TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ድሬዳዋ❤
" ለከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የምንሰጠው #ክብር ትልቅ ነው " - ድሬዳዋ
በመላው ኢትዮጵያ ካሉ ከተሞች ለእንግድነትም ሆነ እዛው በከተማዋ እየሰሩ ለመኖር አስተማማኝ የሰላም እና ፀጥታ ደህንነት ካለባቸው ከተሞች አንዷ ድሬዳዋ ናት።
ከተማይቱ በአንድ ወቅት አጋጥሟት ከነበረው የፀጥታ መንገጫገጭ ከወጣች በኃላ ላለፉት ዓመታት እጅግ አስተማማኝ ደህንነቷና ሰላሟን አስጠብቃ ትገኛለች።
በማታም ሆነ በቀን በከተማዋ ውስጥ ለመንቀሳቀስ እንዲሁም ሰርቶ ለመግባት ያማታሰጋ ሆና ተሰርታለች።
ከዚህ ባለፈም ፤ #የኢትዮጵያ የጀርባ አጥንት በሆነው ዋና መንገድ ላይ በመገኘቷ በርካታ አሸክርካሪዎች በየዕለቱ ታስተናግዳለች።
ብዙ ርቀት በአስቸጋሪ የአየር ፀባይ የሚጓዙ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅና ፤ በሌሎች ቦታዎች ላይ የሚስተዋለው የተንዛዛ የትራፊክ ፖሊስ ጭቅጭቅ እንዳይኖርም እያደረገች ትገኛለች።
የድሬዳዋ ከተማ የትራፊክ ፖሊስም ረጅም መንገድ በረሃና አስቸጋሪ የአየር ንብረት በመቋቋም የሀገሪቱን ገቢ እና ወጪ ንግድ ለሚያፋጥኑ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሚሰጠው #ክብር ትልቅ መሆኑን የሚገልፅ ሲሆን ማንኛውም አሽከርካሪ በከተማው ውስጥ ሆኖ ችግር ከገጠመው ለማስተካከል ዘውትር ዝግጁ ነኝ ብሏል።
#ቪድዮ፦ ከወር በፊት የከተማይቱ አመራሮች ረጅም ርቀት ተጉዘው ድሬዳዋ ከተማ የደረሱ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን ለማክበር የታሸገ ውሃ ሲሰጧቸው የሚያሳይ ነው።
@tikvahethiopia
" ለከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የምንሰጠው #ክብር ትልቅ ነው " - ድሬዳዋ
በመላው ኢትዮጵያ ካሉ ከተሞች ለእንግድነትም ሆነ እዛው በከተማዋ እየሰሩ ለመኖር አስተማማኝ የሰላም እና ፀጥታ ደህንነት ካለባቸው ከተሞች አንዷ ድሬዳዋ ናት።
ከተማይቱ በአንድ ወቅት አጋጥሟት ከነበረው የፀጥታ መንገጫገጭ ከወጣች በኃላ ላለፉት ዓመታት እጅግ አስተማማኝ ደህንነቷና ሰላሟን አስጠብቃ ትገኛለች።
በማታም ሆነ በቀን በከተማዋ ውስጥ ለመንቀሳቀስ እንዲሁም ሰርቶ ለመግባት ያማታሰጋ ሆና ተሰርታለች።
ከዚህ ባለፈም ፤ #የኢትዮጵያ የጀርባ አጥንት በሆነው ዋና መንገድ ላይ በመገኘቷ በርካታ አሸክርካሪዎች በየዕለቱ ታስተናግዳለች።
ብዙ ርቀት በአስቸጋሪ የአየር ፀባይ የሚጓዙ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅና ፤ በሌሎች ቦታዎች ላይ የሚስተዋለው የተንዛዛ የትራፊክ ፖሊስ ጭቅጭቅ እንዳይኖርም እያደረገች ትገኛለች።
የድሬዳዋ ከተማ የትራፊክ ፖሊስም ረጅም መንገድ በረሃና አስቸጋሪ የአየር ንብረት በመቋቋም የሀገሪቱን ገቢ እና ወጪ ንግድ ለሚያፋጥኑ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሚሰጠው #ክብር ትልቅ መሆኑን የሚገልፅ ሲሆን ማንኛውም አሽከርካሪ በከተማው ውስጥ ሆኖ ችግር ከገጠመው ለማስተካከል ዘውትር ዝግጁ ነኝ ብሏል።
#ቪድዮ፦ ከወር በፊት የከተማይቱ አመራሮች ረጅም ርቀት ተጉዘው ድሬዳዋ ከተማ የደረሱ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን ለማክበር የታሸገ ውሃ ሲሰጧቸው የሚያሳይ ነው።
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የማይቻለውን የምታስችል . . . የዕድሜ ልክ መተማመኛ!!
ማን እንደ እናት!
እናት ባንክ
ማን እንደ እናት!
እናት ባንክ
#AddisAbaba
25 የግል ኮሌጆች ለ2016 ዓ.ም ምንም አይነት አዲስ ሰልጣኝ መቀበል እንዳይችሉ እግድ ተጣለባቸው።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ፤ የግል ኮሌጆች የምዝገባ ፍቃድ ለመውሰድ መረጃ እንዲያቀርቡ በደባድቤ የጠየቃቸው ኮሌጆች መረጃ ለማቅረብ ፍቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው እግድ እንደጣለባቸው አሳውቋል።
በመሆኑም፦
- ኩዊንስ ኮሌጅ ሃና ማርያም ካምፓስ
- ኩዊንስ ኮሌጅ መድሃኒዓለም ካምፓስ
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ አቢቹ ካምፓስ
- ሮያል ኮሌጅ ፒያሳ ካምፓስ
- ማይክሮሊንክ ኮሌጅ
- ላየን ኢትየጵያ ሆቴልነና ቢዝነስ ኮሌጅ 4 ኪሎ
- ዩኒየን ቪዥን ኮሌጅ
- ትሮፒካል ኮሌጅ ኦፍ ሚድሲን
- አዲስ ኮሌጅ
- ኩዊንስ ኮሌጅ ቤቴል ዐለም ባንክ ካምፓስ
- ኦርቢት ኮሌጅ
- ባዮስ ኮሌጅ
- ብራይት ኮሌጅ ጀሞ
- ስታንዳርድ ኮሌጅ ዩኒቨርሳል
- አይ ኪዉ ኮሌጅ
- ኬቢ ኢንተርናሽናል የቢዝነስና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
- ካፒታል ሆቴልና ማኔጅመንት ኮሌጅ
- አንድነት ኢንተረናሽናል ኮሌጅ ላም በረት
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ፊንፊኔ ካምፓስ
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ላንቻ ካምፓስ
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ካራ አሎ ካምፓስ
- ኩዊንስ ኮሌጅ መካኒሳ ካምፓ
- ኩዊንስ ኮሌጅ ልደታ ካምፓስ
- ኩዊንስ ኩሌጅ ሜክሲኮ ኬኬር በባለስልጣን መ/ቤቱ በመመሪያ መሰረት የምዘና ግብ ሳያሳኩና የምዝገባ ፍቃድ ሳያገኙ ለ2016 ዓ.ም ምንም አይነት አዲስ ሰልጣኝ መቀበል እንደማይችሉ አሳስቧል።
ተቋማቱ ለመጨረሻ ጊዜ አስፈላጊውን የሰልጣኞች የመረጃ እስከ 30/03/2016 ዓ.ም እንዲያቀርቡ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ሲሆን ይህ ባያደርጉ በመመሪያ 02/2012 እና 01/2014 መሰረት እውቅና ፍቃዳቸው እንደሚሰረዝ አስጠንቅቋል።
(የእግዱ ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
25 የግል ኮሌጆች ለ2016 ዓ.ም ምንም አይነት አዲስ ሰልጣኝ መቀበል እንዳይችሉ እግድ ተጣለባቸው።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ፤ የግል ኮሌጆች የምዝገባ ፍቃድ ለመውሰድ መረጃ እንዲያቀርቡ በደባድቤ የጠየቃቸው ኮሌጆች መረጃ ለማቅረብ ፍቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው እግድ እንደጣለባቸው አሳውቋል።
በመሆኑም፦
- ኩዊንስ ኮሌጅ ሃና ማርያም ካምፓስ
- ኩዊንስ ኮሌጅ መድሃኒዓለም ካምፓስ
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ አቢቹ ካምፓስ
- ሮያል ኮሌጅ ፒያሳ ካምፓስ
- ማይክሮሊንክ ኮሌጅ
- ላየን ኢትየጵያ ሆቴልነና ቢዝነስ ኮሌጅ 4 ኪሎ
- ዩኒየን ቪዥን ኮሌጅ
- ትሮፒካል ኮሌጅ ኦፍ ሚድሲን
- አዲስ ኮሌጅ
