሳሰር ይኖርብናል ይህ አሁንም በስራ ላይ ነው። የመጓጓዣ ስምምነትም ማባጀት አለብን ይሄም ሂደት ላይ ነው።
ከስርዓት አኳያ በሂደት ላይ የሚገኙ የተወሰኑ ጉዳዮች አሉ " ብለዋል።
እንደ ሶማሌላንድ የወደቦች አስተዳደር ዳይሬክተር ሰኢድ ሀሰን አብዱላሂ ማብራሪያ ደግሞ ፥
➡ ህጋዊው ጉዳይ በመንግስታት መካከል የሚፈርም እንደሆነ
➡ ስምምነቱ እየተጠናቀቀ ስለመሆኑ
➡ በአንድ እና ሁለት ቀሪ ጉዳዮች ላይ ውይይት እየተደረገ መሆኑን
➡ በመጪው 60 ቀናት ስምምነቱ ሊጠናቀቅ እንደሚችልን ከ60 ቀናት በኃላ እንደሚፈረምና ኮሪደሩ ጥቅም መስጠት ይጀምራል።
በተጨማሪ ፦
° የUAE ዲፒ ወርልድ እና ሶማሌላንድ ከበርበራ ወደብ 15 ኪ/ሜ ርቀት ነጻ የኢኮኖሚ ቀጣራ ማበጀታቸውን
° ነጻው የኢኮኖሚ ቀጠና ከወደቡ ወደ ኢትዮጵያ በሚያመራው መንገድ ላይ እንደሚገኝ
° ነጻው የኢኮኖሚ ዞን 300 ሺህ ካሬ ጫማ የሚሰፋ ከማብሰያ ዘይት ማሸጊያ ፋብሪካ ጭምር አለው።
ከ6 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ከሶማሌላድ እና ዲፒ ወርልድ ጋር በተፈራረመችው ስምምነት በበርበራ ወደብ ልማት 19% ድርሻ ነበራት ግን አልዘለቀችበትም። ግን አሁን ኢትዮጵያ ወደቡ ላይ ድርሻ እንዲኖራት ትፈልጋለች።
የበርበራ ወደብ ያለበት ቀጠና ለዓለም አቀፍ የመርከብ እንቅስቃሴ ወሳኝ በመሆኑ ሶማሌላንድ እና ዲፒ ወርልድ አሁንም ማስፋታ ይፈልጋሉ።
ግዙፍ የኮንቴነር ተርሚናል ለመገንባት ሙከራ እየተደረገ መሆኑ፣ ተጨማሪ 600 ሜትር የሚሰፋ የመርከብ ማቆሚያ ፣ 7 ግዙፍ የእቃ መጫኛና ማውረጃ ለመጨመር እቅድ እንዳለ ታውቋል።
ይህን ተከትሎ የበርበራ ወደብ መርከብ መቆሚያ 1650 ሜርት እንደሚሆን 2 ሚሊዮን ኮንቴነርም ማስተናገድ እንደሚችል ለኢትዮጵያም ትልቅ አማራጭ መሆኑ በሶማሌላንድ ባለስልጣናት ተገልጿል።
Credit - DW (Eshete Bekele)
@tikvahethiopia
ሶማሌላንድ የበርበራ ወደብ #የኢትዮጵያን 30% ጭነት እንዲያስተናግድ ትፈልጋለች።
ለዚህ ደግሞ አስፈላጊ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ገልጸለች።
አሁን ላይ ስምምነት እንዲፈረም እየተሰራ ነው ተብሏል።
የሶማሌላንድ የፋይናንስ ሚኒስትር ሰዓድ አሊ ሽሬ ምን አሉ ?
