TIKVAH-ETHIOPIA
#ምርቃት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ከነገ ረቡዕ ጀምሮ ተማሪዎቻቸውን ያስመርቃሉ። ተቋማት ለዓመታት ያስተማሯቸውን ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸው ፣ የክብር እንግዶች በተገኙበት ነው የሚያስመርቋቸው። ዘንድሮ ከተሰጠው የመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ በምርቃት መርሃግብር ላይ ከመሳተፍ ጋር በተገናኘ በተመራቂዎች ዘንድ ጥያቄዎች የነበሩ ቢሆንም ትምህርት ሚኒስቴር ይህ ጉዳይ የተቋማቱ #የሴኔት ውሳኔ ጉዳይ መሆኑን ገልጾ…
ከ20 በላይ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው።
በዛሬው ዕለት በርካታ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ።
ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ/ም ፦
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ ካምፓስ)
- ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ (በዋናው ግቢ)
- አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ (ዋናው ግቢ)
- ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ
- ጂንካ ዩኒቨርሲቲ
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
- ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ
- ዲላ ዩኒቨርሲቲ
- እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
- ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ (በዋናው ግቢ)
- መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ
- ቀብሪ ድሃር ዩኒቨርሲቲ
- ወራቤ ዩኒቨርሲቲ
- ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
- ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ
- መቱ ዩኒቨርሲቲ
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ
- ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
- ቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ
- ወልድያ ዩኒቨርሲቲ
- ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ
- ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ።
ተጨማሪ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መረጃዎች በ @tikvahuniversity በኩል ማግኘት ትችላላችሁ።
ተመራቂዎች እና መላው ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ !!
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት በርካታ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ።
ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ/ም ፦
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ ካምፓስ)
- ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ (በዋናው ግቢ)
- አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ (ዋናው ግቢ)
- ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ
- ጂንካ ዩኒቨርሲቲ
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
- ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ
- ዲላ ዩኒቨርሲቲ
- እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
- ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ (በዋናው ግቢ)
- መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ
- ቀብሪ ድሃር ዩኒቨርሲቲ
- ወራቤ ዩኒቨርሲቲ
- ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
- ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ
- መቱ ዩኒቨርሲቲ
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ
- ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
- ቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ
- ወልድያ ዩኒቨርሲቲ
- ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ
- ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ።
ተጨማሪ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መረጃዎች በ @tikvahuniversity በኩል ማግኘት ትችላላችሁ።
ተመራቂዎች እና መላው ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ !!
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከ20 በላይ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው። በዛሬው ዕለት በርካታ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ። ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ/ም ፦ - ጅማ ዩኒቨርሲቲ - ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ ካምፓስ) - ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ (በዋናው ግቢ) - አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ (ዋናው ግቢ) - ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ - ጂንካ ዩኒቨርሲቲ - ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ…
አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመቄዶንያ መስራች አቶ ቢንያም በለጠ እና ለአርቲስት ደበበ እሸቱ ፤ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ለተወዳጇ ድምፃዊት እጅጋየሁ ሽባባው ( #ጂጂ ) የክብር ዶክትሬት ዲግሪ አበርክተዋል።
አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ የመቄዶኒያ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ቢንያም በለጠ ላከናወኗቸው በጎ ስራዎች የክብር ዶክትሬት አበርክቶላቸዋል። በሰሩት ስራ በሰው ልጆች ደህንነት ላይ ለሀገር የማይተካ አስተዋፅኦ ማበርከታቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው አርቲስት ደበበ እሸቱ በኪነጥበብ ዘርፍ ላበረከቱት ውለታ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷል።
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ለድምጻዊት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ሰጥቷል።
ዕውቅናው ሁለገቧ አርቲስት #የኢትዮጵያን ባህልና ሙዚቃ ለዓለም በማስተዋወቅ እንዲሁም በኪነ ጥበብ #የአዊን_ሕዝብ_ቋንቋ እና #ባህል በማሳደግ ላበረከተችው አስተዋፅኦ ነው የክብር ዶክትሬት የተበረከተላት።