- ኩዊንስ ኮሌጅ ቤቴል ዐለም ባንክ ካምፓስ
- ኦርቢት ኮሌጅ
- ባዮስ ኮሌጅ
- ብራይት ኮሌጅ ጀሞ
- ስታንዳርድ ኮሌጅ ዩኒቨርሳል
- አይ ኪዉ ኮሌጅ
- ኬቢ ኢንተርናሽናል የቢዝነስና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
- ካፒታል ሆቴልና ማኔጅመንት ኮሌጅ
- አንድነት ኢንተረናሽናል ኮሌጅ ላም በረት
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ፊንፊኔ ካምፓስ
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ላንቻ ካምፓስ
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ካራ አሎ ካምፓስ
- ኩዊንስ ኮሌጅ መካኒሳ ካምፓ
- ኩዊንስ ኮሌጅ ልደታ ካምፓስ
- ኩዊንስ ኩሌጅ ሜክሲኮ ኬኬር በባለስልጣን መ/ቤቱ በመመሪያ መሰረት የምዘና ግብ ሳያሳኩና የምዝገባ ፍቃድ ሳያገኙ ለ2016 ዓ.ም ምንም አይነት አዲስ ሰልጣኝ መቀበል እንደማይችሉ አሳስቧል።
ተቋማቱ ለመጨረሻ ጊዜ አስፈላጊውን የሰልጣኞች የመረጃ እስከ 30/03/2016 ዓ.ም እንዲያቀርቡ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ሲሆን ይህ ባያደርጉ በመመሪያ 02/2012 እና 01/2014 መሰረት እውቅና ፍቃዳቸው እንደሚሰረዝ አስጠንቅቋል።
(የእግዱ ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የፌስቡክ ገፅን ይወዳጁ፣ በመሳተፍ ይሸለሙ! https://www.facebook.com/globalbankethiopia
#Global_Bank_Ethiopia #Shared_Success #Bank_in_Ethiopia
#Global_Bank_Ethiopia #Shared_Success #Bank_in_Ethiopia
#SafaricomEthiopia
ልጆቻችን ትምርታዊ ነገሮችን እንዲማሩ እንዲሁም የሚወዱትን አዝናኝ ቪደዮዎች እንዲመለከቱ ለቤትም ሆነ ይዘነው ለመንቀሳቀስ የሚመቸውን ቅመም MiFi ዛሬውኑ ወደ ሳፋሪኮም ሱቆች ጎራ ብለን በመግዛት ማርሻችንን አንቀይር
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC
#SafaricomEthiopia
#FurtherAheadTogether
ልጆቻችን ትምርታዊ ነገሮችን እንዲማሩ እንዲሁም የሚወዱትን አዝናኝ ቪደዮዎች እንዲመለከቱ ለቤትም ሆነ ይዘነው ለመንቀሳቀስ የሚመቸውን ቅመም MiFi ዛሬውኑ ወደ ሳፋሪኮም ሱቆች ጎራ ብለን በመግዛት ማርሻችንን አንቀይር
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC
#SafaricomEthiopia
#FurtherAheadTogether
#ኢሰመኮ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፦
#አማራክልል
በአዊ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ አምበላ ቀበሌ በዚገም ወረዳ ሶሪት ቀበሌ ከጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ ቀናት በተፈጠረው ብሔር ተኮር ግጭት ሞት እና የአካል ጉዳት እንዲሁም በኢንቨስትመንት ቦታዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ቡሬ ዙሪያ ወረዳ፣ ፈጣም ሰንቶም እና በቆጣቦ ቀበሌዎች ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. እና በኅዳር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. " ኢመደበኛ " የአማራ ታጣቂዎች መሆናቸው የተገለጸ ቡድኖች በሰነዘሩት ብሔር ተኮር ጥቃት እና ይህንኑ ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት በርካታ ሰዎች ላይ የሞት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት ደርሷል።
በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ነዋሪዎች ተፈናቅለው በቡሬ ዙሪያ ወረዳ በሚገኙ አጎራባች ቀበሌዎች እና ወደ ኦሮሚያ ክልል ለመሄድ ተገደዋል። የቀንድ ከብቶች ተዘርፈዋል።
#ቤኒሻንጉልጉሙዝ
አሶሳ ዞን፣ ኦዳ ብልድግሉ ወረዳ ሥር በሚገኙ ቤልሚሊ፣ አልከሻፊ እና ቤላደሩ ቀበሌዎች በሚኖሩ የቤኒሻንጉል ብሔር ተወላጆች እና አብረው በሚኖሩት የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ላይ ኅዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ-ሸኔ) ታጣቂ ቡድን አባላት በተፈጸመ ጥቃት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡
በጥቃቱ 17 ሰዎች መገደላቸው ፣ አንድ ሽማግሌ ታፍነው መወሰዳቸው፣ በ7 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰ መሆኑን ማወቅ ተችሏል።
በሦስቱ ቀበሌዎች ያሉ መንደሮች በአብዛኛው የተቃጠሉና የወደሙ መሆኑን፣ የእርሻ ሰብልና የቤት እንስሳትን ጨምሮ የንብረት ውድመት ደርሷል።
የቀበሌዎቹ ነዋሪዎች ጥቃቱን በመሸሽ ወደ አጎራባች ቀበሌዎችና በአቅራቢያው ወደ ሚገኘው መነሲቡ ወረዳ (ኦሮሚያ ክልል) ተፈናቅለዋል።
#ኦሮሚያክልል
- በአርሲ ዞን፣ ሸርካ ወረዳ ኅዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም. በጢጆ ለቡ ቀበሌ በግምት ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት በኋላ ማንነታቸው በውል ያልተለየ ታጣቂዎች በፈጸሙት ብሔር/ማንነት ተኮር ጥቃት 7 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና 3 ጎረቤቶቻቸው ጨምሮ በአጠቃላይ 10 ሰዎችን ገድለዋል።
በዚያው ዕለት ታጣቂዎቹ በሶሌ ዲገሉ ቀበሌ ቢያንስ 12 ሲቪል ሰዎችን ገድለዋል።
በሶሌ ዲገሉ ቀበሌ ከተገደሉ 12 ሰዎች መካከል አሥራ አንዱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው።
በኅዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም. በወረዳው በኮኘ ቀበሌ ታጣቂዎቹ በፈጸሙት ጥቃት የአንድ ቤተሰብ አባላት የነበሩ 8 ሰዎችን ገድለዋል።
ጥቃት አድራሾች ሟቾችን ከቤት እያስወጡ #አሰልፈው_እንደገደሏቸው፣ የተወሰኑትም በቤታቸው ውስጥ እንደተገደሉ ለማወቅ ተችሏል።
ከሟቾች መካከል #ጨቅላ_ሕፃንን ጨምሮ ነፍሰጡር ሴቶች እና ከ80 ዓመት በላይ የሆናቸው አረጋዊ ይገኙበታል፡፡
ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው በሕክምና ላይ ይገኛሉ፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች አሁንም ተደጋጋሚ ዛቻ እየደረሳቸው መሆኑን ለኮሚሽኑ ገልጸው፤ መንግሥት በአስቸኳይ እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል፡፡
በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ፣ የመካነ ኢየሱስ ቤተ-ክርስቲያን አባላት የነበሩት 9 ምዕመናን፣ ሽማግሌዎች፣ የወጣቶች ኮሚቴ አባላት እንዲሁም ሌሎች አገልጋዮችን ኅዳር 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ከሌሊት 8፡00 ሰዓት አካባቢ እስካሁን ማንነታቸው ባልተለዩ በታጠቁ ቡድኖች ተገድለዋል።
ግድያው የተፈፀመድ መላኮ መናሞ ቀበሌ ባለው ጫካ ውስጥ ሲሆን ገዳዮችን አስክሬናቸውን መጣላቸው ለማረጋገጥ ተችሏል።
(የኢሰመኮ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፦
#አማራክልል
በአዊ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ አምበላ ቀበሌ በዚገም ወረዳ ሶሪት ቀበሌ ከጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ ቀናት በተፈጠረው ብሔር ተኮር ግጭት ሞት እና የአካል ጉዳት እንዲሁም በኢንቨስትመንት ቦታዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ቡሬ ዙሪያ ወረዳ፣ ፈጣም ሰንቶም እና በቆጣቦ ቀበሌዎች ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. እና በኅዳር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. " ኢመደበኛ " የአማራ ታጣቂዎች መሆናቸው የተገለጸ ቡድኖች በሰነዘሩት ብሔር ተኮር ጥቃት እና ይህንኑ ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት በርካታ ሰዎች ላይ የሞት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት ደርሷል።
በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ነዋሪዎች ተፈናቅለው በቡሬ ዙሪያ ወረዳ በሚገኙ አጎራባች ቀበሌዎች እና ወደ ኦሮሚያ ክልል ለመሄድ ተገደዋል። የቀንድ ከብቶች ተዘርፈዋል።
#ቤኒሻንጉልጉሙዝ
አሶሳ ዞን፣ ኦዳ ብልድግሉ ወረዳ ሥር በሚገኙ ቤልሚሊ፣ አልከሻፊ እና ቤላደሩ ቀበሌዎች በሚኖሩ የቤኒሻንጉል ብሔር ተወላጆች እና አብረው በሚኖሩት የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ላይ ኅዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ-ሸኔ) ታጣቂ ቡድን አባላት በተፈጸመ ጥቃት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡
በጥቃቱ 17 ሰዎች መገደላቸው ፣ አንድ ሽማግሌ ታፍነው መወሰዳቸው፣ በ7 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰ መሆኑን ማወቅ ተችሏል።
በሦስቱ ቀበሌዎች ያሉ መንደሮች በአብዛኛው የተቃጠሉና የወደሙ መሆኑን፣ የእርሻ ሰብልና የቤት እንስሳትን ጨምሮ የንብረት ውድመት ደርሷል።
የቀበሌዎቹ ነዋሪዎች ጥቃቱን በመሸሽ ወደ አጎራባች ቀበሌዎችና በአቅራቢያው ወደ ሚገኘው መነሲቡ ወረዳ (ኦሮሚያ ክልል) ተፈናቅለዋል።
#ኦሮሚያክልል
- በአርሲ ዞን፣ ሸርካ ወረዳ ኅዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም. በጢጆ ለቡ ቀበሌ በግምት ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት በኋላ ማንነታቸው በውል ያልተለየ ታጣቂዎች በፈጸሙት ብሔር/ማንነት ተኮር ጥቃት 7 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና 3 ጎረቤቶቻቸው ጨምሮ በአጠቃላይ 10 ሰዎችን ገድለዋል።
በዚያው ዕለት ታጣቂዎቹ በሶሌ ዲገሉ ቀበሌ ቢያንስ 12 ሲቪል ሰዎችን ገድለዋል።
በሶሌ ዲገሉ ቀበሌ ከተገደሉ 12 ሰዎች መካከል አሥራ አንዱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው።
በኅዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም. በወረዳው በኮኘ ቀበሌ ታጣቂዎቹ በፈጸሙት ጥቃት የአንድ ቤተሰብ አባላት የነበሩ 8 ሰዎችን ገድለዋል።
ጥቃት አድራሾች ሟቾችን ከቤት እያስወጡ #አሰልፈው_እንደገደሏቸው፣ የተወሰኑትም በቤታቸው ውስጥ እንደተገደሉ ለማወቅ ተችሏል።
ከሟቾች መካከል #ጨቅላ_ሕፃንን ጨምሮ ነፍሰጡር ሴቶች እና ከ80 ዓመት በላይ የሆናቸው አረጋዊ ይገኙበታል፡፡
ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው በሕክምና ላይ ይገኛሉ፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች አሁንም ተደጋጋሚ ዛቻ እየደረሳቸው መሆኑን ለኮሚሽኑ ገልጸው፤ መንግሥት በአስቸኳይ እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል፡፡
በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ፣ የመካነ ኢየሱስ ቤተ-ክርስቲያን አባላት የነበሩት 9 ምዕመናን፣ ሽማግሌዎች፣ የወጣቶች ኮሚቴ አባላት እንዲሁም ሌሎች አገልጋዮችን ኅዳር 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ከሌሊት 8፡00 ሰዓት አካባቢ እስካሁን ማንነታቸው ባልተለዩ በታጠቁ ቡድኖች ተገድለዋል።
ግድያው የተፈፀመድ መላኮ መናሞ ቀበሌ ባለው ጫካ ውስጥ ሲሆን ገዳዮችን አስክሬናቸውን መጣላቸው ለማረጋገጥ ተችሏል።
(የኢሰመኮ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#መንገድ
" የመንገዱ ስራ በመጓተቱ ችግር ላይ ወድቀናል " - ነዋሪዎች
የጎሬ - ማሻ - ቴፒ አስፓልት መንገድ ስራ በመጓተቱ ችግር ላይ ወድቀናል ሲሉ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ገልጹ።
የአካባቢዉ ነዋሪዎች ከሸካ ዞን አስተዳዳሪና ከፌደራል መንገዶች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ኢንጅነር ደጀኔ ፈቃዱ ጋር ባደረጉት ወይይት " ስለምን ይቀለድብናል ? " ሲሉ በምሬት ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ መንገዱ ከተጀመረ ወዲህ በክረምት መንቀሳቀስ እንደተቸገሩና አምቡላንሶች እንኳን ስራ ማቆማቸዉን በመግለጽ የሚመለከተዉ አካል መፍትሄ እንዲሰጣቸዉ ጠይቀዋል።
የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በበኩላቸዉ ችግሩ የተከሰተዉ ከአራት አመት በፊት ከፌደራል መንገዶች ባለስልጣን ጋር ተፈራርሞ ወደስራ የገባዉ " ሀይወንዳይ ዲቨሎፕመንት " የተባለ የቻይና ድርጅት በዉሉ መሰረት መስራት ባለመቻሉ መሆኑን በመግለጽ የፌደራል ባለስልጣናት ክትትል እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
የማህበረሰቡን ቅሬታ የሰሙት የፌዴራል መንገዶች ባለስልጣን ምትክል ዳይሬክተር ኢንጅነር ደጀኔ ፈቃዱ በሰጡት ምላሽ ችግሩ መኖሩን ቢያዉቁም ማህበረሰቡ ባነሳዉ ልክ ይሆናል ብለዉ እንዳልገመቱ በመግለፅ በልዩ ክትትል መንገዱን እንደሚጨርሱና ያለዉን ችግር ለመቅረፍም የመንገድ እድሳቶችን እንደሚያከናዉኑ ገልጸዋል።