" አካላዊ መሰረተ ልማትን በተመለከተ ወደቡን ገንበተናል።
☑ አንድ ኪሎሜትር የሚሰፋ የመርከብ ማቆሚያ፤
☑ ኮንቴነሮችን መጫንና ማውረድ የሚችሉ ክሬኖች ያሉት ዓለም አቀፍ ወደብ አለ፤
☑ ከበርበራ ወደብ ድንበር ላይ እስከምትገኘው #ውጫሌ ያለውን መንገድ ገንብተናል፤
ስለዚህ ወደቡ ዝግጁ ነው። መንገዱም ከሞላ ጎደል ዝግጁ ነው። ከዚህ በተጨማሪ በበርበራ ነጻ የኢኮኖሚ ዞኖች አሉን።
የነዳጅ ማጠራቀሚያ ጋኖች ከነዳጅ ጫኝ መርከቦች ማራገፊያ አዘጋጅተናል። አካላዊ ክፍል ከሞላ ጎደል አልቋል።
ለምሳሌ በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል የወደብ አጠቃቀም ስምምነት (Transit Agreement) ሊኖረን ይገባል። የጉምሩክ ስርዓቶቻችን ማገናኘት ወይም ማስተሳሰር ይኖርብናል ይህ አሁንም በስራ ላይ ነው። የመጓጓዣ ስምምነትም ማባጀት አለብን ይሄም ሂደት ላይ ነው።
ከስርዓት አኳያ በሂደት ላይ የሚገኙ የተወሰኑ ጉዳዮች አሉ " ብለዋል።
እንደ ሶማሌላንድ የወደቦች አስተዳደር ዳይሬክተር ሰኢድ ሀሰን አብዱላሂ ማብራሪያ ደግሞ ፥
➡ ህጋዊው ጉዳይ በመንግስታት መካከል የሚፈርም እንደሆነ
➡ ስምምነቱ እየተጠናቀቀ ስለመሆኑ
➡ በአንድ እና ሁለት ቀሪ ጉዳዮች ላይ ውይይት እየተደረገ መሆኑን
➡ በመጪው 60 ቀናት ስምምነቱ ሊጠናቀቅ እንደሚችልን ከ60 ቀናት በኃላ እንደሚፈረምና ኮሪደሩ ጥቅም መስጠት ይጀምራል።
በተጨማሪ ፦
° የUAE ዲፒ ወርልድ እና ሶማሌላንድ ከበርበራ ወደብ 15 ኪ/ሜ ርቀት ነጻ የኢኮኖሚ ቀጣራ ማበጀታቸውን
° ነጻው የኢኮኖሚ ቀጠና ከወደቡ ወደ ኢትዮጵያ በሚያመራው መንገድ ላይ እንደሚገኝ
° ነጻው የኢኮኖሚ ዞን 300 ሺህ ካሬ ጫማ የሚሰፋ ከማብሰያ ዘይት ማሸጊያ ፋብሪካ ጭምር አለው።
ከ6 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ከሶማሌላድ እና ዲፒ ወርልድ ጋር በተፈራረመችው ስምምነት በበርበራ ወደብ ልማት 19% ድርሻ ነበራት ግን አልዘለቀችበትም። ግን አሁን ኢትዮጵያ ወደቡ ላይ ድርሻ እንዲኖራት ትፈልጋለች።
የበርበራ ወደብ ያለበት ቀጠና ለዓለም አቀፍ የመርከብ እንቅስቃሴ ወሳኝ በመሆኑ ሶማሌላንድ እና ዲፒ ወርልድ አሁንም ማስፋታ ይፈልጋሉ።
ግዙፍ የኮንቴነር ተርሚናል ለመገንባት ሙከራ እየተደረገ መሆኑ፣ ተጨማሪ 600 ሜትር የሚሰፋ የመርከብ ማቆሚያ ፣ 7 ግዙፍ የእቃ መጫኛና ማውረጃ ለመጨመር እቅድ እንዳለ ታውቋል።
ይህን ተከትሎ የበርበራ ወደብ መርከብ መቆሚያ 1650 ሜርት እንደሚሆን 2 ሚሊዮን ኮንቴነርም ማስተናገድ እንደሚችል ለኢትዮጵያም ትልቅ አማራጭ መሆኑ በሶማሌላንድ ባለስልጣናት ተገልጿል።
Credit - DW (Eshete Bekele)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AmharaRegion በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ ዞን ፤ የላስታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና የወረዳው ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ በታጣቂዎች ጥቃት መገደላቸውን ቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት ዘግቧል። የላስታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው መልሴ እና የወረዳው የጤና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን አፈወርቅ ትላንት በተፈጸመ ጥቃት ነው የተገደሉት። ባለስልጣናቱ ተኩስ የተከፈተባቸው ወልዲያ ከተማ የነበራቸውን…
“ ማን እንደገደላቸው መረጃ የለኝም ፤ በተተኮሰባቸው ጠይት ተገድለዋል ዞሮ ዞሮ ” - ስሜ አይገለጽ ያሉ ባለስልጣን
በአማራ ክልል፣ ሰሜን ወሎ የላስታ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው መልሴ እና የወረዳው ጤና ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን አፈወርቅ ትላንት በጥይት መገደላቸውን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋገጧል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ አንድ የሰሜን ወሎ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ባለስልጣን በሰጡት ቃል፤ “ ትላንት ከዞን ግምገማ ቆይተው ሲመለሱ ነው ግድያው የተፈጸመው። የሞቱት የወረዳው አስተዳዳሪ የወረዳው ጤና ኃላፊ ናቸው ” ብለዋል።
“ ኩል መስክ የሚባል ቦታ ነው ግድያው የተፈጸመው ” ሲሉ ተናግረዋል።
ሌላ የተጎዳ ሰው አለ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፣ “ ሌላ እዛው ኩል መስክ የቀበሌ ሊቀመንበር የተጎዳ አለ ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“ አርብና ቅዳሜ ግምገማ ነበረ፤ እዚያ ተመልሰው ኩል መስክ ቆይተዋል ለሁለት ቀናት ” ሲሉም አክለዋል።
ግድያውን የፈጸመው ማነው ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ “ እስካሁን መረጃው የለኝም፤ በተተኮሰባቸው ጠይት ተገድለዋል ዞሮ ዞሮ ” ብለው፣ የገዳዮቹን ማንነት ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
“ ዞሮ ዞሮ በግድያ የሚመለስ አንድም ጥያቄ የለም። እነዚህ (ሟቾቹ) የሕዝብ አስተዳዳሪዎች ናቸው። ሕዝብም ጥበቃ ሊያደርግላቸው ይገባል እንጂ መሞት አለባቸው ብዬ አላስብም ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል፣ ሰሜን ወሎ የላስታ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው መልሴ እና የወረዳው ጤና ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን አፈወርቅ ትላንት በጥይት መገደላቸውን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋገጧል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ አንድ የሰሜን ወሎ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ባለስልጣን በሰጡት ቃል፤ “ ትላንት ከዞን ግምገማ ቆይተው ሲመለሱ ነው ግድያው የተፈጸመው። የሞቱት የወረዳው አስተዳዳሪ የወረዳው ጤና ኃላፊ ናቸው ” ብለዋል።
“ ኩል መስክ የሚባል ቦታ ነው ግድያው የተፈጸመው ” ሲሉ ተናግረዋል።
ሌላ የተጎዳ ሰው አለ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፣ “ ሌላ እዛው ኩል መስክ የቀበሌ ሊቀመንበር የተጎዳ አለ ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“ አርብና ቅዳሜ ግምገማ ነበረ፤ እዚያ ተመልሰው ኩል መስክ ቆይተዋል ለሁለት ቀናት ” ሲሉም አክለዋል።
ግድያውን የፈጸመው ማነው ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ “ እስካሁን መረጃው የለኝም፤ በተተኮሰባቸው ጠይት ተገድለዋል ዞሮ ዞሮ ” ብለው፣ የገዳዮቹን ማንነት ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