የክብር ዶክትሬቱን የእጅጋየሁ ሽባባው ወላጅ እናት ተቀብለዋል።
@tikvahethiopia
አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ የመቄዶኒያ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ቢንያም በለጠ ላከናወኗቸው በጎ ስራዎች የክብር ዶክትሬት አበርክቶላቸዋል። በሰሩት ስራ በሰው ልጆች ደህንነት ላይ ለሀገር የማይተካ አስተዋፅኦ ማበርከታቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው አርቲስት ደበበ እሸቱ በኪነጥበብ ዘርፍ ላበረከቱት ውለታ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷል።
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ለድምጻዊት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ሰጥቷል።
ዕውቅናው ሁለገቧ አርቲስት #የኢትዮጵያን ባህልና ሙዚቃ ለዓለም በማስተዋወቅ እንዲሁም በኪነ ጥበብ #የአዊን_ሕዝብ_ቋንቋ እና #ባህል በማሳደግ ላበረከተችው አስተዋፅኦ ነው የክብር ዶክትሬት የተበረከተላት።
የክብር ዶክትሬቱን የእጅጋየሁ ሽባባው ወላጅ እናት ተቀብለዋል።
@tikvahethiopia
#CBE
ትክክለኛ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይከተሉ!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ስምና አርማ በመጠቀም በሚከፈቱ ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት የሌብነት ተግባር የሚፈፅሙ አጭበርባሪዎች አሉ፡፡
በመሆኑም የባንኩን ትክክለኛ የማኅበራዊ ትስስር ገፆች ብቻ በመከተል ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ያግኙ፤ ከአጭበርባሪዎች ይጠበቁ!
የባንኩ ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር ገፆች፡
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh
• YouTube፡- https://www.youtube.com/commercialbankofethiopia
• LinkedIn፡- https://www.linkedin.com/company/commercialbankofethiopia
• Twitter፡- https://twitter.com/combankethiopia
• Telegram፡- https://yangx.top/combankethofficial
• Instagram፡- https://www.instagram.com/commercialbankofethiopia/
• tiktok:- https://www.tiktok.com/@commercialbankofethiopia
ትክክለኛ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይከተሉ!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ስምና አርማ በመጠቀም በሚከፈቱ ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት የሌብነት ተግባር የሚፈፅሙ አጭበርባሪዎች አሉ፡፡
በመሆኑም የባንኩን ትክክለኛ የማኅበራዊ ትስስር ገፆች ብቻ በመከተል ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ያግኙ፤ ከአጭበርባሪዎች ይጠበቁ!
የባንኩ ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር ገፆች፡
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh
• YouTube፡- https://www.youtube.com/commercialbankofethiopia
• LinkedIn፡- https://www.linkedin.com/company/commercialbankofethiopia
• Twitter፡- https://twitter.com/combankethiopia
• Telegram፡- https://yangx.top/combankethofficial
• Instagram፡- https://www.instagram.com/commercialbankofethiopia/
• tiktok:- https://www.tiktok.com/@commercialbankofethiopia
#ፖሊኪዩር_መድሀኒት_ቤት
👉 https://yangx.top/PolyCure
ኦርጂናል የሆኑ የተለያዩ የወንዶች፣ የሴቶች ፣ የህጻናት የቆዳ ፣ የንጽህና እና የዉበት መጠበቂያ ምርቶች ፣ ቫይታሚኖች ፣ ወተቶች እና ኮስሞቲክሶች ከተለያዩ አገሮች አስመጥተን በ መሸጥ ላይ እንገኛለን ።
ባሉበት ቦታ ሆነው ይዘዙን በፍጥነት ያሉበት ቦታ እናደርሳለን። አድራሻ:- 22 ማዞሪያ ኖህ ህንፃ ከ ጎላጉል ህንፃ አጠገብ ። ለበለጠ መረጃ +251978454647
https://www.facebook.com/polycurepharmacy/
https://www.instagram.com/polycurepharmacy1/
@Polycure
👉 https://yangx.top/PolyCure
ኦርጂናል የሆኑ የተለያዩ የወንዶች፣ የሴቶች ፣ የህጻናት የቆዳ ፣ የንጽህና እና የዉበት መጠበቂያ ምርቶች ፣ ቫይታሚኖች ፣ ወተቶች እና ኮስሞቲክሶች ከተለያዩ አገሮች አስመጥተን በ መሸጥ ላይ እንገኛለን ።
ባሉበት ቦታ ሆነው ይዘዙን በፍጥነት ያሉበት ቦታ እናደርሳለን። አድራሻ:- 22 ማዞሪያ ኖህ ህንፃ ከ ጎላጉል ህንፃ አጠገብ ። ለበለጠ መረጃ +251978454647
https://www.facebook.com/polycurepharmacy/
https://www.instagram.com/polycurepharmacy1/
@Polycure
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ለእኔ ሳይሆን ስለእኔ ብዙ ለከፈለችው ወላጅ እናቴ ይሁንልኝ " - ተመራቂው ተማሪ
54 ኮርሶችን A+ ያገኘው ተመራቂ ተማሪ ፤ " ለእኔ ሳይሆን ስለእኔ ብዙ ለከፈለችው ወላጅ እናቴ" ይሁንልኝ በማለት ሜዳልያውን እንደተቀበለ ወደ እናቱ ሮጦ በመሄድ አጥልቆላታል።
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የዋንጫና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የሆነው ተመራቂ ተማሪ ዳግም ተስፋዬ ይህን አስደናቂ ተግባር ፈጸሟል።
ተመራቂው በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በዕፅዋት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ከወሰዳቸው 64 ኮርሶች 54ቱን ኮርሶች A+ በማምጣት የወርቅ ተሸላሚ መሆኑን ኢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
54 ኮርሶችን A+ ያገኘው ተመራቂ ተማሪ ፤ " ለእኔ ሳይሆን ስለእኔ ብዙ ለከፈለችው ወላጅ እናቴ" ይሁንልኝ በማለት ሜዳልያውን እንደተቀበለ ወደ እናቱ ሮጦ በመሄድ አጥልቆላታል።
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የዋንጫና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የሆነው ተመራቂ ተማሪ ዳግም ተስፋዬ ይህን አስደናቂ ተግባር ፈጸሟል።
ተመራቂው በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በዕፅዋት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ከወሰዳቸው 64 ኮርሶች 54ቱን ኮርሶች A+ በማምጣት የወርቅ ተሸላሚ መሆኑን ኢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ወይዘሮ_እህተ_በቀለ #ዮርዳኖስ_ወሮታው👏
" አራት ዓመት ልጄን በዊልቸር እያመላለስኩ አስተምሬ በማዕረግ አስመርቄያለሁ " - ወይዘሮ እህተ በቀለ
ወይዘሮ እህተ በቀለ ይባላሉ። ልጃቸው ዮርዳኖስ ወሮታው አካሏን በራሷ ማንቀሳቀስ የማያስችል ጉዳት አለባት።
ዮርዳኖስ በእናቷ ድጋፍ ዛሬ ትምህርቷን አጠናቃ ከአዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ ከሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል #በማዕረግ ተመርቃለች፡፡
እናት አህተ ፤ " አራት ዓመት ሙሉ ልጄን በዊልቸር እያመላለስኩ አስተምሬ አጠናቅቄያለሁ። አራት ዓመት ለእኔ እንደ አራት ቀን ነው። ምንም አልተሰማኝም ደስ ብሎኝ አልፏል" ብለዋል።
በአራት ዓመት የትምህርት ቆይታዋ የሚሰጣትን ትምህርት ክፍል ውስጥ አብረዋት ቁጭ ብለው እየጻፉላት እንዳስተማሯት እናት ለኢፕድ ተናግረዋል።
" ዮርዳኖስ የማንበብ ችሎታዋን እወድላታለሁ። ያነበበችውን አለመርሳቷንና አስተዋይነቷን እወድላታለሁ፤ ልጄ ትጉህ ናት " ሲሉ ገልጸዋል።
ዮርዳኖስ እስከ 12ኛ ክፍል በሞግዚት ድጋፍ የተማረች መሆኑን ጠቅሰው እንደምትችል መታየት አለበት ብዬ አራት ዓመት በዩኒቨርሲቲ አብሬያት ዘልቀናል ብለዋል፡፡
አትችልም የተባለች ልጅ ለዚህ በመብቃቷ ትልቅ ደስታ እንደተሰማቸው ጠቅሰው፤ የእርስዋ ብርታት እንደ ልጃቸው ቤት ለተዘጋባቸው ልጆች አርአያ የሚሆን መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
መኖሪያ ቤታቸው ከዮኒቨርሲቲው ራቅ ያለ በመሆኑ ጠዋት 12 ሰዓት ተነስተው ለአራት ዓመታት ልጃቸውን ወደ ትምህር ገበታዋ በዊልቸር በማመላለስ ለምረቃ ያበቁት እናት ዛሬ ደስታቸው እጥፍ ድርብ ሆኖ ታይተዋል።
Credit : EPA
@tikvahethiopia
" አራት ዓመት ልጄን በዊልቸር እያመላለስኩ አስተምሬ በማዕረግ አስመርቄያለሁ " - ወይዘሮ እህተ በቀለ
ወይዘሮ እህተ በቀለ ይባላሉ። ልጃቸው ዮርዳኖስ ወሮታው አካሏን በራሷ ማንቀሳቀስ የማያስችል ጉዳት አለባት።
ዮርዳኖስ በእናቷ ድጋፍ ዛሬ ትምህርቷን አጠናቃ ከአዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ ከሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል #በማዕረግ ተመርቃለች፡፡
እናት አህተ ፤ " አራት ዓመት ሙሉ ልጄን በዊልቸር እያመላለስኩ አስተምሬ አጠናቅቄያለሁ። አራት ዓመት ለእኔ እንደ አራት ቀን ነው። ምንም አልተሰማኝም ደስ ብሎኝ አልፏል" ብለዋል።
በአራት ዓመት የትምህርት ቆይታዋ የሚሰጣትን ትምህርት ክፍል ውስጥ አብረዋት ቁጭ ብለው እየጻፉላት እንዳስተማሯት እናት ለኢፕድ ተናግረዋል።
" ዮርዳኖስ የማንበብ ችሎታዋን እወድላታለሁ። ያነበበችውን አለመርሳቷንና አስተዋይነቷን እወድላታለሁ፤ ልጄ ትጉህ ናት " ሲሉ ገልጸዋል።
ዮርዳኖስ እስከ 12ኛ ክፍል በሞግዚት ድጋፍ የተማረች መሆኑን ጠቅሰው እንደምትችል መታየት አለበት ብዬ አራት ዓመት በዩኒቨርሲቲ አብሬያት ዘልቀናል ብለዋል፡፡
አትችልም የተባለች ልጅ ለዚህ በመብቃቷ ትልቅ ደስታ እንደተሰማቸው ጠቅሰው፤ የእርስዋ ብርታት እንደ ልጃቸው ቤት ለተዘጋባቸው ልጆች አርአያ የሚሆን መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
መኖሪያ ቤታቸው ከዮኒቨርሲቲው ራቅ ያለ በመሆኑ ጠዋት 12 ሰዓት ተነስተው ለአራት ዓመታት ልጃቸውን ወደ ትምህር ገበታዋ በዊልቸር በማመላለስ ለምረቃ ያበቁት እናት ዛሬ ደስታቸው እጥፍ ድርብ ሆኖ ታይተዋል።
Credit : EPA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመቄዶንያ መስራች አቶ ቢንያም በለጠ እና ለአርቲስት ደበበ እሸቱ ፤ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ለተወዳጇ ድምፃዊት እጅጋየሁ ሽባባው ( #ጂጂ ) የክብር ዶክትሬት ዲግሪ አበርክተዋል። አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ የመቄዶኒያ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ቢንያም በለጠ ላከናወኗቸው በጎ ስራዎች የክብር ዶክትሬት አበርክቶላቸዋል። በሰሩት ስራ በሰው ልጆች…
#AAU #DrBinyamBelete😢
ዛሬ ከአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት የተበረከተላቸው የሜቄዶንያ በጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ቢንያም በለጠ በመድረኩ ላይ ንግግር አድርገው ነበር።
ያደረጉት ንግግር እጅግ ስሜትን የሚነካ ስለነበር ተመራቂዎች እና ታዳሚያንን #እያለቀሱ ሲያዳምጡ ነበር።
አቶ ቢንያም በለጠ ምን አሉ ?
" ...ለእኔ ብዙ ትልቅ ቦታ አትስጡኝ ፤ እኔ የማልረባ ሰው ነኝ ፤ ቅድም ስለእኔ ስትገልፁ ከብዶኛል።
እውነቴን ነው እግዚአብሔር ይሰራል እሱን አልክድም ሜቄዶንያ ላይ ፤ ምክንያቱም ካለምንም እርዳታ ይሄን ሁሉ ሺህ ሰው በሀገር ውስጥ በየቀኑ አንድ ሚሊዮን የእግዚአብሔርን ስራ መሆኑ ግልፅ ነው በጣም።
እኔኮ በሽተኛ ነኝ ሲጀምር ብዙ ጊዜ ተኝቼ ነው የምውለው ፤ ስራ ያቆምኩ ሰው ነኝ እኔ እንደውም የህብረተሰብ ሸክም መሆን ያለብኝ ሰው ነኝ እውነት ለመናገር።
እንደ እኔ አይነት ሰው ዝም ብላችሁ ብታስቡት እንኳን እንደዚህ ለማድረግ ይቅርና እራሴንም ለመቻል ወይ አግብቶ ወልዶ ለመኖር ሰው ለመርዳት ቀርቶ ለመለመን እንኳን አንድ ሰው ጤነኛ መሆን አለበት ፤ ለመለመን ወጣ ብሎ አንድ ቦታ መቀመጥ አለበት እኔ መቀመጥም አልችልም።
ለመኖር እራሱ የማይገባኝ ሰው ነኝ ፤ በእግዚአብሔር ኃይል ነው ያለሁት ፤ እውነቴን ነው የምነግራችሁ ቀልዴን አይደለም። አንድ ሰው ለመለመን መንገድ ላይ ቁጭ ብሎ ሰው መጠየቅ አለበት አይደል እንደዛ እንኳን የምችል ሰው አይደለሁም። ስለዚህ እግዚአብሔር ነው የሚሰራው።
አንድ የህብረተሰብ ሸክም የሆነ ሰው ፤ እግዚአብሔር ምን ያህል ሃጥያተኛ ሰዎችን በመንፈስም በስጋም ደካማ የሆኑ ሰዎችን እንዴት መርዳት እንደሚችል አንዳንድ ሰዎች በቤተሰብ፣ በትዳር፣ ወይ ሰው አስቀይሟችሁ እንደው እግዚአብሔርን የለም ብላችሁ/ እግዚአብሔር ረሳኝ ብላችሁ ከሆነ እግዚአብሔር እንደዚህ ይሰራል። በማይረቡ ሰዎች፣ በተራ በጣም በወንጀለኛ ሰዎች መስራቱን ስታዩ ሁሉንም ሰው እግዚአብሔር እንደሚረዳ የሚያሳይ ነገር ነው።
ክብር ዶክትሬት ተብሏል ፤ እኔ ትንሽ ከብዶኛል በጣም ምክንያቱም እናተ ሸልማችሁኛል ፤ የእግዚአብሔር ፍርድ ደግሞ ከባድ ነው እውነት የእግዚአብሔር ፍርድ በጣም አስፈሪ ነውና ከሲኦል እንድድን እግዚአብሔር ከዚያ እንዲያወጣኝ ፀሎት አድርጉልኝ የእውነት። ይሄ በጣም ከባድ ነገር ስለሆነ ነው። ቀልድ አይደለም እግዚአብሔር ዝም ብለን ሃጥያት ስንሰራ ዝም የሚለን አምላክ አይደለም። የእግዚአብሔር ፍርድ ከባድ ነውና እኔ የምፈራው እሱን ነው እንኳን ልሸለም ለፍርድ እንዲቀልልኝ የማስብ ሰው ነኝ።
ሜቄዶንያ ላይ ብዙ ሰው አስተዋጽኦ ያደርጋል። እኔ የተለየ አስተዋጽኦ የለኝም ከዛ ያነሰ ነው የእኔ አስተዋፅኦ። በሽተኛ ስለሆንኩኝ ስራም ስለሌለኝ አንደኛው ተደጓሚ ነኝ እራሴ በመቄዶንያ ነገር ግን መቄዶንያ ባልፉት ዓመታት እዚህ ለመድረስ ብዙ አስተዋፅኦ ያደረጋችሁ ሰዎች አላችሁ ምስጋናም ክብርም የሚገባው ለእናተ ነው።
ተማሪዎች፣ ወጣቶች ፣በጎፍቃደኞች፣ የመንግሥት ኃላፊዎች፤ የሚኒስትር መስሪያ ቤቶች ፣ ሚኒስትሮች ፣ ኮሚሽነሮች፣ የመንግስት የልማት ድርጅቶች፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም ሜቄዶንያን አግዘዋል በየቢሮው ያስተናግዱናል፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የክልል መስተዳደሮች በሙሉ፣ ለሜቄዶንያ እዚህ መድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። "
(የክብር ዶክተር ቢንያም በለጠ ሙሉ ንግግር ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ዛሬ ከአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት የተበረከተላቸው የሜቄዶንያ በጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ቢንያም በለጠ በመድረኩ ላይ ንግግር አድርገው ነበር።
ያደረጉት ንግግር እጅግ ስሜትን የሚነካ ስለነበር ተመራቂዎች እና ታዳሚያንን #እያለቀሱ ሲያዳምጡ ነበር።
አቶ ቢንያም በለጠ ምን አሉ ?
" ...ለእኔ ብዙ ትልቅ ቦታ አትስጡኝ ፤ እኔ የማልረባ ሰው ነኝ ፤ ቅድም ስለእኔ ስትገልፁ ከብዶኛል።
እውነቴን ነው እግዚአብሔር ይሰራል እሱን አልክድም ሜቄዶንያ ላይ ፤ ምክንያቱም ካለምንም እርዳታ ይሄን ሁሉ ሺህ ሰው በሀገር ውስጥ በየቀኑ አንድ ሚሊዮን የእግዚአብሔርን ስራ መሆኑ ግልፅ ነው በጣም።
እኔኮ በሽተኛ ነኝ ሲጀምር ብዙ ጊዜ ተኝቼ ነው የምውለው ፤ ስራ ያቆምኩ ሰው ነኝ እኔ እንደውም የህብረተሰብ ሸክም መሆን ያለብኝ ሰው ነኝ እውነት ለመናገር።
እንደ እኔ አይነት ሰው ዝም ብላችሁ ብታስቡት እንኳን እንደዚህ ለማድረግ ይቅርና እራሴንም ለመቻል ወይ አግብቶ ወልዶ ለመኖር ሰው ለመርዳት ቀርቶ ለመለመን እንኳን አንድ ሰው ጤነኛ መሆን አለበት ፤ ለመለመን ወጣ ብሎ አንድ ቦታ መቀመጥ አለበት እኔ መቀመጥም አልችልም።
ለመኖር እራሱ የማይገባኝ ሰው ነኝ ፤ በእግዚአብሔር ኃይል ነው ያለሁት ፤ እውነቴን ነው የምነግራችሁ ቀልዴን አይደለም። አንድ ሰው ለመለመን መንገድ ላይ ቁጭ ብሎ ሰው መጠየቅ አለበት አይደል እንደዛ እንኳን የምችል ሰው አይደለሁም። ስለዚህ እግዚአብሔር ነው የሚሰራው።
አንድ የህብረተሰብ ሸክም የሆነ ሰው ፤ እግዚአብሔር ምን ያህል ሃጥያተኛ ሰዎችን በመንፈስም በስጋም ደካማ የሆኑ ሰዎችን እንዴት መርዳት እንደሚችል አንዳንድ ሰዎች በቤተሰብ፣ በትዳር፣ ወይ ሰው አስቀይሟችሁ እንደው እግዚአብሔርን የለም ብላችሁ/ እግዚአብሔር ረሳኝ ብላችሁ ከሆነ እግዚአብሔር እንደዚህ ይሰራል። በማይረቡ ሰዎች፣ በተራ በጣም በወንጀለኛ ሰዎች መስራቱን ስታዩ ሁሉንም ሰው እግዚአብሔር እንደሚረዳ የሚያሳይ ነገር ነው።
ክብር ዶክትሬት ተብሏል ፤ እኔ ትንሽ ከብዶኛል በጣም ምክንያቱም እናተ ሸልማችሁኛል ፤ የእግዚአብሔር ፍርድ ደግሞ ከባድ ነው እውነት የእግዚአብሔር ፍርድ በጣም አስፈሪ ነውና ከሲኦል እንድድን እግዚአብሔር ከዚያ እንዲያወጣኝ ፀሎት አድርጉልኝ የእውነት። ይሄ በጣም ከባድ ነገር ስለሆነ ነው። ቀልድ አይደለም እግዚአብሔር ዝም ብለን ሃጥያት ስንሰራ ዝም የሚለን አምላክ አይደለም። የእግዚአብሔር ፍርድ ከባድ ነውና እኔ የምፈራው እሱን ነው እንኳን ልሸለም ለፍርድ እንዲቀልልኝ የማስብ ሰው ነኝ።
ሜቄዶንያ ላይ ብዙ ሰው አስተዋጽኦ ያደርጋል። እኔ የተለየ አስተዋጽኦ የለኝም ከዛ ያነሰ ነው የእኔ አስተዋፅኦ። በሽተኛ ስለሆንኩኝ ስራም ስለሌለኝ አንደኛው ተደጓሚ ነኝ እራሴ በመቄዶንያ ነገር ግን መቄዶንያ ባልፉት ዓመታት እዚህ ለመድረስ ብዙ አስተዋፅኦ ያደረጋችሁ ሰዎች አላችሁ ምስጋናም ክብርም የሚገባው ለእናተ ነው።
ተማሪዎች፣ ወጣቶች ፣በጎፍቃደኞች፣ የመንግሥት ኃላፊዎች፤ የሚኒስትር መስሪያ ቤቶች ፣ ሚኒስትሮች ፣ ኮሚሽነሮች፣ የመንግስት የልማት ድርጅቶች፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም ሜቄዶንያን አግዘዋል በየቢሮው ያስተናግዱናል፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የክልል መስተዳደሮች በሙሉ፣ ለሜቄዶንያ እዚህ መድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። "
(የክብር ዶክተር ቢንያም በለጠ ሙሉ ንግግር ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia