TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ትግራይ
በትግራይ የሃዘን ድንኳኖች እየፈረሱ ናቸው። የሃዘን ማቅ ለብሳ የሰነበተችው መቐለ ከተማ ወደ ቀደመው እንቅስቃሴ መመለስ ጀምራለች።
ባንኮች ጨምሮ የተዘጋጉ የንግድ ተቋማት ተከፍተዋል። ሰውና መኪና ተጠምተው የነበሩ መንገዶች መሙላት ጀምረዋል።
የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርአቱ በመቐለ ዓዲሓቂ የሰማእታት ሃውልት በተካሄደ " ይበቃል አንገታችን ለሃዘን አንደፋም " በሚል ሰላማዊ ሰልፍ ማሳረግያ አግኝቷል።
በማሳረግያ ስነ-ሰርዓቱ መልእክት ያስተላለፉት አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ " አንባ ይብቃ ሃዘችን ተቋቁመን ሰማእታቱ የተውልን አደራ ለመፈፀም እንትጋ ፤ ትግራይ መለወጥ የሚችሉ ወድ የህዝብ ልጆች ከፍለናል ፤ የተከፈለው መስዋእት ውድ በመሆኑ የጋራ ስቃያችን ወደ የጋራ ድል ለመቀየር እየተነጋገርን እየተመካከርን መስራት አለብን " ብለዋል።
ፕረዚደንቱ በማከልም ፤ " ላጋጠመን ችግር መንስኤው ምንድን ነው ? ውስጣዊ ወይም ደግሞ ውጫዊ ? የሚለው ጥያቄ በሚገባ በመመለስ ተጠያቂነት በማረጋገጥ ችግሩ ለአንዴና ለመጨረሻ የማይደግምበት ሁኔታ መፈጠር አለብን ፤ የውስጥ የአመራር ድክመታችን በማረም በተከፈለው መስዋእትነት የሃሳብ ብዙህነት እንዲጎመራ ፤ ሰላማዊ የፓለቲካ ትግል ሰር እንዲሰድ ማስቻልና መሰል ለውጦች በማስፋት የተጀመረው ሰላም በማስፋትና በማጠናከር ህያው ሆኖ እንዲኖር መስራት ይጠበቅብናል " ብለዋል።
አቶ ጌታቸው ፤ " ከጎቤታችን ኤርትራ ጨምሮ ከአማራና ዓፋር ክልሎች በሰላምና በወንድማማችነት በመደጋገፍ ለመኖር እንፈልጋለን። በየ30 አመቱ ዋጋ እያስከፈለን ያለው የፓለቲካ አካሄድ ከምንጩ በመመርመር አይነተኛ ለውጥ ለማድረግ የምንገደድበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። " ሲሉ ተናግረዋል።
የትግራይ የሃይማኖት ጉባኤ በመወከል መልእክት ያስተላለፉት የመቐለ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስ አቡነ መርሃ ክርስቶስ " የፈሰሰው ደም የከፈልነው ህይወት ይብቃን ከአሁን በኃላ አንድነታችንና ክብራችን በማፅናት የተፈናቀሉት ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ መሪዎች ሰላማዊ የሆነ ተጨማሪ ጥረት ማድረግ አለባችሁ " ብለዋል።
የሰማእታት ቤተሰብ ተወካይ ወ/ሮ ብርሃን ተካ በበኩላቸው ለህዝባቸው ክቡር መስዋእት የከፈሉ ልጆቻችን ህያው ሆኖው እንዲኖሩ ከተፈለገ ብቃት ባለው አመራር የሚመራ ጤነኛና አስተዋያይ የፓለቲካ ምህዳር ሲፈጠር ነው ፣ ስለሆነም መሪዎቻችን ከትናንት ስህተታችሁ በመማር ህደ ሰፊና ችግሮች ከመፈጠራቸው በፊት ማስቀረት የሚችል አቅም ማጎልበት አለባችሁ " ብለዋል።
በማሳረግያ ስነ-ሰርአቱ ለሰማእታት በጳጳሳትና በእስልምና ሃይማኖት ከፍተኛ አመራሮች የተመራ የፀሎተ ፍትሃትና የዱዓ ስነ-ሰርአት የተከናወነ ሲሆን የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ዶብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጨምሮ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የተፎካካሪ ፓርቲ ኣመራሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ከሰባቱ የመቐለ ክፍለከተሞች የተውጣጡ የሰማእታት ቤተሰቦችና ነዋሪዎች በቦታው መገኘታቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
መረጃው የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
ተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ትግርኛ ፦ @tikvahethiopiaTigrigna
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaTigrigna
በትግራይ የሃዘን ድንኳኖች እየፈረሱ ናቸው። የሃዘን ማቅ ለብሳ የሰነበተችው መቐለ ከተማ ወደ ቀደመው እንቅስቃሴ መመለስ ጀምራለች።
ባንኮች ጨምሮ የተዘጋጉ የንግድ ተቋማት ተከፍተዋል። ሰውና መኪና ተጠምተው የነበሩ መንገዶች መሙላት ጀምረዋል።
የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርአቱ በመቐለ ዓዲሓቂ የሰማእታት ሃውልት በተካሄደ " ይበቃል አንገታችን ለሃዘን አንደፋም " በሚል ሰላማዊ ሰልፍ ማሳረግያ አግኝቷል።
በማሳረግያ ስነ-ሰርዓቱ መልእክት ያስተላለፉት አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ " አንባ ይብቃ ሃዘችን ተቋቁመን ሰማእታቱ የተውልን አደራ ለመፈፀም እንትጋ ፤ ትግራይ መለወጥ የሚችሉ ወድ የህዝብ ልጆች ከፍለናል ፤ የተከፈለው መስዋእት ውድ በመሆኑ የጋራ ስቃያችን ወደ የጋራ ድል ለመቀየር እየተነጋገርን እየተመካከርን መስራት አለብን " ብለዋል።
ፕረዚደንቱ በማከልም ፤ " ላጋጠመን ችግር መንስኤው ምንድን ነው ? ውስጣዊ ወይም ደግሞ ውጫዊ ? የሚለው ጥያቄ በሚገባ በመመለስ ተጠያቂነት በማረጋገጥ ችግሩ ለአንዴና ለመጨረሻ የማይደግምበት ሁኔታ መፈጠር አለብን ፤ የውስጥ የአመራር ድክመታችን በማረም በተከፈለው መስዋእትነት የሃሳብ ብዙህነት እንዲጎመራ ፤ ሰላማዊ የፓለቲካ ትግል ሰር እንዲሰድ ማስቻልና መሰል ለውጦች በማስፋት የተጀመረው ሰላም በማስፋትና በማጠናከር ህያው ሆኖ እንዲኖር መስራት ይጠበቅብናል " ብለዋል።
አቶ ጌታቸው ፤ " ከጎቤታችን ኤርትራ ጨምሮ ከአማራና ዓፋር ክልሎች በሰላምና በወንድማማችነት በመደጋገፍ ለመኖር እንፈልጋለን። በየ30 አመቱ ዋጋ እያስከፈለን ያለው የፓለቲካ አካሄድ ከምንጩ በመመርመር አይነተኛ ለውጥ ለማድረግ የምንገደድበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። " ሲሉ ተናግረዋል።
የትግራይ የሃይማኖት ጉባኤ በመወከል መልእክት ያስተላለፉት የመቐለ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስ አቡነ መርሃ ክርስቶስ " የፈሰሰው ደም የከፈልነው ህይወት ይብቃን ከአሁን በኃላ አንድነታችንና ክብራችን በማፅናት የተፈናቀሉት ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ መሪዎች ሰላማዊ የሆነ ተጨማሪ ጥረት ማድረግ አለባችሁ " ብለዋል።
የሰማእታት ቤተሰብ ተወካይ ወ/ሮ ብርሃን ተካ በበኩላቸው ለህዝባቸው ክቡር መስዋእት የከፈሉ ልጆቻችን ህያው ሆኖው እንዲኖሩ ከተፈለገ ብቃት ባለው አመራር የሚመራ ጤነኛና አስተዋያይ የፓለቲካ ምህዳር ሲፈጠር ነው ፣ ስለሆነም መሪዎቻችን ከትናንት ስህተታችሁ በመማር ህደ ሰፊና ችግሮች ከመፈጠራቸው በፊት ማስቀረት የሚችል አቅም ማጎልበት አለባችሁ " ብለዋል።
በማሳረግያ ስነ-ሰርአቱ ለሰማእታት በጳጳሳትና በእስልምና ሃይማኖት ከፍተኛ አመራሮች የተመራ የፀሎተ ፍትሃትና የዱዓ ስነ-ሰርአት የተከናወነ ሲሆን የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ዶብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጨምሮ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የተፎካካሪ ፓርቲ ኣመራሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ከሰባቱ የመቐለ ክፍለከተሞች የተውጣጡ የሰማእታት ቤተሰቦችና ነዋሪዎች በቦታው መገኘታቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
መረጃው የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
ተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ትግርኛ ፦ @tikvahethiopiaTigrigna
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaTigrigna
በአዲሱ የ5G ኔትወርክ ያለገደብ🏃♂🏃♀
ያልተገደቡ ወርሃዊ የ5G ዳታ ጥቅሎችን ከ10%_ተጨማሪ ጋር በቴሌብር ሱፐርአፕ ወይም በማይ ኢትዮቴል እና በ*999# በመግዛት የአዲሱን ትውልድ ኔትወርክ የኢንተርኔት ፍጥነት ያጣጥሙ!
በአዲስ አበባ የ5G አገልግሎት የሚያስጠቅም ስልክ ያላቸውን ደንበኞቻችንን አገልግሎት ወደ 5G አሳድገናል::
ለዝርዝር መረጃ: https://bit.ly/3RQ2McR
ደንብ እና ሁኔታዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ
#አዲስ_ዓመት_አዲስ_ፍጥነት_ምቾት_እና_አኗኗር
#5G
ያልተገደቡ ወርሃዊ የ5G ዳታ ጥቅሎችን ከ10%_ተጨማሪ ጋር በቴሌብር ሱፐርአፕ ወይም በማይ ኢትዮቴል እና በ*999# በመግዛት የአዲሱን ትውልድ ኔትወርክ የኢንተርኔት ፍጥነት ያጣጥሙ!
በአዲስ አበባ የ5G አገልግሎት የሚያስጠቅም ስልክ ያላቸውን ደንበኞቻችንን አገልግሎት ወደ 5G አሳድገናል::
ለዝርዝር መረጃ: https://bit.ly/3RQ2McR
ደንብ እና ሁኔታዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ
#አዲስ_ዓመት_አዲስ_ፍጥነት_ምቾት_እና_አኗኗር
#5G
ዩኒሴፍ በ98 ሀገራት ተግባራዊ ሲያደርግ የቆየውን የ U-Report ሥርዓት እያስተዋወቀ ነው።
ዩኒሴፍ፥ በኢትዮጵያ ወጣቶች በሚመለከታቸው ነገር ላይ እንዲሁም ማኅበረሰባቸውን በሚጠቅም ጉዳይ ላይ ድምጽ እንዲሆኑና እንዲሳተፉ የሚያስችል ሥርዓት መጀመሩን ገልጿል።
በ98 ሀገራት ላይ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው ይህ ሥርዓት ወጣቶች በልማት ሥራዎች፣ በሰብዓዊ ተግባራት እንዲሁም በራሳቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳባቸውን እንዲያካፍሉና ድምጻቸውን እንዲያሰሙ የሚያግዝ ነው።
በኢትዮጵያ የዩኒሴፍ U-Report አስተባባሪ ሕይወት ገበየው ይህ ሥርዓት በኢትዮጵያ መተግበሩ፥ የወጣቶች ትርጉም ያለው ተሳትፎን ከመጨመር በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማትም የወጣቱን ሀሳብ ትኩረት ያደረገ ሥራዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ።
ይህ አዲስ የሚተገበረው የዩኒሴፍ U-Report ኢኒሽዬቲቭም በጅማሮው ከ200,000 በላይ ወጣቶችን በበጎፈቃደኝነት ለማሳተፍ አስቧል።
ወጣቱ ድምጹን ለማሰማት፣ ተጽዕኖ ለመፍጠርና ለማኅበረሰቡ ድምጽ ለመሆን ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ የጠየቁት አስተባባሪዋ ዩኒሴፍ የ U-Report መመዝገቢያ መንገዱን ለቲክቫህ ቤተሰቦች አስተዋውቀዋል።
በዚህም ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች ቦት(Bot) የተዘጋጀ ሲሆን @ureportethiopia_bot በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።
@tikvahethiopia
ዩኒሴፍ፥ በኢትዮጵያ ወጣቶች በሚመለከታቸው ነገር ላይ እንዲሁም ማኅበረሰባቸውን በሚጠቅም ጉዳይ ላይ ድምጽ እንዲሆኑና እንዲሳተፉ የሚያስችል ሥርዓት መጀመሩን ገልጿል።
በ98 ሀገራት ላይ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው ይህ ሥርዓት ወጣቶች በልማት ሥራዎች፣ በሰብዓዊ ተግባራት እንዲሁም በራሳቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳባቸውን እንዲያካፍሉና ድምጻቸውን እንዲያሰሙ የሚያግዝ ነው።
በኢትዮጵያ የዩኒሴፍ U-Report አስተባባሪ ሕይወት ገበየው ይህ ሥርዓት በኢትዮጵያ መተግበሩ፥ የወጣቶች ትርጉም ያለው ተሳትፎን ከመጨመር በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማትም የወጣቱን ሀሳብ ትኩረት ያደረገ ሥራዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ።
ይህ አዲስ የሚተገበረው የዩኒሴፍ U-Report ኢኒሽዬቲቭም በጅማሮው ከ200,000 በላይ ወጣቶችን በበጎፈቃደኝነት ለማሳተፍ አስቧል።
ወጣቱ ድምጹን ለማሰማት፣ ተጽዕኖ ለመፍጠርና ለማኅበረሰቡ ድምጽ ለመሆን ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ የጠየቁት አስተባባሪዋ ዩኒሴፍ የ U-Report መመዝገቢያ መንገዱን ለቲክቫህ ቤተሰቦች አስተዋውቀዋል።
በዚህም ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች ቦት(Bot) የተዘጋጀ ሲሆን @ureportethiopia_bot በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወልቂጤ ከተማና በቀቤና ልዩ ወረዳ በተቀሰቀሰው ግጭት ንጹሐን መገደላቸውንና ነዋሪዎችና ባለስልጣናት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል። ሥሜ ባይጠቀስ ያሉ አንድ የቀቤና ልዩ ወረዳ ነዋሪ " ሰሞኑን ሁለት የቀቤና ወጣቶች ተገድለዋል " ብለዋል። ሌላኛው የወልቂጤ ከተማ ነዋሪ ደግሞ " አንድ የወልቂጤ ሰው በወጣቶች ተገድሏል " ሲሉ ገልጸዋል። ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ…
#Update
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማና በቀቤና ልዩ ወረዳ 'በወሰን ይገባኛል' ጥያቄ የተነሳው ግጭት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ታማኝ ምንጭ፣ " ግጭቱ ወደ ገጠሩ የመዛመት ሁኔታ ነው የሚስተዋለው። ወልቂጤ ከተማ አልፎ አልፎ ካልሆነ በቀር የከፋ ነገር የለም " ብለዋል።
ወሸርቤ፣ ወልቂጤ ዙሪያ ግጭቱ መዛመት አዝማሚያ ያንዣበበባቸው የገጠር ቦታዎች መሆናቸውን አክለዋል።
ወሸርቤን ጨምሮ በወልቂጤ ገጠራማው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ የጸጥታ አካላት በወጣቶች ላይ ድብደባ እየፈጸሙ ነው ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የቀቤና ልዩ ወረዳ ምንጭ በበኩላችው፣ " ጥያቂያችን ይመለስ በማለት የሚሞግቱ ወጣቶች ለምን ይደበደባሉ ? ይህ ልክ አይደለም። ጉዳዩን በውይይት መፍታት ይሻላል " የሚል አጭር ቃል አስቀምጠዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወልቂጤ ከተማ ምንጭ ግጭቱ እንዴት ወደ ገጠሩ የመዛመት አዝማሚያ ተፈጠረ ምክንያቱ ምንድን ነው ? ብሎ ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፣ " የጸጥታው ኃይል ችግር የፈጠሩ አካላትን አሳዶ መያዝ ሲጀምር ጥፋተኞቹ ለመደበቅ የመሸሽ ሁኔታዎች ይስተዋላል " ሲሉ አስረድተዋል።
በመንግሥት በኩል ግጭቱን ለማስቆም ያለውን እንቅስቃሴ በተለከተም፣ " የተሻለ ነው ብሎ መውሰድ ይቻላል። ተጨማሪ የጸጥታ አካላት የተቀናጀ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናቸው። በዚህ በአሰሳ በርካታ የጦር መሳርያዎች ገጀራ፣ ቆንጮራ በቁጥጥር ስር ውለዋል" ነው ያሉት ብለዋል።
ይሁን እንጅ ግጭቱ ሊቆም የሚችለው በሁለቱም ወገኖች ያሉ ጥያቄዎች መልስ ሲያገኙ እንደመሆኑ መጠን በመንግሥት በኩል እስካሁን (ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ) በተጨባጭ የጸጥታ ስራ ካልሆነ በስተቀር የፖለቲካ ስራው እዚህ ግባ የሚባል አይደለም " ሲሉ አክለዋል።
በግጭቱ ምክንያት ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወልቂጤ በዩንቨርስቲና በዎሊሶ ሆስፒታሎች ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑም ተመላክቷል።
በግጭቱ አንድ ፓሊስ ላይ ጉዳት መድረሱን፣ በሁለቱም ወገኖች ሦስት ሰዎች መገደላችውን መዘገባችን ይታወሳል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።
@tikvahethiopia
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማና በቀቤና ልዩ ወረዳ 'በወሰን ይገባኛል' ጥያቄ የተነሳው ግጭት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ታማኝ ምንጭ፣ " ግጭቱ ወደ ገጠሩ የመዛመት ሁኔታ ነው የሚስተዋለው። ወልቂጤ ከተማ አልፎ አልፎ ካልሆነ በቀር የከፋ ነገር የለም " ብለዋል።
ወሸርቤ፣ ወልቂጤ ዙሪያ ግጭቱ መዛመት አዝማሚያ ያንዣበበባቸው የገጠር ቦታዎች መሆናቸውን አክለዋል።
ወሸርቤን ጨምሮ በወልቂጤ ገጠራማው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ የጸጥታ አካላት በወጣቶች ላይ ድብደባ እየፈጸሙ ነው ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የቀቤና ልዩ ወረዳ ምንጭ በበኩላችው፣ " ጥያቂያችን ይመለስ በማለት የሚሞግቱ ወጣቶች ለምን ይደበደባሉ ? ይህ ልክ አይደለም። ጉዳዩን በውይይት መፍታት ይሻላል " የሚል አጭር ቃል አስቀምጠዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወልቂጤ ከተማ ምንጭ ግጭቱ እንዴት ወደ ገጠሩ የመዛመት አዝማሚያ ተፈጠረ ምክንያቱ ምንድን ነው ? ብሎ ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፣ " የጸጥታው ኃይል ችግር የፈጠሩ አካላትን አሳዶ መያዝ ሲጀምር ጥፋተኞቹ ለመደበቅ የመሸሽ ሁኔታዎች ይስተዋላል " ሲሉ አስረድተዋል።
በመንግሥት በኩል ግጭቱን ለማስቆም ያለውን እንቅስቃሴ በተለከተም፣ " የተሻለ ነው ብሎ መውሰድ ይቻላል። ተጨማሪ የጸጥታ አካላት የተቀናጀ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናቸው። በዚህ በአሰሳ በርካታ የጦር መሳርያዎች ገጀራ፣ ቆንጮራ በቁጥጥር ስር ውለዋል" ነው ያሉት ብለዋል።
ይሁን እንጅ ግጭቱ ሊቆም የሚችለው በሁለቱም ወገኖች ያሉ ጥያቄዎች መልስ ሲያገኙ እንደመሆኑ መጠን በመንግሥት በኩል እስካሁን (ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ) በተጨባጭ የጸጥታ ስራ ካልሆነ በስተቀር የፖለቲካ ስራው እዚህ ግባ የሚባል አይደለም " ሲሉ አክለዋል።
በግጭቱ ምክንያት ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወልቂጤ በዩንቨርስቲና በዎሊሶ ሆስፒታሎች ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑም ተመላክቷል።
በግጭቱ አንድ ፓሊስ ላይ ጉዳት መድረሱን፣ በሁለቱም ወገኖች ሦስት ሰዎች መገደላችውን መዘገባችን ይታወሳል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እንድታውቁት
የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።
ከጥቅምት 6 ቀን 2016 ዓ.ም እኩለ ሌሊት 6:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በመስከረም ወር ሲሸጥበት በነበረው እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
በመስከረም ወር የነበረው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ?
- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም
ምንጭ፦ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።
ከጥቅምት 6 ቀን 2016 ዓ.ም እኩለ ሌሊት 6:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በመስከረም ወር ሲሸጥበት በነበረው እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
በመስከረም ወር የነበረው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ?
- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም
ምንጭ፦ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
#የብድር_ገደብ
ብሔራዊ ባንክ የጣለው የብድር ገደብ በባንኮች እና ተበዳሪዎች ላይ ተግዳሮት መፍጠሩ ተነግሯል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ / #NBE ከጥቂት ወራት በፊት ያወጣው የገንዘብ ፖሊሲ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡
የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ዋነኛ ዓላማ ያደረገው ይህ ፖሊሲ ፣ የባንኮች የብድር ምጣኔ ካለፈው ዓመት ከ14 በመቶ በላይ እንዳይበልጥ ገደብ የጣለ ነው፡፡
በተለይ ባንኮች የሚሰጡት ብድር በገንዘብ ፖሊሲው ከተጣለባቸው ገደብ ጋር ለማጣጣም በማሰብ ቀደም ብለው የፈቀዷቸውን ብድሮች ጭምር ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ ወይም መሰል አሠራርን እንዲከተሉ እያደረጋቸው ስለመሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ከመመርያው መውጣት ቀደም ብለው የተፈቀዱ ብድሮች ሊለቀቅላቸው እንዳልቻለ የተለያዩ ባለሀብቶችና የንግድ አንቀሳቃሾች ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ገልጸዋል።
በዚህም የተፈቀደላቸውን ብድር ታሳቢ በማድረግ የገቧቸው የቢዝነስ ስምምነቶች እየተፋረሱባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ቤትና ተሽከርካሪ ግዥ ውሎች ሳይቀሩ በእንጥልጥል እንዲቆዩ ማድረጉንም ከተበዳሪዎች መገንዘብ ተችሏል፡፡
ብድር እንዲለቀቅላቸው #ማረጋገጫ አግኝተው የነበሩት ተበዳሪዎች አሁን ላይ ብድሩን ማግኘት ለምን እንዳልቻሉ ለሚያቀርቡት ጥያቄ የሚያገኙት ምላሽ " አዲሱ የገንዘብ ፖሊሲ የጣለው የብድር ዕቀባ " መሆኑን ያስረዳሉ።
አንዳንዶቹም የተፈቀደላቸውን ብድር በትዕግሥት እንዲጠብቁ እንደተነገራቸው ያመለክታሉ፡፡
ቤት ለመግዛት ተዋውለው ከሚገለገሉበት ባንክ የፈቀደላቸውን ብድር እየተጠባበቁ የነበሩ አንድ ተበዳሪ ብድሩ እንደሚያገኙት በተገለጸላቸው ወቅት ሊለቀቅላቸው ባለመቻሉ የቤት ሽያጭ ውላቸው ሊፈርስባቸው እንደሆነ ገልጸዋል። እንዲህ ያለው ችግር በአብዛኛው በግል ባንኮች አካባቢ የሚስተዋል ነው፡፡
ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-10-17
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia
ብሔራዊ ባንክ የጣለው የብድር ገደብ በባንኮች እና ተበዳሪዎች ላይ ተግዳሮት መፍጠሩ ተነግሯል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ / #NBE ከጥቂት ወራት በፊት ያወጣው የገንዘብ ፖሊሲ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡
የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ዋነኛ ዓላማ ያደረገው ይህ ፖሊሲ ፣ የባንኮች የብድር ምጣኔ ካለፈው ዓመት ከ14 በመቶ በላይ እንዳይበልጥ ገደብ የጣለ ነው፡፡
በተለይ ባንኮች የሚሰጡት ብድር በገንዘብ ፖሊሲው ከተጣለባቸው ገደብ ጋር ለማጣጣም በማሰብ ቀደም ብለው የፈቀዷቸውን ብድሮች ጭምር ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ ወይም መሰል አሠራርን እንዲከተሉ እያደረጋቸው ስለመሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ከመመርያው መውጣት ቀደም ብለው የተፈቀዱ ብድሮች ሊለቀቅላቸው እንዳልቻለ የተለያዩ ባለሀብቶችና የንግድ አንቀሳቃሾች ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ገልጸዋል።
በዚህም የተፈቀደላቸውን ብድር ታሳቢ በማድረግ የገቧቸው የቢዝነስ ስምምነቶች እየተፋረሱባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ቤትና ተሽከርካሪ ግዥ ውሎች ሳይቀሩ በእንጥልጥል እንዲቆዩ ማድረጉንም ከተበዳሪዎች መገንዘብ ተችሏል፡፡
ብድር እንዲለቀቅላቸው #ማረጋገጫ አግኝተው የነበሩት ተበዳሪዎች አሁን ላይ ብድሩን ማግኘት ለምን እንዳልቻሉ ለሚያቀርቡት ጥያቄ የሚያገኙት ምላሽ " አዲሱ የገንዘብ ፖሊሲ የጣለው የብድር ዕቀባ " መሆኑን ያስረዳሉ።
አንዳንዶቹም የተፈቀደላቸውን ብድር በትዕግሥት እንዲጠብቁ እንደተነገራቸው ያመለክታሉ፡፡
ቤት ለመግዛት ተዋውለው ከሚገለገሉበት ባንክ የፈቀደላቸውን ብድር እየተጠባበቁ የነበሩ አንድ ተበዳሪ ብድሩ እንደሚያገኙት በተገለጸላቸው ወቅት ሊለቀቅላቸው ባለመቻሉ የቤት ሽያጭ ውላቸው ሊፈርስባቸው እንደሆነ ገልጸዋል። እንዲህ ያለው ችግር በአብዛኛው በግል ባንኮች አካባቢ የሚስተዋል ነው፡፡
ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-10-17
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia
Telegraph
Reporter Newspaper
ብሔራዊ ባንክ የጣለው የብድር ገደብ በባንኮችና ተበዳሪዎች ላይ የፈጠረው ተግዳሮት ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከጥቂት ወራት በፊት ያወጣው የገንዘብ ፖሊሲ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ዋነኛ ዓላማ ያደረገው ይህ ፖሊሲ፣ የባንኮች የብድር ምጣኔ ካለፈው ዓመት ከ14 በመቶ በላይ እንዳይበልጥ ገደብ የጣለ ነው፡፡ ይህ መመርያ መተግበር ከጀመረ ወዲህ ግን ከጅምሩ አንዳንድ ተፅዕኖዎች መታየት…
የእርስዎ ስኬት የኛም ስኬት ነው!
ህልምዎን እውን ለማድረግ በጋራ እንሰራለን፡፡
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን
የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ
https://yangx.top/Globalbankethiopia123
#Globalbankethiopia #sharedsuccess
ህልምዎን እውን ለማድረግ በጋራ እንሰራለን፡፡
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን
የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ
https://yangx.top/Globalbankethiopia123
#Globalbankethiopia #sharedsuccess
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ፍልስጤም #እስራኤል
በጋዛ በሚገኝ ሆስፒታል ላይ በተፈፀመ ጥቃት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገደሉ።
ሃማስ ጥቃቱን እስራኤል ነው የፈፀመችው ብሏል።
የእስራኤል መከላከያ ደግሞ " ኢስላሚክ ጂሃድ " የተባለው ቡድን እስራኤል ላይ ያስወነጨፈው ሮኬት ዒላማው ሳይሳካ ቀርቶ የተፈጠረ ነው ብሏል።
ትላንት ጋዛ ውስጥ በሚገኘው "አልአህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ በደረሰ የአየር ጥቃት በትንሹ 500 ሰዎች መገደላቸውን በጋዛ የሚገኘው ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።
ሃማስ ጥቃቱን እስራኤል ነው የፈፀመችው ብሏል። ጥቃቱን " የጦር ወንጀል ነው" ሲል ገልጾ " ሆስፒታሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ የታመሙ እና የቆሰሉ ሰዎች ነበሩበት ብሏል።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ፤ በጋዛ የሚገኘው ሆስፒታል የተመታው ባያልተሳካ የ " እስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ብሏል።
ያልተሳካ ሮኬት ያስወነጨፈው ይኸው ቡድን ለሆስፒታሉ መመታት ተጠያቂ ነው ሲል ገልጿል።
" እኛ ሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀምንም " ብሏል።
የ " ፍልስጤም እስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው የተለመደ ቅጥፈት ነው ብሏል። እስራኤል ከተለመደው ጭፍጨፋ ተጠያቂነት ለማምለጥ በፍልስጤማውያን እና ' ኢስላሚክ ጂሃድ ' ላይ ጣቷን ለመጠቆም የፈጠረችው ሀሰተኛ ፈጠራ ነው ሲል ገልጿል።
" ፍልስጤም እስላሚክ ጂሃድ " እኤአ 1981 የተመሰረተ ሲሆን በጋዛ እና ዌስት ባንክ ውስጥ ይንቀሳቀሳል።
በሌላ በኩል ፤ የፍልስጤም ፕሬዜዳንት ማሃሙድ አባስ በሆስፒታሉ ላይ በተፈፀመው ጥቃት እና በጠፋው የሰው ህይወት ምክንያት የ3 ቀን ሀዘን አውጀዋል።
በሆስፒታል ላይ የተፈፀመውን ጥቃት ሀገራት እና ተቋማት እያወገዙ ይገኛሉ። በተለያዩ ከተሞችም እስራኤልን የሚያወግዙ ሰልፎች እየተደረጉ ይገኛሉ።
ዓለም ለጋዛ ሆስፒታል ለደረሰው ጥቃት ምን ምላሽ ሰጠ ?
እስራኤል የአየር ጥቃቱን ፈፅማለች ብለው የከሰሱና ያወገዙ ፤ በጉዳቱ ሀዘናቸውን የገለፁ ፦
🇪🇬 የግብፅ ፕሬዝዳንት
🇯🇴 የዮርዳኖስ ንጉስ
🇸🇾 የሶሪያ ፕሬዝዳንት
🇨🇺 የኩባ ፕሬዝዳንት
🇮🇶 የኢራቅ መንግስት
🇸🇦 የሳዑዲ አረቢያ መንግስት
🇹🇷የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇻🇪 የቬንዙዌላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🌍 የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሃላፊ
🇮🇷 የኢራን ፕሬዝዳንት (እስራኤል ብቻ ሳትሆን አሜሪካም ጭምር ከእስራኤል ጋር ሀላፊነት ትወስዳለች ብለዋል)
ጥቃቱን ያወገዙ ነገር ግን ማንንም ያልወቀሱ ፤ ይልቁንም ምርመራ እንዲደረግ የጠየቁ ፦
🇪🇺 የአውሮጳ ዲፕሎማሲ ኃላፊ
🇫🇷 የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት
🇳🇱 የኔዘርላንድስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇪🇸 የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇬🇧 የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት
🇯🇵 የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇺🇸 አሜሪካ ማንም ሳትከስ ነገር ግን ስለ ተፈጠረው ሁኔታ ተጨማሪ መረጃዎችን ሰበስባለሁ ብላለች።
" ማስረጃ አቅርቢ " - ሩስያ
🇷🇺 የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል በጥቃቱ ላይ የለሁበትም ካለች የሳተላይ ምስሎችን በማስረጃነት ታቅርብ ብሏል።
እኤአ ጥቅምት 7 ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኋላ እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ ባደረሰችው ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ከ3,200 በልጠዋል።
በእስራኤል ውስጥ በሃማስ ጥቃት የተገደሉ ከ1,400 በላይ ሰዎች ሆነዋል።
More 👉 @Birlikethiopia
በጋዛ በሚገኝ ሆስፒታል ላይ በተፈፀመ ጥቃት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገደሉ።
ሃማስ ጥቃቱን እስራኤል ነው የፈፀመችው ብሏል።
የእስራኤል መከላከያ ደግሞ " ኢስላሚክ ጂሃድ " የተባለው ቡድን እስራኤል ላይ ያስወነጨፈው ሮኬት ዒላማው ሳይሳካ ቀርቶ የተፈጠረ ነው ብሏል።
ትላንት ጋዛ ውስጥ በሚገኘው "አልአህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ በደረሰ የአየር ጥቃት በትንሹ 500 ሰዎች መገደላቸውን በጋዛ የሚገኘው ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።
ሃማስ ጥቃቱን እስራኤል ነው የፈፀመችው ብሏል። ጥቃቱን " የጦር ወንጀል ነው" ሲል ገልጾ " ሆስፒታሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ የታመሙ እና የቆሰሉ ሰዎች ነበሩበት ብሏል።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ፤ በጋዛ የሚገኘው ሆስፒታል የተመታው ባያልተሳካ የ " እስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ብሏል።
ያልተሳካ ሮኬት ያስወነጨፈው ይኸው ቡድን ለሆስፒታሉ መመታት ተጠያቂ ነው ሲል ገልጿል።
" እኛ ሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀምንም " ብሏል።
የ " ፍልስጤም እስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው የተለመደ ቅጥፈት ነው ብሏል። እስራኤል ከተለመደው ጭፍጨፋ ተጠያቂነት ለማምለጥ በፍልስጤማውያን እና ' ኢስላሚክ ጂሃድ ' ላይ ጣቷን ለመጠቆም የፈጠረችው ሀሰተኛ ፈጠራ ነው ሲል ገልጿል።
" ፍልስጤም እስላሚክ ጂሃድ " እኤአ 1981 የተመሰረተ ሲሆን በጋዛ እና ዌስት ባንክ ውስጥ ይንቀሳቀሳል።
በሌላ በኩል ፤ የፍልስጤም ፕሬዜዳንት ማሃሙድ አባስ በሆስፒታሉ ላይ በተፈፀመው ጥቃት እና በጠፋው የሰው ህይወት ምክንያት የ3 ቀን ሀዘን አውጀዋል።
በሆስፒታል ላይ የተፈፀመውን ጥቃት ሀገራት እና ተቋማት እያወገዙ ይገኛሉ። በተለያዩ ከተሞችም እስራኤልን የሚያወግዙ ሰልፎች እየተደረጉ ይገኛሉ።
ዓለም ለጋዛ ሆስፒታል ለደረሰው ጥቃት ምን ምላሽ ሰጠ ?
እስራኤል የአየር ጥቃቱን ፈፅማለች ብለው የከሰሱና ያወገዙ ፤ በጉዳቱ ሀዘናቸውን የገለፁ ፦
🇪🇬 የግብፅ ፕሬዝዳንት
🇯🇴 የዮርዳኖስ ንጉስ
🇸🇾 የሶሪያ ፕሬዝዳንት
🇨🇺 የኩባ ፕሬዝዳንት
🇮🇶 የኢራቅ መንግስት
🇸🇦 የሳዑዲ አረቢያ መንግስት
🇹🇷የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇻🇪 የቬንዙዌላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🌍 የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሃላፊ
🇮🇷 የኢራን ፕሬዝዳንት (እስራኤል ብቻ ሳትሆን አሜሪካም ጭምር ከእስራኤል ጋር ሀላፊነት ትወስዳለች ብለዋል)
ጥቃቱን ያወገዙ ነገር ግን ማንንም ያልወቀሱ ፤ ይልቁንም ምርመራ እንዲደረግ የጠየቁ ፦
🇪🇺 የአውሮጳ ዲፕሎማሲ ኃላፊ
🇫🇷 የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት
🇳🇱 የኔዘርላንድስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇪🇸 የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇬🇧 የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት
🇯🇵 የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇺🇸 አሜሪካ ማንም ሳትከስ ነገር ግን ስለ ተፈጠረው ሁኔታ ተጨማሪ መረጃዎችን ሰበስባለሁ ብላለች።
" ማስረጃ አቅርቢ " - ሩስያ
🇷🇺 የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል በጥቃቱ ላይ የለሁበትም ካለች የሳተላይ ምስሎችን በማስረጃነት ታቅርብ ብሏል።
እኤአ ጥቅምት 7 ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኋላ እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ ባደረሰችው ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ከ3,200 በልጠዋል።
በእስራኤል ውስጥ በሃማስ ጥቃት የተገደሉ ከ1,400 በላይ ሰዎች ሆነዋል።
More 👉 @Birlikethiopia
#GudafTsegay #TigistAssefa
የዓለም አትሌቲክስ የአመቱ ምርጥ ሴት አትሌት ዘርፍ የመጨረሻ እጩዎች ይፋ ተደርገው ድምፅ እየተሰጠ ይገኛል።
ሁለት #ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከምርጥ አስራ አንድ እጩዎች ውስጥ ይገኙበታል።
እጩዎቹም ፤ በቅርቡ የአለም የማራቶን ሪከርድን መስበር የቻለችው ኢትዮጵያዊት አትሌት ትዕግስት አሰፋ እንዲሁም የ5000ሜ የዓለም ክብረወሰን የሰበረችው ጉዳፍ ፀጋይ ናቸው።
አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በዚህ አመት የ5000 ሜትር የአለም ክብረወሰን ከመስበሯም በተጨማሪ የ10,000ሜ የዓለም ሻምፒዮን እንደነበረች ይታወሳል።
ምርጫው እንዴት ይካሄዳል ?
የዓለም አትሌቲክስ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት የአሸናፊዎች ምርጫ ለዓለም አትሌቲክስ ኮሚቴ እና ለዓለም አትሌቲክስ ቤተሰቦች ድምፅ በኢሜል መስጠት እንደሚቻል ተገልጿል።
ደጋፊዎች እንዴት መምረጥ ይችላሉ ?
ሁሉም የአትሌቲክስ ደጋፊዎች የሚመርጧቸውን አትሌቶች ፎቶ በአለም አትሌቲክስ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በመፈለግ በፌስቡክ ፣ ዩቲዩብ እና ኢንስታግራም ላይክ በማድረግ እንዲሁም በ " X " ሪፖስት በማድረግ መምረጥ ይችላሉ።
ጉዳፍ ፀጋይን #ላይክ / #ሪትዊት ለማድረግ ፦
ፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/100064391421386/posts/pfbid0hS68YYaTusAL2g6TrYMbMuuW1pDFv2KBQbfcD4piPiJc3XU1iDyb45k6CKCf3bgYl/?app=fbl
X / የቀድሞ ትዊተር ላይ ሪትዊት ለማድረግ ፦ https://twitter.com/WorldAthletics/status/1712082175250563508?t=rpGi0sYnnozLQvDtN4RTKQ&s=19
ኢንስታግራም ፦ https://www.instagram.com/p/CyQkhc9Mry7/?igshid=NjIwNzIyMDk2Mg==
ትዕግስት አሰፋን #ላይክ / #ሪትዊት ለማድረግ ፦
ፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/100064391421386/posts/pfbid01BPvP9Vb4sF7tRxmX2Lb5BqWDgXjFB17Agijp9vWQWsJufvbrkXL3yH7PZbidcaTl/?app=fbl
X / የቀድሞ ትዊተር ሪትዊት ለማድረግ ፦ https://twitter.com/WorldAthletics/status/1712082042391802157?t=xlF0PNgzEhsBxSb56pANlw&s=19
ኢንስታግራም ፦ https://www.instagram.com/p/CyQjzyRM8Iv/?igshid=NjIwNzIyMDk2Mg==
(ሼር ያድርጉ)
@tikvahethiopia
የዓለም አትሌቲክስ የአመቱ ምርጥ ሴት አትሌት ዘርፍ የመጨረሻ እጩዎች ይፋ ተደርገው ድምፅ እየተሰጠ ይገኛል።
ሁለት #ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከምርጥ አስራ አንድ እጩዎች ውስጥ ይገኙበታል።
እጩዎቹም ፤ በቅርቡ የአለም የማራቶን ሪከርድን መስበር የቻለችው ኢትዮጵያዊት አትሌት ትዕግስት አሰፋ እንዲሁም የ5000ሜ የዓለም ክብረወሰን የሰበረችው ጉዳፍ ፀጋይ ናቸው።
አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በዚህ አመት የ5000 ሜትር የአለም ክብረወሰን ከመስበሯም በተጨማሪ የ10,000ሜ የዓለም ሻምፒዮን እንደነበረች ይታወሳል።
ምርጫው እንዴት ይካሄዳል ?
የዓለም አትሌቲክስ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት የአሸናፊዎች ምርጫ ለዓለም አትሌቲክስ ኮሚቴ እና ለዓለም አትሌቲክስ ቤተሰቦች ድምፅ በኢሜል መስጠት እንደሚቻል ተገልጿል።
ደጋፊዎች እንዴት መምረጥ ይችላሉ ?
ሁሉም የአትሌቲክስ ደጋፊዎች የሚመርጧቸውን አትሌቶች ፎቶ በአለም አትሌቲክስ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በመፈለግ በፌስቡክ ፣ ዩቲዩብ እና ኢንስታግራም ላይክ በማድረግ እንዲሁም በ " X " ሪፖስት በማድረግ መምረጥ ይችላሉ።
ጉዳፍ ፀጋይን #ላይክ / #ሪትዊት ለማድረግ ፦
ፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/100064391421386/posts/pfbid0hS68YYaTusAL2g6TrYMbMuuW1pDFv2KBQbfcD4piPiJc3XU1iDyb45k6CKCf3bgYl/?app=fbl
X / የቀድሞ ትዊተር ላይ ሪትዊት ለማድረግ ፦ https://twitter.com/WorldAthletics/status/1712082175250563508?t=rpGi0sYnnozLQvDtN4RTKQ&s=19
ኢንስታግራም ፦ https://www.instagram.com/p/CyQkhc9Mry7/?igshid=NjIwNzIyMDk2Mg==
ትዕግስት አሰፋን #ላይክ / #ሪትዊት ለማድረግ ፦
ፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/100064391421386/posts/pfbid01BPvP9Vb4sF7tRxmX2Lb5BqWDgXjFB17Agijp9vWQWsJufvbrkXL3yH7PZbidcaTl/?app=fbl
X / የቀድሞ ትዊተር ሪትዊት ለማድረግ ፦ https://twitter.com/WorldAthletics/status/1712082042391802157?t=xlF0PNgzEhsBxSb56pANlw&s=19
ኢንስታግራም ፦ https://www.instagram.com/p/CyQjzyRM8Iv/?igshid=NjIwNzIyMDk2Mg==
(ሼር ያድርጉ)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA #Israel
የአሜሪካው ፕሬዜዳንት #ጆ_ባይደን እስራኤል ገብተዋል።
ባይደን በእስራኤል ቆያታቸው ጦርነቱ ከዚህም በላይ ከፍቶ እንዳይስፋፋ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ያደርጋሉ ተብሏል።
የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቃል አቀባይ ፕሬዝዳንት ባይደን የቀጠለውን ጦርነት #ዓላማን በተመለከተ ለኔታንያሁ ከበድ ያሉ ጥያቄዎችን እንደሚጠይቋቸው ገልጸዋል።
ባይደን በቅድሚያ ይሄዳሉ ተብሎ የነበረው ወደ ዮርዳኖስ ነበር።
በዛም ከአረብ ሀገራት መሪዎች ጋር ይመክራሉ ተብሎ ነበር። ነገር ግን ከአሜሪካ ከተነሱ በኃላ የአረብ ሀገራት መሪዎች ከባይደን ጋር እንደማይገናኙ እና የነበረውም ስብሰባ መሰረዙ ተሰምቷል።
አሜሪካም ፕሬዜዳንቷ ወደ ዮርዳኖስ እንደማይሄዱና ይህም " የጋራ ውሳኔ " መሆኑን ገልጻለች።
" በእናተ አልተፈፀመም " - ባይደን
ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን እስራኤል በሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀመችም ብለዋል።
እስራኤል የሚገኙት ጆ ባይደን በጋዛ በሚገኘው " አል አህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ ፍንዳታ የተፈፀመው በእስራኤል ሳይሆን " በሌላኛው ቡድን " ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ባይደን ለእስራኤሉ ጠ/ሚ ኔታንያሁ ፤ " ትናንትና በጋዛ ሆስፒታል በደረሰው ፍንዳታ በጣም አዝኛለሁ " ያሉ ሲሆን " ባየሁት መሰረት፣ የተደረገው በሌላው ቡድን ይመስላል ፤ እንጂ በአንተ (እስራኤል) አይደለም " ሲሉ ተናግረዋል።
እስራኤል ፤ በሆስፒታሉ ላይ ለደረሰው ጥቃት ያልተሳካ " የኢስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ያለች ሲሆን " ሃማስ " እንዲሁም " የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት ጥቃቱ የተፈፀመው በእስራኤል ነው ብለዋል።
" የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው እንዲሁም ከጭፍጨፋው ተጠያቂነት ለማምለጥ ጣቷን በእስላሚክ ጂሃድ እና ፍልስጤማውያን ላይ የጠቆመችበት የተለመደ የሀሰት እና ቅጥፈት ፈጠራዋ ነው ብሏ
More + @BirlikEthiopia
የአሜሪካው ፕሬዜዳንት #ጆ_ባይደን እስራኤል ገብተዋል።
ባይደን በእስራኤል ቆያታቸው ጦርነቱ ከዚህም በላይ ከፍቶ እንዳይስፋፋ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ያደርጋሉ ተብሏል።
የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቃል አቀባይ ፕሬዝዳንት ባይደን የቀጠለውን ጦርነት #ዓላማን በተመለከተ ለኔታንያሁ ከበድ ያሉ ጥያቄዎችን እንደሚጠይቋቸው ገልጸዋል።
ባይደን በቅድሚያ ይሄዳሉ ተብሎ የነበረው ወደ ዮርዳኖስ ነበር።
በዛም ከአረብ ሀገራት መሪዎች ጋር ይመክራሉ ተብሎ ነበር። ነገር ግን ከአሜሪካ ከተነሱ በኃላ የአረብ ሀገራት መሪዎች ከባይደን ጋር እንደማይገናኙ እና የነበረውም ስብሰባ መሰረዙ ተሰምቷል።
አሜሪካም ፕሬዜዳንቷ ወደ ዮርዳኖስ እንደማይሄዱና ይህም " የጋራ ውሳኔ " መሆኑን ገልጻለች።
" በእናተ አልተፈፀመም " - ባይደን
ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን እስራኤል በሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀመችም ብለዋል።
እስራኤል የሚገኙት ጆ ባይደን በጋዛ በሚገኘው " አል አህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ ፍንዳታ የተፈፀመው በእስራኤል ሳይሆን " በሌላኛው ቡድን " ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ባይደን ለእስራኤሉ ጠ/ሚ ኔታንያሁ ፤ " ትናንትና በጋዛ ሆስፒታል በደረሰው ፍንዳታ በጣም አዝኛለሁ " ያሉ ሲሆን " ባየሁት መሰረት፣ የተደረገው በሌላው ቡድን ይመስላል ፤ እንጂ በአንተ (እስራኤል) አይደለም " ሲሉ ተናግረዋል።
እስራኤል ፤ በሆስፒታሉ ላይ ለደረሰው ጥቃት ያልተሳካ " የኢስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ያለች ሲሆን " ሃማስ " እንዲሁም " የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት ጥቃቱ የተፈፀመው በእስራኤል ነው ብለዋል።
" የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው እንዲሁም ከጭፍጨፋው ተጠያቂነት ለማምለጥ ጣቷን በእስላሚክ ጂሃድ እና ፍልስጤማውያን ላይ የጠቆመችበት የተለመደ የሀሰት እና ቅጥፈት ፈጠራዋ ነው ብሏ
More + @BirlikEthiopia
አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መታሰራቸው ተሰምቷል።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሰሞኑን መሆኑንና አቶ ታምሩ ገምበታ ግን ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል።
የምክትል ዳይሬክተሩ ቤት በፍርድ ቤት የብርበራ ፈቃድ መበርበሩንና ዛሬ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡
የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ እንዳሉም ተመላክቷል።
አገልግሎቱን በዋና ዳይሬክተርነት ይመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙሉጌታ፣ ምክትል ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ፍራኦል ጣፋና አቶ ታምሩ ገምበታን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከ3 ወራት በፊት ሐምሌ መጀመሪያ ሳምንት አካባቢ ከኃላፊነት ማንሳታቸው ይታወሳል፡፡
ተቋሙ ከፓስፖርትና መሰል አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ቅሬታ ሲቀርብበት መቆየቱ ይታወቃል።
በተጨማሪ ከዜጎች ከፍተኛ ገንዘብ በመቀበል በሕወጥ መንገድ ወደ ውጭ አገር ሲልኩ ነበር የተባሉ 16 የተቋሙ ሠራተኞች፣ እንዲሁም 5 በአሠሪና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ስም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሰዎችም ከዚህ ቀደም በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
በተያዘው ሳምንት በቁጥጥር ሥር መዋላቸው የተሰማው ምክትል ዳይሬክተሩን ጨምሮ ሌሎች ሰዎችም ከሙስና ጋር በተያያዘ መጠርጠራቸው ተገልጿል፡፡
ምንጭ፦ #ሪፖርተር_ጋዜጣ
@tikvahethiopia
የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሰሞኑን መሆኑንና አቶ ታምሩ ገምበታ ግን ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል።
የምክትል ዳይሬክተሩ ቤት በፍርድ ቤት የብርበራ ፈቃድ መበርበሩንና ዛሬ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡
የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ እንዳሉም ተመላክቷል።
አገልግሎቱን በዋና ዳይሬክተርነት ይመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙሉጌታ፣ ምክትል ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ፍራኦል ጣፋና አቶ ታምሩ ገምበታን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከ3 ወራት በፊት ሐምሌ መጀመሪያ ሳምንት አካባቢ ከኃላፊነት ማንሳታቸው ይታወሳል፡፡
ተቋሙ ከፓስፖርትና መሰል አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ቅሬታ ሲቀርብበት መቆየቱ ይታወቃል።
በተጨማሪ ከዜጎች ከፍተኛ ገንዘብ በመቀበል በሕወጥ መንገድ ወደ ውጭ አገር ሲልኩ ነበር የተባሉ 16 የተቋሙ ሠራተኞች፣ እንዲሁም 5 በአሠሪና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ስም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሰዎችም ከዚህ ቀደም በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
በተያዘው ሳምንት በቁጥጥር ሥር መዋላቸው የተሰማው ምክትል ዳይሬክተሩን ጨምሮ ሌሎች ሰዎችም ከሙስና ጋር በተያያዘ መጠርጠራቸው ተገልጿል፡፡
ምንጭ፦ #ሪፖርተር_ጋዜጣ
@tikvahethiopia