#DigitalEthiopia
ዛሬ " የዲጂታል ኢትዮጵያ " የግምገማ መድረክ በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል።
ጠ/ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ የፌደራል እንዲሁም የክልል ከፍተኛ አመራሮች እና የዘርፉ ተዋናዮች በመድረኩ ተሳታፊ ነበሩ።
የ " ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 " ስትራቴጂ በዋናነት የዲጂታል መሰረተ ልማት በመገንባት እና በማስፋት የአገሪቱን ምጣኔ ኃብታዊ እድገት ማፋጠንን ዓላማ ያደረገ ሲሆን በአምስት ዓመታት ውስጥ ለመተግበር የታቀደ ነው።
ዛሬ ላይ የስትራቴጂውን የ4 አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል።
- ዲጂታል ሊትረሲን ለማስፋት፤
- የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎቱን የማሳደግ
- የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፤
- የዲጂታል ክፍያ ሥርዓትና የሳይበር ጥበቃ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች በሚመለከታቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ገለጻ ተደርጎባቸዋል።
በዚህ መድረክ በቅርቡ በንግድ ባንክ ላይ ያጋጠመው ጉዳይ በስፋት እንደማሳያ ሲቀርብ ነበር።
ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የብሔራዊ ባንክ ገዢው አቶ ማሞ ምህረቱም አስተያየት ሰጥተው ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን አሉ?
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ፥ " በሳይበር ጥቃት በ2022 በዓለም ላይ 9 ትሪሊዮን ዶላር በጠላፊዎች ተመዝብሯል" ብለዋል።
" ይህ ያጋጠመው ችግር ሰዎች አቅደው አምሯቸውን ተጠቅመው ለማለት ያስቸግራል፤ ከውስጥ ያሉ ሰዎች የፈጠሩት ችግር ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ይሄ ማለት [የሳይበር ጥቃት] አይከሰትም ግን ማለት አይደለም። በሺዎች የሚቆጠሩ አታኮች በየቀኑ ተቋሞቻችን ላይ ይፈጸማሉ፤ ኢንሳ ብትመጡ ይሄንን ትመለከታላችሁ " ብለዋል።
የብሔራዊ ባንክ ገዢው ምን አሉ?
አቶ ማሞ ምህረቱ " የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ችግር በውስጥ ሰዎች የተፈጠረ ነው [ Human Error] ነው " ብለዋል።
" በዚሁ አጋጣሚ የፋይናንስ ሥርዓቱ ግልጽ ነው። ምን አይነት ገንዘብ የት እንደተላከ ከየት እንደወጣ የት እንደገባ ይታወቃል። በእንደዚህ አይነት ስህተቶች የሚጠፋ ገንዘብ አይኖርም " ሲሉ ተደምጠዋል።
" አሁን ላይ 80 በመቶ የወጣው ገንዘብ ተመላሽ ተደርጋል " ብለዋል።
ብሔራዊ ባንክ የዚህን ክስተት ሙሉ የምርመራ ውጤት በሳምንት ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ገልጸዋል።
#AddisAbabaTikvahFamily
@tikvahethiopia
ዛሬ " የዲጂታል ኢትዮጵያ " የግምገማ መድረክ በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል።
ጠ/ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ የፌደራል እንዲሁም የክልል ከፍተኛ አመራሮች እና የዘርፉ ተዋናዮች በመድረኩ ተሳታፊ ነበሩ።
የ " ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 " ስትራቴጂ በዋናነት የዲጂታል መሰረተ ልማት በመገንባት እና በማስፋት የአገሪቱን ምጣኔ ኃብታዊ እድገት ማፋጠንን ዓላማ ያደረገ ሲሆን በአምስት ዓመታት ውስጥ ለመተግበር የታቀደ ነው።
ዛሬ ላይ የስትራቴጂውን የ4 አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል።
- ዲጂታል ሊትረሲን ለማስፋት፤
- የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎቱን የማሳደግ
- የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፤
- የዲጂታል ክፍያ ሥርዓትና የሳይበር ጥበቃ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች በሚመለከታቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ገለጻ ተደርጎባቸዋል።
በዚህ መድረክ በቅርቡ በንግድ ባንክ ላይ ያጋጠመው ጉዳይ በስፋት እንደማሳያ ሲቀርብ ነበር።
ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የብሔራዊ ባንክ ገዢው አቶ ማሞ ምህረቱም አስተያየት ሰጥተው ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን አሉ?
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ፥ " በሳይበር ጥቃት በ2022 በዓለም ላይ 9 ትሪሊዮን ዶላር በጠላፊዎች ተመዝብሯል" ብለዋል።
" ይህ ያጋጠመው ችግር ሰዎች አቅደው አምሯቸውን ተጠቅመው ለማለት ያስቸግራል፤ ከውስጥ ያሉ ሰዎች የፈጠሩት ችግር ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ይሄ ማለት [የሳይበር ጥቃት] አይከሰትም ግን ማለት አይደለም። በሺዎች የሚቆጠሩ አታኮች በየቀኑ ተቋሞቻችን ላይ ይፈጸማሉ፤ ኢንሳ ብትመጡ ይሄንን ትመለከታላችሁ " ብለዋል።
የብሔራዊ ባንክ ገዢው ምን አሉ?
አቶ ማሞ ምህረቱ " የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ችግር በውስጥ ሰዎች የተፈጠረ ነው [ Human Error] ነው " ብለዋል።
" በዚሁ አጋጣሚ የፋይናንስ ሥርዓቱ ግልጽ ነው። ምን አይነት ገንዘብ የት እንደተላከ ከየት እንደወጣ የት እንደገባ ይታወቃል። በእንደዚህ አይነት ስህተቶች የሚጠፋ ገንዘብ አይኖርም " ሲሉ ተደምጠዋል።
" አሁን ላይ 80 በመቶ የወጣው ገንዘብ ተመላሽ ተደርጋል " ብለዋል።
ብሔራዊ ባንክ የዚህን ክስተት ሙሉ የምርመራ ውጤት በሳምንት ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ገልጸዋል።
#AddisAbabaTikvahFamily
@tikvahethiopia
" 2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል " - የአካባቢው ምዕመናን
የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገ/ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሁለት አገልጋዮች #ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው መገደላቸውን የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለጸ።
በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በዶዶላ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን 2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው ጋር ለጊዜው " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት መገደላቸው ተነግሯል።
የቴሌቪዥን ጣቢያው ፤ ግድያው የተፈፀመው ትናንት መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ገደማ መሆኑን የአካባቢው ምዕመናን እንደነገሩት ገልጿል።
በተፈጸመው በዚህ ግድያ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት አንድ መሪጌታና ዲያቆንን ጨምሮ 5 የቤተሰብ አባሎቻቸው በጥይት ተደብድበው መገደላቸው ተገልጿል።
የቴሌቪዥን ጣቢያው ፥ በዶዶላ ከተማ ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም በርካታ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን አስታውሷል።
@tikvahethiopia
የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገ/ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሁለት አገልጋዮች #ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው መገደላቸውን የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለጸ።
በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በዶዶላ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን 2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው ጋር ለጊዜው " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት መገደላቸው ተነግሯል።
የቴሌቪዥን ጣቢያው ፤ ግድያው የተፈፀመው ትናንት መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ገደማ መሆኑን የአካባቢው ምዕመናን እንደነገሩት ገልጿል።
በተፈጸመው በዚህ ግድያ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት አንድ መሪጌታና ዲያቆንን ጨምሮ 5 የቤተሰብ አባሎቻቸው በጥይት ተደብድበው መገደላቸው ተገልጿል።
የቴሌቪዥን ጣቢያው ፥ በዶዶላ ከተማ ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም በርካታ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን አስታውሷል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምን አለ ? " ... አንድ ሰው ያወጣው ትልቁ ገንዘብ 304 ሺህ ብር ነው ፤ 567 ደንበኞች ጠፍተዋል፤ የጠፉት ደንበኞች 9.8 ሚሊዮን ብር ነው ያወጡት " - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህም መግለጫቸው ባንኩ አጋጥሞት ከነበረው ችግር ጋር በተያያዘ እስካሁን ስለደረሰበት ደረጃ አብራርተዋል።…
" ... ብዙዎቹ ወላጆቻቸው እንዲከፍሉ ተደርጓል " - ንግድ ባንክ
ዓርብ መጋቢት 6/2016 ዓ/ም ለሊት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የሲስተም ችግር አጋጥሞት በነበረበት ወቅት ገንዘብ ከኤቲኤሞች ሲያወጡ እንዲሁም ሲያዘዋውሩ (ግብይት ሲፈፅሙ) ከነበሩት መካከል 57 በመቶዎቹ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደሆኑ ተነግሯል።
ባንኩ ፥ በ25,761 ደንበኞች ተወስዷል ካለው ከ801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ 622 ሚሊዮን ያህሉን እስካሁን ተመላሽ መደረጉን ገልጿል።
በቀጣይም የሚመለስም እንዳለ ጠቁሟል።
ብር ከወሰዱት እና ካዘዋወሩ / ግብይት ከፈፀሙ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው።
አሁንም በህገወጥ መንገድ ገንዘብ ከወሰዱት መካከል 567ቱ ብሩን እንዳልመለሱ እነዚህም የወሰዱት የገንዘብ መጠንም 9.8 ሚሊዮን ብር እንደሆነ ተመላክቷል።
በዕለቱ መጀመሪያ ገንዘብ #በኤቲኤም (ATM) አውጥተው የሄዱ ቡድኖች በመጠጥ ቤቶች እና ለሌሎች ጥፋቶች ላይ ማዋላቸው ተመላክቷል።
በእንዲህ ያለ መልኩ የወጣ ገንዘብ ለመመለስ አስቸጋሪ ቢሆንም ብዙዎቹ ግን ወላጆቻቸው እንዲከፍሉ ተደርጓል።
መረጃ ስላለ ለወላጆቻቸው እየተደወለ " ልጃችሁ እንዲህ አድርገዋል " እየተባሉ መክፈላቸው ተመላክቷል።
እስከ ባለፈው ቅዳሜ ድረስ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ገንዘብ ያልመለሱ ደንበኞች የስም ዝርዝራቸው በየዲስትሪክቱ ከትላንት ምሽት ጀምሮ መለጠፍ ተጀምሯል ፣ ከዛሬ ጀምሮ ደግሞ በማህበራዊ ሚዲያ ስማቸው ይሰራጫል ተብሏል።
እስካሁን በአንድ ሰው ተወስዶ ያልተመለሰው ከፍተኛ ገንዘብ 304 ሺህ ብር መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
ዓርብ መጋቢት 6/2016 ዓ/ም ለሊት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የሲስተም ችግር አጋጥሞት በነበረበት ወቅት ገንዘብ ከኤቲኤሞች ሲያወጡ እንዲሁም ሲያዘዋውሩ (ግብይት ሲፈፅሙ) ከነበሩት መካከል 57 በመቶዎቹ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደሆኑ ተነግሯል።
ባንኩ ፥ በ25,761 ደንበኞች ተወስዷል ካለው ከ801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ 622 ሚሊዮን ያህሉን እስካሁን ተመላሽ መደረጉን ገልጿል።
በቀጣይም የሚመለስም እንዳለ ጠቁሟል።
ብር ከወሰዱት እና ካዘዋወሩ / ግብይት ከፈፀሙ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው።
አሁንም በህገወጥ መንገድ ገንዘብ ከወሰዱት መካከል 567ቱ ብሩን እንዳልመለሱ እነዚህም የወሰዱት የገንዘብ መጠንም 9.8 ሚሊዮን ብር እንደሆነ ተመላክቷል።
በዕለቱ መጀመሪያ ገንዘብ #በኤቲኤም (ATM) አውጥተው የሄዱ ቡድኖች በመጠጥ ቤቶች እና ለሌሎች ጥፋቶች ላይ ማዋላቸው ተመላክቷል።
በእንዲህ ያለ መልኩ የወጣ ገንዘብ ለመመለስ አስቸጋሪ ቢሆንም ብዙዎቹ ግን ወላጆቻቸው እንዲከፍሉ ተደርጓል።
መረጃ ስላለ ለወላጆቻቸው እየተደወለ " ልጃችሁ እንዲህ አድርገዋል " እየተባሉ መክፈላቸው ተመላክቷል።
እስከ ባለፈው ቅዳሜ ድረስ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ገንዘብ ያልመለሱ ደንበኞች የስም ዝርዝራቸው በየዲስትሪክቱ ከትላንት ምሽት ጀምሮ መለጠፍ ተጀምሯል ፣ ከዛሬ ጀምሮ ደግሞ በማህበራዊ ሚዲያ ስማቸው ይሰራጫል ተብሏል።
እስካሁን በአንድ ሰው ተወስዶ ያልተመለሰው ከፍተኛ ገንዘብ 304 ሺህ ብር መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ... ብዙዎቹ ወላጆቻቸው እንዲከፍሉ ተደርጓል " - ንግድ ባንክ ዓርብ መጋቢት 6/2016 ዓ/ም ለሊት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የሲስተም ችግር አጋጥሞት በነበረበት ወቅት ገንዘብ ከኤቲኤሞች ሲያወጡ እንዲሁም ሲያዘዋውሩ (ግብይት ሲፈፅሙ) ከነበሩት መካከል 57 በመቶዎቹ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደሆኑ ተነግሯል። ባንኩ ፥ በ25,761 ደንበኞች ተወስዷል ካለው ከ801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ 622…
#1
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት ከባንኩ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ወስደው እስካሁን ድረስ ያለመለሱ የ565 ደንበኞቹን ስም ዝርዝር ከአካውንት ቁጥራቸው ጋር ይፋ አደርጓል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት ከባንኩ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ወስደው እስካሁን ድረስ ያለመለሱ የ565 ደንበኞቹን ስም ዝርዝር ከአካውንት ቁጥራቸው ጋር ይፋ አደርጓል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#1 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት ከባንኩ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ወስደው እስካሁን ድረስ ያለመለሱ የ565 ደንበኞቹን ስም ዝርዝር ከአካውንት ቁጥራቸው ጋር ይፋ አደርጓል። @tikvahethiopia
#2
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት ከባንኩ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ወስደው እስካሁን ድረስ ያለመለሱ የ565 ደንበኞቹን ስም ዝርዝር ከአካውንት ቁጥራቸው ጋር ይፋ አደርጓል።
ባንኩ ፥ ግለሰቦቹ የወሰዱትን ገንዘብ ካልመለሱ በቀጣይ በህግ እንደሚጠይቃቸው በጥብቅ አስጠንቅቋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት ከባንኩ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ወስደው እስካሁን ድረስ ያለመለሱ የ565 ደንበኞቹን ስም ዝርዝር ከአካውንት ቁጥራቸው ጋር ይፋ አደርጓል።
ባንኩ ፥ ግለሰቦቹ የወሰዱትን ገንዘብ ካልመለሱ በቀጣይ በህግ እንደሚጠይቃቸው በጥብቅ አስጠንቅቋል።
@tikvahethiopia