TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። መግለጫውን የሰጡት የክልሉ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አቶ ኃይሉ አዱኛ ሲሆኑ ታንዛኒያ ውስጥ እየተካሄደ ነው ስለተባለው የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሰላም ድርድር ተጠይቀው ቀጥተኛ ምላሽ ሳይሰጡ አልፈዋል። አቶ ኃይሉ ፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አሁንም በክልሉ ዘላቂ ለሰላም እና ደህንነት እንዲሰፍን ፅኑ…
" ድርድሮች መፍትሔ ይዘው የሚመጡት ሁሉን አቀፍ፣ ግልጽነት የተላበሱና በአግባቡ የሚመሩ ሲሆኑ ብቻ ነው " - የ5 ፓርቲዎች የጋራ መግለጫ
መኢአድ ፣ ኢህአፓ ፣ የዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲና እናት ፓርቲ ዛሬ ከጋራ መግለጫ አውጥተዋል።
ፓርቲዎቹ ምን አሉ ?
- ማንኛውም የሚደረጉ ድርድሮችና ዉይይቶችን የኢትዮጵያ ሕዝብ በይፋ ሊያውቃቸው ይገባል።
- ግልጽ ያልሆኑና ከመጋረጃ ጀርባ የሚደረጉ ድርድሮችና ስምምነቶች ከመድረኩ እንደተወጣ ጥያቄ የሚያስነሱ መሆናቸዉ እንዳለ ሆኖ ዉለዉ አድረዉ ወደ ከፋ ጥፋት አገርንና ሕዝብን እንደሚወስዱ ከቅርብ ጊዜ ታሪካችን የምንረዳዉ ጉዳይ ነዉ፡፡
ለምሳሌ ፦
* " ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር ጋር ከአምስት ዓመታት በፊት አስመራ ላይ ተደረገ " የተባለዉና የኢትዮጵያ ሕዝብ በግልፅ ምንነቱን ያላወቀዉ ኋላም " የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት " ብሎ ራሱን ለሚጠራዉ ታጣቂ ኃይል መፈጠር ምክንያት እንደሆነ የሚነገረዉ ድብቅ ስምምነት አንዱ ነው።
* ፕሪቶሪያ ላይ የተደረገዉና እርሱን ተከትሎ ናይሮቢ ላይ በፌደራል መንግሥት እና በሕወሃት መካከል የተደረጉ የተሸፋፈኑ ድርድሮችና ተደረሰባቸዉ የተባሉ ስምምነቶች ዛሬም ድረስ ጥያቄ የሚያስነሱና ወደፊትም ጥያቄ በማስነሳት የሚቀጥሉ ናቸዉ።
- ለፖለቲካዊ ጥያቄ ፖለቲካዊ መፍትሄ ብቻ ሊሰጥ ይገባል። ለዚህም ግልፅነት የተላበሰ ድርድር ብቸኛ አማራጭ ነው።
- ከጥቂት ቀናት ወዲህ በመንግሥትና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል ድርድር እየተደረገ ነዉ " በተባለዉና የፌዴራል መንግሥት ድርድሩ ስለመታሰቡም ሆነ ስለመጀመሩ እንዲሁም የድርድሩ ተሳታፊዎችን ማንነት ባልገለፀበት ሁኔታ ላይ መረጃዎች መደመጣቸው የተደበላለቀ ስሜትና ከፍተኛ #ስጋት_አንዲሰማን አድርጓል፡፡
- አብዛኛዉ የኦሮሚያ አካባቢ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ በተሰነዘሩ የተለያዩ ዘግናኝ ጥቃቶች በግንባር ቀደምነት የአማራ ማኅበረሰብ ለአሰቃቂ ጅምላ ጭፍጨፋ መዳረጉ የማይታበል ሐቅ ሲሆን፤ ቀን በብልጽግና ማታ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ቀንበር ሥር ወድቆ የመከራ ህይወት እየገፋ ለሚገኘዉ የኦሮሞ ማኅበረሰብም ከመከራዉ ቀንበር የሚገላገልበት የተስፋ ጭላንጭል የሚፈጥር በመሆኑ የፖለቲካ ልዩነቶች በድርድር እንዲፈቱ ዛሬም ጽኑ ፍላጎታችን ነው።
- ድርድሩ እየተካሄደበት ያለዉ መንገድ የተሸፋፈነ መሆን፣ ለድረድሩ ምክንያት የሆኑ አጀንዳዎች ይፋ አለመደረጋቸው እና ከአገራችን ሕዝብ ጀርባ እየተከናወነ የሚገኝ ድርድር መሆኑ፣ ሠላም የራቀዉ ህዝባችንን ተስፋ መልሶ የሚያጨልም የጎራ ድርድር እንዳይሆን ያለንን ስጋት እንገልጻለን።
- የአገራችን ጉዳይ በመጠነ ሰፊ ችግሮች የተሞላ ሆኖ ሳለና ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ባሻገር ድርድሩ ሁሉን አቀፍ መሆን ሲገባዉ የተድበሰበሰና ቁንጽል መሆኑ ያሳስበናል።
(ከፓርቲዎቹ የተላከው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
NB. ምንም እንኳን መንግሥትም ይሁን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግሥት ሸኔ እያለ የሚጠራው) በታንዛኒያ ዳሬሰላም ለሰላም ድርድር መቀመጣቸውን እስካሁን በይፋ ባያሳውቁም / ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ ባይሰጡም ፤ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የዲፕሎማቲክ ሰዎች ግን የሰላም ድርድር እየተካሄደ መሆኑን አሳውቀዋል። ድርድሩ እየተመራ ያለውም በጦር አዛዦች ነው።
@tikvahethiopia
መኢአድ ፣ ኢህአፓ ፣ የዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲና እናት ፓርቲ ዛሬ ከጋራ መግለጫ አውጥተዋል።
ፓርቲዎቹ ምን አሉ ?
- ማንኛውም የሚደረጉ ድርድሮችና ዉይይቶችን የኢትዮጵያ ሕዝብ በይፋ ሊያውቃቸው ይገባል።
- ግልጽ ያልሆኑና ከመጋረጃ ጀርባ የሚደረጉ ድርድሮችና ስምምነቶች ከመድረኩ እንደተወጣ ጥያቄ የሚያስነሱ መሆናቸዉ እንዳለ ሆኖ ዉለዉ አድረዉ ወደ ከፋ ጥፋት አገርንና ሕዝብን እንደሚወስዱ ከቅርብ ጊዜ ታሪካችን የምንረዳዉ ጉዳይ ነዉ፡፡
ለምሳሌ ፦
* " ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር ጋር ከአምስት ዓመታት በፊት አስመራ ላይ ተደረገ " የተባለዉና የኢትዮጵያ ሕዝብ በግልፅ ምንነቱን ያላወቀዉ ኋላም " የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት " ብሎ ራሱን ለሚጠራዉ ታጣቂ ኃይል መፈጠር ምክንያት እንደሆነ የሚነገረዉ ድብቅ ስምምነት አንዱ ነው።
* ፕሪቶሪያ ላይ የተደረገዉና እርሱን ተከትሎ ናይሮቢ ላይ በፌደራል መንግሥት እና በሕወሃት መካከል የተደረጉ የተሸፋፈኑ ድርድሮችና ተደረሰባቸዉ የተባሉ ስምምነቶች ዛሬም ድረስ ጥያቄ የሚያስነሱና ወደፊትም ጥያቄ በማስነሳት የሚቀጥሉ ናቸዉ።
- ለፖለቲካዊ ጥያቄ ፖለቲካዊ መፍትሄ ብቻ ሊሰጥ ይገባል። ለዚህም ግልፅነት የተላበሰ ድርድር ብቸኛ አማራጭ ነው።
- ከጥቂት ቀናት ወዲህ በመንግሥትና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል ድርድር እየተደረገ ነዉ " በተባለዉና የፌዴራል መንግሥት ድርድሩ ስለመታሰቡም ሆነ ስለመጀመሩ እንዲሁም የድርድሩ ተሳታፊዎችን ማንነት ባልገለፀበት ሁኔታ ላይ መረጃዎች መደመጣቸው የተደበላለቀ ስሜትና ከፍተኛ #ስጋት_አንዲሰማን አድርጓል፡፡
- አብዛኛዉ የኦሮሚያ አካባቢ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ በተሰነዘሩ የተለያዩ ዘግናኝ ጥቃቶች በግንባር ቀደምነት የአማራ ማኅበረሰብ ለአሰቃቂ ጅምላ ጭፍጨፋ መዳረጉ የማይታበል ሐቅ ሲሆን፤ ቀን በብልጽግና ማታ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ቀንበር ሥር ወድቆ የመከራ ህይወት እየገፋ ለሚገኘዉ የኦሮሞ ማኅበረሰብም ከመከራዉ ቀንበር የሚገላገልበት የተስፋ ጭላንጭል የሚፈጥር በመሆኑ የፖለቲካ ልዩነቶች በድርድር እንዲፈቱ ዛሬም ጽኑ ፍላጎታችን ነው።
- ድርድሩ እየተካሄደበት ያለዉ መንገድ የተሸፋፈነ መሆን፣ ለድረድሩ ምክንያት የሆኑ አጀንዳዎች ይፋ አለመደረጋቸው እና ከአገራችን ሕዝብ ጀርባ እየተከናወነ የሚገኝ ድርድር መሆኑ፣ ሠላም የራቀዉ ህዝባችንን ተስፋ መልሶ የሚያጨልም የጎራ ድርድር እንዳይሆን ያለንን ስጋት እንገልጻለን።
- የአገራችን ጉዳይ በመጠነ ሰፊ ችግሮች የተሞላ ሆኖ ሳለና ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ባሻገር ድርድሩ ሁሉን አቀፍ መሆን ሲገባዉ የተድበሰበሰና ቁንጽል መሆኑ ያሳስበናል።
(ከፓርቲዎቹ የተላከው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
NB. ምንም እንኳን መንግሥትም ይሁን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግሥት ሸኔ እያለ የሚጠራው) በታንዛኒያ ዳሬሰላም ለሰላም ድርድር መቀመጣቸውን እስካሁን በይፋ ባያሳውቁም / ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ ባይሰጡም ፤ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የዲፕሎማቲክ ሰዎች ግን የሰላም ድርድር እየተካሄደ መሆኑን አሳውቀዋል። ድርድሩ እየተመራ ያለውም በጦር አዛዦች ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
ለዓመታት ተቋርጦ የነበረው ከግልገል በለስ - ድኋንዝ ባጉና - ድባጤ የመወስደው መንገድ ክፍት እንዲሆን መደረጉን የመተከል ዞን አስታወቀ።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ለሜሳ ዋውያ ፤ በአካባቢው በነበረው የጸጥታ ችግር ለዓመታት ተቋርጦ የነበው መንገድ አገልግሎት ጀምሯል ብለዋል።
መንገዱ ወደ አገልግሎት የተመለሰው በተደረገው የሰላም ስምምነት መሆኑን ጠቁመዋል።
በማንዱራ ወረዳ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጉህዴን ታጣቂዎች ትላንት የሰላም ስምምነት ማድረጋቸውን የገለፁት አስተዳዳሪው ይህን ተከትሎ መንገዱ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቀዋል።
መንገዱ ክፍት እንዲደረግ የሀገር ሽማግሌዎች እና ከፍተኛ አመራሮች ከሰላም ተመላሾች ጋር ውይይት ማድረጋቸውም ተመልክቷል።
ከዚህ ባለፈ ከፍተኛ አመራሮች በአካባቢው የሚገኙ የቱኒ ዳዱሽ እና የገሰስ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ምልከታ ያደረጉ ሲሆን ተቋማቱ ውስጥ ምንም አይነት የመማሪያ ቁሳቁስ ባለመኖሩ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ ፤ የነበሩ መምህራ አሁን ያለውን ሰላም ተጠቅመው ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