“ ዞሮ ዞሮ በግድያ የሚመለስ አንድም ጥያቄ የለም። እነዚህ (ሟቾቹ) የሕዝብ አስተዳዳሪዎች ናቸው። ሕዝብም ጥበቃ ሊያደርግላቸው ይገባል እንጂ መሞት አለባቸው ብዬ አላስብም ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#CAR
የ77 ዓመቱ የቀድሞው የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ፍራንሷ ቦዚዜ ላይ የእስር ማዘዣ ትዕዛዝ ወጣ።
ማዘዣው የወጣው ሠራዊታቸው ከእአአ 2009 እስከ 2013 ባለው ጊዜ ውስጥ በሰብዓዊነት ላይ ወንጀል ፈጽሟል በሚል ነው።
ማዘዣውን ያወጣው በባንጊ ላይ የተሰየመውና ከሃገር ውጪ ካሉ ፍርድ ቤቶች ጋራ የሚሠራው ልዩ የወንጀል ችሎት ነው።
ይህ ችሎት በእ.አ.አ 2015 በተመድ እገዛ የተቋቋመ እንደሆነ ተገልጿል።
የቀድሞ የሀገሪቱ መሪ ቦዚዜ ፦
- ግድያ፣
- አስገድዶ መሰወር፣
- ሰቆቃ፣
- መድፈር እና ሌሎች ኢሰብዓዊ ድርጊቶችን ፈፅመዋል በሚል ተከሰዋል።
ቦዚዜ በመፈንቅለ መንግስት ወደ ስልጣን የመጡት በእ.አ.አ 2003 ሲሆን ከአስር (10) ዓመታት በኋላ ከወንበራቸው ተወግደዋል።
ቦዚዜ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጀምሮ #በስደት ጊኒ ቢሳዉ የሚገኙ ሲሆን፣ ከዛ ሆነው ዋናኛ የሚባል አማጺ ቡድን በመምራት ላይ ይገኛሉ።
ጊኒ ቢሳዉ ተጠርጣሪውን ቦዚዜ #ይዛ እንድታስረክብ ተጠይቋል። #VOA
@tikvahethiopia
የ77 ዓመቱ የቀድሞው የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ፍራንሷ ቦዚዜ ላይ የእስር ማዘዣ ትዕዛዝ ወጣ።
ማዘዣው የወጣው ሠራዊታቸው ከእአአ 2009 እስከ 2013 ባለው ጊዜ ውስጥ በሰብዓዊነት ላይ ወንጀል ፈጽሟል በሚል ነው።
ማዘዣውን ያወጣው በባንጊ ላይ የተሰየመውና ከሃገር ውጪ ካሉ ፍርድ ቤቶች ጋራ የሚሠራው ልዩ የወንጀል ችሎት ነው።
ይህ ችሎት በእ.አ.አ 2015 በተመድ እገዛ የተቋቋመ እንደሆነ ተገልጿል።
የቀድሞ የሀገሪቱ መሪ ቦዚዜ ፦
- ግድያ፣
- አስገድዶ መሰወር፣
- ሰቆቃ፣
- መድፈር እና ሌሎች ኢሰብዓዊ ድርጊቶችን ፈፅመዋል በሚል ተከሰዋል።
ቦዚዜ በመፈንቅለ መንግስት ወደ ስልጣን የመጡት በእ.አ.አ 2003 ሲሆን ከአስር (10) ዓመታት በኋላ ከወንበራቸው ተወግደዋል።
ቦዚዜ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጀምሮ #በስደት ጊኒ ቢሳዉ የሚገኙ ሲሆን፣ ከዛ ሆነው ዋናኛ የሚባል አማጺ ቡድን በመምራት ላይ ይገኛሉ።
ጊኒ ቢሳዉ ተጠርጣሪውን ቦዚዜ #ይዛ እንድታስረክብ ተጠይቋል። #VOA
@tikvahethiopia
https://yangx.top/LionBankSC
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ መጪዎቹን የትንሳኤ እና ፋሲካ በዓላት ምክንያት በማድረግ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የሚያስገኙ የጥያቄና መልስ ውድድር ይዞላችሁ መጥቷል፡፡
እርስዎም የሽልማቱ ተሳታፊ ለመሆን ከታች ያሉትን የባንኩን ይፋዊ የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገፆች በመቀላቀል እና ጥያቄውን ቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉl
ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የውድድሩ ተሳታፊ ይሁኑ!!
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ
የስኬትዎ አጋር!
