በቴሌኮም ዘርፍ፣ ዲጂታል ሶሉሽኖች፣ በቴክኖሎጂ እና በአገልግሎቶቻችን ዙሪያ:-
👉 የሚወያዩበት
👉 ሃሳብ የሚሰጡበት
👉 ልምድና ተሞክሮ የሚጋሩበትን
ቴሌፎረም የድረ-ገጽ መድረክ https://teleforum.ethiotelecom.et ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 የሚወያዩበት
👉 ሃሳብ የሚሰጡበት
👉 ልምድና ተሞክሮ የሚጋሩበትን
ቴሌፎረም የድረ-ገጽ መድረክ https://teleforum.ethiotelecom.et ቤተሰብ ይሁኑ!
#ጥቆማ #ከጠቀማችሁ
☑ የአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ተወርሰው የሚገኙ 171 ተሽከርካሪዎችን በግልፅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ተጨራቾች የጨረታ ሰንድ በመግዛት በጨረታው ላይ የሚወጡትን ተሽከርካሪዎች በአካል በመመልከት መጫረት ትችላላችሁ ተብሏል። ጨረታው በ26/02/2016 ዓ/ም ጥዋት 4 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4:15 ላይ የጨረታ ሳጥኑ ይከፈታል። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ 0221118429 ላይ መወደል ይቻላል።
☑ አዲስ አበባ ቃሊት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የተተው፣ የተወረሱ እና በኮንትሮባንድ ተይዘው የሚገኙ የተለያዩ የቤትና የጭነት ተሸከርካሪዎች ፦
- DUMP TRUCK፣
- IVECO FIAT፣
- TOYOTA HAILUX፣
- TOYOTA COROLLA፣
- TOYOTA VITZ፣
- TOYOTA HAICE፣
- TOYOTA YARIS፣
- TOYOTA CHR፣
- HYUNDAI፣
- SUZUKI፣
- MISTUBUSHI ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችን፣ የሞባይል ክፍሎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን፣ የተለያዩ የተዘጋጁ አልባሳትና ጫማዎች፣ የውብት መጠበቂያ ዕቃዎች እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅና በሃራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። የተጠቀሱት ተሸከርካሪዎች የጨረታ ሰነድ ከቀን 20/02/2016 ዓ.ም ጀምሮ ማግኘት ይቻላል።
(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)
☑ የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ዕዳ የያዛቸውን ተሽከርካሪዎችና ሌሎች የተለያዩ ንብረቶች ለመሸጥ ይፈልጋል።
ከፎኔክስ ኢንደስትሪ ኃ/የ/የግ/ማህበር የተያዘ፦
- የኘላስቲክ ወንበር ማምረቻ ማሽን፣ የማሽኑ ማቀዝቀዣ (cooler)፣ የማሽኑ ጥሬ ዕቃዎችና ሌሎች ተጓዳኝ ዕቃዎች፣
ከተክለብርሃን አምባየ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተያዙ ፦
- የተለያዩ መጠን ያላቸው የመብራት አምፖሎች፣
- ፍሎረሰንቶች፣
- ፖውዛዎች እና የውሃ ተቀባሪና ተንጠልጣይ የተለያዩ ቧንቧዎች፣
🚘 ከቲ.አይ.ቢ ኬተሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህ እና ኦክስፎርድ አማልጌትድ ኃ/የተ/ የግ/ማህበር የተያዙ የተለያየ ሞዴል ያላቸውን 3 ተሽከርካሪዎች ናቸው።
(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)
#ጉምሩክኮሚሽን #አዲስዘመን #ገቢዎችሚኒስቴር
* ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በጥቆማ መልክ የቀረበ።
@tikvahethiopia
☑ የአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ተወርሰው የሚገኙ 171 ተሽከርካሪዎችን በግልፅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ተጨራቾች የጨረታ ሰንድ በመግዛት በጨረታው ላይ የሚወጡትን ተሽከርካሪዎች በአካል በመመልከት መጫረት ትችላላችሁ ተብሏል። ጨረታው በ26/02/2016 ዓ/ም ጥዋት 4 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4:15 ላይ የጨረታ ሳጥኑ ይከፈታል። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ 0221118429 ላይ መወደል ይቻላል።
☑ አዲስ አበባ ቃሊት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የተተው፣ የተወረሱ እና በኮንትሮባንድ ተይዘው የሚገኙ የተለያዩ የቤትና የጭነት ተሸከርካሪዎች ፦
- DUMP TRUCK፣
- IVECO FIAT፣
- TOYOTA HAILUX፣
- TOYOTA COROLLA፣
- TOYOTA VITZ፣
- TOYOTA HAICE፣
- TOYOTA YARIS፣
- TOYOTA CHR፣
- HYUNDAI፣
- SUZUKI፣
- MISTUBUSHI ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችን፣ የሞባይል ክፍሎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን፣ የተለያዩ የተዘጋጁ አልባሳትና ጫማዎች፣ የውብት መጠበቂያ ዕቃዎች እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅና በሃራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። የተጠቀሱት ተሸከርካሪዎች የጨረታ ሰነድ ከቀን 20/02/2016 ዓ.ም ጀምሮ ማግኘት ይቻላል።
(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)
☑ የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ዕዳ የያዛቸውን ተሽከርካሪዎችና ሌሎች የተለያዩ ንብረቶች ለመሸጥ ይፈልጋል።
ከፎኔክስ ኢንደስትሪ ኃ/የ/የግ/ማህበር የተያዘ፦
- የኘላስቲክ ወንበር ማምረቻ ማሽን፣ የማሽኑ ማቀዝቀዣ (cooler)፣ የማሽኑ ጥሬ ዕቃዎችና ሌሎች ተጓዳኝ ዕቃዎች፣
ከተክለብርሃን አምባየ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተያዙ ፦
- የተለያዩ መጠን ያላቸው የመብራት አምፖሎች፣
- ፍሎረሰንቶች፣
- ፖውዛዎች እና የውሃ ተቀባሪና ተንጠልጣይ የተለያዩ ቧንቧዎች፣
🚘 ከቲ.አይ.ቢ ኬተሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህ እና ኦክስፎርድ አማልጌትድ ኃ/የተ/ የግ/ማህበር የተያዙ የተለያየ ሞዴል ያላቸውን 3 ተሽከርካሪዎች ናቸው።
(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)
#ጉምሩክኮሚሽን #አዲስዘመን #ገቢዎችሚኒስቴር
* ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በጥቆማ መልክ የቀረበ።
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
በአፖሎ ሲገበያዩ ሁሉም ነገር ቅናሽ አለው! ምን ቅናሽ ብቻ ከንክኪ ነጻ የሆነ ቀልጣፋ እና ፈጣን አገልግሎትም ያገኛሉ!
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
የቴሌግራም ቻነላችንን ይቀላቀሉ
https://yangx.top/BoAEth
#Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
በአፖሎ ሲገበያዩ ሁሉም ነገር ቅናሽ አለው! ምን ቅናሽ ብቻ ከንክኪ ነጻ የሆነ ቀልጣፋ እና ፈጣን አገልግሎትም ያገኛሉ!
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
የቴሌግራም ቻነላችንን ይቀላቀሉ
https://yangx.top/BoAEth
#Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" መንግስት የሚወስነውን የሆነ አካል ተነስቶ ' ይህ ይሁን ፤ ይህ ደግሞ አይሁን ' ማለት ትክክል አይደለም " - አቶ ረዳኢ ኃለፎም
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ " ወቅቱን ያልጠበቀና ህገወጥ ነው " በማለት እንዳይካሄድ ክልከላ ያስተላለፉበት የህወሓት የካድሬዎች ስብሰባ የአጠራሩን አግባብነት ከተነጋገሩበት በኃላ ፓርቲው ያጋጠሙትን አደጋዎች አስመልክቶ ባፀደቀው ዋና አጀንዳ ላይ ከ2 ሳምንት በኃላ ተገናኝቶ ለመወያየት ወስነው ተበትነዋል።
ምንም እንኳን የጊዜያዊ አስተዳደሩ ክልከላ ቢጥልም የህወሓት ካድሬዎች ቅዳሜና እሁድ መቐለ ሰማዕታት አዳራሽ ውስጥ ተሰብስበው ነበር።
የስብሰባው መጠናቀቅን ተከትሎ ፓርቲው ባሰራጨው መግለጫ ፤ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አስቀድሞ ካድሬዎችን ሰብሰበው ባለማናገራቸው ወቅሷል።
በፓርቲው ላይ ያጠላው አደጋ ምንድነው ? በሚል በተቀረፀ ዋና መነጋገሪያ አጀንዳ ላይ ችግሩን በተረጋጋ መንፈስ ለመገምገምና የውስጥ ማጥራት ለማድረግ ከስምምነት ላይ መደረሱን ፓርቲው ገልጿል።
በዶክተር ደብረፅዮ ገ/ሚካኤል የተመራው የፓርቲው የካድሬዎች ስብሰባ የስብሰባው ዋና አጀንዳዎች በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከሁለት ሳምንታት በኃላ እንዲታዩ ውሳኔውን አሳልፎ ተበትኗል።
የጊዜያዊ አስተዳደሩ በፓርቲው ካድሬዎች ላይ የወሰደው እርምጃ ተቋማዊ አሰራርን ያልተከተለ ነው በሚል የተቸው ፓርቲው እርምት እንዲደረግ ጠይቋል።
ባለፈው ሳምንት ከመንግስት የስራ ኃላፊነት ውጭ ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 6 ከዞን አመራሮች ከአቶ ጌታቸው ረዳ በተላከላቸው ደብዳቤ ከስልጥን እንዲነሱ መደረጉ አይዘነጋም።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምን አለ ?
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ረዳኢ ኃለፎም ስብሰባው እንዳይካሄድ ያገድነው ተሳታፊዎቹ የመንግስት ሰራተኞች እና አመራሮች እንደመሆናቸው ጊዜያዊ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሰጣቸው ተግባራት በመኖራቸው ነው ብለዋል።
አቶ ረዳኢ ሃለፎም ፦
" ጊዜያዊ አስተዳደሩ ስብሰባው ትክክል አይደለም ያለው በአሁን ሰዓት መሰራት ለሚገባቸው ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በምርት ላይ ጉዳት ሳያደርስ የመሰብሰብ እና አንበጣን የመከላከል ተግባራት የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጡ ነው።
ይኸውም ቅድሚ እንዲሰጠው በጊዜያዊ አስተዳደሩ ብቻ ሳይሆን በህወሓት መሪዎችም ጭምር መግባባት ላይ ተደርሶ ስብሰባው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ስለተወሰነ ነው።
ስብሰባው የተካሄደው ከዚህ የጋራ ውሳኔ በኃላ ነው። መንግስት የሚወስነውን የሆነ አካል ተነስቶ ' ይህ ይሁን ፤ ይህ ደግሞ አይሁን ' ማለት ትክክል አይደለም።
ከኃላፊነት የተነሱት ሰዎች ከአሁን በፊት የተመደቡት በስብሰባ አይደለም፤ ከስራ ቦታ ሲነሱም በስብሰባ አይሆንም። በስብሰባ እገሌን መድቡት እገሌን ደግሞ አቆዩት ማለት ትክክል አይደለም።
ሹመት በሚገባቸው ቦታዎች ላይ ሰዎች ይሾማሉ ከስራ ምድብ ማንሳት በሚያስፈልግበት ጊዜ ደግሞ ይነሳሉ። ከዚህ ውጭ ያለው ስክነትና ማስተዋል የጎደለበት ጩኸት ነው። "
የዚህ መረጃ ባለቤት ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ መሆኑን እንገልፃለን።
@tikvahethiopia
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ " ወቅቱን ያልጠበቀና ህገወጥ ነው " በማለት እንዳይካሄድ ክልከላ ያስተላለፉበት የህወሓት የካድሬዎች ስብሰባ የአጠራሩን አግባብነት ከተነጋገሩበት በኃላ ፓርቲው ያጋጠሙትን አደጋዎች አስመልክቶ ባፀደቀው ዋና አጀንዳ ላይ ከ2 ሳምንት በኃላ ተገናኝቶ ለመወያየት ወስነው ተበትነዋል።
ምንም እንኳን የጊዜያዊ አስተዳደሩ ክልከላ ቢጥልም የህወሓት ካድሬዎች ቅዳሜና እሁድ መቐለ ሰማዕታት አዳራሽ ውስጥ ተሰብስበው ነበር።
የስብሰባው መጠናቀቅን ተከትሎ ፓርቲው ባሰራጨው መግለጫ ፤ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አስቀድሞ ካድሬዎችን ሰብሰበው ባለማናገራቸው ወቅሷል።
በፓርቲው ላይ ያጠላው አደጋ ምንድነው ? በሚል በተቀረፀ ዋና መነጋገሪያ አጀንዳ ላይ ችግሩን በተረጋጋ መንፈስ ለመገምገምና የውስጥ ማጥራት ለማድረግ ከስምምነት ላይ መደረሱን ፓርቲው ገልጿል።
በዶክተር ደብረፅዮ ገ/ሚካኤል የተመራው የፓርቲው የካድሬዎች ስብሰባ የስብሰባው ዋና አጀንዳዎች በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከሁለት ሳምንታት በኃላ እንዲታዩ ውሳኔውን አሳልፎ ተበትኗል።
የጊዜያዊ አስተዳደሩ በፓርቲው ካድሬዎች ላይ የወሰደው እርምጃ ተቋማዊ አሰራርን ያልተከተለ ነው በሚል የተቸው ፓርቲው እርምት እንዲደረግ ጠይቋል።
ባለፈው ሳምንት ከመንግስት የስራ ኃላፊነት ውጭ ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 6 ከዞን አመራሮች ከአቶ ጌታቸው ረዳ በተላከላቸው ደብዳቤ ከስልጥን እንዲነሱ መደረጉ አይዘነጋም።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምን አለ ?
