TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ-ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ…
#BDU

ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ሲጀመር ተማሪዎች ኃላፊነት ለመውሰድም ይዘጋጁ ብሏል።

በአማራ ክልል የሚገኙ 10 የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት 2 ሳምንታት መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ እንደሚጀምሩ ትምህርት ሚኒስቴር ማስታወቁ ይታወሳል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድ ፖስት፣ የፀጥታ አደረጃጀቶች፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ፀጥታ አካላት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ተከታታይ ውይይቶችን ሲያደርግ ቆይቶ የውይይቶቹ የመጨረሻው ክፍል ሐሙስ ከተደረገ በኃላ ነው ውሳኔው የተላለፈው።

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

- ከመስከረም 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተማሪዎችን ለመቀበል ተዘጋጅተን የነበረ ቢሆንም፣ በክልሉ የፀጥታ ሁኔታ ሳቢያ ተሰናክሏል።

- በእኛ በኩል የዝግጅት ክፍተት የለብንም።

- በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቁጥጥር ሥር የሆነ የፀጥታ ሁኔታ አለ። ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆነም የፀጥታ ሁኔታ አለ። ከእኛ ውጪ በሆነው ጉዳይ ላይ ምንም ማድረግ አንችልም። ምንም ማድረግ ባልቻልንበት ሁኔታ የሰው ልጅ ጠርቼ አንድ መጥፎ ነገር ቢከሰት ምንድነው የምለው ? የሚለውን ተማሪዎችም፣ ወላጅንም ታሳቢ አድርገን ተማምነን ይቆይ የሚል አቋም ስለነበረን በዚህ ምክንያት ነው እስካሁን ቀስ እያልን የመጣነው።

- የመማር ማስተማሩ እንዲጀመር በነበረው ውይይት ሒደት አቅደን የነበረው ተመራቂ ተማሪዎችን ወደ የትምህርት ግቢያቸው ማስገባት ነበር።

- እስካሁን ባለን ልምድ ግጭቶች እዚህም እዚያም ሊቀሰቀሱ ይችላሉ። ቀጣይነታቸው ግን ብዙም አይደለም። አንድ ቀን ወይ ሁለት ቀን መስተጓጎል ሊፈጠር ይችላል ከዚያ ግን ያበቃል።

- ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ተጠርተው ሲመጡ ታሳቢ ማድረግ ያለባቸው ጉዳዮች አሉ ፤ ሁሉም የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ሊያጋጥሙ የሚችሉ ዕክሎችን ከግምት በማስገባት ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው።

- ተማሪውም፣ ወላጅም፣ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብም እንደ አገር የሚመለከታቸውም አንድ ላይ ሆነን መደበኛ ትምህርት መጀመር አለብን ብለን ወስነናል።

- የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ተቋማቸው ከልደት (ገና) በዓል በኋላ ባሉት ቀናት ለተማሪዎቹ ጥሪ ያደርጋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
አዲስ መኪና የማሸነፍ እድል እንፈልጋለን? M-PESA ላይ በቀላሉ እንመዝገብ እና በM-PESA ግብይቶችን ፈፅመን አዲሱን መኪና የግላችን እናድርግ

የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ ያውርዱ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia

አሸናፊ ኮዶችን ከታች በሚገኘው ሊንክ ማግኘት ትችላላቹህ
https://safaricom.et/index.php/faqs

#MPESASafaricom #TerekBeMPESA
#FurtherAheadTogether
#ኢትዮጵያ #ሶማሌላንድ

በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ እና በሶማሌ ላንድ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል።

ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የባሕር በር የምታገኝበትን መንገድ ይጠርጋል ተብሏል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ታሪካዊ ነው የተባለውን የመግባቢያ ሠንድ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል፡፡

የኢፌዴሪ መንግሥት እና የሶማሌላንድ መንግሥት የፈረሙት የትብብር እና የአጋርነት መግባቢያ ሠነድ በተለያዩ ዘርፎች በቀጣይ ለሚኖራቸው ግንኙነቶች ማዕቀፍ  እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ጽኅፈት ቤት ይፋ ባደረገው መረጃ አሳውቋል።

የመግባቢያ ሠነዱ ፦
* የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት ፍላጎት ዕውን የሚያደርግ ፣
* የባሕር በር አማራጮቿን የሚያሠፋ
* የሁለቱን ወገኖች የፖለቲካ ፣ የዲፕሎማሲ ፣ የፀጥታ እና የኢኮኖሚ ትብብር የሚያጠናከር ነው ብሏል።

በተጨማሪም ሠነዱ ሀገራቱ በፖለቲካ እና በዲፕሎማሲው ዘርፍ የሚኖራቸውን ግንኙነት የሚጎለብትበትን አካሄድ የሚያካትት መሆኑን ገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በሰጥቶ መቀበል መርኅ እና ሀገሪቷ ለጋራ ጥቅም ከጎረቤቶቿ ጋር የመሥራት ፍላጎት እና አቋሟን መልሶ የሚያጸና እንደሆነም አመላክቷል፡፡

ሠነዱ ፤ አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እና ለአፍሪካ ቀንድ ትሥሥር የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑን ጠቁሟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ሶማሌላንድ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ እና በሶማሌ ላንድ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል። ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የባሕር በር የምታገኝበትን መንገድ ይጠርጋል ተብሏል። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ታሪካዊ ነው የተባለውን የመግባቢያ ሠንድ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል፡፡ የኢፌዴሪ መንግሥት እና የሶማሌላንድ መንግሥት የፈረሙት የትብብር…
#Update

የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ፤ ዛሬ በነበረው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ፊርማ ወቅት ፤ ኢትዮጵያ ከስምምነቱ በኃላ " ለሶማሌላንድ ነፃ ሀገርነት እውቅና የምትሰጥ የመጀመሪያዋ ሀገር እንደምትሆን " በምላሹ ደግሞ ሶማሌላንድ ፤ ኢትዮጵያ የባህር በር እና የባህር ኃይል ቤዝ እንዲኖራት በቀይ ባህር በኩል 20 ኪሎ ሜትር የሆነ መሬት ለኢትዮጵያ በሊዝ እንደምትሰጥ ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ኢትዮጵያ ግን የሶማሊላንድን የነፃ ሀገርነት እውቅና እንደምትቀበል በይፋ አላረጋገጠችም።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የሶማሌላንዱ ፕሬዜዳንት ይህን ጉዳይ ሲናገሩ ከጎን ተቀምጠው የነበረ ቢሆንም ንግግራቸውን አልተቃረኑም።

ከዚህ በተጨማሪ የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ፤ በስምምነቱ መሰረት ሶማሌለንድ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ድርሻ እንደሚኖራት ዝርዝር ነገር ሳይገልጹ ተናግረዋል።

አጠቃላይ የዛሬው ስምምነት ዝርዝር ጉዳይ በአንድ ወር ውስጥ ይፋ ይደረጋል።

ራስ ገዟ ሶማሌላንድ ለሶስት አስርት ዓመታት ዓለማቀፍ እውቅና ማግኘት ያልቻለች ስትሆን ሶማሊያ ደግሞ አንድ አንድ የራሷ ግዛት ነው የምታያት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

የሶማሊያ ካቢኔ በነገው ዕለት አስቸኳይ ስብሰባ እንደተጠራ ተሰምቷል።

አስቸኳይ ስብሰባው ፤ ዛሬ በሶማሌላንድ (ሶማሊያ ሶማሌላንድን እንደ ሰሜናዊ ክልሏ ነው የምትቆጥራት) እና በኢትዮጵያ መካከል ተደርጓል ስለተባለው ስምምነት በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ነው ተብሏል።

ከዚሁ ከነገው አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ ዝግጅት ጋር በተያያዘ #በአሁን_ሰዓት በሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ስብሰባ እየተካሄደ እንደሆነ ተሰምቷል።

ስብሰባው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ምክትላቸው እና ከፍተኛ የካቢኔ አባላት እንደሚገኙ ታውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ሶማሌላንድ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ እና በሶማሌ ላንድ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል። ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የባሕር በር የምታገኝበትን መንገድ ይጠርጋል ተብሏል። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ታሪካዊ ነው የተባለውን የመግባቢያ ሠንድ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል፡፡ የኢፌዴሪ መንግሥት እና የሶማሌላንድ መንግሥት የፈረሙት የትብብር…
#ETHIOPIA 🤝 #Somaliland #RedSea #Port

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ምን አሉ ?

" ... እንኳን የኢትዮጵያ ስብራት ጥገና ቀን በጋራ አደረሰን፤ አደረሳችሁ።

በተደጋጋሚ ለህዝባችን ቃል በገባነው መሰረት ኢትዮጵያ ካሏት ዋና ዋና ስብራቶች መካከል አንዱ የሆነው ቀይ ባህርን #access የማድረግ በዛውም #የማልማት ፍላጎት ከሶማሌላንድ ወንድሞቻችን ጋር በተደረገው የትብብር ስምምነት ዛሬ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራርመናል።

ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንዳነሳነው እኛ ያሉንን ሃብቶች የመጋራት ፣ የመካፈልና በጋራ የመልማት ፍላጎት እንጂ ማንንም በኃይል የማስገደድ ፍላጎት የለንም ስንል የነበረው ሃሳብ በተግባር ዛሬ በአዲሱ ዓመት የመጀመሪያው ቀን ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ፣ የሶማሌላንድ ህዝብና ለሰላም ወዳድ ህዝብ ለልማት ወዳድ ህዝብ የምናበስረው የምስራች ይሆናል።

ስብራቶቻችን ይጠገናሉ፣ ኢትዮጵያ ትበለፅጋለች። በገባነው ቃል መሰረት ሀገራችንን ወደሚቀጥለው ደረጃ እናሸጋግራለን።

ስለሆነው ሁሉ ያደረገልንን ፈጣሪን እናመሰግናለን። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ ካቢኔ በነገው ዕለት አስቸኳይ ስብሰባ እንደተጠራ ተሰምቷል። አስቸኳይ ስብሰባው ፤ ዛሬ በሶማሌላንድ (ሶማሊያ ሶማሌላንድን እንደ ሰሜናዊ ክልሏ ነው የምትቆጥራት) እና በኢትዮጵያ መካከል ተደርጓል ስለተባለው ስምምነት በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ነው ተብሏል። ከዚሁ ከነገው አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ ዝግጅት ጋር በተያያዘ #በአሁን_ሰዓት በሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት…
#Ethiopia 🤝 #Somaliland

" ታሪክ እየተሰራ ነው " - አሊ ሀሰን ሞሃመድ

ኢትዮጵያ እስካሁን በይፋ ከሶማሌላንድ ጋር በተፈረመው የትብብር ስምምነት የባህር በር ለመጠቀም እና የባህር ኃይል ቤዝ እንዲኖራት በምላሹ ደግሞ የ " ሶማሌላንድን " የነፃ ሀገርነት እውቅና እንደምትሰጥ አንዲትም ቃል #አልተናገረችም

የሶማሌላንዱ ፕሬዜዳንት ግን ከስምምነቱ በኃላ ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ የነፃ ሀገርነት ውቅና እንደምትሰጥ በምላሹ የባህር በር እና የባህር ኃይል እንዲኖራት 20 ኪሎሜትር መሬት በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።

የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ባለስልጣናትም ተመሳሳይ መረጃዎችን ሰጥተዋል።

ለአብነት አሊ ሀሰን ሞሃመድ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ፤ " ታሪክ እየተሰራ ነው " ብለዋል።

ኢትዮጵያ በሊዝ የ20 ኪሎሜትር የባህር በር ተጠቃሚ እንድትሆን በምላሹ ደግሞ #እውቅና እና የኢኮኖሚ እድገት እንደምትሰጥ ገልጸዋል።

" ይህ ጨዋታ ቀያሪ፤ ትልቅ ትርጉም ያለው ስምምነት ነው " ያሉት ባለስልጣኑ " ትልቅና ደፍረትን የሚጠይቅ እርምጃ ነው ፤ ወደፊት ለሶማሌላንድ እና ኢትዮጵያ የብሩህ አድማስ በሮችን የሚከፍት ነው " ብለዋል።

ይህንኑ የአሊ ሀሰን ሞሀመድ ሃሳብን ሞባረክ ታኒ የተባሉት የፕሬዜዳንቱ ዋና ፀሐፊ ተጋርተውታል።

በሌላ በኩል ፤ ሶማሊያ እንደራሷ አንድ ግዛት የምታያት " ሶማሌላንድ " ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመች ስለተባለው የመግባቢያ ስምምነት በተመለከተ ነገ ካቢኔዎቿ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሏል።

ለነገው አስቸኳይ ስብሰባ ዝግጅት ዛሬ ምሽት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ምክትላቸው እና ከፍተኛ የካቢኔ አባላት የተገኙበት ሰብሰባ ሲደረግ አምሽቷል።

የሶማሊያ ባለስልጣናትም የመግባቢያ ስምምነቱ ክፉኛ እንዳስቆጣቸው ተነግሯል።

የሶማሊያ የማዕድን እና ነዳጅ ሚኒስትሩ አብዲሪዛቅ ሞሀመድ ፤ " ሶማሊያ አትከፋፈልም ፤ በሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነታችን አንደራደርም " ብለዋል።

ሚኒስትሩ ፤ " ኢትዮጵያ ከግዛት (ክልል) አስታዳዳሪ ጋር ወደብን ለመከራየት / ወታደራዊ ስምምነት (MOU) ማድረግ እንደማትችል በደንብ አድርጋ ታውቃለች ይህ ስልጣን ሙሉ በሙሉ የፌዴራላዊ ሶማሊያ መንግሥት ነው ፤ ኢትዮጵያ የግዛት አንድነታችንን የሚጥስ ተግባር መፈፀም አትችልም " ሲሉ ገልጸዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የዛሬውን " ታሪካዊ " የተባለ የትብብር ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ " ኢትዮጵያ #ቀይ_ባህርን የመጠቀምና በዛውም የማልማት ፍላጎት ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል " ሲሉ አብስረዋል።

ዶክተር ዐቢይ፤ " እኛ ያሉንን ሃብቶች የመጋራት ፣ የመካፈልና በጋራ የመልማት ፍላጎት እንጂ ማንንም በኃይል የማስገደድ ፍላጎት የለንም ስንል የነበረው ሃሳብ በተግባር ታይቷል " ሲሉም ነው ያሳውቁት።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

የገና ስጦታ!
ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
5ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 25 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ከ4ኛ ዙር ጀምሮ ባሉት ውድድሮች አስር አስር አሸናፊዎች በየሳምንቱ ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://yangx.top/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የሶማሊላንዱ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ምን አሉ ?

የሶማሊላንዱ ፕሬዝደንት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ መፈረሙን ገልጸዋል።

በዚህም ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ እውቅና እንደምትሰጥ ፤ ሶማሊላንድ በበኩሏ ኢትዮጵያ የባህር ኃይል እና የንግድ ባህር በር መዳረሻ እንዲኖራት ለ50 ዓመታት #በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንቱ ይህንን ጉዳይ በትላንትናው መግለጫ ወቅትም የተናገሩት ሲሆን አሁንም በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አረጋግጠዋል።

ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት በኩል እስካሁን በስምምነቱ መሰረት ለሶማሊላንድ የነፃ ሀገርነት እውቅና እንሰጣለን የሚል ቃል አልወጣም።

በሌላ በኩል ስምምነቱ ያስቆጣቸው የሶማሊያ መንግሥት የካቢኔ አባላት ዛሬ ተሰብሰበው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሏል።

ሶማሊያ ፤ ራዝ ገዟን ሶማሊላንድ እንደ አንድ ሉኣላዊ ግዛቷ ነው የምትቆጥራት።

ለሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ ይቅርታ ካልጠየቁ እና ለሶማሊያ ልዓላዊነት ክብር ካልሰጡ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን እንደምታቋርጥ ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ሶማሊያ ፤ በኢትዮጵያ እና በሶማሌላንድ መካከል የተደረሰውን ስምምነት በመቃወም እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል እኚሁ ለፅ/ቤቱ ቅርብ የሆኑት ምንጮች አመልክተዋል።

ተጨማሪ . . .

በኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መካከል ከተፈረመው ስምምነት ጋር በተያያዘ ዛሬ ማክሰኞ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ እንደሚያደርጉና የሶማሊያው ፕሬዝዳንትም ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር እንደሚያደርጉ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሶማሊላንዱ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ምን አሉ ? የሶማሊላንዱ ፕሬዝደንት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ መፈረሙን ገልጸዋል። በዚህም ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ እውቅና እንደምትሰጥ ፤ ሶማሊላንድ በበኩሏ ኢትዮጵያ የባህር ኃይል እና የንግድ ባህር በር መዳረሻ እንዲኖራት ለ50 ዓመታት #በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል። ፕሬዝዳንቱ…
ዛሬ በራዝ ገዟ ሶማሊላንድ ይፋዊ መግለጫ ወጥቷል።

በዚህም መግለጫ ስምምነቱ ታሪካዊ ነው ተብሏል።

ይህ ታሪካዊ ስምምነት ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እውቅና በመስጠት በሊዝ የባህር በር / ለባህርኃይሎቿ የባህር መዳረሻ እንደምታገኝ መግለጫው ይገልጻል።

" ስምምነቱ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ነው " ያለው መግለጫው ለኢትዮጵያ የባህር ኃይል ተጠቃሚነት 20 ኪሎሜትር የባህር በር እንደሚሰጥ ይህም በሊዝ ለ50 ዓመት እንደሚቆይ ተመላክቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዛሬ በራዝ ገዟ ሶማሊላንድ ይፋዊ መግለጫ ወጥቷል። በዚህም መግለጫ ስምምነቱ ታሪካዊ ነው ተብሏል። ይህ ታሪካዊ ስምምነት ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እውቅና በመስጠት በሊዝ የባህር በር / ለባህርኃይሎቿ የባህር መዳረሻ እንደምታገኝ መግለጫው ይገልጻል። " ስምምነቱ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ነው " ያለው መግለጫው ለኢትዮጵያ የባህር ኃይል ተጠቃሚነት 20 ኪሎሜትር የባህር በር እንደሚሰጥ…
#Ethiopia #Seaport

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከሶማሊለንድ ጋር ስለተፈረመው ስምምነት ምን አሉ ?

- ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚ እንድትሆን በምክክር፣ በሰላማዊ መንገድ ብቻ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተለያዩ የዲፕሎማሲ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።

- ከሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጋር ብዙ ሞክረን ያልተሳካው ከሶማሊላንድ ጋር በተመሳሳይ መንገድ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል።

- መንግሥት አቋሙን ይፋ ካደረገ በኃላ ያሉ ሃብቶችን ከመጋራት አንፃር የነበረው ጉዳይ ጥርቶ ከወጣ በኃላ ዝርዝር ውይይት ሲካሄድ ነው የቆየው።

- ጉዳዩ መልክ እስኪይዝ በተወሰነ በጠባብ ቡድን፣ በመሪዎች ደረጃ እና በተወሰኑ አካላት ደረጃ እንዲያዝ እየበሰለ ሲሄድ ደግሞ ሁለቱም አካላት የየራሳቸውን አመራር እያሳተፉ የሚሄዱበት ሁኔታ እንዲፈጠር ተደርጓል።

- የወደብ ስምምነት ተጠቃሚነት በሊዝ አማካኝነት የሚፈፀም ነው።

- ይህ የስምምነት ማዕቀፍ ሶማሌለንድ እና ኢትዮጵያ አንዳቸው ጋር ያለውን ሃብት ለመጋራት በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እድል የሚያሰፋበት፣ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ ኢትዮጵያ ያላትን አቅምና ልምድ ለሶማሊላንድ የምታጋራበት ፤ የጋራ ጥቅማቸውን ማስጠበቅ የሚችሉበት አቅም ይገነባል።

- የስምምነቱ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ ሶማሌላንድ ውስጥ Military base እና Commercial maritime ሰፈር እንዲኖራት ይፈቅዳል። ይህ #በሊዝ የሚታሰብ ይሆናል። ለ50 ዓመት እና ከዛ በላይ #በማራዘም የሚካሄድ እንዲሆን ያደርጋል።

- ኢትዮጵያ አማራጭ ወደብን እድል ለማግኘት በርበራ ኮሊደርን የምታሰፋበት ፣ የመከላከያ አቅሟን አዲስ በምትከራየው ቦታ የምታጠናክርበት እድል ይሰጣል።

- ኢትዮጵያ ለሊዝ ተጠቃሚነቷ ቴሌኮም ይሁን፣ አየር መንገድ ይሁን ጥቅም በሚያስገኙ መሰረተ ልማቶች ላይ ድርሻ ትሰጣለች። ምን ያህል ነው ? የሚለው የሚከፈለው ሊዝም ምን ያህል ይሆናል ? የሚለው በዝርዝር ውይይቶች ይወሠናል።

- በጤና፣ በትምህርት ፣ በመከላከያ የሚሰሩት ዝርዝር ስምምነቶች በተናጠል ውይይት ይካሄድባቸዋል። ወደ ፓርላማ ሄደው የሚፀድቁ በርካታ ስምምነቶች ከዚህ ይፈልቃሉ።

- የጋራ የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ አጠቃላይ ማዕቀፍ ሁለቱ አካላት በጋራ ተባብረው የሚያድጉበትን ማዕቀፍ ነው የሚያስቀምጠው። ዋና ዋና አንጓዎች ተቀምጠዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር የምታገኝበትን ዕድል በተጨባጭ ወደመሬት ለማውረድ እድል ይሰጣል።

- ስምምነቱ በ1 ወር ጊዜ ውስጥ ሂደቱ ያልቃል / ወደ ተግባር / ስራ ይገባል።

- ከሌሎች ሀገራት ጋር የጀመርናቸው አሉ #ከኤርትራ ጋር በዝርዝር ውይይት ተጀምሮ የሆነ ቦታ ላይ ነው የቆመው።

- ኢትዮጵያ አንድ ወደብ ፣ ሁለት ወደብ ፣ ሶስት ወደብ ሳይሆን ፤ ኢትዮጵያ አሁን ባለው ሁኔታ እያደገች ከሄደች ሁሉም ቀጠናዎች የሁሉም ጫፎች የኢትዮጵያን ምርቶች የሚያስገቡበት በር ያስፈልጋል።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በማብራሪያቸው በስምምነቱ ሶማሊያ ልዓላዊ ግዛቴ ናት ለምትለው ራስ ገዟ #ሶማሌላንድ በይፋ የነፃ ሀገርነት እውቅናን ትስጠ እንደሆነ የተናግሩት አንዳች ነገር የለም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ ካቢኔ በነገው ዕለት አስቸኳይ ስብሰባ እንደተጠራ ተሰምቷል። አስቸኳይ ስብሰባው ፤ ዛሬ በሶማሌላንድ (ሶማሊያ ሶማሌላንድን እንደ ሰሜናዊ ክልሏ ነው የምትቆጥራት) እና በኢትዮጵያ መካከል ተደርጓል ስለተባለው ስምምነት በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ነው ተብሏል። ከዚሁ ከነገው አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ ዝግጅት ጋር በተያያዘ #በአሁን_ሰዓት በሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት…
#Update #Seaport

ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን ጠራች።

ሶማሊያ እንደ ራሷ ግዛት በምታያት ሱማሊላንድ እና ኢትዮጵያ መካከል ትላንት በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ እንዳስቆጣት መነገሩ ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ ከኢትዮጵያ አምባሳደሯን ለምክክር በሚል ጠርታለች።

የሀገሪቱ ካቢኔ ዛሬ ማክሰኞ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ፦
- የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት)
- አፍሪካ ህብረት
- ኦአይሲ
- ኢጋድ
- አረብ ሊግ ጣልቃ እንዲገቡ ጥሪ አቅርቧል።

በተጨማሪ የሶማሊያ ካቢኔ በሶማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል ለወደብ አጠቃቀም የተፈረመው ስምምነት " ዋጋ ቢስ እና ህጋዊ መሰረት የሌለው " ነው ማለቱ ተነግሯል።

ካቢኔው የኢትዮጵያ እርምጃ የቀጠናውን መረጋጋት እና ሰላም አደጋ ላይ የሚጥል ነው ማለቱም ተዘግቧል።

የካቢኔውን ስብሰባ የመሩት ጠ/ሚ ሃምዛ አብዲ ባሬ " ሉዓላዊነታችንን ለመጠበቅ ቁርጠኛ ነን " ብለው " ማንም የሶማሊያን የመሬት፣ የባህር እና የአየር ክፍል ሊጥስ አይችልም " ሲሉ ተደምጠዋል።

ራስ ገዟ ሶማሌላንድ ለሶስት አስርት ዓመታት ዓለም አቀፍ እውቅናን ማግኘት ያልቻለች ሲሆን ከኢትዮጵያ ጋር ባደረገችው ስምምነት ኢትዮጵያ በሊዝ የባህር ኃይል እና የንግድ የባህር በር እንዲኖራት አድርጋ በምላሹ እውቅናን ትጠብቃለች። ከዚህ ባለፈ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ድርሻ ይኖራታል።

ለሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ ይቅርታ ካልጠየቁ እና ለሶማሊያ ልዓላዊነት ክብር ካልሰጡ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን #እንደምታቋርጥ እየገለፁ ናቸው።

@tikvahethiopia