[Telegram] [Facebook]
#LIB #lioninternationalbank #anbesabank #keytosuccess
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ መጪዎቹን የትንሳኤ እና ፋሲካ በዓላት ምክንያት በማድረግ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የሚያስገኙ የጥያቄና መልስ ውድድር ይዞላችሁ መጥቷል፡፡
እርስዎም የሽልማቱ ተሳታፊ ለመሆን ከታች ያሉትን የባንኩን ይፋዊ የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገፆች በመቀላቀል እና ጥያቄውን ቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉl
ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የውድድሩ ተሳታፊ ይሁኑ!!
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ
የስኬትዎ አጋር!
[Telegram] [Facebook]
#LIB #lioninternationalbank #anbesabank #keytosuccess
#DStvEthiopia
🏆የዋንጫው ደረሰ🏆
በታላላቅ የዓለማችን እግር ኳስ ሊጎች ዋንጫ ለመሳም የሚደረጉትን ግስጋሴዎችን በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ቻናሎች በቀጥታ ይከታተሉ!
አንድም ደቂቃ እዳያመልጦ አሁኑኑ ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ወርሃዊ ካፍያዎን ይፈፅሙ!
💥 የአውሮፓ ምርጥ ተጫዋቾችን ፍልሚያ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ቻናሎች ይከታተሉ!
የዲኤስቲቪ ዲኮደር በ1,999 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
🏆የዋንጫው ደረሰ🏆
በታላላቅ የዓለማችን እግር ኳስ ሊጎች ዋንጫ ለመሳም የሚደረጉትን ግስጋሴዎችን በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ቻናሎች በቀጥታ ይከታተሉ!
አንድም ደቂቃ እዳያመልጦ አሁኑኑ ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ወርሃዊ ካፍያዎን ይፈፅሙ!
💥 የአውሮፓ ምርጥ ተጫዋቾችን ፍልሚያ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ቻናሎች ይከታተሉ!
የዲኤስቲቪ ዲኮደር በ1,999 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በአዲስ አበባ ከተማ ከትላንት ለሊት አንስቶ ከበድ ያለ ዝናብ ሲጥል ነበር። ዛሬ ንጋት ላይ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ደግሞ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ወረገኑ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል። @tikvahethiopia
#AddisAbaba
" የ4 ሰዎች አስክሬን ከተለያየ ቦታ አውጥተናል። ...‘13 ሰዎች በጎርፍ ተወሰዱ’ የሚለው ትክክለኛ መረጃ አይደለም " - አቶ ንጋቱ ማሞ
ከቀናት በፊት “ ሰዓሊተ ምህረት ጀርባ ያድሩ የነበሩ 13 የጎዳና ተዳዳሪ ልጆች በጎርፍ ተወስደው ሕይወታቸው እንዳለፈ አካባቢው ላይ ተነግሯል ” ሲሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በስፍራው የእሳት አደጋ ሠራተኞች ፣ ዋናተኞች፣ የፌደራል ፓሊስ አባላት ተገኝተው አስክሬን ለማውጣት እንቅስቃሴ ሲያደርጉ እንደተመለከቱ የገለጹ ሲሆን ፤ ቲክቫህ ኢትዮጵያም ስለጉዳዩ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ሥራ አመረራር ኮሚሽንን ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡት ምላሽ፤ “ ባለፈው እንደገለጽነው የ4 ሰዎች አስከሬን አውጥተናል። ‘13 ሰዎች በጎርፍ ተወሰዱ’ የሚለው ትክክለኛ መረጃ አይደለም። ጥቆማ ከሆነ ሊሆን ይችላል ” ብለዋል።
“ ምክንያቱም በየትኛውም ጉዳይ ሕይወቱ ያለፈ ሰው ቢኖር ወይ እሳት አደጋ ወይ ፓሊስ ነው የሚያነሳው፤ በግለሰብ ደረጃ አስከሬን አንስቶ ቀብር ያለ አይመስለኝም ” ነው ያሉት።
“ በቦታው ነበርን ግን ይሄ አሁን የተጠቀሰው ቁጥር (13) አስከሬን አልተገኘም። ያገኘነው 4 አስከሬን ነው ” ያሉት አቶ ንጋቱ ፣ 4ቱን አስክሬን ለፓሊስ አስረክበናል ሲሉ አስረድተዋል።
4 አስክሬን የት አካባቢ ነው የተገኘው ? ለሚለው ጥያቄ፣ “ ሰዓሊተ ምህረትም፤ ከተለያዩ ቦታም ነው የገኘነው። ጎዳና ተዳዳሪ ይሁኑ፣ እዛው አካባቢ ነዋሪ ይሁኑ እኛ መረጃ የለንም። ፓሊስ ነው የሚያረጋግጠው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“ አሁን የሚሉት ጥቆማ ትክክለኛነቱ የሚረጋገጥ ከሆነ ከፓሊስ ጋር ሆነን ፍለጋ እናካሂዳለን። አንዳንድ ጊዜ ጥቆማ ትክክል አይደለም የሚል መደምደሚያ ላይኖር ይችላል” ሲሉ ተናግረዋል።
ጎርፉ ተቋማትን ጨምሮ በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን፣ በተደጋጋሚ እየደረሰ ያለው ኑሯቸውንና እንቅስቃሴያቸውን ወንዝ አካባቢ ባደረጉ ሰዎች እንደሆነ፣ ማህበረሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ አደጋ ከደረሰም በ #939 የኮሚሽኑ ስልክ በፍጥነት ደውለው እንዲያሳውቁ አስገንዝበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የ4 ሰዎች አስክሬን ከተለያየ ቦታ አውጥተናል። ...‘13 ሰዎች በጎርፍ ተወሰዱ’ የሚለው ትክክለኛ መረጃ አይደለም " - አቶ ንጋቱ ማሞ
ከቀናት በፊት “ ሰዓሊተ ምህረት ጀርባ ያድሩ የነበሩ 13 የጎዳና ተዳዳሪ ልጆች በጎርፍ ተወስደው ሕይወታቸው እንዳለፈ አካባቢው ላይ ተነግሯል ” ሲሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በስፍራው የእሳት አደጋ ሠራተኞች ፣ ዋናተኞች፣ የፌደራል ፓሊስ አባላት ተገኝተው አስክሬን ለማውጣት እንቅስቃሴ ሲያደርጉ እንደተመለከቱ የገለጹ ሲሆን ፤ ቲክቫህ ኢትዮጵያም ስለጉዳዩ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ሥራ አመረራር ኮሚሽንን ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡት ምላሽ፤ “ ባለፈው እንደገለጽነው የ4 ሰዎች አስከሬን አውጥተናል። ‘13 ሰዎች በጎርፍ ተወሰዱ’ የሚለው ትክክለኛ መረጃ አይደለም። ጥቆማ ከሆነ ሊሆን ይችላል ” ብለዋል።
“ ምክንያቱም በየትኛውም ጉዳይ ሕይወቱ ያለፈ ሰው ቢኖር ወይ እሳት አደጋ ወይ ፓሊስ ነው የሚያነሳው፤ በግለሰብ ደረጃ አስከሬን አንስቶ ቀብር ያለ አይመስለኝም ” ነው ያሉት።
“ በቦታው ነበርን ግን ይሄ አሁን የተጠቀሰው ቁጥር (13) አስከሬን አልተገኘም። ያገኘነው 4 አስከሬን ነው ” ያሉት አቶ ንጋቱ ፣ 4ቱን አስክሬን ለፓሊስ አስረክበናል ሲሉ አስረድተዋል።
4 አስክሬን የት አካባቢ ነው የተገኘው ? ለሚለው ጥያቄ፣ “ ሰዓሊተ ምህረትም፤ ከተለያዩ ቦታም ነው የገኘነው። ጎዳና ተዳዳሪ ይሁኑ፣ እዛው አካባቢ ነዋሪ ይሁኑ እኛ መረጃ የለንም። ፓሊስ ነው የሚያረጋግጠው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“ አሁን የሚሉት ጥቆማ ትክክለኛነቱ የሚረጋገጥ ከሆነ ከፓሊስ ጋር ሆነን ፍለጋ እናካሂዳለን። አንዳንድ ጊዜ ጥቆማ ትክክል አይደለም የሚል መደምደሚያ ላይኖር ይችላል” ሲሉ ተናግረዋል።
ጎርፉ ተቋማትን ጨምሮ በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን፣ በተደጋጋሚ እየደረሰ ያለው ኑሯቸውንና እንቅስቃሴያቸውን ወንዝ አካባቢ ባደረጉ ሰዎች እንደሆነ፣ ማህበረሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ አደጋ ከደረሰም በ #939 የኮሚሽኑ ስልክ በፍጥነት ደውለው እንዲያሳውቁ አስገንዝበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፈተና መቼ ይሰጣል ?
እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል።
ፈተናው ለ15 ቀናት በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት እየተሠራ ነው።
ከ70 በመቶ የሚዘጋጀው ፈተና በኦንላይንና በወረቀት ወይም በጥብቅ ቁጥጥር በወረቀት ይሰጣል ተብሏል።
ባለፈው ዓመት የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ የሪሚዲያል ፈተናውን በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች #ብቻ ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራበት ነው።
ዘንድሮ 32,500 ተማሪዎች 50 በመቶ በላይ ውጤት በማምጣት በቀጥታ ዩኒቨርሲቲ ገብተው መደበኛ ትምህርት እየተከታተሉ ሲሆን ከ78 ሺህ በላይ ተማሪዎች ደግሞ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ሪሚዲያል ትምህርት እየወሰዱ እንደሚገኙ ሚኒስቴሩ ለኢፕድ ከሰጠው መረጃ ተመልክተናል።
በሌላ በኩል ፤ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ የሬሜዲያ ተማሪዎች ከታህሳስ ወር ጀምሮ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ቢሆንም በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የተመደቡ ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገላቸውም።
ተማሪዎቹ የትምህርት ጊዜያቸው እያለፈ እንደሆነና አስቸጋሪ ጊዜ እያሳለፉ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ቅሬታ አቅርበዋል።
70% ፈተናው በሰኔ ወር ይሰጣ መባሉ ደግሞ እንዳስጨነቃቸው ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
- የነዚህ ልጆች ዕጣ ፋንታ ምንድነው ?
- ከዚህ በኃላ መቼ ተጠርተው ተምረው ለፈተና ይቀርባሉ ?
- ለምን ምቹ ሁኔታ ከሌለ ቀደም ብሎ ሌላ ግቢ አይመደቡም ነበር ?
- አሁን መፍትሄ ምንድነው ? የሚሉ ጥያቄዎችን ይዞ የዩኒቨርሲቲውን አመራሮች በተደጋጋሚ በድምጽ እና በፅሁፍ ለማናገር ጥረት ቢያደርግም #ቁርጥ ያለ ምላሽ ማግኘት አልቻለም።
በቀጣይም ጥረቱን ይቀጥላል።
ዩኒቨርሲቲውም ሆነ ከትምህርት ሚኒስቴር ምላሽ ካገኘ ያቀርባል።
Via @tikvahUniversity
@tikvahethiopia
እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል።
ፈተናው ለ15 ቀናት በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት እየተሠራ ነው።
ከ70 በመቶ የሚዘጋጀው ፈተና በኦንላይንና በወረቀት ወይም በጥብቅ ቁጥጥር በወረቀት ይሰጣል ተብሏል።
ባለፈው ዓመት የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ የሪሚዲያል ፈተናውን በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች #ብቻ ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራበት ነው።
ዘንድሮ 32,500 ተማሪዎች 50 በመቶ በላይ ውጤት በማምጣት በቀጥታ ዩኒቨርሲቲ ገብተው መደበኛ ትምህርት እየተከታተሉ ሲሆን ከ78 ሺህ በላይ ተማሪዎች ደግሞ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ሪሚዲያል ትምህርት እየወሰዱ እንደሚገኙ ሚኒስቴሩ ለኢፕድ ከሰጠው መረጃ ተመልክተናል።
በሌላ በኩል ፤ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ የሬሜዲያ ተማሪዎች ከታህሳስ ወር ጀምሮ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ቢሆንም በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የተመደቡ ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገላቸውም።
ተማሪዎቹ የትምህርት ጊዜያቸው እያለፈ እንደሆነና አስቸጋሪ ጊዜ እያሳለፉ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ቅሬታ አቅርበዋል።
70% ፈተናው በሰኔ ወር ይሰጣ መባሉ ደግሞ እንዳስጨነቃቸው ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
- የነዚህ ልጆች ዕጣ ፋንታ ምንድነው ?
- ከዚህ በኃላ መቼ ተጠርተው ተምረው ለፈተና ይቀርባሉ ?
- ለምን ምቹ ሁኔታ ከሌለ ቀደም ብሎ ሌላ ግቢ አይመደቡም ነበር ?
- አሁን መፍትሄ ምንድነው ? የሚሉ ጥያቄዎችን ይዞ የዩኒቨርሲቲውን አመራሮች በተደጋጋሚ በድምጽ እና በፅሁፍ ለማናገር ጥረት ቢያደርግም #ቁርጥ ያለ ምላሽ ማግኘት አልቻለም።
በቀጣይም ጥረቱን ይቀጥላል።
ዩኒቨርሲቲውም ሆነ ከትምህርት ሚኒስቴር ምላሽ ካገኘ ያቀርባል።
Via @tikvahUniversity
@tikvahethiopia
#ማኅብረቅዱሳን
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።
የሁለቱም አገልጋዮች የመኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል።
በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ይገኛሉ የተባለ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት እንዳልታወቀ የቴሌቪዥን ጣቢያው ገልጿል።
@tikvahethiopia
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።
የሁለቱም አገልጋዮች የመኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል።
በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ይገኛሉ የተባለ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት እንዳልታወቀ የቴሌቪዥን ጣቢያው ገልጿል።
@tikvahethiopia
#ጸሎተ_ሐሙስ
የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት ተከናወነ።
ዛሬ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክሃይማኖት መሪነት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት ተከናወነ።
በስነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ቆሞሳት ፣ ካህናትና በርካታ ምዕመናን ተገኝተው እንደነበር ከቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
Photo Credit - TMC
@tikvahethiopia
የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት ተከናወነ።
ዛሬ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክሃይማኖት መሪነት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት ተከናወነ።
በስነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ቆሞሳት ፣ ካህናትና በርካታ ምዕመናን ተገኝተው እንደነበር ከቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
Photo Credit - TMC
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ማኅብረቅዱሳን በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል። የሁለቱም አገልጋዮች የመኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል…
የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12:00 በፌዴራል ፖሊስ " #ለጥያቄ_ይፈለጋሉ " በሚል ከቤታቸው ተወስደው መታሠራቸውን ቤተሰቦቻቸው መናገራቸውን ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ዘግቧል።
ቀደም ብሎ ፥ የሰንበት ት/ ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ከቤታቸው በጸጥታ ኃይል መወሰዳቸውና ቤታቸው ላክ ፍተሻ መደረጉን የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን መዝገቡ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
ቀደም ብሎ ፥ የሰንበት ት/ ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ከቤታቸው በጸጥታ ኃይል መወሰዳቸውና ቤታቸው ላክ ፍተሻ መደረጉን የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን መዝገቡ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
#ጸሎተ_ሐሙስ
ጸሎተ ሐሙስ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ተከብሯል።
በአዲስ አበባ ፒያሳ ልደታ ማርያም ካቴድራል የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሀነኢየሱስ ሱራፌልን ጨምሮ ካህናት፣ ደናግላንና ምዕመናን በተገኙበት መሥዋዕተ ቅዳሴና የቅባ ቅዱስ ቡራኬ ተካሂዷል።
Photo Credit - FBC & Emdiber Catholic Secretariat
@tikvahethiopia
ጸሎተ ሐሙስ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ተከብሯል።
በአዲስ አበባ ፒያሳ ልደታ ማርያም ካቴድራል የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሀነኢየሱስ ሱራፌልን ጨምሮ ካህናት፣ ደናግላንና ምዕመናን በተገኙበት መሥዋዕተ ቅዳሴና የቅባ ቅዱስ ቡራኬ ተካሂዷል።
Photo Credit - FBC & Emdiber Catholic Secretariat
@tikvahethiopia