መረጃው ከክልሉ ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
ለዓመታት ተቋርጦ የነበረው ከግልገል በለስ - ድኋንዝ ባጉና - ድባጤ የመወስደው መንገድ ክፍት እንዲሆን መደረጉን የመተከል ዞን አስታወቀ።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ለሜሳ ዋውያ ፤ በአካባቢው በነበረው የጸጥታ ችግር ለዓመታት ተቋርጦ የነበው መንገድ አገልግሎት ጀምሯል ብለዋል።
መንገዱ ወደ አገልግሎት የተመለሰው በተደረገው የሰላም ስምምነት መሆኑን ጠቁመዋል።
በማንዱራ ወረዳ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጉህዴን ታጣቂዎች ትላንት የሰላም ስምምነት ማድረጋቸውን የገለፁት አስተዳዳሪው ይህን ተከትሎ መንገዱ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቀዋል።
መንገዱ ክፍት እንዲደረግ የሀገር ሽማግሌዎች እና ከፍተኛ አመራሮች ከሰላም ተመላሾች ጋር ውይይት ማድረጋቸውም ተመልክቷል።
ከዚህ ባለፈ ከፍተኛ አመራሮች በአካባቢው የሚገኙ የቱኒ ዳዱሽ እና የገሰስ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ምልከታ ያደረጉ ሲሆን ተቋማቱ ውስጥ ምንም አይነት የመማሪያ ቁሳቁስ ባለመኖሩ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ ፤ የነበሩ መምህራ አሁን ያለውን ሰላም ተጠቅመው ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
መረጃው ከክልሉ ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
#TecnoPhantomVFlip5G
ዘመኑ የደረሰበትን የመጨረሻ ቴክኖሎጂ ከፋሽን ጋር አጣምሮ የያዘውን ፋንተም ቪ ፍሊፕ 5ጂ ምርጫዎ ያድርጉ ።
ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#PhantomVFlip#TecnoMobile #TecnoEthiopia
ዘመኑ የደረሰበትን የመጨረሻ ቴክኖሎጂ ከፋሽን ጋር አጣምሮ የያዘውን ፋንተም ቪ ፍሊፕ 5ጂ ምርጫዎ ያድርጉ ።
ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#PhantomVFlip#TecnoMobile #TecnoEthiopia
#SafaricomEthiopia
ሰላም ድሬ! በኦአይ ብራይት ኢንተርናሽናል ኮሌጅ አካባቢ ፈጣኑ ኔትወርክ መጥቶልናል። የ07 ኔትዎርክን በመቀላቀል ማርሻችንን ወደ ፈጣኑ ያልተገደበ ኢንተርኔት ፍጥነት ያለው 4G ኔትዎርክ እንቀይር።
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
ሰላም ድሬ! በኦአይ ብራይት ኢንተርናሽናል ኮሌጅ አካባቢ ፈጣኑ ኔትወርክ መጥቶልናል። የ07 ኔትዎርክን በመቀላቀል ማርሻችንን ወደ ፈጣኑ ያልተገደበ ኢንተርኔት ፍጥነት ያለው 4G ኔትዎርክ እንቀይር።
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
የበርካታ ስደተኞች ደብዛቸው ጠፋ።
ከቀይ ባሕር ዳርቻ ስደተኞች የጫነች ጀልባ ሰጥማ አብዛኞቹ ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት የሆኑ ስደተኞች ደብዛቸው መጥፋቱን የየመን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
ጀልባዋ 75 ስደተኞች እንደጫነች ትላንት እሁድ መስጠሟን የየመን የባሕር ድንበር ጠባቂ ኃይል አሳውቋል።
ከስደተኞቹ መካከል 26 ሲተርፉ የቀሩት 49 ሰዎች የገቡበት አይታወቅም ተብሏል።
የጠፉትን ስደተኞች ለማግኘት ዛሬ ሰኞ ፍለጋ እየተካሔደ ነው ተብሏል።
የየመን መንግሥት የሚቆጣጠረው " ሳባ " የዜና ወኪል ጀልባዋ በኃይለኛ ንፋስ ሳቢያ ስትሰምጥ #ሴቶች እና #ሕጻትን ጨምሮ የጫነቻቸው ስደተኞች ወደ ባሕር መውደቃቸውን ስማቸው ያልተጠቀሰ የየመን ባሕር ድንበር ጠባቂ ኃይል ባለሥልጣን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
የተሻለ ገቢ እና የሥራ ዕድል ፍለጋ ወደ ባሕረ ሰላጤው ሀገራት ለማምራት የሚሞክሩ የአፍሪካ ቀንድ ሰዎች የጫነ ጀልባ በቀይ ባሕር ዳርቻዎች የመስጠም አደጋ ሲገጥመው የአሁኑ የመጀመሪያው አይደለም።
በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በየዓመቱ ከኢትዮጵያ፣ ከጅቡቲ እና ከሶማሊያ በየመን በኩል አድርገው ሳዑዲ አረቢያን ወደመሳሰሉ ሀገራት ለመጓዝ ጥረት ያደርጋሉ።
መረጃው የዶቼቨለ ሬድዮ / አሶሼትድ ፕሬስ / ሳባ ነው።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
ከቀይ ባሕር ዳርቻ ስደተኞች የጫነች ጀልባ ሰጥማ አብዛኞቹ ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት የሆኑ ስደተኞች ደብዛቸው መጥፋቱን የየመን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
ጀልባዋ 75 ስደተኞች እንደጫነች ትላንት እሁድ መስጠሟን የየመን የባሕር ድንበር ጠባቂ ኃይል አሳውቋል።
ከስደተኞቹ መካከል 26 ሲተርፉ የቀሩት 49 ሰዎች የገቡበት አይታወቅም ተብሏል።
የጠፉትን ስደተኞች ለማግኘት ዛሬ ሰኞ ፍለጋ እየተካሔደ ነው ተብሏል።
የየመን መንግሥት የሚቆጣጠረው " ሳባ " የዜና ወኪል ጀልባዋ በኃይለኛ ንፋስ ሳቢያ ስትሰምጥ #ሴቶች እና #ሕጻትን ጨምሮ የጫነቻቸው ስደተኞች ወደ ባሕር መውደቃቸውን ስማቸው ያልተጠቀሰ የየመን ባሕር ድንበር ጠባቂ ኃይል ባለሥልጣን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
የተሻለ ገቢ እና የሥራ ዕድል ፍለጋ ወደ ባሕረ ሰላጤው ሀገራት ለማምራት የሚሞክሩ የአፍሪካ ቀንድ ሰዎች የጫነ ጀልባ በቀይ ባሕር ዳርቻዎች የመስጠም አደጋ ሲገጥመው የአሁኑ የመጀመሪያው አይደለም።
በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በየዓመቱ ከኢትዮጵያ፣ ከጅቡቲ እና ከሶማሊያ በየመን በኩል አድርገው ሳዑዲ አረቢያን ወደመሳሰሉ ሀገራት ለመጓዝ ጥረት ያደርጋሉ።
መረጃው የዶቼቨለ ሬድዮ / አሶሼትድ ፕሬስ / ሳባ ነው።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በእኛ ክልል ደረጃ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው የሚታሰሩ ሰዎች የሉም " - አቶ ወንሰንየለህ ስምዖን (የሲዳማ ክልል ኮሚኒኬሽን ኃላፊ) የሲዳማ ክልል መንግሥት በሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) ለሚቀርበው ክስ ምላሽ ሰጠ። ክልሉ ምላሽ የሰጠው በኮሚኒኬሽን ቢሮው አማካኝነት ነው። የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ምንድነው ያለው ? (አቶ ገነነ ሀሰና - የፓርቲው የፅ/ቤት ኃላፊ / ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሀዋሳ…
#Update
" የቢሮ ቁልፍ ተሰብሮ ዶክመንት ተዘረፈብኝ " ያለው የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ የክልሉን መንግስት በመክሰስ ለምርጫ ቦርድ የአቤቱታ ደብዳቤ ጻፈ።
ፓርቲው ከሳምንት በፊት ተሰብሮብኛል ያለዉን ቢሮና የተዘረፈውን ዶክሜንት በተመለከተ ለምርጫ ቦርድ ከማሳወቅ ባለፈ ጉዳዩ ባፋጣኝ እንዲጣራለት ጠይቋል።
የፓርቲዉ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገነነ ሆሳና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳው ቤተሰብ አባል ባሳወቁት መሠረት ፤ አሁን ላይ የፓርቲዉን ቢሮ ቁልፍ በመቀየር የተቆጣጠረው የቀድሞ አባልና በዲስፕሊን ግድፈት የተባረረ ግለሰብ ከምርጫ ቦርድ እዉቅና አለኝ ማለቱን ተከትሎ ጉዳዩ እንዳሳሰባቸዉ ገለጸዋል።
በመሆኑም ምርጫ ቦርድ በነዚህ ጉዳዮች ላይ አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ እርምጃ እንዲወስድ በደብዳቤ መጠየቁን አሳውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ፓርቲው የክልሉ መንግስት በተለያየ ጊዜ የሚያደርስበትን ጫናና ወክቢያ እንዲያቆም ጠይቋል።
የታፔላዎች መነሳትና መጥፋት፣ የአባላት ያለፍርድቤት ትእዛዝ መታሰር ተጠናክሮ መቀጠሉን ፓርቲው ገልጿል።
በመሆኑም ምርጫ ቦርድ አስፈላጊዉን ምርመራ አድርጎ ፈጣን ማስተካከያ በማድረግ ጫናዉን እንዲያስቆምለት በጻፈዉ ደብዳቤ ጠይቋል።
ከቀናት በፊት የሲዳማ ክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን ፓርቲው በክልሉ ላይ የሚቀርበው ክስ እና ወቀሳ መሰረተቢስ ውንጀላ ነው ማለቱ ይታወሳል።
ከዚህ በተጨማሪ በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች እንደታሰሩ ፤ በክልሉ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው የሚታሰሩ ሰዎች እንደሌሉ አሳውቆ ነበር።
መረጃዉ የሀዋሳ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
" የቢሮ ቁልፍ ተሰብሮ ዶክመንት ተዘረፈብኝ " ያለው የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ የክልሉን መንግስት በመክሰስ ለምርጫ ቦርድ የአቤቱታ ደብዳቤ ጻፈ።
ፓርቲው ከሳምንት በፊት ተሰብሮብኛል ያለዉን ቢሮና የተዘረፈውን ዶክሜንት በተመለከተ ለምርጫ ቦርድ ከማሳወቅ ባለፈ ጉዳዩ ባፋጣኝ እንዲጣራለት ጠይቋል።
የፓርቲዉ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገነነ ሆሳና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳው ቤተሰብ አባል ባሳወቁት መሠረት ፤ አሁን ላይ የፓርቲዉን ቢሮ ቁልፍ በመቀየር የተቆጣጠረው የቀድሞ አባልና በዲስፕሊን ግድፈት የተባረረ ግለሰብ ከምርጫ ቦርድ እዉቅና አለኝ ማለቱን ተከትሎ ጉዳዩ እንዳሳሰባቸዉ ገለጸዋል።
በመሆኑም ምርጫ ቦርድ በነዚህ ጉዳዮች ላይ አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ እርምጃ እንዲወስድ በደብዳቤ መጠየቁን አሳውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ፓርቲው የክልሉ መንግስት በተለያየ ጊዜ የሚያደርስበትን ጫናና ወክቢያ እንዲያቆም ጠይቋል።
የታፔላዎች መነሳትና መጥፋት፣ የአባላት ያለፍርድቤት ትእዛዝ መታሰር ተጠናክሮ መቀጠሉን ፓርቲው ገልጿል።
በመሆኑም ምርጫ ቦርድ አስፈላጊዉን ምርመራ አድርጎ ፈጣን ማስተካከያ በማድረግ ጫናዉን እንዲያስቆምለት በጻፈዉ ደብዳቤ ጠይቋል።
ከቀናት በፊት የሲዳማ ክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን ፓርቲው በክልሉ ላይ የሚቀርበው ክስ እና ወቀሳ መሰረተቢስ ውንጀላ ነው ማለቱ ይታወሳል።
ከዚህ በተጨማሪ በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች እንደታሰሩ ፤ በክልሉ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው የሚታሰሩ ሰዎች እንደሌሉ አሳውቆ ነበር።
መረጃዉ የሀዋሳ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
#መቐለ
ዛሬ ህደር 3 ቀን 2016 ዓ.ም በመቐለ የታክሲ አገልግሎት ተቋርጦ ውሏል።
የመቋረጡ ምክንያት የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች በአጠቃላይ አድማ ላይ በመሆናቸው ነው።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የመቐለ ታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች አጠቃላይ አድማን ተከትሎ የተፈጠረውን መስተጓጎል በአካል ተገኝቶ ቃኝቷል።
ከለሊቱ 11:30 የታክሲ ረዳቶች ጩኸት የማይለይባት የመቐለ ከተማ ያለወትሮዋ የህዝብ ታክሲ የጠፉባት ሆና ውላለች።
ከከተማዋ የተለያዩ ጫፎች ወደ መሃል ከተማ ከ20 እስከ 10 ብር በመክፈል ሰው በሰው ላይ ተደራርበው ተጨናንቀው የሚጓጓዙት ተሳፋሪዎች በመንገድ ዳር ቆመው በብዛት ታክሲ ሲጠብቁ ነበር።
ተገልጋዮች ዝር የሚል ታክሲ ሲያጡ የመክፈል አቅም ያላቸው በባጃጅ ኮንትራት ከፍለው ሲጓዙ አቅሙ የሚያጥራቸው ደግሞ በእግራቸው ለመጓዝ ተገደዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ሪፓርተር ረፋድ አከባቢ ታክሲዎች አድማ መምታቸውን ለመገንዘብ ችሏል።
የታክሲ አገልግሎቱ መቋረጥ አስመልክቶ ተገልጋዮች አነጋግሯል።
ወዲ ቐሺ ፣ ዘርኣያዕቆብና ሰናይት የተባሉት ተጠቃሚዎች እንደሚሉት ፤ " የታክሲዎች አድማ በክልሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚታየው በሃይል በመጫን ፍላጎት ለማሳካት የመሻት ዝንባሌ ነው " ብለዋል።
የታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ግን የተገልጋዮቹን አስተያየት ፍፁም በመቃረን ፤ ህዝብ የመበዝበዝና የማጉላላት ፍላጎት እንደሌላቸው ገልጸዋል።
ቢሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየናረ በመሄድ ላይ የሚገኘው የኑሮ ሁኔታ ፣ የመኪና እቃ መለዋወጫ መወደድ (የመኪና 5 ሊትር ዘይት ከብር 500 በአምስት እጥፍ ጨምሮ ወደ ብር 2500 ከፍ ማለቱ እንደ ማሳያ ይጠቅሳሉ) ፤ የሹፌርና የረዳት ክፍያን ገበያ ላይ ባለው ታሪፍ መሸፈን እጅግ እንደከበዳቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ገልፀዋል።
የታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች በማከልም አሁን ባለው 10 ብር ለአንድ ተሳፋሪ ታሪፍ ኑሮአቸውን አሸንፈው የመኪኖቻቸው ድህንነት ለመጠበቅ እንደሚቸገሩ ፤ ስለሆነም መንግስት ታሪፉ እንዲያስተካክል ከአንድ ወር በፊት በማህበራቸው በኩል ጥያቄ እንዳቀረቡ ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ መንግስት ጥያቄያቸው መመለስ ትቶ አንድ ሰው ተርፍ ጭነው ከተገኙ ብር 500 መቅጣቱ አጠቃላይ የስራ የማቆም አድማ እንዲያደርጉ ምክንያት እንደሆነ ተናግረዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ስለ ጉዳዩ የመንግስት ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም ፤ ከመንግስት የሚሰጠው ምላሽና የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች ቀጣይ እርምጃ ተከታትሎ ያቀርባል።
@tikvahethiopia
ዛሬ ህደር 3 ቀን 2016 ዓ.ም በመቐለ የታክሲ አገልግሎት ተቋርጦ ውሏል።
የመቋረጡ ምክንያት የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች በአጠቃላይ አድማ ላይ በመሆናቸው ነው።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የመቐለ ታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች አጠቃላይ አድማን ተከትሎ የተፈጠረውን መስተጓጎል በአካል ተገኝቶ ቃኝቷል።
ከለሊቱ 11:30 የታክሲ ረዳቶች ጩኸት የማይለይባት የመቐለ ከተማ ያለወትሮዋ የህዝብ ታክሲ የጠፉባት ሆና ውላለች።
ከከተማዋ የተለያዩ ጫፎች ወደ መሃል ከተማ ከ20 እስከ 10 ብር በመክፈል ሰው በሰው ላይ ተደራርበው ተጨናንቀው የሚጓጓዙት ተሳፋሪዎች በመንገድ ዳር ቆመው በብዛት ታክሲ ሲጠብቁ ነበር።
ተገልጋዮች ዝር የሚል ታክሲ ሲያጡ የመክፈል አቅም ያላቸው በባጃጅ ኮንትራት ከፍለው ሲጓዙ አቅሙ የሚያጥራቸው ደግሞ በእግራቸው ለመጓዝ ተገደዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ሪፓርተር ረፋድ አከባቢ ታክሲዎች አድማ መምታቸውን ለመገንዘብ ችሏል።
የታክሲ አገልግሎቱ መቋረጥ አስመልክቶ ተገልጋዮች አነጋግሯል።
ወዲ ቐሺ ፣ ዘርኣያዕቆብና ሰናይት የተባሉት ተጠቃሚዎች እንደሚሉት ፤ " የታክሲዎች አድማ በክልሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚታየው በሃይል በመጫን ፍላጎት ለማሳካት የመሻት ዝንባሌ ነው " ብለዋል።
የታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ግን የተገልጋዮቹን አስተያየት ፍፁም በመቃረን ፤ ህዝብ የመበዝበዝና የማጉላላት ፍላጎት እንደሌላቸው ገልጸዋል።
ቢሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየናረ በመሄድ ላይ የሚገኘው የኑሮ ሁኔታ ፣ የመኪና እቃ መለዋወጫ መወደድ (የመኪና 5 ሊትር ዘይት ከብር 500 በአምስት እጥፍ ጨምሮ ወደ ብር 2500 ከፍ ማለቱ እንደ ማሳያ ይጠቅሳሉ) ፤ የሹፌርና የረዳት ክፍያን ገበያ ላይ ባለው ታሪፍ መሸፈን እጅግ እንደከበዳቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ገልፀዋል።
የታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች በማከልም አሁን ባለው 10 ብር ለአንድ ተሳፋሪ ታሪፍ ኑሮአቸውን አሸንፈው የመኪኖቻቸው ድህንነት ለመጠበቅ እንደሚቸገሩ ፤ ስለሆነም መንግስት ታሪፉ እንዲያስተካክል ከአንድ ወር በፊት በማህበራቸው በኩል ጥያቄ እንዳቀረቡ ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ መንግስት ጥያቄያቸው መመለስ ትቶ አንድ ሰው ተርፍ ጭነው ከተገኙ ብር 500 መቅጣቱ አጠቃላይ የስራ የማቆም አድማ እንዲያደርጉ ምክንያት እንደሆነ ተናግረዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ስለ ጉዳዩ የመንግስት ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም ፤ ከመንግስት የሚሰጠው ምላሽና የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች ቀጣይ እርምጃ ተከታትሎ ያቀርባል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሶማሊያ ሶማሊያ ቲክቶክ እና ቴሌግራም እንዲሁም 1ኤክስቤት (1XBet) የተባለውን የስፖርት ውርርድ ገጽን እንዲዘጉ አዘዘች። " ቲክቶክ " እና " ቴሌግራም " የአሸባሪዎች መረጃ ማስተላለፊያ ሆነዋል ብሏል የሶማሊያ መንግሥት። መተግበሪያዎቹ " አሸባሪ ድርጅቶች እና ቡድኖች አሰቃቂ የሆኑ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን እንዲሁም ፎቶግራፎችን በማሰራጨት ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ጥቅም ላይ ውለዋል " ሲል ገልጿል።…
ኔፓል ሀገሪቱ ላይ " ቲክቶክ " እንዲታገድ ወሰነች።
ኔፓል ፤ ማህበራዊ መስተጋብርን የሚረብሹና የቤተሰብን መዋቅር እንዲሁም ማህበራዊ ግንኙነቶችን የሚያውኩ ይዘቶችን ለማጋራት ጥቅም ላይ እየዋለ ነው ያለችውን የቻይናውን " #ቲክቶክ " መተግበሪያ እንዲታገድ ውሳኔ አሳለፈች።
ሀገሪቱ ፤ " ቲክቶክ " በማህበራዊ መስተጋብር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው ያለች ሲሆን በመተግበሪያው ላይ የሚለቀቁት ተንቀሳቃሽ ምስሎችና የሚተላለፉት መልዕክቶች ለሀገሪቱ ህዝብ ባሕል እንግዳ የሆኑና ቀድሞ በማህበረሰቡ ዘንድ የነበረውን ማህበራዊ መስተጋብር የሚሸረሸሩ ናቸው ስትል አሳውቃለች።
የመገናኛ ና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሬካ ሻርማ ፤ የቲክቶክ ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ የሀገሪቱ ካቢኔ ተሰብስቦ መመክሩንና #ለማገድ ውሳኔ እንዳሳለፈ ይፋ አድርገል።
የቴሌኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን ኃላፊ የሆኑት ፑሩሾታም ካናል በሰጡት ቃል ፤ በኔፓል የሚገኙ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢዎች " ቲክቶክ " ን እንዲዘጉ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል፡፡
አንዳንዶች መዝጋታቸውን ሌሎችም በቀጣይ እንደሚያደርጉት ጠቁመዋል።
" ቲክቶክ " የማህበራዊ ህይወት ላይ እያሳደረ ነው ከተባለው አሉታዊ ተፅእኖ በተጨማሪ በርካታ ከመተግበሪያው ጋር የተያያዙ የሳይበር ደኅንነት ወንጀሎች መመዝገባቸው ተመላክቷል።
የኔፓል መንግስት ተቃዋሚዎች ውሳኔው " ውጤታማነት ፣ ብስለት እና ኃላፊነት " የጎደለው ነው ሲሉ ተቃውመዋል።
አንድ የእገዳው ተቃዋሚ ፤ በሌሎችም ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ብዙ የማያስፈልጉ ነገሮች እንዳሉ አንስተው መደረግ ያለበት እነሱን መቆጣጠር ነው እንጂ መገደብ አይደለም ብለዋል።
ወደ አንድ ቢሊዮን የሚጠጉ ወርሃዊ ተጠቃሚዎች አሉት የሚባለው ታዋቂው የቪዲዮ ማጋሪያ መድረክ " ቲክቶክ " መረጃን በመበርበር እና በወጣቶች ላይ ጎጂ ተፅእኖ እያመጣነው በሚል ከዚህ ቀደም በአንዳንድ ሀገራት እገዳ ገጥሞታል።
አንዳንድ ሀገራት መተግበሪያው የቻይና መንግሥት መረጃ ለመበርበር ይጠቀምበታል በሚል ይተቹታል።
የቻይናው ባይትዳንስ ኩባንያ ንብረት የሆነው " ቲክቶክ " በቤጂንግ ቀጥተኛ ቁጥጥር ስር ነው እየተባለ የሚቀርቡበትን ክስና ትችቶችን በተደጋጋሚ #እንደማይቀበል አሳውቋል።
@tikvahethiopia
ኔፓል ፤ ማህበራዊ መስተጋብርን የሚረብሹና የቤተሰብን መዋቅር እንዲሁም ማህበራዊ ግንኙነቶችን የሚያውኩ ይዘቶችን ለማጋራት ጥቅም ላይ እየዋለ ነው ያለችውን የቻይናውን " #ቲክቶክ " መተግበሪያ እንዲታገድ ውሳኔ አሳለፈች።
ሀገሪቱ ፤ " ቲክቶክ " በማህበራዊ መስተጋብር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው ያለች ሲሆን በመተግበሪያው ላይ የሚለቀቁት ተንቀሳቃሽ ምስሎችና የሚተላለፉት መልዕክቶች ለሀገሪቱ ህዝብ ባሕል እንግዳ የሆኑና ቀድሞ በማህበረሰቡ ዘንድ የነበረውን ማህበራዊ መስተጋብር የሚሸረሸሩ ናቸው ስትል አሳውቃለች።
የመገናኛ ና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሬካ ሻርማ ፤ የቲክቶክ ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ የሀገሪቱ ካቢኔ ተሰብስቦ መመክሩንና #ለማገድ ውሳኔ እንዳሳለፈ ይፋ አድርገል።
የቴሌኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን ኃላፊ የሆኑት ፑሩሾታም ካናል በሰጡት ቃል ፤ በኔፓል የሚገኙ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢዎች " ቲክቶክ " ን እንዲዘጉ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል፡፡
አንዳንዶች መዝጋታቸውን ሌሎችም በቀጣይ እንደሚያደርጉት ጠቁመዋል።
" ቲክቶክ " የማህበራዊ ህይወት ላይ እያሳደረ ነው ከተባለው አሉታዊ ተፅእኖ በተጨማሪ በርካታ ከመተግበሪያው ጋር የተያያዙ የሳይበር ደኅንነት ወንጀሎች መመዝገባቸው ተመላክቷል።
የኔፓል መንግስት ተቃዋሚዎች ውሳኔው " ውጤታማነት ፣ ብስለት እና ኃላፊነት " የጎደለው ነው ሲሉ ተቃውመዋል።
አንድ የእገዳው ተቃዋሚ ፤ በሌሎችም ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ብዙ የማያስፈልጉ ነገሮች እንዳሉ አንስተው መደረግ ያለበት እነሱን መቆጣጠር ነው እንጂ መገደብ አይደለም ብለዋል።
ወደ አንድ ቢሊዮን የሚጠጉ ወርሃዊ ተጠቃሚዎች አሉት የሚባለው ታዋቂው የቪዲዮ ማጋሪያ መድረክ " ቲክቶክ " መረጃን በመበርበር እና በወጣቶች ላይ ጎጂ ተፅእኖ እያመጣነው በሚል ከዚህ ቀደም በአንዳንድ ሀገራት እገዳ ገጥሞታል።
አንዳንድ ሀገራት መተግበሪያው የቻይና መንግሥት መረጃ ለመበርበር ይጠቀምበታል በሚል ይተቹታል።
የቻይናው ባይትዳንስ ኩባንያ ንብረት የሆነው " ቲክቶክ " በቤጂንግ ቀጥተኛ ቁጥጥር ስር ነው እየተባለ የሚቀርቡበትን ክስና ትችቶችን በተደጋጋሚ #እንደማይቀበል አሳውቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ፦ ዛሬ ህዳር 3/2016 ዓ.ም በመቐለ የተካሄደው የታክሲ አገልግሎት የማቆም አድማ ከማህበራቱ እውቅና ውጪ የተፈፀመና ተቀባይነት የሌለው ተግባር መሆኑን ሶስት የታክሲ ማህበራት ባወጡት መግለጫ አሳወቁ።
ማህበራቱ ከሰዓት በኃላ ባሰራጩት ይፋዊ መግለጫ ፤ " ለመንግስት ያቀረብነው ጥያቄ በህጋዊ መንገድ እንዲመለስ ጥረት እያካሄድን ባለንበት ጊዜ አገልግሎት ማቋረጥ አግባብ አይደለም " ብለዋል።
አድማ የመቱ ሁሉ ችግሩ ከመባባሱ በፊት ወደ ስራ መመለስ አለባቸው ብለዋል።
ዛሬ በመቐለ የታክሲ አድማ በመመታቱ በርካቶች መጉላላት ደርሶባቸዋል ፤ ያላቸው በባጃጅ ኮንትራት እየያዙ ሲሄዱ አቅም የሚያንሳቸው ደግሞ በእግራቸው ለመጓዝ ተገደው ውለዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል በዚሁ ርእሰ ጉዳይ ዙሪያ ያሉ መረጃዎችን እየተከታተለ እንደሚያቀርብ ያሳውቃል።
@tikvahethiopia
ማህበራቱ ከሰዓት በኃላ ባሰራጩት ይፋዊ መግለጫ ፤ " ለመንግስት ያቀረብነው ጥያቄ በህጋዊ መንገድ እንዲመለስ ጥረት እያካሄድን ባለንበት ጊዜ አገልግሎት ማቋረጥ አግባብ አይደለም " ብለዋል።
አድማ የመቱ ሁሉ ችግሩ ከመባባሱ በፊት ወደ ስራ መመለስ አለባቸው ብለዋል።
ዛሬ በመቐለ የታክሲ አድማ በመመታቱ በርካቶች መጉላላት ደርሶባቸዋል ፤ ያላቸው በባጃጅ ኮንትራት እየያዙ ሲሄዱ አቅም የሚያንሳቸው ደግሞ በእግራቸው ለመጓዝ ተገደው ውለዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል በዚሁ ርእሰ ጉዳይ ዙሪያ ያሉ መረጃዎችን እየተከታተለ እንደሚያቀርብ ያሳውቃል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። መግለጫውን የሰጡት የክልሉ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አቶ ኃይሉ አዱኛ ሲሆኑ ታንዛኒያ ውስጥ እየተካሄደ ነው ስለተባለው የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሰላም ድርድር ተጠይቀው ቀጥተኛ ምላሽ ሳይሰጡ አልፈዋል። አቶ ኃይሉ ፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አሁንም በክልሉ ዘላቂ ለሰላም እና ደህንነት እንዲሰፍን ፅኑ…
#Update
የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግሥት ሸኔ እያለ የሚጠራው የታጠቀ ኃይል) በታንዛኒያ የሰላም ድርድር እየተደረገ ነው ሲል መግለጫ አወጣ።
ምንም እንኳን ከቀናት በፊት የዲፕሎማቲክ ምንጮች በታንዛኒያ ዳሬሰላም የኢትዮጵያ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት በወታደራዊ አዛዦች አማካኝነት ለሰላም ድርድር መቀመጣቸውን ቢያሳውቁም እስከዛሬ ደረስ ከሁለቱም በኩል ምንም ነገር ሳይባል ቆይቷል።
በዛሬው ዕለት ግን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ድርድሩን በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ አጭር መግለጫ አውጥቷል።
በዚህም መግለጫው ፤ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር-የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የልዑካን ቡድን በዋና አዛዥ ጃል መሮ ድሪባ እና ምክትላቸው ጃል ገመቹ አቦዬ እየተመራ ለከፍተኛ የሰላም ድርድር ታንዛኒያ መግባቱን አሳውቋል።
አመራሮቹ ደህንነታቸው ተጠብቆ ከነበሩበት ኦሮሚያ ወደ ድርድሩ ቦታ ታንዛኒያ እንዲገቡ ለማድረግ ሲባል በሰዓቱ ይፋዊ መግለጫ / መረጃ እንዳልተሰጠ ጠቁሟል።
" የህዝባችንን ምኞት እውን የሚያደርግ እና የሰማዕቶቻችንን መስዋዕትነት የሚያከብር ሰላማዊ የፖለቲካ እልባት ለማግኘት በቁርጠኝነት እንቀጥላለን " ያለው ይኸው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት መግለጫ የሰላም ድርድሩ ሲጠናቀቅ ተጨማሪ መረጃዎችን እንሰጣለን ብሏል።
እስካሁን በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የሰላም ድርድሩን በተመለከተ የተባለ ነገር የለም። ነገር ግን ኦሮሚያ ላይ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት የፌዴራሉ መንግስት የወታደራዊ እንዲሁም የፖለቲካ ሰዎች ታንዛኒያ እንደሚገኙ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ዲፕሎማቶች ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግሥት ሸኔ እያለ የሚጠራው የታጠቀ ኃይል) በታንዛኒያ የሰላም ድርድር እየተደረገ ነው ሲል መግለጫ አወጣ።
ምንም እንኳን ከቀናት በፊት የዲፕሎማቲክ ምንጮች በታንዛኒያ ዳሬሰላም የኢትዮጵያ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት በወታደራዊ አዛዦች አማካኝነት ለሰላም ድርድር መቀመጣቸውን ቢያሳውቁም እስከዛሬ ደረስ ከሁለቱም በኩል ምንም ነገር ሳይባል ቆይቷል።
በዛሬው ዕለት ግን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ድርድሩን በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ አጭር መግለጫ አውጥቷል።
በዚህም መግለጫው ፤ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር-የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የልዑካን ቡድን በዋና አዛዥ ጃል መሮ ድሪባ እና ምክትላቸው ጃል ገመቹ አቦዬ እየተመራ ለከፍተኛ የሰላም ድርድር ታንዛኒያ መግባቱን አሳውቋል።
አመራሮቹ ደህንነታቸው ተጠብቆ ከነበሩበት ኦሮሚያ ወደ ድርድሩ ቦታ ታንዛኒያ እንዲገቡ ለማድረግ ሲባል በሰዓቱ ይፋዊ መግለጫ / መረጃ እንዳልተሰጠ ጠቁሟል።
" የህዝባችንን ምኞት እውን የሚያደርግ እና የሰማዕቶቻችንን መስዋዕትነት የሚያከብር ሰላማዊ የፖለቲካ እልባት ለማግኘት በቁርጠኝነት እንቀጥላለን " ያለው ይኸው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት መግለጫ የሰላም ድርድሩ ሲጠናቀቅ ተጨማሪ መረጃዎችን እንሰጣለን ብሏል።
እስካሁን በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የሰላም ድርድሩን በተመለከተ የተባለ ነገር የለም። ነገር ግን ኦሮሚያ ላይ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት የፌዴራሉ መንግስት የወታደራዊ እንዲሁም የፖለቲካ ሰዎች ታንዛኒያ እንደሚገኙ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ዲፕሎማቶች ተናግረዋል።
@tikvahethiopia