TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ ሰለሞን ባረጋ ለኢትዮጵያ የነሃስ ሜዳሊያ አምጥቷል። በግላስኮ ዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በወንዶች 3 ሺህ ሜትር ኢትዮጵያ በአትሌት ሰለሞን ባረጋ አማካኝነት የነሃስ ሜዳሊያ ማግኘት ችላለች። ጌትነት ዋለ 4ኛ ወጥቷል። ኢትዮጵያ በዚህ ርቀት በዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ላይ የወርቅ ሜዳሊያ ሳታሸንፍ ስትቀር ከ3 ተከታታይ ውድድሮች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ሰለሞን ባረጋ…
#ኢትዮጵያ❤
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 1ኛ ሆና አጠናቀቀች።
በዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም ደግሞ 5 በመሆን አጠናቃለች።
ከማርች 1-3/2024 በእንግሊዝ ግላስጎ ሲካሄድ የ19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሲካሄድ ነበር። በሻምፒዮናው ከ130 በላይ አገሮች የተውጣጡ ከ650 በላይ አትሌቶቸ ተሳትፈዋል።
ሀገራችን ኢትዮጵያ በ800 ሜትር፣ በ1500 ሜትር እና በ3000 ሜትር በሴትና በወንድ በአጠቃላይ በ8 ሴቶች እና በ5 ወንዶች በድምሩ በ13 አትሌቶች ተሳትፋለች።
በዚህም #በሴቶች 800 ሜትር ፅጌ ዱጉማ እና በሴቶች 1500 ሜትር ፍሬወይኒ ሀይሉ #የወርቅ፣ በሴቶች 3000 ሜትር ጉዳፍ ፀጋይ የብር እንዲሁም #በወንዶች 3000 ሜትር ሰለሞን ባረጋ የነሃስ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል።
ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ በሁለት ወርቅ አንድ ነሀስ በአንድ ብር በአጠቃላይ በአራት ሜዳሊያዎች በሜዳልያ ሰንጠረዡ ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም 5ኛ ደረጃን በመያዝ ጨርሳለች።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 1ኛ ሆና አጠናቀቀች።
በዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም ደግሞ 5 በመሆን አጠናቃለች።
ከማርች 1-3/2024 በእንግሊዝ ግላስጎ ሲካሄድ የ19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሲካሄድ ነበር። በሻምፒዮናው ከ130 በላይ አገሮች የተውጣጡ ከ650 በላይ አትሌቶቸ ተሳትፈዋል።
ሀገራችን ኢትዮጵያ በ800 ሜትር፣ በ1500 ሜትር እና በ3000 ሜትር በሴትና በወንድ በአጠቃላይ በ8 ሴቶች እና በ5 ወንዶች በድምሩ በ13 አትሌቶች ተሳትፋለች።
በዚህም #በሴቶች 800 ሜትር ፅጌ ዱጉማ እና በሴቶች 1500 ሜትር ፍሬወይኒ ሀይሉ #የወርቅ፣ በሴቶች 3000 ሜትር ጉዳፍ ፀጋይ የብር እንዲሁም #በወንዶች 3000 ሜትር ሰለሞን ባረጋ የነሃስ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል።
ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ በሁለት ወርቅ አንድ ነሀስ በአንድ ብር በአጠቃላይ በአራት ሜዳሊያዎች በሜዳልያ ሰንጠረዡ ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም 5ኛ ደረጃን በመያዝ ጨርሳለች።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
@tikvahethiopia
#ቅሬታ
የፓስፖርት ጉዳይ ...
ከፓስፖርት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ወገኖች አሰፈላጊው ማስተካከያ እንዲደረግ አሳሰቡ።
" የተሰራ ፓስፖርት ለመስጠት ህዝቡ እጅግ በጣም ዘግናኝ በሆነ መልኩ እየተንገላታ ይገኛል። " ያሉት ለቲክቫህ መልዕክታቸውን ያደረሱ ወገኖች ፤ በቀን የሚሰጠው ፓስፖርት ውስን ነው ብለዋል።
" በቀኑ ስለማይሰጥም ባስቀመጡት ቀን ተገልጋዩ እየተመላለሰ መከራ እየበላ ነው። " ሲሉ ሁኔታውን ገልጸውታል።
በተለይ ጎተራ አካባቢ ሌሊት ወረፋ ለመያዝ ብር የሚጠይቁ እንዳሉ ፤ አንዳንዱ ከፍሎ ወረፋ እንደሚይዝ የሌለው ደግሞ ሌሊት ሂዶ ከገባ በኋላ ሰልፋን ይበትኑና ቀኑን ሙሉ በህዝብ ሲጫወቱ ውለው 10 ሰዓት ላይ በዱላ ደብድበው እንደሚያስወጡ በምሬት ገልጸዋል።
" በቀጣዩ ሳምንትም እንደዛው። " ሲሉ አክለዋል።
" የብዙ ሰው ቪዛ እየተቃጠለበት ለብዙ ወጪ እየተዳረገ " መሆኑን የሚገልፁት እነዚህ ወገኖች " በየወረዳው ቢበትኑ እንዲሁ። በፊደል ተራ በተለቀቀበት ቀን ቢሰጡ/they mix it/ ጥሩ ነው። የህዝብ እንግልት ግድ የሚሰጠው ካለ መፍትሄ ይፈልግ !! " ሲሉ አሳስበዋል።
@tikvahethiopia
የፓስፖርት ጉዳይ ...
ከፓስፖርት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ወገኖች አሰፈላጊው ማስተካከያ እንዲደረግ አሳሰቡ።
" የተሰራ ፓስፖርት ለመስጠት ህዝቡ እጅግ በጣም ዘግናኝ በሆነ መልኩ እየተንገላታ ይገኛል። " ያሉት ለቲክቫህ መልዕክታቸውን ያደረሱ ወገኖች ፤ በቀን የሚሰጠው ፓስፖርት ውስን ነው ብለዋል።
" በቀኑ ስለማይሰጥም ባስቀመጡት ቀን ተገልጋዩ እየተመላለሰ መከራ እየበላ ነው። " ሲሉ ሁኔታውን ገልጸውታል።
በተለይ ጎተራ አካባቢ ሌሊት ወረፋ ለመያዝ ብር የሚጠይቁ እንዳሉ ፤ አንዳንዱ ከፍሎ ወረፋ እንደሚይዝ የሌለው ደግሞ ሌሊት ሂዶ ከገባ በኋላ ሰልፋን ይበትኑና ቀኑን ሙሉ በህዝብ ሲጫወቱ ውለው 10 ሰዓት ላይ በዱላ ደብድበው እንደሚያስወጡ በምሬት ገልጸዋል።
" በቀጣዩ ሳምንትም እንደዛው። " ሲሉ አክለዋል።
" የብዙ ሰው ቪዛ እየተቃጠለበት ለብዙ ወጪ እየተዳረገ " መሆኑን የሚገልፁት እነዚህ ወገኖች " በየወረዳው ቢበትኑ እንዲሁ። በፊደል ተራ በተለቀቀበት ቀን ቢሰጡ/they mix it/ ጥሩ ነው። የህዝብ እንግልት ግድ የሚሰጠው ካለ መፍትሄ ይፈልግ !! " ሲሉ አሳስበዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቅሬታ የፓስፖርት ጉዳይ ... ከፓስፖርት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ወገኖች አሰፈላጊው ማስተካከያ እንዲደረግ አሳሰቡ። " የተሰራ ፓስፖርት ለመስጠት ህዝቡ እጅግ በጣም ዘግናኝ በሆነ መልኩ እየተንገላታ ይገኛል። " ያሉት ለቲክቫህ መልዕክታቸውን ያደረሱ ወገኖች ፤ በቀን የሚሰጠው ፓስፖርት ውስን ነው ብለዋል። " በቀኑ ስለማይሰጥም ባስቀመጡት ቀን ተገልጋዩ እየተመላለሰ መከራ እየበላ…
#ፓስፖርት
ፓስፖርት ፈልገው/ በሥራ ምክንያት ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጎራ ካሉ ረዥም ሰልፍ እና መጨናነቅ ማየት የተለመደ ነው።
የሰልፍ አሰላፊዎች ዱላም ሊያጋጥም ይችላል።
ወጣት፣ሴት፣ወንድ፣ልጅ ያዘሉ እናቶች እንዲሁም " ፓስፖርት ፈልገው ነው ? " እያሉ እግር በእግር የሚከተሉ ሕገወጥ ደላሎችም በአካባቢው ውር ውር ይላሉ።
አገልግሎቱ 24 ሰዓት የፓስፖርት ህትመትና በበይነ መረብ ምዝገባ አሠራር ዘርግቻለሁ ቢልም አሁንም በርካታ ተገልጋዮችን አገልግሎቱ ደጃፍ ላይ መመልከት አልቀረም።
ተገልጋዮች ዐሻራ ለመስጠት እና ፎቶ ለመነሳት በመ/ቤቱ መገኘት ግዴታቸው በመሆኑ ከተለያዩ አካባቢዎች መጥተው በወረፋው ምክንያት ላልተፈለገ እንግልት ይዳረጋሉ።
እንግልቱ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ከእንቅልፍ ተነስቶ ረዥም ሰልፍ ከመሰለፍ ይጀምራል።
በሌቦች መዘረፍም የሚያጋጥም ክስተት መሆኑን ተገልጋዮች በምሬት ይናገራሉ።
ለአላስፈላጊ እንግልት እና ወጪ ተዳርገናል የሚሉ ተገልጋዮች ሃሳባቸውን አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት በበይነ መረብ አማካኝነት ከተመዘገቡ ወራት እንዳለፋቸው ይገልጻሉ።
ተገልጋዮቹ አገልግሎቱ አካባቢ ወረፋ ለመያዝ ስንሞክር " እኔ ቅድሚያ ወረፋ ልያዝላችሁ ክፈሉኝ " በሚሉ ደላሎች እንዋከባለን ይላሉ።
እነሱ እንደሚሉት የመሥሪያ ቤቱን ሰልፍ አሰላፊዎች ወከባና ዱላ አልፎ ውስጥ መግባት መቻል መታደል ነው።
ተገልጋዮቹ በሌሊት ለመነሳት ሲሉ በአካባቢው ለአልጋ ኪራይ ከፍለው እንደሚያድሩና ለአላስፈላጊ ወጪም እንደሚዳረጉም ይገልጻሉ።
ሰልፉ ረዝሞ ወረፋ ሳይደርሳቸው ከቀረም ቅጣት እንደማይቀርላቸው ይናገራሉ።
በርካታ አገልግሎት ፈላጊ ሕዝብ በተገቢው መንገድ ከማስተናገድ ይልቅ በዱላ በመደብደብ ሥርዓት ለማስያዝ ሲሞከር ይታያል። ወደ መግቢያ በሩ ተጠግቶ መረጃ ማግኘት የማይታሰብ ነው።
የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱ ተስተካክሏል ይባል እንጂ አሁንም ችግሮቹ እንደነበሩ ናቸው ይላሉ ተገልጋዮች።
የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱ ሳይዘምን እንደዘመነ አድርጎ ማስተዋወቅም ፍጹም ተገቢነት እንደሌለውና ሕዝብ በለውጥ እንዳያምን እንደሚያደርግም ያስገነዝባሉ።
ሰሞኑን የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱን ለመመልከት በመ/ቤቱ የተገኙት የኢፕድ ጋዜጠኞች መረጃ ለመሰብሰብ ያደረጉት ሙከራ በፖሊሶች ክልከላ ተደርጎበታል።
የተቋሙ ኮሙኒኬሽን ዳሬክተር ወ/ሮ ማስተዋል ገዳ ምን ምላሽ ሰጡ ?
- ተገልጋዮች ወደ ተቋሙ በሚመጡበት ወቅት በክብር መስተናገድ እንዳለባቸው እናውቃለን። ተገልጋዮችን በአግባቡ ባለማስተናገድ የዲሲፕሊን ችግር ያለባቸው ሠራተኞች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው።
- ተገልጋዮች ቅሬታ ሲኖራቸው ቅሬታ ለተቋሙ ማቅረብ አለባቸው።
- አዲስ ፓስፖርት ፈልገው በድረ ገጽ ሲያመለክቱ ፎቶግራፍ የሚነሱበትን እና ዐሻራ የሚሰጡበትን ቀንና ሰዓት የሚያሳውቅ በመሆኑ ተገልጋዮች በሰዓቱ ብቻ ቢመጡ ሰልፉ ሊቀንስ ይችላል። የተቀጠሩ ተገልጋዮች ሳይስተናገዱ አይቀሩም።
- በአካባቢው መጨናነቅ የሚፈጠረው ቀጠሮ ባላቸው ተገልጋዮች ብቻ ሳይሆን " ፓስፖርት ዘግይቶብናል " ብለው ለመጠየቅ በሚመጡ ተገልጋዮች ነው። አንድ ጉዳይ ለመጨረስ ከአንድ በላይ ሰው ስለሚመጣ ነው።
- የሌሊት ሰልፉ ከአገልግሎቱ እውቅና ውጪ ነው። ለሰልፉ ሰዓት የመገደቡን ጉዳይ በቀጣይ በጋራ የሚታይ ነገር ነው።
- ተገልጋዮች ለአስቸኳይ ፓስፖርት በሕገ ወጥ ደላሎች በኩል ለማስጨረስ ከመሞከር ይልቅ እራሳቸው በጥቂት ቀናት መጨረስ ይችላሉ።
ያንብቡ https://telegra.ph/EPA-03-04
ይህ መረጃ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው።
ፎቶ፦ Tikvah Family
@tikvahethiopia
ፓስፖርት ፈልገው/ በሥራ ምክንያት ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጎራ ካሉ ረዥም ሰልፍ እና መጨናነቅ ማየት የተለመደ ነው።
የሰልፍ አሰላፊዎች ዱላም ሊያጋጥም ይችላል።
ወጣት፣ሴት፣ወንድ፣ልጅ ያዘሉ እናቶች እንዲሁም " ፓስፖርት ፈልገው ነው ? " እያሉ እግር በእግር የሚከተሉ ሕገወጥ ደላሎችም በአካባቢው ውር ውር ይላሉ።
አገልግሎቱ 24 ሰዓት የፓስፖርት ህትመትና በበይነ መረብ ምዝገባ አሠራር ዘርግቻለሁ ቢልም አሁንም በርካታ ተገልጋዮችን አገልግሎቱ ደጃፍ ላይ መመልከት አልቀረም።
ተገልጋዮች ዐሻራ ለመስጠት እና ፎቶ ለመነሳት በመ/ቤቱ መገኘት ግዴታቸው በመሆኑ ከተለያዩ አካባቢዎች መጥተው በወረፋው ምክንያት ላልተፈለገ እንግልት ይዳረጋሉ።
እንግልቱ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ከእንቅልፍ ተነስቶ ረዥም ሰልፍ ከመሰለፍ ይጀምራል።
በሌቦች መዘረፍም የሚያጋጥም ክስተት መሆኑን ተገልጋዮች በምሬት ይናገራሉ።
ለአላስፈላጊ እንግልት እና ወጪ ተዳርገናል የሚሉ ተገልጋዮች ሃሳባቸውን አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት በበይነ መረብ አማካኝነት ከተመዘገቡ ወራት እንዳለፋቸው ይገልጻሉ።
ተገልጋዮቹ አገልግሎቱ አካባቢ ወረፋ ለመያዝ ስንሞክር " እኔ ቅድሚያ ወረፋ ልያዝላችሁ ክፈሉኝ " በሚሉ ደላሎች እንዋከባለን ይላሉ።
እነሱ እንደሚሉት የመሥሪያ ቤቱን ሰልፍ አሰላፊዎች ወከባና ዱላ አልፎ ውስጥ መግባት መቻል መታደል ነው።
ተገልጋዮቹ በሌሊት ለመነሳት ሲሉ በአካባቢው ለአልጋ ኪራይ ከፍለው እንደሚያድሩና ለአላስፈላጊ ወጪም እንደሚዳረጉም ይገልጻሉ።
ሰልፉ ረዝሞ ወረፋ ሳይደርሳቸው ከቀረም ቅጣት እንደማይቀርላቸው ይናገራሉ።
በርካታ አገልግሎት ፈላጊ ሕዝብ በተገቢው መንገድ ከማስተናገድ ይልቅ በዱላ በመደብደብ ሥርዓት ለማስያዝ ሲሞከር ይታያል። ወደ መግቢያ በሩ ተጠግቶ መረጃ ማግኘት የማይታሰብ ነው።
የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱ ተስተካክሏል ይባል እንጂ አሁንም ችግሮቹ እንደነበሩ ናቸው ይላሉ ተገልጋዮች።
የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱ ሳይዘምን እንደዘመነ አድርጎ ማስተዋወቅም ፍጹም ተገቢነት እንደሌለውና ሕዝብ በለውጥ እንዳያምን እንደሚያደርግም ያስገነዝባሉ።
ሰሞኑን የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱን ለመመልከት በመ/ቤቱ የተገኙት የኢፕድ ጋዜጠኞች መረጃ ለመሰብሰብ ያደረጉት ሙከራ በፖሊሶች ክልከላ ተደርጎበታል።
የተቋሙ ኮሙኒኬሽን ዳሬክተር ወ/ሮ ማስተዋል ገዳ ምን ምላሽ ሰጡ ?
- ተገልጋዮች ወደ ተቋሙ በሚመጡበት ወቅት በክብር መስተናገድ እንዳለባቸው እናውቃለን። ተገልጋዮችን በአግባቡ ባለማስተናገድ የዲሲፕሊን ችግር ያለባቸው ሠራተኞች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው።
- ተገልጋዮች ቅሬታ ሲኖራቸው ቅሬታ ለተቋሙ ማቅረብ አለባቸው።
- አዲስ ፓስፖርት ፈልገው በድረ ገጽ ሲያመለክቱ ፎቶግራፍ የሚነሱበትን እና ዐሻራ የሚሰጡበትን ቀንና ሰዓት የሚያሳውቅ በመሆኑ ተገልጋዮች በሰዓቱ ብቻ ቢመጡ ሰልፉ ሊቀንስ ይችላል። የተቀጠሩ ተገልጋዮች ሳይስተናገዱ አይቀሩም።
- በአካባቢው መጨናነቅ የሚፈጠረው ቀጠሮ ባላቸው ተገልጋዮች ብቻ ሳይሆን " ፓስፖርት ዘግይቶብናል " ብለው ለመጠየቅ በሚመጡ ተገልጋዮች ነው። አንድ ጉዳይ ለመጨረስ ከአንድ በላይ ሰው ስለሚመጣ ነው።
- የሌሊት ሰልፉ ከአገልግሎቱ እውቅና ውጪ ነው። ለሰልፉ ሰዓት የመገደቡን ጉዳይ በቀጣይ በጋራ የሚታይ ነገር ነው።
- ተገልጋዮች ለአስቸኳይ ፓስፖርት በሕገ ወጥ ደላሎች በኩል ለማስጨረስ ከመሞከር ይልቅ እራሳቸው በጥቂት ቀናት መጨረስ ይችላሉ።
ያንብቡ https://telegra.ph/EPA-03-04
ይህ መረጃ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው።
ፎቶ፦ Tikvah Family
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓስፖርት ፓስፖርት ፈልገው/ በሥራ ምክንያት ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጎራ ካሉ ረዥም ሰልፍ እና መጨናነቅ ማየት የተለመደ ነው። የሰልፍ አሰላፊዎች ዱላም ሊያጋጥም ይችላል። ወጣት፣ሴት፣ወንድ፣ልጅ ያዘሉ እናቶች እንዲሁም " ፓስፖርት ፈልገው ነው ? " እያሉ እግር በእግር የሚከተሉ ሕገወጥ ደላሎችም በአካባቢው ውር ውር ይላሉ። አገልግሎቱ 24 ሰዓት የፓስፖርት ህትመትና በበይነ መረብ ምዝገባ…
#ፓስፖርት
አዳማ ላይም ፖስፖርት ለመውሰድ አስቸጋሪ መሆኑን ተገልጋዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት ቅሬታ አመላክተዋል።
" ሰው ከመብዛቱ የተነሳ ሰው በየቀኑ ፓስፖርቱን ሳይወስድ ሳምንት ተመለሱ ይባላል። " ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎች " ፓስፖርት ለመስጠት የሚጠሩት በአልፋቤት ብሆንም Order የጠበቃ አይደለም። " ብለዋል።
" አንዱ የጠረውን በድጋሚ ሌላም አንስቶ የመጥራት ክስተት እንዳለ " አመላክተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ አንድ ተገልጋይ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ይህንን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አጋርቷል።
N ከአዳማ ፦
" አዲስ ፓስፖርትን ለመውሰድ ያለው እንግልት አለ።
አዲስ ፓስፖርት ካመለከትኩ አሁን ላይ 11 ወራት ሆኖኛል፡፡
በየካቲት ወር 7ኛው (February 15) ቀን በቴሌግራም አካውንት ላይ አዲስ ፓስፖርት የመጣላቸው ስም ዝርዝር ውስጥ ስሜን ስላገኘሁት ልቀበል አውራ ጎዳና በሚገኘው አዳማ ቢሯቸው ሄድኩኝ፡፡
ሆኖም ግን እዛ ስድርስ የመ/ቤቱ ጥበቃዎች በዱላ ጥያቄ ለመጠየቅ ግራ ገብቶት ያለውን ሰው መምታቱትን ተያይዘውታል፡፡
ከዛም ብቸኛ የመረጃ ምንጭ የሆኑት እነርሱ (ጥበቃዎቹ) ስለሆኑ ዱላው ሳያገኘኝ ጥያቄዬን ለመጠየቅ ተጋፍቼ ሳበቃ የአንተ ዛሬ አይደለም የሚቀጥለው ሳምንተ ከሰኞ በኃላ ና አሉኝ የሄድኩት ማክሰኞ እለት ነበር (February 19)፡፡
ወደ መስሪያ ቤቱ የሚያስገባው በር ሁለት ሰው እንኩዋን የማያስገባ ነው እናም መረጃ ለማግኘት ወደ ውስጥ መግባት የማይታሰብ ነው፡፡
ቀጥሎም አርብ እለት (February 23) ሄድኩ እንደምንም ተጋፍቼ ስጠይቅ አንድ ጊዜ ረቡህ አንዴ ሃሙስ አለኝ ጥበቃው፡፡
በቀጣይ ስለተጠራጠርኩ ቀደም ብዬ ማክሰኞ (February 26) ሄድኩ ከዛም በዛ ቀን የነበረው ጥበቃ አርብ እለት ነው አለኝ፡፡አርብ ስሄድ(March 01) ስሄድ ሰልፍ ያዝ ተባልኩ፡፡
ሰልፍ ከያዝኩ በኃላ ተሰላፊዎቹን ስጠይቅ የአንተ እኮ ሀሙስ ነበር አሉኝ(February 29)፡፡
መስሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ላይ ያለ ማስታወቂያ አሳኙኝ ማስታወቂያውን አነበብኩት የተለጠፈው February 23 ነው፡፡ እናም ጥበቃዎች ቢያንስ ተገልጋይ ማስታወቂያ እንዲያይ ቢያደርጉ የሰውን እንግልት ይቀንሳሉ፡፡
እኔ ቤተሰብ አዳማ ስለሆነ መመላለስ እችላለሁ ነገር ግን ከሩቅ ቦታ ለሚመጡ ምን ያህል ከባድ ነው በዚ ላይ የጥበቃዎቹ ዱላ ተጨምሮበት ?
አመሰግናለሁ፡፡ "
@tikvahethiopia
አዳማ ላይም ፖስፖርት ለመውሰድ አስቸጋሪ መሆኑን ተገልጋዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት ቅሬታ አመላክተዋል።
" ሰው ከመብዛቱ የተነሳ ሰው በየቀኑ ፓስፖርቱን ሳይወስድ ሳምንት ተመለሱ ይባላል። " ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎች " ፓስፖርት ለመስጠት የሚጠሩት በአልፋቤት ብሆንም Order የጠበቃ አይደለም። " ብለዋል።
" አንዱ የጠረውን በድጋሚ ሌላም አንስቶ የመጥራት ክስተት እንዳለ " አመላክተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ አንድ ተገልጋይ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ይህንን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አጋርቷል።
N ከአዳማ ፦
" አዲስ ፓስፖርትን ለመውሰድ ያለው እንግልት አለ።
አዲስ ፓስፖርት ካመለከትኩ አሁን ላይ 11 ወራት ሆኖኛል፡፡
በየካቲት ወር 7ኛው (February 15) ቀን በቴሌግራም አካውንት ላይ አዲስ ፓስፖርት የመጣላቸው ስም ዝርዝር ውስጥ ስሜን ስላገኘሁት ልቀበል አውራ ጎዳና በሚገኘው አዳማ ቢሯቸው ሄድኩኝ፡፡
ሆኖም ግን እዛ ስድርስ የመ/ቤቱ ጥበቃዎች በዱላ ጥያቄ ለመጠየቅ ግራ ገብቶት ያለውን ሰው መምታቱትን ተያይዘውታል፡፡
ከዛም ብቸኛ የመረጃ ምንጭ የሆኑት እነርሱ (ጥበቃዎቹ) ስለሆኑ ዱላው ሳያገኘኝ ጥያቄዬን ለመጠየቅ ተጋፍቼ ሳበቃ የአንተ ዛሬ አይደለም የሚቀጥለው ሳምንተ ከሰኞ በኃላ ና አሉኝ የሄድኩት ማክሰኞ እለት ነበር (February 19)፡፡
ወደ መስሪያ ቤቱ የሚያስገባው በር ሁለት ሰው እንኩዋን የማያስገባ ነው እናም መረጃ ለማግኘት ወደ ውስጥ መግባት የማይታሰብ ነው፡፡
ቀጥሎም አርብ እለት (February 23) ሄድኩ እንደምንም ተጋፍቼ ስጠይቅ አንድ ጊዜ ረቡህ አንዴ ሃሙስ አለኝ ጥበቃው፡፡
በቀጣይ ስለተጠራጠርኩ ቀደም ብዬ ማክሰኞ (February 26) ሄድኩ ከዛም በዛ ቀን የነበረው ጥበቃ አርብ እለት ነው አለኝ፡፡አርብ ስሄድ(March 01) ስሄድ ሰልፍ ያዝ ተባልኩ፡፡
ሰልፍ ከያዝኩ በኃላ ተሰላፊዎቹን ስጠይቅ የአንተ እኮ ሀሙስ ነበር አሉኝ(February 29)፡፡
መስሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ላይ ያለ ማስታወቂያ አሳኙኝ ማስታወቂያውን አነበብኩት የተለጠፈው February 23 ነው፡፡ እናም ጥበቃዎች ቢያንስ ተገልጋይ ማስታወቂያ እንዲያይ ቢያደርጉ የሰውን እንግልት ይቀንሳሉ፡፡
እኔ ቤተሰብ አዳማ ስለሆነ መመላለስ እችላለሁ ነገር ግን ከሩቅ ቦታ ለሚመጡ ምን ያህል ከባድ ነው በዚ ላይ የጥበቃዎቹ ዱላ ተጨምሮበት ?
አመሰግናለሁ፡፡ "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓስፖርት ፓስፖርት ፈልገው/ በሥራ ምክንያት ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጎራ ካሉ ረዥም ሰልፍ እና መጨናነቅ ማየት የተለመደ ነው። የሰልፍ አሰላፊዎች ዱላም ሊያጋጥም ይችላል። ወጣት፣ሴት፣ወንድ፣ልጅ ያዘሉ እናቶች እንዲሁም " ፓስፖርት ፈልገው ነው ? " እያሉ እግር በእግር የሚከተሉ ሕገወጥ ደላሎችም በአካባቢው ውር ውር ይላሉ። አገልግሎቱ 24 ሰዓት የፓስፖርት ህትመትና በበይነ መረብ ምዝገባ…
#AddisAbaba
4 ኪሎ አካባቢ የሚገኙ ሁለት የእግረኛ መሸጋገሪያ የብረት ድልድዮች የማንሳት ስራ እየተከናወነ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ዓለም አቀፍ የስማርት ሲቲ ስታንደሰርድን የሚያሟሉ አዳዲስ አራት የመንገድ ኮሪደሮች ግንባታ እንዲከናወን ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ 4 ኪሎ አካባቢ የሚገኙትን ሁለት የእግኛ መሸጋገሪያ የብረት ድልድዮች የማንሳት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን አሳውቋል።
" 4 ኪሎ ዳግማዊ ምኒልክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠገብ የሚገኘው የእግረኞች መሸጋገሪያ ድልድይ ጉዳት ደርሶበታል " በሚል የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ የተላለፈው ዘገባ የተሳሳተ መሆኑ ተገልጿል።
የብረት ድልድዮችን የማንሳት ስራ በሁለት ቀናት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
4 ኪሎ አካባቢ የሚገኙ ሁለት የእግረኛ መሸጋገሪያ የብረት ድልድዮች የማንሳት ስራ እየተከናወነ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ዓለም አቀፍ የስማርት ሲቲ ስታንደሰርድን የሚያሟሉ አዳዲስ አራት የመንገድ ኮሪደሮች ግንባታ እንዲከናወን ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ 4 ኪሎ አካባቢ የሚገኙትን ሁለት የእግኛ መሸጋገሪያ የብረት ድልድዮች የማንሳት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን አሳውቋል።
" 4 ኪሎ ዳግማዊ ምኒልክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠገብ የሚገኘው የእግረኞች መሸጋገሪያ ድልድይ ጉዳት ደርሶበታል " በሚል የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ የተላለፈው ዘገባ የተሳሳተ መሆኑ ተገልጿል።
የብረት ድልድዮችን የማንሳት ስራ በሁለት ቀናት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
#JASIRI: ታለንት ኢንቨስተር
- ለፈጣን ዕድገት አቅም ካላችሁ እና አዲስ ቢዝነስ ለመፍጠር ከቆረጣችሁ፤
- በማንኛናውም ዘርፍ ውስጥ ክፍተቶችን መለየት እና እድሎችን ማወቅ ከቻሉ፤
- ትኩረት ባደረጋቹበት ቦታ ሁሉ የስኬት፣ የችግር አፈታት እና ዋጋ የመፍጠር ልምድ ካላቹ፤
- በሙያዊ መስካችሁ ከፍተኛ መረጃ እና እውቀት ያላቹ ከሆነ፤
- በቡድናቹ ውስጥ ካሉ ተመሳሳይ ትልቅ ፍላጎት ካላቸው መስራቾች ጋር ለመገናኘት እና ከመሰረቱ ቬንቸር ለመገንባት እና በቡድን ለመስራት ዝግጁ ከሆናችሁ፤
- ስራዎን በሙሉ ጊዜ ለመገንባት ቃል ገብታቹ እና በሁሉም ታለንት ኢንቬስተር ደረጃዎች ለ14ወራት እንዲሁም በሩዋንዳ ባለው ፕሮግራም ለ3 ወር ተገኝታቹ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጁ ከሆናቹ፤
አሁኑኑ በ jasiri.org/application ላይ ይመዝገቡ
ሴት ስራ ፈጣሪዎች እንዲመዘገቡ በጣም እናበረታታለን!
- ለፈጣን ዕድገት አቅም ካላችሁ እና አዲስ ቢዝነስ ለመፍጠር ከቆረጣችሁ፤
- በማንኛናውም ዘርፍ ውስጥ ክፍተቶችን መለየት እና እድሎችን ማወቅ ከቻሉ፤
- ትኩረት ባደረጋቹበት ቦታ ሁሉ የስኬት፣ የችግር አፈታት እና ዋጋ የመፍጠር ልምድ ካላቹ፤
- በሙያዊ መስካችሁ ከፍተኛ መረጃ እና እውቀት ያላቹ ከሆነ፤
- በቡድናቹ ውስጥ ካሉ ተመሳሳይ ትልቅ ፍላጎት ካላቸው መስራቾች ጋር ለመገናኘት እና ከመሰረቱ ቬንቸር ለመገንባት እና በቡድን ለመስራት ዝግጁ ከሆናችሁ፤
- ስራዎን በሙሉ ጊዜ ለመገንባት ቃል ገብታቹ እና በሁሉም ታለንት ኢንቬስተር ደረጃዎች ለ14ወራት እንዲሁም በሩዋንዳ ባለው ፕሮግራም ለ3 ወር ተገኝታቹ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጁ ከሆናቹ፤
አሁኑኑ በ jasiri.org/application ላይ ይመዝገቡ
ሴት ስራ ፈጣሪዎች እንዲመዘገቡ በጣም እናበረታታለን!
ከባንክ ሂሳብዎ ወደ M-PESA 1,000 ብር እና ከዚያ በላይ በማስተላለፍ ከ0.5% እስከ 50 ብር ድረስ ስጦታ ያግኙ።
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፡ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም የቻት ግሩፕ
https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC https://yangx.top/SafaricomETForum እንዲሁም @SafaricomETCare
24/7 መጠየቅ ይቻላል!
#SafaricomET
#MPESASafaricom
#FurtherAheadTogether
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፡ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም የቻት ግሩፕ
https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC https://yangx.top/SafaricomETForum እንዲሁም @SafaricomETCare
24/7 መጠየቅ ይቻላል!
#SafaricomET
#MPESASafaricom
#FurtherAheadTogether
የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መሥሪያቤት ህንፃ ሽያጭ ተቋረጠ።
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ መካከል ሲካሄድ የቆየው ድርድር የሽያጭ ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡን ቢጂአይ-ኢትዮጵያ ለቲክቫህ ገልጿል።
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ የሽያጭ ውል በተዋዋይ ወገኖች መካከል እንዲኖር እና የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጩ እውን እንዲሆን ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን የገለፀ ሲሆን " በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅ እና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎት እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ምክንያት የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ሂደቱን ለማቋረጥ ተገደናል። " ሲል አሳውቋል።
" ስለዚህም በተዋዋይ ወገኖቹ ቀድም ሲል በተፈረመው የቀብድ ውል ውስጥ በተገለጹት ድንጋጌዎች መሠረት የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጩ በይፋ ተቋርጧል " ብሏል።
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ ከዋና መስርያ ቤቱ ሽያጭ ድርድር ጋር በተገናኘ በዚህ ወቅት ምንም አይነት ተጨማሪ አስተያየት እንደማይሰጥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው የኢሜል መልዕክት አሳውቋል።
ቀደም ብሎ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሜክሲኮ የሚገኘውንና የቢጂአይ ኢትዮጵያ ለረዥም ጊዜ ዋና መሥሪያ ቤት አድርጎ ሲጠቀምበት የነበረውን ሥፍራ ለመግዛት መስማማታቸውን ከሁለቱም ወገን መገለጹ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ መካከል ሲካሄድ የቆየው ድርድር የሽያጭ ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡን ቢጂአይ-ኢትዮጵያ ለቲክቫህ ገልጿል።
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ የሽያጭ ውል በተዋዋይ ወገኖች መካከል እንዲኖር እና የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጩ እውን እንዲሆን ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን የገለፀ ሲሆን " በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅ እና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎት እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ምክንያት የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ሂደቱን ለማቋረጥ ተገደናል። " ሲል አሳውቋል።
" ስለዚህም በተዋዋይ ወገኖቹ ቀድም ሲል በተፈረመው የቀብድ ውል ውስጥ በተገለጹት ድንጋጌዎች መሠረት የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጩ በይፋ ተቋርጧል " ብሏል።
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ ከዋና መስርያ ቤቱ ሽያጭ ድርድር ጋር በተገናኘ በዚህ ወቅት ምንም አይነት ተጨማሪ አስተያየት እንደማይሰጥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው የኢሜል መልዕክት አሳውቋል።
ቀደም ብሎ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሜክሲኮ የሚገኘውንና የቢጂአይ ኢትዮጵያ ለረዥም ጊዜ ዋና መሥሪያ ቤት አድርጎ ሲጠቀምበት የነበረውን ሥፍራ ለመግዛት መስማማታቸውን ከሁለቱም ወገን መገለጹ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል። ሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር ሲሸጥ በነበረበት ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ? - ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም - ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም - ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም …
#እንድታውቁት
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል።
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በየካቲት ወር ሲሸጥ በነበረበት ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ?
- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም ነው።
@tikvahethiopia
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል።
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በየካቲት ወር ሲሸጥ በነበረበት ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ?
- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም ነው።
@tikvahethiopia
#ትግራይ
"...መግለጫው የኤርትራ ጦር የተለያዩ አካባቢዎችን በኃይል ይዞ እንደሚገኝ ያመላከተ ነው " - አቶ ረዳኢ ኃለፎም
የትግራይ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ የኤርትራ ጦር የኢትዮጵያን መሬት በኃይል ተቆጣጥሮ እንደሚገኝ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላም ቢሆን መሬቱን ለቆ እንዳልወጣ የትግራይ ጊዜዊ አስተዳደርን ጨምሮ ሀገራትና ተቋም በተደጋጋሚ መግለፃቸው ይታወሳል።
በቅርቡ እንግሊዝ የሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲ አውጥቶት በነበረ አንድ መግለጫ የኤርትራ ጦር በትግራይ ግዛት ውስጥ እንደሌለ፣ ባድመም ጨምሮ ሌሎችም አከባቢዎች ህወሓት በህገወጥ መንገድ ለሁለት አስርት ዓመታት ይዟቸው የቆዩ የኤርትራ ሉዓላዊ ግዛቶች ናቸው ብሏል።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የኤርትራ ጦር በምስራቃዊና ሰሜን ምዕራብ የትግራይ አካባቢዎች ጨምሮ በተለያየ አካባቢ እንዳለ በተደጋጋሚ በመግለፅ በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ያሉ የውጭ ኃይሎችን የማስወጣትና ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው የመመለስ ኃላፊነት የፌዴራል መንግሥት መሆኑን ገልጿል።
የትግራይ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ረዳዒ ኃለፎም በኤርትራ መግለጫ ዙሪያ ምን አሉ ?
- የኤርትራው ኤምባሲ መግለጫ የኤርትራ ጦር የተለያዩ አካባቢዎችን በኃይል ይዞ እንደሚገኝ አመላካች ነው።
- ከአልጀርስ ስምምነት አፈፃፀምናና ሌሎች የድሮ በ90ዎቹ የሚነሱ ጥያቄዎች ጉዳዮች ካሉ በህጋዊ መንገድ በዓለም አቀፍ ስርዓት እንዲፈፀም ማድረግ እንጂ ጉልበት አለኝ ብሎ በጉልበት የያዛቸውን አካባቢዎች " የኔ ናቸው " የሚል መግለጫ መስጠቱ ተቀባይነት የለውም።
- ከአልጀርስ ስምምነት አፈፃፀም ጋር በተያያዘ በኃይል የተወረረው መሬት ከተመለሰ በኃላ በህጋዊ መንገድ ሊፈፀም የሚችል ነው።
- መግለጫው አንድ ውለታ የዋለው በኃይል የያዧቸው አካባቢዎች እንዳሉ ገልጸ " በኃይል የያዝኩት የኔ ነው " የሚል መስፋፋት ነው። " የለሁም " አላለም መኖሩን አምኗል ይሄ የያዘው ቦታ ነው በጉልበት ስለያዝኩት " የኔ ነው " እያለ ያለው ይሄ በፍፁም ተቀባይነት የለውም።
- የፌዴራል መንግሥት ማስወጣት አለበት እነዚህን ኃይሎች ሁሌም እያልን ነው። ማለት ያለበትን ማለትም አለበት። ኃላፊነቱን መወጣት አለበት።
- በትግራይ ከኤርትራ ጦር በተጨማሪ የአማራ ክልል ታጣቂዎችም አሉ። ይህ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የሚፃረር በትግራይ ያለውን አሳሳቢ የተፈናቃዮች ችግር እንዳይፈታ ያደረገ ነው።
- እንዚህ ኃይሎች እያሉ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ ማድረግና ማቋቋም አይቻልም። ከሞት አምልጠው የመጡ ገዳዮች ወዳሉበት እንዴት ነው የሚመለሱት ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የዶቼቨለ ሬድዮ መሆኑን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
"...መግለጫው የኤርትራ ጦር የተለያዩ አካባቢዎችን በኃይል ይዞ እንደሚገኝ ያመላከተ ነው " - አቶ ረዳኢ ኃለፎም
የትግራይ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ የኤርትራ ጦር የኢትዮጵያን መሬት በኃይል ተቆጣጥሮ እንደሚገኝ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላም ቢሆን መሬቱን ለቆ እንዳልወጣ የትግራይ ጊዜዊ አስተዳደርን ጨምሮ ሀገራትና ተቋም በተደጋጋሚ መግለፃቸው ይታወሳል።
በቅርቡ እንግሊዝ የሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲ አውጥቶት በነበረ አንድ መግለጫ የኤርትራ ጦር በትግራይ ግዛት ውስጥ እንደሌለ፣ ባድመም ጨምሮ ሌሎችም አከባቢዎች ህወሓት በህገወጥ መንገድ ለሁለት አስርት ዓመታት ይዟቸው የቆዩ የኤርትራ ሉዓላዊ ግዛቶች ናቸው ብሏል።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የኤርትራ ጦር በምስራቃዊና ሰሜን ምዕራብ የትግራይ አካባቢዎች ጨምሮ በተለያየ አካባቢ እንዳለ በተደጋጋሚ በመግለፅ በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ያሉ የውጭ ኃይሎችን የማስወጣትና ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው የመመለስ ኃላፊነት የፌዴራል መንግሥት መሆኑን ገልጿል።
የትግራይ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ረዳዒ ኃለፎም በኤርትራ መግለጫ ዙሪያ ምን አሉ ?
- የኤርትራው ኤምባሲ መግለጫ የኤርትራ ጦር የተለያዩ አካባቢዎችን በኃይል ይዞ እንደሚገኝ አመላካች ነው።
- ከአልጀርስ ስምምነት አፈፃፀምናና ሌሎች የድሮ በ90ዎቹ የሚነሱ ጥያቄዎች ጉዳዮች ካሉ በህጋዊ መንገድ በዓለም አቀፍ ስርዓት እንዲፈፀም ማድረግ እንጂ ጉልበት አለኝ ብሎ በጉልበት የያዛቸውን አካባቢዎች " የኔ ናቸው " የሚል መግለጫ መስጠቱ ተቀባይነት የለውም።
- ከአልጀርስ ስምምነት አፈፃፀም ጋር በተያያዘ በኃይል የተወረረው መሬት ከተመለሰ በኃላ በህጋዊ መንገድ ሊፈፀም የሚችል ነው።
- መግለጫው አንድ ውለታ የዋለው በኃይል የያዧቸው አካባቢዎች እንዳሉ ገልጸ " በኃይል የያዝኩት የኔ ነው " የሚል መስፋፋት ነው። " የለሁም " አላለም መኖሩን አምኗል ይሄ የያዘው ቦታ ነው በጉልበት ስለያዝኩት " የኔ ነው " እያለ ያለው ይሄ በፍፁም ተቀባይነት የለውም።
- የፌዴራል መንግሥት ማስወጣት አለበት እነዚህን ኃይሎች ሁሌም እያልን ነው። ማለት ያለበትን ማለትም አለበት። ኃላፊነቱን መወጣት አለበት።
- በትግራይ ከኤርትራ ጦር በተጨማሪ የአማራ ክልል ታጣቂዎችም አሉ። ይህ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የሚፃረር በትግራይ ያለውን አሳሳቢ የተፈናቃዮች ችግር እንዳይፈታ ያደረገ ነው።
- እንዚህ ኃይሎች እያሉ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ ማድረግና ማቋቋም አይቻልም። ከሞት አምልጠው የመጡ ገዳዮች ወዳሉበት እንዴት ነው የሚመለሱት ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የዶቼቨለ ሬድዮ መሆኑን ይገልጻል።
@tikvahethiopia