የጎሬ ማሻ ቴፒ አስፓልት መንገድ ከ138 ሚሊዮን ዶላር በላይ ተመድቦለት ከአራት አመት በፊት ቢጀመርም ያልቃል በተባለበት በዚህ ወቅት ግን 40 በመቶ ላይ ቆሟል።
ከሰሞኑን የመንገዱ ስራ ያለበት ደረጃ በሚመለከታቸው አካላት ተጎብኝቷል።
መረጃውን ያደረሰን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
" የመንገዱ ስራ በመጓተቱ ችግር ላይ ወድቀናል " - ነዋሪዎች
የጎሬ - ማሻ - ቴፒ አስፓልት መንገድ ስራ በመጓተቱ ችግር ላይ ወድቀናል ሲሉ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ገልጹ።
የአካባቢዉ ነዋሪዎች ከሸካ ዞን አስተዳዳሪና ከፌደራል መንገዶች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ኢንጅነር ደጀኔ ፈቃዱ ጋር ባደረጉት ወይይት " ስለምን ይቀለድብናል ? " ሲሉ በምሬት ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ መንገዱ ከተጀመረ ወዲህ በክረምት መንቀሳቀስ እንደተቸገሩና አምቡላንሶች እንኳን ስራ ማቆማቸዉን በመግለጽ የሚመለከተዉ አካል መፍትሄ እንዲሰጣቸዉ ጠይቀዋል።
የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በበኩላቸዉ ችግሩ የተከሰተዉ ከአራት አመት በፊት ከፌደራል መንገዶች ባለስልጣን ጋር ተፈራርሞ ወደስራ የገባዉ " ሀይወንዳይ ዲቨሎፕመንት " የተባለ የቻይና ድርጅት በዉሉ መሰረት መስራት ባለመቻሉ መሆኑን በመግለጽ የፌደራል ባለስልጣናት ክትትል እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
የማህበረሰቡን ቅሬታ የሰሙት የፌዴራል መንገዶች ባለስልጣን ምትክል ዳይሬክተር ኢንጅነር ደጀኔ ፈቃዱ በሰጡት ምላሽ ችግሩ መኖሩን ቢያዉቁም ማህበረሰቡ ባነሳዉ ልክ ይሆናል ብለዉ እንዳልገመቱ በመግለፅ በልዩ ክትትል መንገዱን እንደሚጨርሱና ያለዉን ችግር ለመቅረፍም የመንገድ እድሳቶችን እንደሚያከናዉኑ ገልጸዋል።
የጎሬ ማሻ ቴፒ አስፓልት መንገድ ከ138 ሚሊዮን ዶላር በላይ ተመድቦለት ከአራት አመት በፊት ቢጀመርም ያልቃል በተባለበት በዚህ ወቅት ግን 40 በመቶ ላይ ቆሟል።
ከሰሞኑን የመንገዱ ስራ ያለበት ደረጃ በሚመለከታቸው አካላት ተጎብኝቷል።
መረጃውን ያደረሰን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
" ከቅጣት በኋላ ካላስተካከሉ የማሸግ እንዲሁም ከዚህ አለፍ ሲል ከዘርፉ እስከማሰናበት እርምጃ ይወሰዳል " - በአ/አ ባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ
በአዲስ አበባ የሚገኙ ሆቴሎች እና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተጋጆቻቸውን " የተራቆተ " ልብስ የሚያስለብሱ ከሆነ ከ50 ሺህ ብር እስከ #እገዳ የሚደርስ ቅጣት የሚጥል ረቂቅ መዘጋጀቱ ታውቋል።
የረቂቁ ስያሜ ፦ " በሆቴል እና መሰል አገልግሎቶች ሰጪ ተቋማት የሚሠሩ ባለሙያዎች የደንብ ልብስ አለባበስ፣ የጌጣ ጌጥ እና የመዋቢያ አጠቃቀም ደንብ " ይሰኛል።
የተዘጋጀው ፦ በአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ነው።
በተለይም እንደ #ሥጋ_ቤቶች ባሉ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ በታየው የአስተናጋጆች " የተራቆተ አለባበስ " ምክንያት ረቂቁ ተዘጋጅቷል።
ረቂቁ ምን ያላል ?
- ከመስተንግዶ ስነምግባር እና ከሀገሪቱ ባህል የወጣ አለባበስ ይከለክላል።
- አስተናጋጆች ከባህል፣ ከጨዋነት ያፈነገጠ እና የተራቆተ አለባበስ እንዳይኖራቸው ይከለክላል።
- አስተናጋጆች #በሚታይ የሰውነት አካል ላይ ንቅሳት እንዳይኖራቸው ይከለክላል።
- #ወንዶች በምንም ተአምር ጆሮ ጌጥ አድርገው እንዳያስተናግዱ አይፈቀድም።
- የተቋማቱ ሠራተኞች ከሸሚዝ በላይ የሚሆን የአንገት ጌጥ እንዲሁም የእጅ ጌጥ እንዳይጠቀሙ ይከለክላል።
- ከጌጣ ጌጥ ጋር ተያይዞ ለሴቶች ጆሮ ጌጥ ይፈቀዳል። ነገር ግን ወደታች ያልወረደ እዚያው ላይ ልጥፍ የሚል መሆን አለበት። በተለይ በጆሮ ዙሪያ ላይ የሚደረግ ጆሮ ጌጥ አይፈቀድም።
- በሚታዩ የሰውነት አካላት ላይ . . . ምንም ዓይነት ንቅሳትም ሆነ ሌላም በሥዕል ተጠቅሞ ማስተናገድ አይቻልም። ይሁንና ከንቅሳት ጋር በተያየዘ የሚነሱ የባህል ጉዳዮች የደንቡን መጽደቅ ተከትሎ በሚወጣ መመሪያ ይታያል።
- ከአለባበስ፣ በሚታዩ የሰውነት አካላት ላይ ከሚደረጉ የጌጣ ጌጦች አጠቃቀም በተጨማሪ የፀጉር አያያዝን እንዲሁም የሚጠቀሟቸው ሽቶዎች መጠንን ላይ ገደብ ተቀምጧል።
ክልከላው እነማንን ይመለከታል ?
ሁሉንም ሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪዎችን ይመለከታል።
* ሆቴሎች፣
* ካፍቴሪያዎች፣
* ምሽት ቤቶች፣
* ማሳጅ ቤቶች፣
* ጂሞች
* የስቲም እና ሳውና አገልግሎት ሰጪዎች ክልከላው ከሚመለከታቸው ውስጥ ናቸው።
ቅጣትን በተመለከተ ረቂቅ ደንቡ ምን ይላል ?
ደንቡ ላይ የተቀመጠውን ድንጋጌ የሚተላለፉ ፦
☑ በ15 ቀናት ውስጥ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ማስጠንቀቂያ ይሰጣቸዋል።
☑ በ15 ቀን ጊዜ ውስጥ ማስተካከያ ያማያደርጉ ከሆነ የ50 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል።
☑ ከቅጣት በኋላም ካላስተካከለ የማሸግ እርምጃ ይወሰዳል። ከዚህ አለፍ ሲልም ከዘርፉ እስከማሰናበት እርምጃ ይወሰዳል።
መቼ ተግባራዊ ይደረጋል ?
ደንቡ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው ለአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ ቀርቦ ከጸደቀ በኋላ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ማግኘቱን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
" ከቅጣት በኋላ ካላስተካከሉ የማሸግ እንዲሁም ከዚህ አለፍ ሲል ከዘርፉ እስከማሰናበት እርምጃ ይወሰዳል " - በአ/አ ባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ
በአዲስ አበባ የሚገኙ ሆቴሎች እና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተጋጆቻቸውን " የተራቆተ " ልብስ የሚያስለብሱ ከሆነ ከ50 ሺህ ብር እስከ #እገዳ የሚደርስ ቅጣት የሚጥል ረቂቅ መዘጋጀቱ ታውቋል።
የረቂቁ ስያሜ ፦ " በሆቴል እና መሰል አገልግሎቶች ሰጪ ተቋማት የሚሠሩ ባለሙያዎች የደንብ ልብስ አለባበስ፣ የጌጣ ጌጥ እና የመዋቢያ አጠቃቀም ደንብ " ይሰኛል።
የተዘጋጀው ፦ በአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ነው።
በተለይም እንደ #ሥጋ_ቤቶች ባሉ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ በታየው የአስተናጋጆች " የተራቆተ አለባበስ " ምክንያት ረቂቁ ተዘጋጅቷል።
ረቂቁ ምን ያላል ?