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ረዳኢ ኃለፎም ስብሰባው እንዳይካሄድ ያገድነው ተሳታፊዎቹ የመንግስት ሰራተኞች እና አመራሮች እንደመሆናቸው ጊዜያዊ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሰጣቸው ተግባራት በመኖራቸው ነው ብለዋል።
አቶ ረዳኢ ሃለፎም ፦
" ጊዜያዊ አስተዳደሩ ስብሰባው ትክክል አይደለም ያለው በአሁን ሰዓት መሰራት ለሚገባቸው ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በምርት ላይ ጉዳት ሳያደርስ የመሰብሰብ እና አንበጣን የመከላከል ተግባራት የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጡ ነው።
ይኸውም ቅድሚ እንዲሰጠው በጊዜያዊ አስተዳደሩ ብቻ ሳይሆን በህወሓት መሪዎችም ጭምር መግባባት ላይ ተደርሶ ስብሰባው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ስለተወሰነ ነው።
ስብሰባው የተካሄደው ከዚህ የጋራ ውሳኔ በኃላ ነው። መንግስት የሚወስነውን የሆነ አካል ተነስቶ ' ይህ ይሁን ፤ ይህ ደግሞ አይሁን ' ማለት ትክክል አይደለም።
ከኃላፊነት የተነሱት ሰዎች ከአሁን በፊት የተመደቡት በስብሰባ አይደለም፤ ከስራ ቦታ ሲነሱም በስብሰባ አይሆንም። በስብሰባ እገሌን መድቡት እገሌን ደግሞ አቆዩት ማለት ትክክል አይደለም።
ሹመት በሚገባቸው ቦታዎች ላይ ሰዎች ይሾማሉ ከስራ ምድብ ማንሳት በሚያስፈልግበት ጊዜ ደግሞ ይነሳሉ። ከዚህ ውጭ ያለው ስክነትና ማስተዋል የጎደለበት ጩኸት ነው። "
የዚህ መረጃ ባለቤት ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ መሆኑን እንገልፃለን።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ድሬዳዋ 🔹" የትውልድን ስነምግባር የምትቀርጽ እና በይዞታዋም ህጋዊ የሆነችን ቤተክርስቲያን አፍርሶ ሆቴል መስራት አግባብነት የለውም " - ቤተክርስቲያን 🔸" ቦታውን ለልማት ተፈልጎ ነው ፤ ካቢኔው የልማት ጥያቄዎችን የማስተናገድ ሃላፊነት አለበት " - የድሬዳዋ ከንቲባ ጽ/ቤት የድሬደዋ መካነ-ኢየሱስ ቤተክርስቲያን የድሬደዋ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ቤተክርስቲያኗ ካለችበት ቦታ እንድትነሳ የሚል ደብዳቤ…
የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ጉዳይ መፍትሄ አግኝቷል ?
ዛሬ የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናንን ወቅታዊ ሁኔታ በመሚመለከት በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ መግለጫ ሰጥታለች።
በዚህም መግለጫ ፤ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ፤ የድሬዳዋ ማህበረ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያን ህንጻና ሌሎች ተያያዥ ህንጻዎች ያሉበትን ይዞታ ለሌላ አገልግሎት ለማዋል በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የተላለፈው ውሳኔ ቤተ ክርሰቲያኗን ብቻ ሳይሆን መላውን ህዝበ ምዕመን በእጅጉ ማስደንገጡ ተገልጿል።
ይህ ውሳኔ እንደገና እንዲጤን ቤተ ክርስቲያኒቱ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር ብርቱ ክትትል በማድረግ ላይ እንደምትገኝ ተመላክቷል።
የከተማው አስተዳደርም በተለይም ከንቲባው ሁኔታውን በጥንቃቄና በሃላፊነት ስሜት እየተከታተሉ ሲሆን ከቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ጋርም ለመምከር ቀጠሮ መያዛቸው በመግለጫው ላይ ተመላክቷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጉዳዩ የማይመለከተውና በየትኛም መንገድ ድርሻ የሌለው አንድ አካል፤ ችግሩ መፍትሔ እንዳገኘ አድርጎ በዛሬው ዕለት በራሱ ማህበራዊ ገጽ (Facebook) የተሳሳተ መረጃ አውጥቷል ብሏል የቤተክርስቲያንኒቱ መግለጫ።
ስም ያልጠቀሰው መግለጫው ይኸው አካል ይህንን ስህተት በአስቸኳይ እንዲያርም ጥብቅ ማሳሰቢያ የደረሰው መሆኑን ገልጿል።
ቤተ ክርስቲያኒቱ እስከምታውቀው ድረስ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ምንም ዓይነት ውሳኔ ያልተሠጠ መሆኑንና ለወደፊትም ቤተ ክርስቲያኒቱ በራስዋ አሠራር ኦፊሴላዊ መረጃ እስከምትሰጥ ድረስ ህዝበ ምዕመኑ በትዕግስትና በጸሎት እንዲጠባበቅ አሳስባለች።
@tikvahethiopia
ዛሬ የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናንን ወቅታዊ ሁኔታ በመሚመለከት በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ መግለጫ ሰጥታለች።
በዚህም መግለጫ ፤ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ፤ የድሬዳዋ ማህበረ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያን ህንጻና ሌሎች ተያያዥ ህንጻዎች ያሉበትን ይዞታ ለሌላ አገልግሎት ለማዋል በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የተላለፈው ውሳኔ ቤተ ክርሰቲያኗን ብቻ ሳይሆን መላውን ህዝበ ምዕመን በእጅጉ ማስደንገጡ ተገልጿል።
ይህ ውሳኔ እንደገና እንዲጤን ቤተ ክርስቲያኒቱ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር ብርቱ ክትትል በማድረግ ላይ እንደምትገኝ ተመላክቷል።
የከተማው አስተዳደርም በተለይም ከንቲባው ሁኔታውን በጥንቃቄና በሃላፊነት ስሜት እየተከታተሉ ሲሆን ከቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ጋርም ለመምከር ቀጠሮ መያዛቸው በመግለጫው ላይ ተመላክቷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጉዳዩ የማይመለከተውና በየትኛም መንገድ ድርሻ የሌለው አንድ አካል፤ ችግሩ መፍትሔ እንዳገኘ አድርጎ በዛሬው ዕለት በራሱ ማህበራዊ ገጽ (Facebook) የተሳሳተ መረጃ አውጥቷል ብሏል የቤተክርስቲያንኒቱ መግለጫ።
ስም ያልጠቀሰው መግለጫው ይኸው አካል ይህንን ስህተት በአስቸኳይ እንዲያርም ጥብቅ ማሳሰቢያ የደረሰው መሆኑን ገልጿል።
ቤተ ክርስቲያኒቱ እስከምታውቀው ድረስ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ምንም ዓይነት ውሳኔ ያልተሠጠ መሆኑንና ለወደፊትም ቤተ ክርስቲያኒቱ በራስዋ አሠራር ኦፊሴላዊ መረጃ እስከምትሰጥ ድረስ ህዝበ ምዕመኑ በትዕግስትና በጸሎት እንዲጠባበቅ አሳስባለች።
@tikvahethiopia
ብርቱ አጋር!!
ለስኬትዎ መዳረሻ ለህልምዎ እውን መሆን ብርቱ አጋር ነን
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ !!
ለጋራ ስኬታችን !!
የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የቴሌግራም ቻናል
https://yangx.top/Globalbankethiopia123
#globalbankethiopia #GBE #banksinethiopia #fintech #bank #finance #ethiopia #ethiopian #digitalbanking #Globaldigital
ለስኬትዎ መዳረሻ ለህልምዎ እውን መሆን ብርቱ አጋር ነን
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ !!
ለጋራ ስኬታችን !!
የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የቴሌግራም ቻናል
https://yangx.top/Globalbankethiopia123
#globalbankethiopia #GBE #banksinethiopia #fintech #bank #finance #ethiopia #ethiopian #digitalbanking #Globaldigital
#ምደባ
ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ማብራሪያ ፦
- የምደባ ስርዓቱ በተፈጥሮም ሆነ በማህበራዊ ሳይንስ መስኮች 1000 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በመጀመሪያ የዩኒቨርስቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸው ምደባ የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።
- የምደባ ስርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ያስመዘገበውን አጠቃላይ ውጤት በምደባ ስርዓት ሂደት ውስጥ መለያ አድርጎ ይጠቀማል፡፡ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ሌሎች ተፈጻሚ የሚሆኑ ህግና ደንቦችን ባልጣሰ መልኩ ምርጫቸውን በመጠበቅ ረገድ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል።
- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የቅበላ አቅም ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ተማሪዎች 46 ዩኒቨርሲቲዎች ለምርጫ ቀርበውላቸዋል፤ በነዚህ ውስጥ ይመደባሉ።
- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች እና የተመረጡት ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የትምህርት ፕሮግራም መሰረት ያደረገ ነው ተብሏል።
- በተቋማት የጾታ ተዋጽኦን ለመጠበቅ በሚኖረው የምደባ ስርዓት የጾታ ተዋጽኦና ሚዛን እንዲጠበቅ መደረጉ ተገልጿል።
- የምደባ ስርዓቱ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሚመደቡ ተማሪዎችን ተዋጽኦ በጠበቀ መልኩ እንዲሆን እንደሚያግፅ ተነላክቷል። ይህም ከአንድ ት/ቤት የወጡ ተማሪዎች በአንድ ዩኒቨርሲቲ ወይም ፕሮግራም ውስጥ እንዳይታጨቁ ይደርጋል።
- የምደባ ስርዓቱ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ታሳቢ ያረገ ሲሆን ይህም ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች አንድ ላይ እንዳይመደቡ በማድረግ የተለያየ ችሎታና ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎችን ቀላቅሎ ለማስተማር እንደሚያግዝ ተገልጿል።
- የምደባ ስርዓቱ እንደ ወሊድ ያሉ ልዩ ሁኔታዎችን ያማከለ ነው ተብሏል። በመሰል ሁኔታ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ለመቀጠል የሚቸገሩ ከሆነ ትክክለኛ ለውጥና ድጋፍ የሚደረግ ይሆናል፡፡
- በምደባ ወቅት የጤና ችግር ኖሮባቸው ትክክለኛ የሕክምና ማስረጃ ላላቸው ተማሪዎች ምደባው በተለየ መልኩ ሊታይ ይችላል።
- በተማሪዎቹ መካከል ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትዮች ካሉ የምደባ ስርዓቱ ከፍተኛ ነጥብ ያገኘው/ችው ተማሪ ከተመደበበት/ችበት የትምህርት ተቋም ቀሪው መንትያ ደግሞ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በቀጥታ ይመድባል።
- የምደባ ሲስተሙ የአካል ችግር ላለባቸው ተማሪዎች እኩል እድሎችን የሚሰጥ ሲሆን ልዩ ፍላጎቶቻቸውን እና ለምደባ መስፈርቶቻቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት የሚሰራ ይሆናል።
ትምህርት ሚኒስቴር ሀሰተኛ የህክምና ማስረጃ የሚያቀርብ ተማሪ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከምደባ ውጭ የሚሆን መሆኑን አሳስቧል።
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ማብራሪያ ፦
- የምደባ ስርዓቱ በተፈጥሮም ሆነ በማህበራዊ ሳይንስ መስኮች 1000 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በመጀመሪያ የዩኒቨርስቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸው ምደባ የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።
- የምደባ ስርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ያስመዘገበውን አጠቃላይ ውጤት በምደባ ስርዓት ሂደት ውስጥ መለያ አድርጎ ይጠቀማል፡፡ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ሌሎች ተፈጻሚ የሚሆኑ ህግና ደንቦችን ባልጣሰ መልኩ ምርጫቸውን በመጠበቅ ረገድ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል።
- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የቅበላ አቅም ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ተማሪዎች 46 ዩኒቨርሲቲዎች ለምርጫ ቀርበውላቸዋል፤ በነዚህ ውስጥ ይመደባሉ።
- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች እና የተመረጡት ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የትምህርት ፕሮግራም መሰረት ያደረገ ነው ተብሏል።
- በተቋማት የጾታ ተዋጽኦን ለመጠበቅ በሚኖረው የምደባ ስርዓት የጾታ ተዋጽኦና ሚዛን እንዲጠበቅ መደረጉ ተገልጿል።
- የምደባ ስርዓቱ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሚመደቡ ተማሪዎችን ተዋጽኦ በጠበቀ መልኩ እንዲሆን እንደሚያግፅ ተነላክቷል። ይህም ከአንድ ት/ቤት የወጡ ተማሪዎች በአንድ ዩኒቨርሲቲ ወይም ፕሮግራም ውስጥ እንዳይታጨቁ ይደርጋል።
- የምደባ ስርዓቱ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ታሳቢ ያረገ ሲሆን ይህም ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች አንድ ላይ እንዳይመደቡ በማድረግ የተለያየ ችሎታና ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎችን ቀላቅሎ ለማስተማር እንደሚያግዝ ተገልጿል።
- የምደባ ስርዓቱ እንደ ወሊድ ያሉ ልዩ ሁኔታዎችን ያማከለ ነው ተብሏል። በመሰል ሁኔታ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ለመቀጠል የሚቸገሩ ከሆነ ትክክለኛ ለውጥና ድጋፍ የሚደረግ ይሆናል፡፡
- በምደባ ወቅት የጤና ችግር ኖሮባቸው ትክክለኛ የሕክምና ማስረጃ ላላቸው ተማሪዎች ምደባው በተለየ መልኩ ሊታይ ይችላል።
- በተማሪዎቹ መካከል ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትዮች ካሉ የምደባ ስርዓቱ ከፍተኛ ነጥብ ያገኘው/ችው ተማሪ ከተመደበበት/ችበት የትምህርት ተቋም ቀሪው መንትያ ደግሞ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በቀጥታ ይመድባል።
- የምደባ ሲስተሙ የአካል ችግር ላለባቸው ተማሪዎች እኩል እድሎችን የሚሰጥ ሲሆን ልዩ ፍላጎቶቻቸውን እና ለምደባ መስፈርቶቻቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት የሚሰራ ይሆናል።
ትምህርት ሚኒስቴር ሀሰተኛ የህክምና ማስረጃ የሚያቀርብ ተማሪ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከምደባ ውጭ የሚሆን መሆኑን አሳስቧል።
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#SafaricomEthiopia
ቡና በምንገባበዝበት ብር የሳፋሪኮምን 4GB YouTube ጥቅል ገዝተን 200ደቂቃ ሙሉ ባልተገደበ የኢንተርኔት ፍጥነት በአዝናኝ ቪዲዮዎች ፈታ እንበል። ዛሬውኑ ወደ *777# በመደወል ጥቅሉን እንግዛ።
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
ቡና በምንገባበዝበት ብር የሳፋሪኮምን 4GB YouTube ጥቅል ገዝተን 200ደቂቃ ሙሉ ባልተገደበ የኢንተርኔት ፍጥነት በአዝናኝ ቪዲዮዎች ፈታ እንበል። ዛሬውኑ ወደ *777# በመደወል ጥቅሉን እንግዛ።
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
መምህራን ምን አሉ ?
• " የመምህራን ደመወዝ ይቆረጣል የሚሰጠው ምክንያት ደግሞ አሳማኝ አይደለም "
• " የፌዴራል መንግሥት የዓመቱን በጀት ወደ ክልሎች ቢልክም፣ ክልሎች ለወረዳዎች አይልኩም "
• " አንዳንዴ ደመወዝ ለበርካታ ወራት ሳይከፈላቸው ይጠብቃሉ፤ ግማሽ ደመወዝ ብቻ የሚከፈልበት ጊዜም አለ "
የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር በጅግጅጋ ከተማ ባካሄደው 36ኛው ጉባዔ ላይ፣ በክልሎች የበርካታ መምህራን ደመወዝ ያላግባብ እንደሚቆረጥ በስፋት መነሳቱ ተገልጿል።
የማኅበሩ ጉባዔ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ ከኦሮሚያ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ከሲዳማና ከሌሎቸም ክልሎች መምህራን ደመወዛቸው ያላግባብ እንደሚቆረጥ በስፋት መነሳቱን በስብሰባው የተሳተፉ የማኅበሩ አመራሮች ተናግረዋል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ አማኑኤል ጳውሎስ እንደገለጹት፣ በክልሉ እስከ 60 በመቶ የሚደርስ የመምህራን ደመወዝ እንደሚቆረጥና ለዚህም የሚሰጠው ምክንያት አሳማኝ አይደለም ብለዋል።
የፌዴራል መንግሥት የዓመቱን በጀት ወደ ክልሎች ቢልክም፣ ክልሎች ለወረዳዎች እንደማይልኩ፣ በጀቱ ለማዳበሪያ ክፍያ ዋለ በሚል ወደ መምህራን ሳይደረስ እንደሚቀር መምህራን መናገራቸው ተሰምቷል፡፡
አንዳንዴ ደመወዝ ለበርካታ ወራት ሳይከፈላቸው እንደሚጠብቁና ግማሽ ደመወዝ ብቻ እንደሚከፈላቸውም ተነግሯል፡፡
መንግሥት በአንድ በኩል ስለትምህርት ጥራት እየተናገረ፣ በሌላ በኩል የመምህራን ደመወዝ እንደማይከፈል፣ የደረጃ ዕድገትና የትምህርት ማሻሻያ እንደማይደረግ በጉባዔው ላይ መነጋገሪያ ነበር ተብሏል፡፡
የማኅበሩ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እንዳሉት፣ በክልሉ በርካታ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው መምህራን ውስን መሆናቸውን፣ የበጀት እጥረቱ በከፍተኛ ሁኔታ ያጠቃቸው መምህራን በ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት ለሚከናወን ሥራ ከ2017 ዓ.ም. በጀት መበደራቸው ተገልጿል፡፡
ማኅበሩ በጅግጅጋ ባከሄደው ወይይት የመምህራኑ ጉዳዩ በስፋት መነሳቱ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ለዚህ ችግር ክልሎች ጉዳዩን በባለቤትነት ወስደው መፍትሔ እንዲፈልጉ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) መናገራቸውን፣ የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበሩ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ በንቲ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ከሚኒስትሩ ጋር በነበረው ውይይትም ማኅበሩ ከዚህ ቀደም በደብዳቤና በሪፖርት መልክ ሲያቀርባቸው የነበሩ ጥያቄዎችን፣ የትምህርት ሚኒስትሩን በአካል በማግኘት የመምህራኑን ሕይወት ሊቀይሩ የሚችሉ ጥያቄዎች ተነስተው ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል ብለዋል፡፡
በሁሉም ክልሎች የሚገኙ መምህራን በጉባዔው የኑሮ ሁኔታቸው እንዲሻሻል ለመንግሥት ጥያቄ አቅርበው ሚኒስትሩ እንደ ሁኔታው እየታየ ወደፊት የመምህራኑን ሕይወት ሊቀይር የሚችል ሥራ ይከናወናል ማለታቸውን ዮሐንስ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
በመድረኩ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል ከአፋር ክልል ተፈናቅለው ወደ ትግራይ ክልል የሄዱ 500 መምህራን ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ ምክክር ተደርጎበታል ብለዋል፡፡
በ2015 ዓ.ም. ክረምት ተቋርጦ የነበረው የመምህራን የክረምት ትምህርት እንዲቀጥል ስምምነት ላይ መደረሱን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ጉባዔውን በተመለከተ ሚኒስትሩን ጠቅሶ በድረ ገጹ እንዳሠፈረው፣ አገሪቱ አሁን ላለችበት አገራዊ ችግር የትምህርት ሥርዓት መውደቁ ምክንያት በመሆኑ፣ የመምህራን ማኅበር ችግሩን ተነጋግሮ መፍታት እንዳለበትና ማኅበሩ የሙያውን ክብር ለመመለስ ከኅብረተሰቡ ጋር ወይይት በማድረግ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡
የዚህ መረጃ ባለቤት ሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
• " የመምህራን ደመወዝ ይቆረጣል የሚሰጠው ምክንያት ደግሞ አሳማኝ አይደለም "
• " የፌዴራል መንግሥት የዓመቱን በጀት ወደ ክልሎች ቢልክም፣ ክልሎች ለወረዳዎች አይልኩም "
• " አንዳንዴ ደመወዝ ለበርካታ ወራት ሳይከፈላቸው ይጠብቃሉ፤ ግማሽ ደመወዝ ብቻ የሚከፈልበት ጊዜም አለ "
የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር በጅግጅጋ ከተማ ባካሄደው 36ኛው ጉባዔ ላይ፣ በክልሎች የበርካታ መምህራን ደመወዝ ያላግባብ እንደሚቆረጥ በስፋት መነሳቱ ተገልጿል።
የማኅበሩ ጉባዔ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ ከኦሮሚያ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ከሲዳማና ከሌሎቸም ክልሎች መምህራን ደመወዛቸው ያላግባብ እንደሚቆረጥ በስፋት መነሳቱን በስብሰባው የተሳተፉ የማኅበሩ አመራሮች ተናግረዋል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ አማኑኤል ጳውሎስ እንደገለጹት፣ በክልሉ እስከ 60 በመቶ የሚደርስ የመምህራን ደመወዝ እንደሚቆረጥና ለዚህም የሚሰጠው ምክንያት አሳማኝ አይደለም ብለዋል።
የፌዴራል መንግሥት የዓመቱን በጀት ወደ ክልሎች ቢልክም፣ ክልሎች ለወረዳዎች እንደማይልኩ፣ በጀቱ ለማዳበሪያ ክፍያ ዋለ በሚል ወደ መምህራን ሳይደረስ እንደሚቀር መምህራን መናገራቸው ተሰምቷል፡፡
አንዳንዴ ደመወዝ ለበርካታ ወራት ሳይከፈላቸው እንደሚጠብቁና ግማሽ ደመወዝ ብቻ እንደሚከፈላቸውም ተነግሯል፡፡
መንግሥት በአንድ በኩል ስለትምህርት ጥራት እየተናገረ፣ በሌላ በኩል የመምህራን ደመወዝ እንደማይከፈል፣ የደረጃ ዕድገትና የትምህርት ማሻሻያ እንደማይደረግ በጉባዔው ላይ መነጋገሪያ ነበር ተብሏል፡፡
የማኅበሩ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እንዳሉት፣ በክልሉ በርካታ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው መምህራን ውስን መሆናቸውን፣ የበጀት እጥረቱ በከፍተኛ ሁኔታ ያጠቃቸው መምህራን በ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት ለሚከናወን ሥራ ከ2017 ዓ.ም. በጀት መበደራቸው ተገልጿል፡፡
ማኅበሩ በጅግጅጋ ባከሄደው ወይይት የመምህራኑ ጉዳዩ በስፋት መነሳቱ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ለዚህ ችግር ክልሎች ጉዳዩን በባለቤትነት ወስደው መፍትሔ እንዲፈልጉ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) መናገራቸውን፣ የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበሩ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ በንቲ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ከሚኒስትሩ ጋር በነበረው ውይይትም ማኅበሩ ከዚህ ቀደም በደብዳቤና በሪፖርት መልክ ሲያቀርባቸው የነበሩ ጥያቄዎችን፣ የትምህርት ሚኒስትሩን በአካል በማግኘት የመምህራኑን ሕይወት ሊቀይሩ የሚችሉ ጥያቄዎች ተነስተው ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል ብለዋል፡፡
በሁሉም ክልሎች የሚገኙ መምህራን በጉባዔው የኑሮ ሁኔታቸው እንዲሻሻል ለመንግሥት ጥያቄ አቅርበው ሚኒስትሩ እንደ ሁኔታው እየታየ ወደፊት የመምህራኑን ሕይወት ሊቀይር የሚችል ሥራ ይከናወናል ማለታቸውን ዮሐንስ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
በመድረኩ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል ከአፋር ክልል ተፈናቅለው ወደ ትግራይ ክልል የሄዱ 500 መምህራን ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ ምክክር ተደርጎበታል ብለዋል፡፡
በ2015 ዓ.ም. ክረምት ተቋርጦ የነበረው የመምህራን የክረምት ትምህርት እንዲቀጥል ስምምነት ላይ መደረሱን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ጉባዔውን በተመለከተ ሚኒስትሩን ጠቅሶ በድረ ገጹ እንዳሠፈረው፣ አገሪቱ አሁን ላለችበት አገራዊ ችግር የትምህርት ሥርዓት መውደቁ ምክንያት በመሆኑ፣ የመምህራን ማኅበር ችግሩን ተነጋግሮ መፍታት እንዳለበትና ማኅበሩ የሙያውን ክብር ለመመለስ ከኅብረተሰቡ ጋር ወይይት በማድረግ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡
የዚህ መረጃ ባለቤት ሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ በአማራ ክልል ለወራት ከቀጠለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በርካቶች በድሮን ጥቃት መገደላቸው እና በክልሉ ከፍርድ ውጭ ግድያዎች መቀጠላቸውን ዛሬ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከተላከልን መግለጫ መረዳት ችለናል። ከኢሰመኮ በደረሰን መግለጫ ፤ ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ የአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በተለያየ ደረጃና ጊዜ የትጥቅ ግጭት ተካሂዶባቸዋል። …
" ሪፖርቱ የመንግሥትን እንቅስቃሴ አውድ ከግምት ያላስገባ፣ በበቂ መረጃ ላይ ያልተመሠረተ እና ከእውነታ ያፈነገጠ ነው " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ
የመንግሥት ኮሚኒኬሽን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የአማራ ክልል የሰብዓዊ ሁኔታን በተመለከተ ያወጣውን መግለጫ " ከእውነታው ያፈነገጠና ሚዛናዊነት የጎደለው ነው " አለ።
ዛሬ መግለጫ የሰጡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አግልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ኢሰመኮ በአማራ ክልል ጉዳይ ያወጣው ሪፖርት የመንግሥትን እንቅስቃሴ አውድ ከግምት ያላስገባ፣ በበቂ መረጃ ላይ ያልተመሠረተ እና ከእውነታ ያፈነገጠ ነው ብለዋል።
በተጨማሪ ፤ መንግሥት ክልሉ ወደ ሰላማዊና መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲመለስ ያደረገውን ጥረት ከግምት ያላስገባ ነው ሲሉ ጠቁመዋል።
" መንግሥት ገለልተኛ ተቋማት እንዲኖሩ የሚፈልገው የተዛቡ መረጃዎች አንዲታረሙ እና ዴሞክራሲ እንዲጠናከር አስቦ ነው " ያሉት ሚኒስትሩ " ነገር ግን እነዚህ ገለልተኛ ተቋማት በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ ባሉ የተዛቡ መረጃዎች ከተጠለፉ የምንፈልገውን ዴሞክራሲ ልንገነባ አንችልም " ሲሉ ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ ፤ ኢሰመኮ የሚያወጣቸውን መረጃዎች ከትክክለኛ መንጭ በመረዳት እና ትክክለኛውን አውድ ከግምት ያስገባ መሆን እንሚገባው ገልጸዋል።
ከሰሞኑን ያወጣውን መግለጫም ቆም ብሎ እንዲገመግም አሳስበዋል።
መንግሥት በአማራ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት እና የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት ለማረጋገጥ ጥንቃቄ የተሞላባቸው እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ዶ/ር ለገሰ ቱሉ በዛሬው መግለጫቸው ወቅት ተናግረዋል።
ኢሰመኮ ከቀናት በፊት በላከልን መግለጫ ፤ በአማራ ክልል ለወራት ከቀጠለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በርካቶች በድሮን ጥቃት መገደላቸው እና በክልሉ ከፍርድ ውጭ ግድያዎች መቀጠላቸውን ፣ እንዲሁም በመንግሥት ኃላፊዎች ላይ ግድያ መፈፀሙን አሳውቆ ነበር።
በተለይም #የአየር /#ድሮን መሣሪያን ጨምሮ በከባድ መሣሪያዎች ጥቃት የተነሳ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን ፣ ሰዎች መኖሪያ አካባቢያቸውን ጥለው መሸሻቸውን የኢሰመኮ መግለጫ ያስረዳል።
በተለይም በመጥተህ ብላ ከተማ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት የአንድ አመት ከ7 ወር ህፃንን ጨምሮ በርካቶች መገደላቸውን ፣ በደብረ ማርቆስ በተመሳሳይ በድሮን 8 ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን ፤ እንዲሁ በደንበጫ በከባድ መሳሪያ ሲቪሎች መገደላቸውን በመግለጫው አሳውቋል።
ኢሰመኮ በመግለጫው ላይ ቀጥሏል ባለው ከፍርድ ውጭ ግድያ ግጭት በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦ " ፋኖን ትደግፋላችሁ " ፤ " ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ " ፤ " መሣሪያ አምጡ "፤ " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ ግድያዎች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ ተዓማኒ መረጃዎች መገኘታቸውን ገልጿል።
ከዚህ ባለፈ ፤ በየደረጃው የሚገኙ ሲቪል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች፣ ግድያዎችና እገታዎች በታጠቁ ኃይሎች መፈፀማቸውን ኢሰመኮ በመግለጫ አሳውቆ ነበር።
ኢሰመኮ ልኮት የነበረው ሙሉ መግለጫ በዚህ ይገኛል፦ https://yangx.top/tikvahethiopia/82610
@tikvahethiopia
የመንግሥት ኮሚኒኬሽን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የአማራ ክልል የሰብዓዊ ሁኔታን በተመለከተ ያወጣውን መግለጫ " ከእውነታው ያፈነገጠና ሚዛናዊነት የጎደለው ነው " አለ።
ዛሬ መግለጫ የሰጡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አግልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ኢሰመኮ በአማራ ክልል ጉዳይ ያወጣው ሪፖርት የመንግሥትን እንቅስቃሴ አውድ ከግምት ያላስገባ፣ በበቂ መረጃ ላይ ያልተመሠረተ እና ከእውነታ ያፈነገጠ ነው ብለዋል።
በተጨማሪ ፤ መንግሥት ክልሉ ወደ ሰላማዊና መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲመለስ ያደረገውን ጥረት ከግምት ያላስገባ ነው ሲሉ ጠቁመዋል።
" መንግሥት ገለልተኛ ተቋማት እንዲኖሩ የሚፈልገው የተዛቡ መረጃዎች አንዲታረሙ እና ዴሞክራሲ እንዲጠናከር አስቦ ነው " ያሉት ሚኒስትሩ " ነገር ግን እነዚህ ገለልተኛ ተቋማት በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ ባሉ የተዛቡ መረጃዎች ከተጠለፉ የምንፈልገውን ዴሞክራሲ ልንገነባ አንችልም " ሲሉ ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ ፤ ኢሰመኮ የሚያወጣቸውን መረጃዎች ከትክክለኛ መንጭ በመረዳት እና ትክክለኛውን አውድ ከግምት ያስገባ መሆን እንሚገባው ገልጸዋል።
ከሰሞኑን ያወጣውን መግለጫም ቆም ብሎ እንዲገመግም አሳስበዋል።
መንግሥት በአማራ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት እና የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት ለማረጋገጥ ጥንቃቄ የተሞላባቸው እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ዶ/ር ለገሰ ቱሉ በዛሬው መግለጫቸው ወቅት ተናግረዋል።
ኢሰመኮ ከቀናት በፊት በላከልን መግለጫ ፤ በአማራ ክልል ለወራት ከቀጠለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በርካቶች በድሮን ጥቃት መገደላቸው እና በክልሉ ከፍርድ ውጭ ግድያዎች መቀጠላቸውን ፣ እንዲሁም በመንግሥት ኃላፊዎች ላይ ግድያ መፈፀሙን አሳውቆ ነበር።
በተለይም #የአየር /#ድሮን መሣሪያን ጨምሮ በከባድ መሣሪያዎች ጥቃት የተነሳ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን ፣ ሰዎች መኖሪያ አካባቢያቸውን ጥለው መሸሻቸውን የኢሰመኮ መግለጫ ያስረዳል።
በተለይም በመጥተህ ብላ ከተማ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት የአንድ አመት ከ7 ወር ህፃንን ጨምሮ በርካቶች መገደላቸውን ፣ በደብረ ማርቆስ በተመሳሳይ በድሮን 8 ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን ፤ እንዲሁ በደንበጫ በከባድ መሳሪያ ሲቪሎች መገደላቸውን በመግለጫው አሳውቋል።
ኢሰመኮ በመግለጫው ላይ ቀጥሏል ባለው ከፍርድ ውጭ ግድያ ግጭት በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦ " ፋኖን ትደግፋላችሁ " ፤ " ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ " ፤ " መሣሪያ አምጡ "፤ " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ ግድያዎች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ ተዓማኒ መረጃዎች መገኘታቸውን ገልጿል።
ከዚህ ባለፈ ፤ በየደረጃው የሚገኙ ሲቪል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች፣ ግድያዎችና እገታዎች በታጠቁ ኃይሎች መፈፀማቸውን ኢሰመኮ በመግለጫ አሳውቆ ነበር።
ኢሰመኮ ልኮት የነበረው ሙሉ መግለጫ በዚህ ይገኛል፦ https://yangx.top/tikvahethiopia/82610
@tikvahethiopia
" በከተማ ውስጥ ረጅም የመኪና ማብራት ፈጽሞ አይፈቀድም ፤ ልዩ ክትትልም እናደርጋለን ፤ ... ደንብ የሚተላለፉት ላይ ቅጣቱ ከመደበኛ ቅጣቶች ከፍ ያለ ይሆናል " - ትራፊክ ማኔጅመት ኤጀንሲ
በአዲስ አበባ ከተማ የረጅም የመኪና መብራት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትል ሊደረግ መሆኑን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አሳወቀ።
ረጅም የመኪና መብራት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትል ይደረጋል ያለው ኤጀንሲው ፤ በከተማ ውስጥ ረጅም የመኪና ማብራት ፈጽሞ አይፈቀድም፤ ህጉም በግልፅ ይሄንን ይከለክላል ሲል አስገንዝቧል።
ነገር ግን አሁን ላይ ረጅም የመኪና መብራት የሚጠቀሙ አካላት በብዛት እየተስተዋሉ እንደሚገኝ የጠቆመው ኤጀንሲው ይህን የሕግ መተላለፍ ለመግታት ረጅም የመኪና መብራት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትል ይደረጋል ሲል አሳውቋል።
በቁጥጥር ሂደቱ ውስጥ ሕግ ተላልፈው የተገኙ አካላት ተቆጣጣሪዎች ሕጉን መሠረት ያደረገና ከመደበኛው ቅጣት ከፍ ያለ ርምጃ እንዲወስዱ እንደሚደረግ ተገልጿል።
በከተማ ውስጥ ረጅም የመኪና መብራት መጠቀም አሽከርካሪዎች በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እንዲያደርሱ እንደሚያደርግ ኤጀንሲው አስገንዝቧል።
ከዚህ ባለፈ በተሽከርካሪ ላይ ያልነበረ ሌላ ተጨማሪ የመብራት አካል እየገጠሙ የሚጠቀሙ አሽከርካሪዎች መኖራቸውን አንስቶ ተግባሩ በቀጥታ ደንብ የተላለፈ በመሆኑ ቅጣቱ ከመደበኛ ቅጣቶች ከፍ ያለ እንዲሆን ተደርጓል ሲል አሳውቋል።
አሽከርካሪዎች ይህ ድርጊት በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ከዚህ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ፤ አሁን ላይ የሌላ ተሽከርካሪ የፊት መብራት አስገጥመው የሚጠቀሙ በርካታ አሽከርካሪዎች ላይ ርምጃ እየተወሰደ ነው ያለ ሲሆን በአጠቃላይ የመኪና መብራት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትል ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑንና ልዩ ክትትሉ ራሱን የቻለ ፦
- እቅድ፣
- የአፈፃጸም ሥርዓት፣
- የቅጣት ደረጃ፣
- የሰው ኃይል እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በውስጡ መካተታቸውን አመልክቷል።
ደንብ ጥሰቱ ከሌሎች ጥሰቶች እኩል የሚታይ አለመሆኑን አሽከርካሪዎች ሊገነዘቡ ይገባል ሲል ማሳስቡን ኢፕድ ዘግቧል።
ከዚሁ ከረጅም የመኪና መብራት ጋር በተያያዘ በርካቶች የተማረሩበት ጉዳይ ስለመሆኑ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው አሽከርካሪዎች ገልጻዋል።
አንዳንዶች የትኛው ረጅም የትኛው አጭር እንደሆነ በማያውቁበት ሁኔታ እንደሚያሽከርክሩ የገለፁት እኙሁ አስተያየት ሰጪዎች ይህ ድርጊት ለከፍተኛ አደጋ እንደሚያጋልጥ ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል አንዳንድ የከተማው መንገዶች የመንገድ ላይ መብራት ስለሌላቸው በምሽት ለማሽከርከር አዳጋች እንደሚሆን ገልጸው መንግሥት አስፈላጊውን ነገር ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
እርምጃዎች ሲወሰዱም ያሉትን ችግሮች ታሳቢ ያደረገ ፣ የመንገዶቹን የጥራት እና ለረጅምም ሆነ ለቅርብ እይታ በቂ የመንገድ መብራት መኖራቸውን ከግምት ያስገባ ሊሆን እንደሚገባ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የቤተሰባችን አባላት ጠቁመዋል።
* የመረጃው መነሻ ኢፕድ ሲሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ተንተርሶ የቤተሰቡን አባላት አነጋግሮ ነው ያቀረበው።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ የረጅም የመኪና መብራት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትል ሊደረግ መሆኑን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አሳወቀ።
ረጅም የመኪና መብራት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትል ይደረጋል ያለው ኤጀንሲው ፤ በከተማ ውስጥ ረጅም የመኪና ማብራት ፈጽሞ አይፈቀድም፤ ህጉም በግልፅ ይሄንን ይከለክላል ሲል አስገንዝቧል።
ነገር ግን አሁን ላይ ረጅም የመኪና መብራት የሚጠቀሙ አካላት በብዛት እየተስተዋሉ እንደሚገኝ የጠቆመው ኤጀንሲው ይህን የሕግ መተላለፍ ለመግታት ረጅም የመኪና መብራት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትል ይደረጋል ሲል አሳውቋል።
በቁጥጥር ሂደቱ ውስጥ ሕግ ተላልፈው የተገኙ አካላት ተቆጣጣሪዎች ሕጉን መሠረት ያደረገና ከመደበኛው ቅጣት ከፍ ያለ ርምጃ እንዲወስዱ እንደሚደረግ ተገልጿል።
በከተማ ውስጥ ረጅም የመኪና መብራት መጠቀም አሽከርካሪዎች በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እንዲያደርሱ እንደሚያደርግ ኤጀንሲው አስገንዝቧል።
ከዚህ ባለፈ በተሽከርካሪ ላይ ያልነበረ ሌላ ተጨማሪ የመብራት አካል እየገጠሙ የሚጠቀሙ አሽከርካሪዎች መኖራቸውን አንስቶ ተግባሩ በቀጥታ ደንብ የተላለፈ በመሆኑ ቅጣቱ ከመደበኛ ቅጣቶች ከፍ ያለ እንዲሆን ተደርጓል ሲል አሳውቋል።
አሽከርካሪዎች ይህ ድርጊት በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ከዚህ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ፤ አሁን ላይ የሌላ ተሽከርካሪ የፊት መብራት አስገጥመው የሚጠቀሙ በርካታ አሽከርካሪዎች ላይ ርምጃ እየተወሰደ ነው ያለ ሲሆን በአጠቃላይ የመኪና መብራት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትል ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑንና ልዩ ክትትሉ ራሱን የቻለ ፦
- እቅድ፣
- የአፈፃጸም ሥርዓት፣
- የቅጣት ደረጃ፣
- የሰው ኃይል እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በውስጡ መካተታቸውን አመልክቷል።
ደንብ ጥሰቱ ከሌሎች ጥሰቶች እኩል የሚታይ አለመሆኑን አሽከርካሪዎች ሊገነዘቡ ይገባል ሲል ማሳስቡን ኢፕድ ዘግቧል።
ከዚሁ ከረጅም የመኪና መብራት ጋር በተያያዘ በርካቶች የተማረሩበት ጉዳይ ስለመሆኑ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው አሽከርካሪዎች ገልጻዋል።
አንዳንዶች የትኛው ረጅም የትኛው አጭር እንደሆነ በማያውቁበት ሁኔታ እንደሚያሽከርክሩ የገለፁት እኙሁ አስተያየት ሰጪዎች ይህ ድርጊት ለከፍተኛ አደጋ እንደሚያጋልጥ ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል አንዳንድ የከተማው መንገዶች የመንገድ ላይ መብራት ስለሌላቸው በምሽት ለማሽከርከር አዳጋች እንደሚሆን ገልጸው መንግሥት አስፈላጊውን ነገር ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
እርምጃዎች ሲወሰዱም ያሉትን ችግሮች ታሳቢ ያደረገ ፣ የመንገዶቹን የጥራት እና ለረጅምም ሆነ ለቅርብ እይታ በቂ የመንገድ መብራት መኖራቸውን ከግምት ያስገባ ሊሆን እንደሚገባ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የቤተሰባችን አባላት ጠቁመዋል።
* የመረጃው መነሻ ኢፕድ ሲሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ተንተርሶ የቤተሰቡን አባላት አነጋግሮ ነው ያቀረበው።
@tikvahethiopia
#CBE
ይመልሱ፤ ይሸለሙ!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲቢኢ ኑርን 10ኛ ዓመት በማስመልከት በማኅበራዊ ትስስር ገፆቹ የጥያቄና መልስ ውድድር አዘጋጅቷል፡፡
እርስዎም የባንኩን ትክክለኛ የማኅበራዊ ትስስር ገፆች በመቀላቀል ከጥቅምት 23 ቀን 2016 ጀምሮ በሚካሄደው የጥያቄና መልስ ውድድር ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡
🔗 ፌስቡክ 🔗 ኦሮምኛ የፌስ ቡክ ገፅ
🔗 የሲቢኢ ኑር የፌስቡክ ገፅ
🔗 ቴሌግራም 🔗 የሲቢኢ ኑር ቴሌግራም ገፅ
*****
ማሳሰቢያ፡
ለአሸናፊዎች ሽልማቱ የሚደርሰው በሲቢኢ ብር በመሆኑ የሲቢኢ ብር ደንበኛ በመሆን ሽልማቱን ይቀበሉ፡
የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለማውረድ፡
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
ይመልሱ፤ ይሸለሙ!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲቢኢ ኑርን 10ኛ ዓመት በማስመልከት በማኅበራዊ ትስስር ገፆቹ የጥያቄና መልስ ውድድር አዘጋጅቷል፡፡
እርስዎም የባንኩን ትክክለኛ የማኅበራዊ ትስስር ገፆች በመቀላቀል ከጥቅምት 23 ቀን 2016 ጀምሮ በሚካሄደው የጥያቄና መልስ ውድድር ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡
🔗 ፌስቡክ 🔗 ኦሮምኛ የፌስ ቡክ ገፅ
🔗 የሲቢኢ ኑር የፌስቡክ ገፅ
🔗 ቴሌግራም 🔗 የሲቢኢ ኑር ቴሌግራም ገፅ
*****
ማሳሰቢያ፡
ለአሸናፊዎች ሽልማቱ የሚደርሰው በሲቢኢ ብር በመሆኑ የሲቢኢ ብር ደንበኛ በመሆን ሽልማቱን ይቀበሉ፡
የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለማውረድ፡
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787