#Wolkite
ለአመታት በውሃ ችግር የሚፈተነው የወልቂጤ ከተማ ህዝብ ዛሬም " የመንግስት ያለህ " እያለ ነዉ።
ችግሩን ለመፍታት ጥረት ላይ እየተደረገ ነዉ የሚለው የከተማው አስተዳደር በበኩሉ " ሩጫ ላይ ነኝ " ይላል።
የከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች የውሀ ጀሪካኖች በጫኑ ባጃጆችና ጋሪዎች ተሞልተዉ ይታያሉ። ሆቴሎች የሻወር አገልግሎትን ከረሱ የቆዩ ይመስላሉ።
በአጠቃላይ ውሀ ቅንጦት መሆኑ ግለጽ ነዉ ይህን ጉዳይ ተመልክቶ የአካባቢዉን ማህበረሰብ ስለጉዳዩ የጠየቀዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ችግሩ ለአመታት የቀጠለ መሆኑን ተረድቷል።
እንደነዋሪዎቹ ገለጻ የቧንቧ ውሀ በወር አንዴ በጣም ፈጠነ ሲባል በሁለት ሳምንት አንዴ ያውም ለሰአታት ብትመጣም አንዳንዴ የምትመጣዉ ሌሊት ሲሆን እንደምታመልጣቸዉ ይገልጻሉ።
ለሽንኩርትና ቲማቲም ከሚያወጡት እኩል ለውሀ ግዥ እንደሚያወጡ የሚገልጹት ነዋሪዎቹ መንግስት ችግራቸዉን ይቀርፍላቸዉ ዘንድ በምሬት ይጠይቃሉ።
በዚህ ጉዳይ ላይ ጠንካራ ጥያቄ ከሰሞኑ በነበረ የምክር ቤት ጉባኤ የቀረበለት የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በበኩሉ የውሀ ችግሮች ያለመፈታታቸዉ ምክኒያት በየዞንና ከተሞች የተጀመሩ የውሀ ጉድጓድ ፕሮጀክቶች እየተጀመሩ በመቆማቸዉ የተከሰተ መሆኑን ገልጾ የማህበረሰቡን ጥያቄ ለመመለስ በሙሉ ሀይሉ እንደሚሰራ ገልጾ ነበር።
ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ የህዝብ ጥያቄ የቀረበላቸዉ የወልቂጤ ከተማ የውሀና ፍሳሽ አገልግሎት ቢሮ ሀላፊዉ አቶ ዳዊት ሀይሌ በበኩላቸዉ ችግሩ መኖሩን በመግለጽ አሁን ላይ የቅሀ አጥረቱ ከተማዉን እየፈተነ መሆኑና ችግሩን ለመቅረፍ የተጀመሩ ስራዎች እንዳሉና ከሚጠበቁ መፍትሄዎች አንዱ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ስራው ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ዳዊት አክለዉም ፤ በቅርቡ የጉራጌ ዞን የውሀና መአድን ቢሮ ጋር በመሆን ሁኔታዎች እንደሚገመገሙና ለህዝብ አስፈላጊዉ መረጃ እንደሚሰጥ በመግለጽ ሁኔታዉን ከከተማዉ ባለስልጣናት ባለፈ የዞኑም ሆነ የበላይ አካላት በትኩረት እየሰሩበት መሆኑን ጠቁመዋል።
መረጃው ወደ ወልቂጤ ተጉዞ የነበረው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው አዘጋጅቶ የላከው።
ፎቶ ፦ Tikvah Family
@tikvahethiopia
ለአመታት በውሃ ችግር የሚፈተነው የወልቂጤ ከተማ ህዝብ ዛሬም " የመንግስት ያለህ " እያለ ነዉ።
ችግሩን ለመፍታት ጥረት ላይ እየተደረገ ነዉ የሚለው የከተማው አስተዳደር በበኩሉ " ሩጫ ላይ ነኝ " ይላል።
የከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች የውሀ ጀሪካኖች በጫኑ ባጃጆችና ጋሪዎች ተሞልተዉ ይታያሉ። ሆቴሎች የሻወር አገልግሎትን ከረሱ የቆዩ ይመስላሉ።
በአጠቃላይ ውሀ ቅንጦት መሆኑ ግለጽ ነዉ ይህን ጉዳይ ተመልክቶ የአካባቢዉን ማህበረሰብ ስለጉዳዩ የጠየቀዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ችግሩ ለአመታት የቀጠለ መሆኑን ተረድቷል።
እንደነዋሪዎቹ ገለጻ የቧንቧ ውሀ በወር አንዴ በጣም ፈጠነ ሲባል በሁለት ሳምንት አንዴ ያውም ለሰአታት ብትመጣም አንዳንዴ የምትመጣዉ ሌሊት ሲሆን እንደምታመልጣቸዉ ይገልጻሉ።
ለሽንኩርትና ቲማቲም ከሚያወጡት እኩል ለውሀ ግዥ እንደሚያወጡ የሚገልጹት ነዋሪዎቹ መንግስት ችግራቸዉን ይቀርፍላቸዉ ዘንድ በምሬት ይጠይቃሉ።
በዚህ ጉዳይ ላይ ጠንካራ ጥያቄ ከሰሞኑ በነበረ የምክር ቤት ጉባኤ የቀረበለት የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በበኩሉ የውሀ ችግሮች ያለመፈታታቸዉ ምክኒያት በየዞንና ከተሞች የተጀመሩ የውሀ ጉድጓድ ፕሮጀክቶች እየተጀመሩ በመቆማቸዉ የተከሰተ መሆኑን ገልጾ የማህበረሰቡን ጥያቄ ለመመለስ በሙሉ ሀይሉ እንደሚሰራ ገልጾ ነበር።
ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ የህዝብ ጥያቄ የቀረበላቸዉ የወልቂጤ ከተማ የውሀና ፍሳሽ አገልግሎት ቢሮ ሀላፊዉ አቶ ዳዊት ሀይሌ በበኩላቸዉ ችግሩ መኖሩን በመግለጽ አሁን ላይ የቅሀ አጥረቱ ከተማዉን እየፈተነ መሆኑና ችግሩን ለመቅረፍ የተጀመሩ ስራዎች እንዳሉና ከሚጠበቁ መፍትሄዎች አንዱ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ስራው ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ዳዊት አክለዉም ፤ በቅርቡ የጉራጌ ዞን የውሀና መአድን ቢሮ ጋር በመሆን ሁኔታዎች እንደሚገመገሙና ለህዝብ አስፈላጊዉ መረጃ እንደሚሰጥ በመግለጽ ሁኔታዉን ከከተማዉ ባለስልጣናት ባለፈ የዞኑም ሆነ የበላይ አካላት በትኩረት እየሰሩበት መሆኑን ጠቁመዋል።
መረጃው ወደ ወልቂጤ ተጉዞ የነበረው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው አዘጋጅቶ የላከው።
ፎቶ ፦ Tikvah Family
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
የደብረ ብርሃን 2 - ሸዋ ሮቢት - ኮምቦልቻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ ማምሻውን ሥራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል።
በሸዋ ሮቢት አቅራቢያ ጉዳት ደርሶበት የነበረው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገኑ ካለፈው እሁድ ጀምሮ ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ የአፋር መዲና ሠመራን ጨምሮ በሰሜን ምሥራቅ የሚገኙ ከተሞች ዳግም ኃይል አግኝተዋል ብሏል።
በአሁኑ ሰዓት ኤሌክትሪክ ተቋርጦባቸው የቆዩት ሁሉም የሰሜን ምሥራቅ ከተሞች ኤሌክትሪክ ዳግም አግኝተዋል ተብሏል።
@tikvahethiopia
የደብረ ብርሃን 2 - ሸዋ ሮቢት - ኮምቦልቻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ ማምሻውን ሥራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል።
በሸዋ ሮቢት አቅራቢያ ጉዳት ደርሶበት የነበረው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገኑ ካለፈው እሁድ ጀምሮ ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ የአፋር መዲና ሠመራን ጨምሮ በሰሜን ምሥራቅ የሚገኙ ከተሞች ዳግም ኃይል አግኝተዋል ብሏል።
በአሁኑ ሰዓት ኤሌክትሪክ ተቋርጦባቸው የቆዩት ሁሉም የሰሜን ምሥራቅ ከተሞች ኤሌክትሪክ ዳግም አግኝተዋል ተብሏል።
@tikvahethiopia
በዲጂታል እና ፋይናንሻል አካታችነት ሴቶችን ማብቃት!
ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል ስርዓተ-ፆታ ልዩነትን ለማጥበብ እና የሴቶችን የዲጂታል ተካታችነት ለማሳደግ የሚያስችል ስምምነት “Connected Women” ኢኒሼቲቭ- ከ GSMA ጋር በባርሴሎና ስፔን ተፈራርሟል::
ስምምነቱ በሀገራችን የሴቶችን የሞባይል ኢንተርኔት እና የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት /ቴሌብር/ ተጠቃሚ ቁጥር እ.ኤ.አ እስከ 2026 በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ ያለመ ሲሆን ኩባንያው ለተግባራዊነቱ የተለያዩ ስትራቴጂዎችን በመንደፍ እና በመተግበር እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሴቶች የሚያጋጥሟቸውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መፍታት ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት አካታች የሞባይል ኢንተርኔት እና የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ማቅረብን ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡
በስምምነቱ ወቅት የኩባንያው ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ “ሴቶች በሀገራችን ልማት ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ፡፡ ኩባንያችን አሁን የሚታየውን የዲጂታል ስርዓተ-ፆታ ክፍተት ለማጥበብ የሞባይል ኢንተርኔትና የሞባይል ፋይናንሺያል አገልግሎቶችን ለሴቶች ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ሴቶች በዲጂታል ኢኮኖሚው ንቁ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል፡፡” ብለዋል፡፡
#DigitalEthiopia #DigitalAfrica #DigitalEconomy #EthiopianCommunicationAuthority #GSMA #AU #ITU #WorldBank #OECD #G6countries #SmartAfrica #HOPR #HOF
ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል ስርዓተ-ፆታ ልዩነትን ለማጥበብ እና የሴቶችን የዲጂታል ተካታችነት ለማሳደግ የሚያስችል ስምምነት “Connected Women” ኢኒሼቲቭ- ከ GSMA ጋር በባርሴሎና ስፔን ተፈራርሟል::
ስምምነቱ በሀገራችን የሴቶችን የሞባይል ኢንተርኔት እና የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት /ቴሌብር/ ተጠቃሚ ቁጥር እ.ኤ.አ እስከ 2026 በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ ያለመ ሲሆን ኩባንያው ለተግባራዊነቱ የተለያዩ ስትራቴጂዎችን በመንደፍ እና በመተግበር እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሴቶች የሚያጋጥሟቸውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መፍታት ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት አካታች የሞባይል ኢንተርኔት እና የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ማቅረብን ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡
በስምምነቱ ወቅት የኩባንያው ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ “ሴቶች በሀገራችን ልማት ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ፡፡ ኩባንያችን አሁን የሚታየውን የዲጂታል ስርዓተ-ፆታ ክፍተት ለማጥበብ የሞባይል ኢንተርኔትና የሞባይል ፋይናንሺያል አገልግሎቶችን ለሴቶች ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ሴቶች በዲጂታል ኢኮኖሚው ንቁ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል፡፡” ብለዋል፡፡
#DigitalEthiopia #DigitalAfrica #DigitalEconomy #EthiopianCommunicationAuthority #GSMA #AU #ITU #WorldBank #OECD #G6countries #SmartAfrica #HOPR #HOF
መልካም የሴቶች ቀን!
እርስዎ ዛሬ አድንቆታችሁን እንዲያውቁላችሁ የምትፈልጉትን ሴቶች ታግ ያድርጓቸው።
የሀገራችን ምርጥ ተዋናይቶች በአቦል ቲቪ ቻናል ቁጥር 465 ይከታተሉ!
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
እርስዎ ዛሬ አድንቆታችሁን እንዲያውቁላችሁ የምትፈልጉትን ሴቶች ታግ ያድርጓቸው።
የሀገራችን ምርጥ ተዋናይቶች በአቦል ቲቪ ቻናል ቁጥር 465 ይከታተሉ!
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
#Amhara
“ ወደ 1.8 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የዕለት ምግብ ይፈልጋሉ ” - አማራ ክልል
የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙት ኃላፊ ወ/ሮ ፍቅሬ ሙሉጌታ፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ በክልሉ “ በአጠቃላይ ወደ 1.8 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የዕለት ምግብ ይፈልጋሉ ” ብለዋል።
“ በአማራ ክልል በ2015/16 የምርት ዘመንን ተከትሎ የዝናብ መቆራረጥ ተከስቷል። በተለይ ደግሞ ተከዜ ተፋሰስ የሚያዋስናቸው ወረዳዎችና ዞኖች ድርቅ ተከስቶባቸል” ሲሉም አስረድተዋል።
* “ዘጠኝ ዞኖች
* 43 ወረዳዎች
* 429 ቀበሌዎች ላይ ተጋላጭ ሆነዋል ለድርቅ ” ነው ያሉት ኃላፊዋ።
በገለጻው መሠረት፣ “ከተጎዱት ዘጠኝ ዞኖች ውስጥ በተለይ ደግሞ በጣም ተጋላጭ የሆኑት ከሰሜን ጎንደር 3 ወረዳዎች፣ ከዋግኽምራ ብሔረሰብ 3 ወረዳዎች በብዛት ተጋላጭ ሆነዋል በድርቁ። " ብለዋል።
“ የድርቅ መከሰትን ተከትሎ የዕለት የምግብ ምላሽ ለመስጠት የክልሉ መንግስት ከመጠባበቂያ በጀት መድቧል ” ያሉት ወ/ሮ ፍቅሬ፣ “ወደ 430 ሚሊዮን ብር የክልሉ መንግሥት ፈቅዷል የዕለት ምግብ የሚገዛበት። ከዚህ ውስጥ ወደ 300 ሚሊዮን ብር የምግብ እህል ተገዝቷል። ስርጭትም ተከናውኗል” ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም፣ “ከዚህ ባሻገር ደግሞ የተለያዩ በጎ አድራጊ ግለሰቦች፣ መግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ልዩ ልዩ ተቋማት እንደዚሁ ባገኙት መረጃ መሠረት በተለያየ ጊዜ የምግብ እህል እየገዙ እያጓጓዙ እያቀረቡ ነው” ብለዋል።
ድርቅ ከተጋረጠባቸው ወገኖች ባሻገር በክልሉ መጠለያዎች ጣቢያዎች፣ ከህብረተሰቡ ጋር የሚኖሩ ተፈናቃዮች እንዳሉ የገለጹት ኃላፊዋ፣ “ላለፉት 2 ዓመታት የሰሜኑ ጦርነት ነበረ አሁንም የፀጥታ ችግር አለ በክልሉ። እነዚህ ጉዳዩች ተደራራቢ ችግር እንዳለ ያሳያን። ይህን መሰረት በማድረግ ስራዎች እየተሰሩ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
በክልሉ ያለው የጸጥታ ችግር አለ ለስራዎች እንቅፋት እየሆነ መሆኑን አመልክተዋል።
“የፀጥታው ችግር የዕለት ምግብ ለማድረስ በትራንስፖርት ለመንቀሳቀስ ችግር ፈጥሮብን ቆይቷል። በቀጣይም ተደራራቢ ችግሮች ናቸው። እነዚህ ተደራራቢ ችግሮች ህብረተሰቡ ችግር ላይ እንዳይወድቅ የሚላኩት የድጋፍ እህሎች በወቅቱ ሊደርሱ ይገባልና በየአካባቢው የሚጓጓዙት ትራንስፖቴሽኖችን ሊተባበሯቸው ይገባል ” ሲሉ አሳስበዋል።
መረጃው ተዘጋጅቶ የተላከው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
“ ወደ 1.8 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የዕለት ምግብ ይፈልጋሉ ” - አማራ ክልል
የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙት ኃላፊ ወ/ሮ ፍቅሬ ሙሉጌታ፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ በክልሉ “ በአጠቃላይ ወደ 1.8 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የዕለት ምግብ ይፈልጋሉ ” ብለዋል።
“ በአማራ ክልል በ2015/16 የምርት ዘመንን ተከትሎ የዝናብ መቆራረጥ ተከስቷል። በተለይ ደግሞ ተከዜ ተፋሰስ የሚያዋስናቸው ወረዳዎችና ዞኖች ድርቅ ተከስቶባቸል” ሲሉም አስረድተዋል።
* “ዘጠኝ ዞኖች
* 43 ወረዳዎች
* 429 ቀበሌዎች ላይ ተጋላጭ ሆነዋል ለድርቅ ” ነው ያሉት ኃላፊዋ።
በገለጻው መሠረት፣ “ከተጎዱት ዘጠኝ ዞኖች ውስጥ በተለይ ደግሞ በጣም ተጋላጭ የሆኑት ከሰሜን ጎንደር 3 ወረዳዎች፣ ከዋግኽምራ ብሔረሰብ 3 ወረዳዎች በብዛት ተጋላጭ ሆነዋል በድርቁ። " ብለዋል።
“ የድርቅ መከሰትን ተከትሎ የዕለት የምግብ ምላሽ ለመስጠት የክልሉ መንግስት ከመጠባበቂያ በጀት መድቧል ” ያሉት ወ/ሮ ፍቅሬ፣ “ወደ 430 ሚሊዮን ብር የክልሉ መንግሥት ፈቅዷል የዕለት ምግብ የሚገዛበት። ከዚህ ውስጥ ወደ 300 ሚሊዮን ብር የምግብ እህል ተገዝቷል። ስርጭትም ተከናውኗል” ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም፣ “ከዚህ ባሻገር ደግሞ የተለያዩ በጎ አድራጊ ግለሰቦች፣ መግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ልዩ ልዩ ተቋማት እንደዚሁ ባገኙት መረጃ መሠረት በተለያየ ጊዜ የምግብ እህል እየገዙ እያጓጓዙ እያቀረቡ ነው” ብለዋል።
ድርቅ ከተጋረጠባቸው ወገኖች ባሻገር በክልሉ መጠለያዎች ጣቢያዎች፣ ከህብረተሰቡ ጋር የሚኖሩ ተፈናቃዮች እንዳሉ የገለጹት ኃላፊዋ፣ “ላለፉት 2 ዓመታት የሰሜኑ ጦርነት ነበረ አሁንም የፀጥታ ችግር አለ በክልሉ። እነዚህ ጉዳዩች ተደራራቢ ችግር እንዳለ ያሳያን። ይህን መሰረት በማድረግ ስራዎች እየተሰሩ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
በክልሉ ያለው የጸጥታ ችግር አለ ለስራዎች እንቅፋት እየሆነ መሆኑን አመልክተዋል።
“የፀጥታው ችግር የዕለት ምግብ ለማድረስ በትራንስፖርት ለመንቀሳቀስ ችግር ፈጥሮብን ቆይቷል። በቀጣይም ተደራራቢ ችግሮች ናቸው። እነዚህ ተደራራቢ ችግሮች ህብረተሰቡ ችግር ላይ እንዳይወድቅ የሚላኩት የድጋፍ እህሎች በወቅቱ ሊደርሱ ይገባልና በየአካባቢው የሚጓጓዙት ትራንስፖቴሽኖችን ሊተባበሯቸው ይገባል ” ሲሉ አሳስበዋል።
መረጃው ተዘጋጅቶ የተላከው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
" በትግራይ ከተሞች የሚታየው የፀጥታ ስጋት ልዩ ትኩረት ያሻዋል " - ነዋሪዎች
በሳምንት ውስጥ 2 ወጣቶች ተገድለዋል ፤ ገዳዮቹ አስከ አሁን አልተያዙም።
በመቐለ ከተማ በሳምንት ውስጥ 2 ወጣቶች " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ ሰዎች መገደላቸውን የመቐለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የላከው መረጃ ያሳያል።
ሟቾች በክልሉ ጦርነት በነበረበት ወቅት በትጥቅ ትግል ተሳታፊ የነበሩ ናቸው ተብሏል።
ወጣት በሪሁ ኪዱ ባለፈው ሳምንት ሌሊት ላይ ተገድሎ መንገድ ላይ ተጥሎ የተገኘ ሲሆን ፤ ወጣት ሃይሉሽ መሰረት ደግሞ የካቲት 28 /2016 ዓ.ም ሌሊት በመዝናኛ ቦታ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ ሰዎች #በቢላዋ ተወግቶ ተገዷል።
ቃላቸውን የሰጡ የመቐለ ነዋሪዎች ፤ ገዳዮቹ አለመያዛቸው እጅግ እንዳሳሰባቸው ገልጸው በትግራይ ከተሞች የሚታየው የፀጥታ ስጋት ልዩ ትኩረት ያሻዋል ብለዋል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የመቐለው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
በሳምንት ውስጥ 2 ወጣቶች ተገድለዋል ፤ ገዳዮቹ አስከ አሁን አልተያዙም።
በመቐለ ከተማ በሳምንት ውስጥ 2 ወጣቶች " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ ሰዎች መገደላቸውን የመቐለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የላከው መረጃ ያሳያል።
ሟቾች በክልሉ ጦርነት በነበረበት ወቅት በትጥቅ ትግል ተሳታፊ የነበሩ ናቸው ተብሏል።
ወጣት በሪሁ ኪዱ ባለፈው ሳምንት ሌሊት ላይ ተገድሎ መንገድ ላይ ተጥሎ የተገኘ ሲሆን ፤ ወጣት ሃይሉሽ መሰረት ደግሞ የካቲት 28 /2016 ዓ.ም ሌሊት በመዝናኛ ቦታ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ ሰዎች #በቢላዋ ተወግቶ ተገዷል።
ቃላቸውን የሰጡ የመቐለ ነዋሪዎች ፤ ገዳዮቹ አለመያዛቸው እጅግ እንዳሳሰባቸው ገልጸው በትግራይ ከተሞች የሚታየው የፀጥታ ስጋት ልዩ ትኩረት ያሻዋል ብለዋል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የመቐለው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
" አሸናፊዎች ባለመቅረባቸው ገንዘቡ ወደ ተቋሙ ገብቷል " - ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር
እያንዳንዳቸው 4 ሚሊዮን ብር ዕጣ ያላቸው ሁለት የሎተሪ ቲኬቶች አሸናፊዎች ባለመቅረባቸው ስምንት ሚሊዮን ብር ዛሬ የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ተመላሽ መደረጉን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር አስታውቋል።
ተቋሙ ለቢቢሲ አማርኛው ክፍል በሰጠው ቃል ፤ እነዚህ ሁለት ዕጣዎች ብሔራዊ ሎተሪ ከሚያሳትማቸው ከፍተኛ ዕጣ የሆነው 20 ሚሊዮን ብር የሚያስገኘው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ቲኬቶች ናቸው ብሏል።
በእንቁጣጣሽ ሎተሪ ከቀረቡት 5 ቲኬቶች ሶስቱ ቀርበው 12 ሚሊዮን ብር ሁለት አሸናፊዎች ቢረከቡም የቀሪዎቹ ሁለት ቲኬቶች አሸናፊዎች ባለመቅረባቸው ገንዘቡ ወደ ተቋሙ ገብቷል ሲል አሳውቋል።
ጳጉሜ 2015 ዓ.ም የወጣው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ የሁለቱ ቲኬቶች ወይም የ8 ሚሊዮን ብር አሸናፊ በቀን ስራ የሚተዳደር አንድ ግለሰብ ሲሆን ዕጣው ከወጣ ከ3 ወር በኋላም ወስዷል።
ሌላኛው አሸናፊ የቀን ሰራተኛው የሚሰራበት መኪና አሽከርካሪ የሆነ ግለሰብ ሲሆን መስከረም ወር መጨረሻ ላይ መጥቶ የ4 ሚሊዮን ብር ሽልማቱን መውሰዱን ቢቢሲ አማርኛው ክፍል የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደርን ዋቢ በማድረግ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
እያንዳንዳቸው 4 ሚሊዮን ብር ዕጣ ያላቸው ሁለት የሎተሪ ቲኬቶች አሸናፊዎች ባለመቅረባቸው ስምንት ሚሊዮን ብር ዛሬ የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ተመላሽ መደረጉን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር አስታውቋል።
ተቋሙ ለቢቢሲ አማርኛው ክፍል በሰጠው ቃል ፤ እነዚህ ሁለት ዕጣዎች ብሔራዊ ሎተሪ ከሚያሳትማቸው ከፍተኛ ዕጣ የሆነው 20 ሚሊዮን ብር የሚያስገኘው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ቲኬቶች ናቸው ብሏል።
በእንቁጣጣሽ ሎተሪ ከቀረቡት 5 ቲኬቶች ሶስቱ ቀርበው 12 ሚሊዮን ብር ሁለት አሸናፊዎች ቢረከቡም የቀሪዎቹ ሁለት ቲኬቶች አሸናፊዎች ባለመቅረባቸው ገንዘቡ ወደ ተቋሙ ገብቷል ሲል አሳውቋል።
ጳጉሜ 2015 ዓ.ም የወጣው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ የሁለቱ ቲኬቶች ወይም የ8 ሚሊዮን ብር አሸናፊ በቀን ስራ የሚተዳደር አንድ ግለሰብ ሲሆን ዕጣው ከወጣ ከ3 ወር በኋላም ወስዷል።
ሌላኛው አሸናፊ የቀን ሰራተኛው የሚሰራበት መኪና አሽከርካሪ የሆነ ግለሰብ ሲሆን መስከረም ወር መጨረሻ ላይ መጥቶ የ4 ሚሊዮን ብር ሽልማቱን መውሰዱን ቢቢሲ አማርኛው ክፍል የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደርን ዋቢ በማድረግ አስነብቧል።
@tikvahethiopia