- ከመስተንግዶ ስነምግባር እና ከሀገሪቱ ባህል የወጣ አለባበስ ይከለክላል።
- አስተናጋጆች ከባህል፣ ከጨዋነት ያፈነገጠ እና የተራቆተ አለባበስ እንዳይኖራቸው ይከለክላል።
- አስተናጋጆች #በሚታይ የሰውነት አካል ላይ ንቅሳት እንዳይኖራቸው ይከለክላል።
- #ወንዶች በምንም ተአምር ጆሮ ጌጥ አድርገው እንዳያስተናግዱ አይፈቀድም።
- የተቋማቱ ሠራተኞች ከሸሚዝ በላይ የሚሆን የአንገት ጌጥ እንዲሁም የእጅ ጌጥ እንዳይጠቀሙ ይከለክላል።
- ከጌጣ ጌጥ ጋር ተያይዞ ለሴቶች ጆሮ ጌጥ ይፈቀዳል። ነገር ግን ወደታች ያልወረደ እዚያው ላይ ልጥፍ የሚል መሆን አለበት። በተለይ በጆሮ ዙሪያ ላይ የሚደረግ ጆሮ ጌጥ አይፈቀድም።
- በሚታዩ የሰውነት አካላት ላይ . . . ምንም ዓይነት ንቅሳትም ሆነ ሌላም በሥዕል ተጠቅሞ ማስተናገድ አይቻልም። ይሁንና ከንቅሳት ጋር በተያየዘ የሚነሱ የባህል ጉዳዮች የደንቡን መጽደቅ ተከትሎ በሚወጣ መመሪያ ይታያል።
- ከአለባበስ፣ በሚታዩ የሰውነት አካላት ላይ ከሚደረጉ የጌጣ ጌጦች አጠቃቀም በተጨማሪ የፀጉር አያያዝን እንዲሁም የሚጠቀሟቸው ሽቶዎች መጠንን ላይ ገደብ ተቀምጧል።
ክልከላው እነማንን ይመለከታል ?
ሁሉንም ሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪዎችን ይመለከታል።
* ሆቴሎች፣
* ካፍቴሪያዎች፣
* ምሽት ቤቶች፣
* ማሳጅ ቤቶች፣
* ጂሞች
* የስቲም እና ሳውና አገልግሎት ሰጪዎች ክልከላው ከሚመለከታቸው ውስጥ ናቸው።
ቅጣትን በተመለከተ ረቂቅ ደንቡ ምን ይላል ?
ደንቡ ላይ የተቀመጠውን ድንጋጌ የሚተላለፉ ፦
☑ በ15 ቀናት ውስጥ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ማስጠንቀቂያ ይሰጣቸዋል።
☑ በ15 ቀን ጊዜ ውስጥ ማስተካከያ ያማያደርጉ ከሆነ የ50 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል።
☑ ከቅጣት በኋላም ካላስተካከለ የማሸግ እርምጃ ይወሰዳል። ከዚህ አለፍ ሲልም ከዘርፉ እስከማሰናበት እርምጃ ይወሰዳል።
መቼ ተግባራዊ ይደረጋል ?
ደንቡ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው ለአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ ቀርቦ ከጸደቀ በኋላ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ማግኘቱን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
#CBE
በቀጥታ ወደ ወዳጅ ዘመድዎ ሂሳብ!
EthioDirect
===========
በኢትዮ-ዳይሬክት ከውጭ ሀገር ገንዘብ መላኪያ መተግበሪያ የማስተር ወይም የቪዛ ካርድዎን ተጠቅመው በማንኛውም ጊዜና ቦታ በሞባይል ስልክዎ ቀጥታ ወደ ወዳጅ ዘመድዎ ሂሳብ መላክ ይችላሉ፡፡
#ቀላል #ፈጣን #አስተማማኝ #ነፃ
===========
የEthioDirect የሞባይል መተግበሪያ ከPlay Store ወይም App Store በማውረድ አገልግሎቱን ይጠቀሙ።
• ለአንድሮይድ ስልኮች
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.combanketh.ethiodirect
• ለአፕል ስልኮች
https://apps.apple.com/us/app/ethiodirect/id1602064491
በቀጥታ ወደ ወዳጅ ዘመድዎ ሂሳብ!
EthioDirect
===========
በኢትዮ-ዳይሬክት ከውጭ ሀገር ገንዘብ መላኪያ መተግበሪያ የማስተር ወይም የቪዛ ካርድዎን ተጠቅመው በማንኛውም ጊዜና ቦታ በሞባይል ስልክዎ ቀጥታ ወደ ወዳጅ ዘመድዎ ሂሳብ መላክ ይችላሉ፡፡
#ቀላል #ፈጣን #አስተማማኝ #ነፃ
===========
የEthioDirect የሞባይል መተግበሪያ ከPlay Store ወይም App Store በማውረድ አገልግሎቱን ይጠቀሙ።
• ለአንድሮይድ ስልኮች
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.combanketh.ethiodirect
• ለአፕል ስልኮች
https://apps.apple.com/us/app/ethiodirect/id1602064491
#Ethiopia #Adama
ሰላም ሚኒስቴር " የአገር ግንባታ መሠረታዊያን በሚል ርዕስ ለሚዲያ አካላት ከቅን ልቦች በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር " ትላንት በአዳማ ከተማ የአንድ ቀን የምክክር መድረክ አካሂዶ ነበር።
በመርሀ ግብሩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላም ሚኒስትር አቶ ታዬ ደንደኣ፣ መሰል የውይይት መድረክ በኢትዮጵያ ለሚስተዋለው ግጭትና አለመግባባት መፍትሄ ሊያመጣ እንደሚችል ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ ብዙ የሚያለያዩ ጉዳዮች ቢኖሩም፤ ብዙ የጋራ ትስስር የሚፈጥሩ ነገሮች እንዳሉ፣ ይሁን እንጅ ልዩነት ላይ በማተኮር ግጭቶችና አለመግባባቶች እየተፈጠሩ ከዚህ መደረሱን ገልጸዋል።
በመርሀ ግብሩ የተገኙት የቅን ልቦች በጎ ሥራ ድርጅት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ስንሻው፣ ኤዲቶሪያል ፖሊሲ በሌለበት ማኅበራዊ ሚዲያ ሰላምን መገንባት እንዴት እንደሚቻል በገለጹበት አውድ ጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበዋል።
አክለውም፣ ሰፊ ውይይት በማድረግ አገራችን ከድጡ ወደ ማጡ የምትሄድበትን ሁኔታ መቀልበስ እንደሚገባ አስረድተዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ ፦
አገር፣ አገረ መንግሥት፣ አገረ ብሔር
አገራዊ ማንነት፣ ምንነት፣ የአገራት ተሞክሮ
አገራዊ እሴት፣ ምንነት፣ የአገራት ተሞክሮ
አገራዊ ጥቅም፣ ምንነት፣ የአገራት ተሞክሮ
የሚዲያ ሚና ሰላምን ከመገንባት ረገድ
በሚሉት ነጥቦች ላይ ውይይት ተደርጓል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋግቶ የተላከ ነው።
@tikvahethiopia
ሰላም ሚኒስቴር " የአገር ግንባታ መሠረታዊያን በሚል ርዕስ ለሚዲያ አካላት ከቅን ልቦች በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር " ትላንት በአዳማ ከተማ የአንድ ቀን የምክክር መድረክ አካሂዶ ነበር።
በመርሀ ግብሩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላም ሚኒስትር አቶ ታዬ ደንደኣ፣ መሰል የውይይት መድረክ በኢትዮጵያ ለሚስተዋለው ግጭትና አለመግባባት መፍትሄ ሊያመጣ እንደሚችል ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ ብዙ የሚያለያዩ ጉዳዮች ቢኖሩም፤ ብዙ የጋራ ትስስር የሚፈጥሩ ነገሮች እንዳሉ፣ ይሁን እንጅ ልዩነት ላይ በማተኮር ግጭቶችና አለመግባባቶች እየተፈጠሩ ከዚህ መደረሱን ገልጸዋል።
በመርሀ ግብሩ የተገኙት የቅን ልቦች በጎ ሥራ ድርጅት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ስንሻው፣ ኤዲቶሪያል ፖሊሲ በሌለበት ማኅበራዊ ሚዲያ ሰላምን መገንባት እንዴት እንደሚቻል በገለጹበት አውድ ጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበዋል።
አክለውም፣ ሰፊ ውይይት በማድረግ አገራችን ከድጡ ወደ ማጡ የምትሄድበትን ሁኔታ መቀልበስ እንደሚገባ አስረድተዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ ፦
አገር፣ አገረ መንግሥት፣ አገረ ብሔር
አገራዊ ማንነት፣ ምንነት፣ የአገራት ተሞክሮ
አገራዊ እሴት፣ ምንነት፣ የአገራት ተሞክሮ
አገራዊ ጥቅም፣ ምንነት፣ የአገራት ተሞክሮ
የሚዲያ ሚና ሰላምን ከመገንባት ረገድ
በሚሉት ነጥቦች ላይ ውይይት ተደርጓል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋግቶ የተላከ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #Adama ሰላም ሚኒስቴር " የአገር ግንባታ መሠረታዊያን በሚል ርዕስ ለሚዲያ አካላት ከቅን ልቦች በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር " ትላንት በአዳማ ከተማ የአንድ ቀን የምክክር መድረክ አካሂዶ ነበር። በመርሀ ግብሩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላም ሚኒስትር አቶ ታዬ ደንደኣ፣ መሰል የውይይት መድረክ በኢትዮጵያ ለሚስተዋለው ግጭትና አለመግባባት መፍትሄ ሊያመጣ እንደሚችል…
#ETHIOPIA
" ለመሆኑ ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ ? " - አቶ ወንድሙ ኢብሳ
" መከላከያ ወንድሞቹን መግደል የለበትም፤ ወንድሞቹም መከላከያን መግደል የለባቸውም " - አቶ ታዬ ደንደአ
ሰላም ሚኒስቴር ረቡዕ ኅዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም አዳማ ከተማ አዘጋጅቶት በነበረው የውይይት መድረክ የተጋበዙት ጠበቃና የሕግ አማካሪ አቶ ወንድሙ ኢብሳ፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሌሎችም ጋዜጠኞች ፦
° ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ለማምጣት እየሄደበት ያለው ሁኔታ ፣
° ሁለት ጊዜ የከሸፈው የመንግሥትና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት / " ኦነግ ሸኔ " ድርድርን በተመለከተ የተሻለ አማራጭ ሊመጣ የሚችለው ምን ቢደረግ እንደሆነ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ተከታዮቹን ምላሾች እንካችሁ ብለዋል።
አቶ ወንድሙ ኢብሳ ስለሰላም ሚኒስቴር ምን አሉ?
* የሰላም ሚኒስቴር ላይ ጥያቄ አለኝ። ለመሆኑ እራሱ ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ ? ሰላም ሚኒስቴር በራሱ ጊዜ ሰላምን መስበክ አለበት በስውርም በአደባባይም ፡ አሁን ላይ ሰላም ሚኒስቴር ውስጥ የማያቸው ሰዎች በስውር አማፂያንን ሲደግፉ አያለሁ።
* ለምሳሌ የሁለተኛው የ " ሸኔ " እና የመንግሥት ድርድር ሲደረግ ከሰላም ሚኒስቴር ውስጥ የሆኑ ሰዎች (ስማቸው ከተፃፈ አላውቅም) ከሕውሓት ጋር የተደራደርክ፣ ሰላም የፈጠርክ " ሸኔ " ኦሮሞዎችን ለምንድን ነው እነርሱ የጠየቁትን ጥያቄ በሙሉ መልስ እሺ ያላልከው ? ያሉ አሉ።
* ጥያቄያቸው ደግሞ (የሸኔ) " የሽመልስ አብዲሳ ቦታ ለእኛ ይሰጠን፣ የኦሮሚያ መንግሥት አሁን ያለው ይፍረስና አዲስ ምርጫ ይካሄድ የሚል ነበር። ሰላም ሚኒስቴስ ውስጥ ሆኖ ይህን የሚጠይቅ ሰው ስላለ ሰላም ሚኒስቴር ጤናማ አይመስለኝም።
* አንድ ኢንጅነር ቢመረቅና ሥራ ቢያገኝ ለበርካታ ሰዎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል። ፖለቲከኛ ግን 'ስንት ሰው ልግደል' ነው የሚለው። በእኔ ምክንያት አንድ። ሰው መሞት የለበትም የሚል ፓርቲ ያስፈልጋል። በፖርቲ ሥም የሚፈጠር ሞትን የኢትዮጵያ ሕዝብ #ማውገዝ አለበት።
የመንግሥትና የሸኔ (ኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) ድርድር ዘላቂ መፍትሄው ምንድን ነው ? ለሚለው ጥያቄም፣ መንግሥትና የ " ሸኔ " ድርድር አሁንም መቀጠል አለበት ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ተሳታፊ ጋዜጠኞችና ሌሎች ምሁራን በበኩላቸው ፦
° ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየሄደበት ባለው ተደጋጋሚ መንገድ ለሰላም ለውጥ ማምጣት ይችላል ወይ ?
° በግጭት ምክንያት #የሚፈናቀሉ ሰዎችን አሁንም ማስቆም አልቻለም በዚህ ሁኔታ እንዴት ሰላምን መፍጠር ይቻላል ?
° መስሪያ ቤቱ ሰላምን ልማስረፅ ምን እየሰራ ነው ?
° የሚቀርቡ ጥናታዊ ፅሑፎች ለችግሮችን ይመጥናሉ ወይ ?
° በተጨባጭ መሬት ላይ ያለው ችግር እንዴት ይታያል ?
° በአማራና በኦሮሚያ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለመፍታት ለምን መግባባት ላይ ማድረስ አልተቻለም ?.... የሚሉ ጥያቄዎች ተሰንዝረዋል።
የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንድአ ምን ምላሽ ሰጡ ?
- ብዙ ሥራ እየሰራን መጥተናል ገና ብዙ ይቀረናል። ነገር ግን የሚገባንን ሁሉ #ሥልጣን ተሰጥቶናል ብለን አናምንም እንደ ሰላም ሚኒስቴር። አዎንታዊ ሰላም ከማስረፅ አኳያ ትልቅ ስልጣን አለን እየሰራን ነው። የሰላም ችግር ሲፈጠር፣ #ሰው ሲፈናቀል ያንን የማስቆም ስልጣን ግን ለእኛ አልተሰጠንም። ይሄ #የአወቃቀር ችግር ነው።
- የአደጋ ሥጋት እንኳ #ለእኛ አይደለም ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስቴር ፅሕፈት ቤት ነው። #ፓሊስ ለእኛ ተጠሪ አይደለም። መሆን የነበረበት እዚህ ነው። #የግጭት ሥጋት ሲኖር የምናዘው አንድም #ሚሊሻ የለንም። ስለዚህም ለሚፈጠሩ ግጭቶች የሰላም ሚኒስቴር #ሊወቀስ_አይገባም።
- ትክክል ነው በተመሳሳይ አይነት ሥራ የተለየ ውጤት አይፈጠርም። በእኛ በኩል ግን ተመሳሳይ ሥራ እየሰራን ነው ብለን አናምንም።
- ጥናታዊ ፅሑፎች እና በመሬት ላይ ያለውን ችግር በተመለከተ ለተነሳው ጥያቄ፣ የስልጣን፣ የኢኮኖሚ፣ የፍትህ ችግሮች አሉብን። ሥልጣን ካልተገደበ፣ ተጠያቂነት ካልተረጋገጠ፣ ኢኮኖሚው በፍትሃዊነት ካልተሰራጨ፣ ሌቦች ከተቆጣጠሩት…ሰላም ሊመጣ አይችልም።
- የተሰጠን ስልጣን ወቅታዊ ችግር መፍታት ሳይሆን ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት ነው።
- ተጠያቂነትን መስፈን አለበት። ከተጠያቂነት አኳያ ደግሞ ሥልጣን የተሰጣቸው አሉ። ለምሳሌ የፍትህ ሚኒስቴሩ ሥራው ተጠያቂነትን ከማስፈን አኳያ መሆን ነበረበት #ድርድር ከመሄድ ይልቅ።
- ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ? ለሚለው ጥያቄ አዎ ሰላም ነው። ሰላም የማንሆንበት ምክንያት የለንም። እኛ እያደረግን ያለነው የአገር አንድነት እንዲጠናከር፣ ሰላም እንዲሰፍን ተባብረን እየሰራን ነው።
- በኦሮሚያ ክልል ለ5 ዓመታት ጦርነት እየተካሄደ በአማራ፣ በኦሮሚያ ክልል የሚስተዋለው ችግር አለ። የትግራይ ክልሉም በጣም ይጸጽተናል። ግን ይህንን የሚያደርገው ከጀርባ ያለው ማነው? እሱን ነው ማወቅ የሚያስፈልገው።
- መከላከያ ሰራዊት ወንድሞቹን መግደል የለበትም፤ ወንድሞቹም መከላከያን መግደል የለባቸውም። ከብሔርተኝነት አኳያ ኦሮሞም ፣ አማራም ፣ ትግራይም በጣም አስቸጋሪ ችግር ነው ያለው። ለአማራ ችግር ኮዙ ኦሮሞ ነው፣ ለትግራይ አማራ ነው ተብሎ ይወሰዳል። ግን ችግሩ በእውነት ምንድን ነው ? ከዚያ ጀርባ ያሉት እነማን ናቸው? ይህንን ሚዲያዎች ለሕዝብ ማስገንዘብ አለባቸው ብለዋል።
ጥንቅሩ በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።
@tikvahethiopia
" ለመሆኑ ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ ? " - አቶ ወንድሙ ኢብሳ
" መከላከያ ወንድሞቹን መግደል የለበትም፤ ወንድሞቹም መከላከያን መግደል የለባቸውም " - አቶ ታዬ ደንደአ
ሰላም ሚኒስቴር ረቡዕ ኅዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም አዳማ ከተማ አዘጋጅቶት በነበረው የውይይት መድረክ የተጋበዙት ጠበቃና የሕግ አማካሪ አቶ ወንድሙ ኢብሳ፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሌሎችም ጋዜጠኞች ፦
° ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ለማምጣት እየሄደበት ያለው ሁኔታ ፣
° ሁለት ጊዜ የከሸፈው የመንግሥትና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት / " ኦነግ ሸኔ " ድርድርን በተመለከተ የተሻለ አማራጭ ሊመጣ የሚችለው ምን ቢደረግ እንደሆነ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ተከታዮቹን ምላሾች እንካችሁ ብለዋል።
አቶ ወንድሙ ኢብሳ ስለሰላም ሚኒስቴር ምን አሉ?
* የሰላም ሚኒስቴር ላይ ጥያቄ አለኝ። ለመሆኑ እራሱ ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ ? ሰላም ሚኒስቴር በራሱ ጊዜ ሰላምን መስበክ አለበት በስውርም በአደባባይም ፡ አሁን ላይ ሰላም ሚኒስቴር ውስጥ የማያቸው ሰዎች በስውር አማፂያንን ሲደግፉ አያለሁ።
* ለምሳሌ የሁለተኛው የ " ሸኔ " እና የመንግሥት ድርድር ሲደረግ ከሰላም ሚኒስቴር ውስጥ የሆኑ ሰዎች (ስማቸው ከተፃፈ አላውቅም) ከሕውሓት ጋር የተደራደርክ፣ ሰላም የፈጠርክ " ሸኔ " ኦሮሞዎችን ለምንድን ነው እነርሱ የጠየቁትን ጥያቄ በሙሉ መልስ እሺ ያላልከው ? ያሉ አሉ።
* ጥያቄያቸው ደግሞ (የሸኔ) " የሽመልስ አብዲሳ ቦታ ለእኛ ይሰጠን፣ የኦሮሚያ መንግሥት አሁን ያለው ይፍረስና አዲስ ምርጫ ይካሄድ የሚል ነበር። ሰላም ሚኒስቴስ ውስጥ ሆኖ ይህን የሚጠይቅ ሰው ስላለ ሰላም ሚኒስቴር ጤናማ አይመስለኝም።
* አንድ ኢንጅነር ቢመረቅና ሥራ ቢያገኝ ለበርካታ ሰዎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል። ፖለቲከኛ ግን 'ስንት ሰው ልግደል' ነው የሚለው። በእኔ ምክንያት አንድ። ሰው መሞት የለበትም የሚል ፓርቲ ያስፈልጋል። በፖርቲ ሥም የሚፈጠር ሞትን የኢትዮጵያ ሕዝብ #ማውገዝ አለበት።
የመንግሥትና የሸኔ (ኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) ድርድር ዘላቂ መፍትሄው ምንድን ነው ? ለሚለው ጥያቄም፣ መንግሥትና የ " ሸኔ " ድርድር አሁንም መቀጠል አለበት ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ተሳታፊ ጋዜጠኞችና ሌሎች ምሁራን በበኩላቸው ፦
° ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየሄደበት ባለው ተደጋጋሚ መንገድ ለሰላም ለውጥ ማምጣት ይችላል ወይ ?
° በግጭት ምክንያት #የሚፈናቀሉ ሰዎችን አሁንም ማስቆም አልቻለም በዚህ ሁኔታ እንዴት ሰላምን መፍጠር ይቻላል ?
° መስሪያ ቤቱ ሰላምን ልማስረፅ ምን እየሰራ ነው ?
° የሚቀርቡ ጥናታዊ ፅሑፎች ለችግሮችን ይመጥናሉ ወይ ?
° በተጨባጭ መሬት ላይ ያለው ችግር እንዴት ይታያል ?
° በአማራና በኦሮሚያ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለመፍታት ለምን መግባባት ላይ ማድረስ አልተቻለም ?.... የሚሉ ጥያቄዎች ተሰንዝረዋል።
የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንድአ ምን ምላሽ ሰጡ ?
- ብዙ ሥራ እየሰራን መጥተናል ገና ብዙ ይቀረናል። ነገር ግን የሚገባንን ሁሉ #ሥልጣን ተሰጥቶናል ብለን አናምንም እንደ ሰላም ሚኒስቴር። አዎንታዊ ሰላም ከማስረፅ አኳያ ትልቅ ስልጣን አለን እየሰራን ነው። የሰላም ችግር ሲፈጠር፣ #ሰው ሲፈናቀል ያንን የማስቆም ስልጣን ግን ለእኛ አልተሰጠንም። ይሄ #የአወቃቀር ችግር ነው።
- የአደጋ ሥጋት እንኳ #ለእኛ አይደለም ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስቴር ፅሕፈት ቤት ነው። #ፓሊስ ለእኛ ተጠሪ አይደለም። መሆን የነበረበት እዚህ ነው። #የግጭት ሥጋት ሲኖር የምናዘው አንድም #ሚሊሻ የለንም። ስለዚህም ለሚፈጠሩ ግጭቶች የሰላም ሚኒስቴር #ሊወቀስ_አይገባም።
- ትክክል ነው በተመሳሳይ አይነት ሥራ የተለየ ውጤት አይፈጠርም። በእኛ በኩል ግን ተመሳሳይ ሥራ እየሰራን ነው ብለን አናምንም።
- ጥናታዊ ፅሑፎች እና በመሬት ላይ ያለውን ችግር በተመለከተ ለተነሳው ጥያቄ፣ የስልጣን፣ የኢኮኖሚ፣ የፍትህ ችግሮች አሉብን። ሥልጣን ካልተገደበ፣ ተጠያቂነት ካልተረጋገጠ፣ ኢኮኖሚው በፍትሃዊነት ካልተሰራጨ፣ ሌቦች ከተቆጣጠሩት…ሰላም ሊመጣ አይችልም።
- የተሰጠን ስልጣን ወቅታዊ ችግር መፍታት ሳይሆን ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት ነው።
- ተጠያቂነትን መስፈን አለበት። ከተጠያቂነት አኳያ ደግሞ ሥልጣን የተሰጣቸው አሉ። ለምሳሌ የፍትህ ሚኒስቴሩ ሥራው ተጠያቂነትን ከማስፈን አኳያ መሆን ነበረበት #ድርድር ከመሄድ ይልቅ።
- ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ? ለሚለው ጥያቄ አዎ ሰላም ነው። ሰላም የማንሆንበት ምክንያት የለንም። እኛ እያደረግን ያለነው የአገር አንድነት እንዲጠናከር፣ ሰላም እንዲሰፍን ተባብረን እየሰራን ነው።
- በኦሮሚያ ክልል ለ5 ዓመታት ጦርነት እየተካሄደ በአማራ፣ በኦሮሚያ ክልል የሚስተዋለው ችግር አለ። የትግራይ ክልሉም በጣም ይጸጽተናል። ግን ይህንን የሚያደርገው ከጀርባ ያለው ማነው? እሱን ነው ማወቅ የሚያስፈልገው።
- መከላከያ ሰራዊት ወንድሞቹን መግደል የለበትም፤ ወንድሞቹም መከላከያን መግደል የለባቸውም። ከብሔርተኝነት አኳያ ኦሮሞም ፣ አማራም ፣ ትግራይም በጣም አስቸጋሪ ችግር ነው ያለው። ለአማራ ችግር ኮዙ ኦሮሞ ነው፣ ለትግራይ አማራ ነው ተብሎ ይወሰዳል። ግን ችግሩ በእውነት ምንድን ነው ? ከዚያ ጀርባ ያሉት እነማን ናቸው? ይህንን ሚዲያዎች ለሕዝብ ማስገንዘብ አለባቸው ብለዋል።
ጥንቅሩ በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።
@tikvahethiopia
" ከተፈታኝ መምህራኑ 49 በመቶ የሚሆኑት ከ50% በታች ዉጤት በማስመዝገባቸው ወደ ማስተማር እንዳይገቡ ተደርጓል " - የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ በዞኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመምህራን የመግቢያ ፈተና መስጠቱ ተሰምቷል።
ለመጀመርያ ጊዜ በዞኑ ትምርት መምሪያ ተዘጋጅቶ በተሰጠዉ የመግቢያ ፈተና ከአጠቃላይ ተፈታኞች 51 በመቶ ተፈታኞች ብቻ ናቸው 50% እና በላይ በማምጣት ያለፉት።
ከተፈታኝ መምህራኑ 49 በመቶ የሚሆኑት ከ50% በታች ዉጤት በማስመዝገባቸው ወደ ማስተማር ስራ እንዳይገቡ መደረጉንም መምሪያው አስታውቋል፡፡
ወደ ማስተማር አይገቡም የተባሉት ተፈትነው ከ50% በታች ያመጡ መምራን በቀጣይ ዕጣ ፋንታቸው ምንእንደሆነ በግልፅ አልተነገረም።
ፈተናውን ማለፍ ባልቻሉ መምህራን ክፍተት እንዳይፈጠር #አዳዲስ_መምህራን እየተመዘኑ እንዲቀጠሩ ይደረጋል ተብሏል፡፡
የዞኑ ትምህርት መምርያ በመምህርነት የተመረቁትን ለመጀመርያ ጊዜ የመግቢያ ፈተናን በመፈተን ወደ መማር ማስተማሩ ስራ እንዲገቡ መደረጉንና ይህ አሰራር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል።
የተማሪ ዉጤትና ስነ ምግባርን ለማሻሻል ከሚሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል የሰው ሀይል ልማትና ብቃት ወሳኝ በመሆኑ በቀጣይነት አዲስ የሚቀጠሩ መምህራን ለሚያስተምሩት የትምህርት እርከን የሚመጥንና ከመማር ማስተማሩ ጋር ተያያዠነት ያለዉ የመግቢያ ፈተና እየተሰጠ ብቁ የሰዉ ሀይል የትምህርት ዘርፉን እንዲቀላቀል በትኩረት ይሰራል ብሏል።
ምንም እንኳ ስራዉ ዘንድሮ የተጀመረ ቢሆንም በቀጣይነት የተቋሙ አሰራር ሁኖ እንዲፈፀም በትምህርት መምርያዉ ማኔጅመት ተወስኖ ወደ ስራ መገባቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚዛና ፋና ኤፍ ኤም / ከቤንች ሸኮ ዞን ኮሚኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ በዞኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመምህራን የመግቢያ ፈተና መስጠቱ ተሰምቷል።
ለመጀመርያ ጊዜ በዞኑ ትምርት መምሪያ ተዘጋጅቶ በተሰጠዉ የመግቢያ ፈተና ከአጠቃላይ ተፈታኞች 51 በመቶ ተፈታኞች ብቻ ናቸው 50% እና በላይ በማምጣት ያለፉት።
ከተፈታኝ መምህራኑ 49 በመቶ የሚሆኑት ከ50% በታች ዉጤት በማስመዝገባቸው ወደ ማስተማር ስራ እንዳይገቡ መደረጉንም መምሪያው አስታውቋል፡፡
ወደ ማስተማር አይገቡም የተባሉት ተፈትነው ከ50% በታች ያመጡ መምራን በቀጣይ ዕጣ ፋንታቸው ምንእንደሆነ በግልፅ አልተነገረም።
ፈተናውን ማለፍ ባልቻሉ መምህራን ክፍተት እንዳይፈጠር #አዳዲስ_መምህራን እየተመዘኑ እንዲቀጠሩ ይደረጋል ተብሏል፡፡
የዞኑ ትምህርት መምርያ በመምህርነት የተመረቁትን ለመጀመርያ ጊዜ የመግቢያ ፈተናን በመፈተን ወደ መማር ማስተማሩ ስራ እንዲገቡ መደረጉንና ይህ አሰራር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል።
የተማሪ ዉጤትና ስነ ምግባርን ለማሻሻል ከሚሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል የሰው ሀይል ልማትና ብቃት ወሳኝ በመሆኑ በቀጣይነት አዲስ የሚቀጠሩ መምህራን ለሚያስተምሩት የትምህርት እርከን የሚመጥንና ከመማር ማስተማሩ ጋር ተያያዠነት ያለዉ የመግቢያ ፈተና እየተሰጠ ብቁ የሰዉ ሀይል የትምህርት ዘርፉን እንዲቀላቀል በትኩረት ይሰራል ብሏል።
ምንም እንኳ ስራዉ ዘንድሮ የተጀመረ ቢሆንም በቀጣይነት የተቋሙ አሰራር ሁኖ እንዲፈፀም በትምህርት መምርያዉ ማኔጅመት ተወስኖ ወደ ስራ መገባቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚዛና ፋና ኤፍ ኤም / ከቤንች ሸኮ ዞን ኮሚኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia