በጦርነት የደቀቀችውን ከተማ ያበረታቱ !
የሰሜን ወሎዋ ወልድያ ከተማ በኢንቨስትመንቱ ዘርፉ በሯን ክፍት ማድረጓን አሳውቃል።
ከተማዋ ጥር 6 ቀን 2015 ዓ.ም የኢንቨስትመንት ፎረም ያዘጋጀች ሲሆን " ቢዝነስ ብሔር አልባ መሆኑን የተረዱ እና እራሳቸውን ብቻ ሳይሆን ሕዝብን ለመጥቅም ሁለተናዊ አቅሙና ክህሎቱ ያላቸውን ትክክለኛ ባለሀብቶች ጋብዛለች " ሲል የከተማው አስተዳደር ገልጿል።
የከተማው አስተዳደር ወልድያ " በ5 አገር አቋራጭ መንገዶች የምትማከል ዲዛይኑ በተሻሻለው ከጅቡቲ ወደብ፤ አዲስ አበባ እና ከመተማ ወረታ መስመር የሚገናኘው የባቡር መስመር ደረቅ ወደቧን ከጎና ያደረገች ለንግድ ማዕከልነት ምቹ እና ተማራጭ፤ ነዋሪዋቿ ብቻ ሳይሆኑ የዓየር ንብረቷም እንግዳ ተቀባይ፤ የበርካታ የቱሪዝም ቦታዎች መዳረሻ ፤ ዛሬም እንደጥንቱ ጠላትን በፍቅር ድል የሚነሱ አባቶች መፍለቂያና መገኛ " መሆኗን ገልጾ የሚመለከታቸው ሁሉ የኢንቨስትመንት ፎረሙን እንዲታደሙ ጥሪ አቅርቧል።
" የቢሮክራሲው በር ተሰብሮ፤ አቅም ላላቸው አረንጓዴ መብራት ፈንጥቆ እየጠበቀዎት ነውም " ብሏል።
በኢንቨስትመንት ፎረሙ ዜጎችን ሀብታቸውን ብቻ ሳይሆን ሀሳብ እውቀታቸውንና በጎ ልምዳቸውን ኢንቨስት በማድግ በጦርነት የደቀቀችው ከተማ እንዲያበረታቱ ይፋዊ ጥሪ ቀርቧል።
መረጃው ከወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
የሰሜን ወሎዋ ወልድያ ከተማ በኢንቨስትመንቱ ዘርፉ በሯን ክፍት ማድረጓን አሳውቃል።
ከተማዋ ጥር 6 ቀን 2015 ዓ.ም የኢንቨስትመንት ፎረም ያዘጋጀች ሲሆን " ቢዝነስ ብሔር አልባ መሆኑን የተረዱ እና እራሳቸውን ብቻ ሳይሆን ሕዝብን ለመጥቅም ሁለተናዊ አቅሙና ክህሎቱ ያላቸውን ትክክለኛ ባለሀብቶች ጋብዛለች " ሲል የከተማው አስተዳደር ገልጿል።
የከተማው አስተዳደር ወልድያ " በ5 አገር አቋራጭ መንገዶች የምትማከል ዲዛይኑ በተሻሻለው ከጅቡቲ ወደብ፤ አዲስ አበባ እና ከመተማ ወረታ መስመር የሚገናኘው የባቡር መስመር ደረቅ ወደቧን ከጎና ያደረገች ለንግድ ማዕከልነት ምቹ እና ተማራጭ፤ ነዋሪዋቿ ብቻ ሳይሆኑ የዓየር ንብረቷም እንግዳ ተቀባይ፤ የበርካታ የቱሪዝም ቦታዎች መዳረሻ ፤ ዛሬም እንደጥንቱ ጠላትን በፍቅር ድል የሚነሱ አባቶች መፍለቂያና መገኛ " መሆኗን ገልጾ የሚመለከታቸው ሁሉ የኢንቨስትመንት ፎረሙን እንዲታደሙ ጥሪ አቅርቧል።
" የቢሮክራሲው በር ተሰብሮ፤ አቅም ላላቸው አረንጓዴ መብራት ፈንጥቆ እየጠበቀዎት ነውም " ብሏል።
በኢንቨስትመንት ፎረሙ ዜጎችን ሀብታቸውን ብቻ ሳይሆን ሀሳብ እውቀታቸውንና በጎ ልምዳቸውን ኢንቨስት በማድግ በጦርነት የደቀቀችው ከተማ እንዲያበረታቱ ይፋዊ ጥሪ ቀርቧል።
መረጃው ከወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
የ16 ዓመት ታዳጊ አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በ8 አመት ከ5 ወር እስራት ተቀጣ።
በደሴ ከተማ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመዉ አባወራ በእስራት መቀጣቱ ተሰምቷል።
ተከሳሹ ሳሙኤል ሹሙ ይባላል በደሴ ከተማ ቧንቧ ዉሃ ክፍለ ከተማ በመገናኛ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት ነዉ፡፡
የ28 አመቱ ተከሳሽ አባወራ በቤቱ ዉስጥ በሠራተኝነት የቀጠራትን የ16 አመት ታዳጊ ህፃንን በማስፈራራት አስገድዶ መድፈሩን በደሴ ከተማ የ4ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ገልጿል።
ተከሳሹ ድርጊቱን የፈፀመዉ ባለቤቱ ወደስራ የምትሄድበትን ሠአት እና እቤት ዉስጥ ሠዉ የማይኖርበትን አጋጣሚ በመጠቀም ታዳጊዋን በማስፈራራትና አፍና አፍንጫዋን በማፈን በተለያየ ግዜ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት መቆየቱ ተገልጿል።
ታዳጊዋ ህፃን ከደፋሪዋ ቤት ከወጣች በሗላ የደረሰባትን ጥቃት ለቤተሠቦቹዋ በመናገሯ ለፖሊስ ጥቆማ በማድረጋቸዉ አስገድዶ ደፋሪዉ አባወራ በቁጥጥር ስር ዉሎ ምርመራ ሲጣራበት ቆይቷል።
ፖሊስ በሠዉና ሀኪም ማስረጃ መዝገቡን በማጠናከር ወደሚመለከተዉ የፍትህ አካል ልኳል፡፡
መዝገቡን የተመለከተዉ የደሴ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት በቅርቡ በዋለዉ ችሎት ጥፋተኝነቱን በማረጋገጡ ተከሳሽ ሳሙኤል ሹሙ በ8 አመት ከ5 ወር እስራት እንዲቀጣ የወሠነበት መሆኑን በደሴ ከተማ የ4ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ህዝብ ግንኙነት ክፍል ዘግቧል፡፡
@tikvahethiopia
በደሴ ከተማ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመዉ አባወራ በእስራት መቀጣቱ ተሰምቷል።
ተከሳሹ ሳሙኤል ሹሙ ይባላል በደሴ ከተማ ቧንቧ ዉሃ ክፍለ ከተማ በመገናኛ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት ነዉ፡፡
የ28 አመቱ ተከሳሽ አባወራ በቤቱ ዉስጥ በሠራተኝነት የቀጠራትን የ16 አመት ታዳጊ ህፃንን በማስፈራራት አስገድዶ መድፈሩን በደሴ ከተማ የ4ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ገልጿል።
ተከሳሹ ድርጊቱን የፈፀመዉ ባለቤቱ ወደስራ የምትሄድበትን ሠአት እና እቤት ዉስጥ ሠዉ የማይኖርበትን አጋጣሚ በመጠቀም ታዳጊዋን በማስፈራራትና አፍና አፍንጫዋን በማፈን በተለያየ ግዜ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት መቆየቱ ተገልጿል።
ታዳጊዋ ህፃን ከደፋሪዋ ቤት ከወጣች በሗላ የደረሰባትን ጥቃት ለቤተሠቦቹዋ በመናገሯ ለፖሊስ ጥቆማ በማድረጋቸዉ አስገድዶ ደፋሪዉ አባወራ በቁጥጥር ስር ዉሎ ምርመራ ሲጣራበት ቆይቷል።
ፖሊስ በሠዉና ሀኪም ማስረጃ መዝገቡን በማጠናከር ወደሚመለከተዉ የፍትህ አካል ልኳል፡፡
መዝገቡን የተመለከተዉ የደሴ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት በቅርቡ በዋለዉ ችሎት ጥፋተኝነቱን በማረጋገጡ ተከሳሽ ሳሙኤል ሹሙ በ8 አመት ከ5 ወር እስራት እንዲቀጣ የወሠነበት መሆኑን በደሴ ከተማ የ4ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ህዝብ ግንኙነት ክፍል ዘግቧል፡፡
@tikvahethiopia
#IstanbulAddis
18ኛው አለም አቀፍ የግብርና እና የቁም እንስሳት ኤግዚብሽን ከጥር 23 እስከ 28 በቱርክ ሀገር ኢዝሚር ከተማ ይካሄዳል ።
በኤግዚቢሽኑ ትራክተሮች፣፣የዶሮ እርባታ እና የንብ እርባታ ቴክኖሎጂዎች፣ ግንባታ ማሽነሪዎች እና መለዋወጫዎች፣ የእንስሳት እርባታ፣ የእፅዋት ምርት እና ማዳበሪያ ቴክኖሎጂዎች፣ እንዲሁም መሰል የግብርናው ዘርፍ ውጤቶች ለእይታ የሚቀርቡበት አለም አቀፍ ኤግዚብሽን ከኢስታንቡል አዲስ ።
• ለድርጅትዎ አዳዲስ ግንዛቤዎችን የሚያገኙበት እና ልምድ የሚቀስሙበት ታላቅ ኤግዚብሽን ላይ እንዲሳተፉ ኢስታንቡል አስጎብኚ እና የጉዞ ወኪል ቅድመ ዝግጂቱን ጨርሶ እየጋበዞት ይገኛል።
አድራሻ ቦሌ ዲ ኤች ገዳ ህንፃ 2ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 205
☎️ 0983568383/ 0944000006
18ኛው አለም አቀፍ የግብርና እና የቁም እንስሳት ኤግዚብሽን ከጥር 23 እስከ 28 በቱርክ ሀገር ኢዝሚር ከተማ ይካሄዳል ።
በኤግዚቢሽኑ ትራክተሮች፣፣የዶሮ እርባታ እና የንብ እርባታ ቴክኖሎጂዎች፣ ግንባታ ማሽነሪዎች እና መለዋወጫዎች፣ የእንስሳት እርባታ፣ የእፅዋት ምርት እና ማዳበሪያ ቴክኖሎጂዎች፣ እንዲሁም መሰል የግብርናው ዘርፍ ውጤቶች ለእይታ የሚቀርቡበት አለም አቀፍ ኤግዚብሽን ከኢስታንቡል አዲስ ።
• ለድርጅትዎ አዳዲስ ግንዛቤዎችን የሚያገኙበት እና ልምድ የሚቀስሙበት ታላቅ ኤግዚብሽን ላይ እንዲሳተፉ ኢስታንቡል አስጎብኚ እና የጉዞ ወኪል ቅድመ ዝግጂቱን ጨርሶ እየጋበዞት ይገኛል።
አድራሻ ቦሌ ዲ ኤች ገዳ ህንፃ 2ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 205
☎️ 0983568383/ 0944000006
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እንድታውቁት
በአዲስ አበባ ታግዶ የቆየው የነዋሪነት መታወቂያ #የጠፋባቸው ነዋሪዎች ምትክ አገልግሎት ከፊታችን ሰኞ ይጀምራል።
የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አገልግሎቱ ከሰኞ ታህሳስ 24 ጀምሮ ለመጀመር ዝግጅት እንዳጠናቀቀ አረጋግጧል።
ኤጀንሲው ፤ በቀድሞ አሰራር ፖሊስ ግለሰቦች በነዋሪነት የተመዝገቡ ነዋሪ መሆናቸው በተቋሙ ሳይረጋገጥ የጠፋ ሰነዶችን ማስረጃ ሲሰጥበት የነበረበት አሰራር ግለሰቦች በሃሰተኛ የእምነት ቃል የነዋሪነት መታወቂያ ሳይኖራቸው ማስረጃውን በማውጣት በተለያዩ ቦታዎች ማስረጃውን እየጠተቀሙ እያጭበረበሩ መሆኑን የፖሊስ ምርመራ በተለያዩ ግዝያት ማረጋገጡን ገልጿል።
አሁን ካለው ጥብቅ የነዋሪነት መታወቂያ አሰጣጥ ቁጥጥር ስርዓት አንፃር ማንኛውም የጠፋበት ምትክ ጠያቂ ነዋሪዎች ቀድሞ ነዋሪ መሆናቸውን ከሚኖሩበት የወረዳ ጽ/ቤቶች ማረጋገጫ ለፖሊስ ሲያቀረቡና ከፖሊስ የጠፋ ሰነድ #ማስረጃ_ሲሰጣቸው _ብቻ አገልግሎቱን እንደሚያገኙ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
ኤጀንሲው ፤ የጤና እክል ያለባቸው እንዲሁም ለአቅመ ደካሞች ልዩ ድጋፍ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ታግዶ የቆየው የነዋሪነት መታወቂያ #የጠፋባቸው ነዋሪዎች ምትክ አገልግሎት ከፊታችን ሰኞ ይጀምራል።
የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አገልግሎቱ ከሰኞ ታህሳስ 24 ጀምሮ ለመጀመር ዝግጅት እንዳጠናቀቀ አረጋግጧል።
ኤጀንሲው ፤ በቀድሞ አሰራር ፖሊስ ግለሰቦች በነዋሪነት የተመዝገቡ ነዋሪ መሆናቸው በተቋሙ ሳይረጋገጥ የጠፋ ሰነዶችን ማስረጃ ሲሰጥበት የነበረበት አሰራር ግለሰቦች በሃሰተኛ የእምነት ቃል የነዋሪነት መታወቂያ ሳይኖራቸው ማስረጃውን በማውጣት በተለያዩ ቦታዎች ማስረጃውን እየጠተቀሙ እያጭበረበሩ መሆኑን የፖሊስ ምርመራ በተለያዩ ግዝያት ማረጋገጡን ገልጿል።
አሁን ካለው ጥብቅ የነዋሪነት መታወቂያ አሰጣጥ ቁጥጥር ስርዓት አንፃር ማንኛውም የጠፋበት ምትክ ጠያቂ ነዋሪዎች ቀድሞ ነዋሪ መሆናቸውን ከሚኖሩበት የወረዳ ጽ/ቤቶች ማረጋገጫ ለፖሊስ ሲያቀረቡና ከፖሊስ የጠፋ ሰነድ #ማስረጃ_ሲሰጣቸው _ብቻ አገልግሎቱን እንደሚያገኙ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
ኤጀንሲው ፤ የጤና እክል ያለባቸው እንዲሁም ለአቅመ ደካሞች ልዩ ድጋፍ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#STEMPower #TikvahEthiopia
ስቴም ፖወር ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት ግቢ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ላለፉት 7 ቀናት ሲሰጥ የነበረው የወጣቶች የመጀመሪያ ደረጃ የአቅም ግንባታ ሥልጠና የምርቃትና የማበረታቻ መርሐግብር በትላንትናው ዕለት ተከናውኗል።
ሥልጠናውን ለመውሰድ 2,289 ወጣቶች የተመዘገቡ ሲሆን 578 ወጣቶች በስልጠናው ተካፍለዋል (ቢያንስ የስልጠናውን አንዱን ክፍል ወስደዋል።
ከሰልጣኞቹ 60% የሚሆኑት ወንዶች ሲሆኑ 40% የሚሆኑት ሴቶች ናቸው።
በዕለቱ ከ5 ቀናት በላይ የተሰጡ ስልጠናዎችን የተከታተሉ ሰልጣኞች ከስቴም ፖወርና ከቲክቫህ የተዘጋጀላቸውን ሰርተፊኬት የወሰዱ ሲሆን ሌሎች ሰልጣኞች ዲጂታል ሰርተፊኬት የሚደርሳቸው ይሆናል።
በመርሐግብሩ ላይ በስቴም ፖወር፣ ቪዛና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ትብብር በተሰጡ ስልጠናዎች አልፈው የራሳቸውን ድርጅት የመሰረቱትና በፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ላይ የተሰማሩት ውጆ አፕ (Wujo App) ለተመራቂዎች ሥራቸውን አስተዋውቀው አስመርቀዋል።
በቀጣይ ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ሥልጠናዎችን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
@tikvahethiopia
ስቴም ፖወር ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት ግቢ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ላለፉት 7 ቀናት ሲሰጥ የነበረው የወጣቶች የመጀመሪያ ደረጃ የአቅም ግንባታ ሥልጠና የምርቃትና የማበረታቻ መርሐግብር በትላንትናው ዕለት ተከናውኗል።
ሥልጠናውን ለመውሰድ 2,289 ወጣቶች የተመዘገቡ ሲሆን 578 ወጣቶች በስልጠናው ተካፍለዋል (ቢያንስ የስልጠናውን አንዱን ክፍል ወስደዋል።
ከሰልጣኞቹ 60% የሚሆኑት ወንዶች ሲሆኑ 40% የሚሆኑት ሴቶች ናቸው።
በዕለቱ ከ5 ቀናት በላይ የተሰጡ ስልጠናዎችን የተከታተሉ ሰልጣኞች ከስቴም ፖወርና ከቲክቫህ የተዘጋጀላቸውን ሰርተፊኬት የወሰዱ ሲሆን ሌሎች ሰልጣኞች ዲጂታል ሰርተፊኬት የሚደርሳቸው ይሆናል።
በመርሐግብሩ ላይ በስቴም ፖወር፣ ቪዛና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ትብብር በተሰጡ ስልጠናዎች አልፈው የራሳቸውን ድርጅት የመሰረቱትና በፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ላይ የተሰማሩት ውጆ አፕ (Wujo App) ለተመራቂዎች ሥራቸውን አስተዋውቀው አስመርቀዋል።
በቀጣይ ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ሥልጠናዎችን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
@tikvahethiopia
January 1,2023
የግሪጎሪያን ቀን አቆጣጠርን የሚከተሉት እጅግ በርካታ የዓለማችን ሀገራት አዲሱን 2023 ዓመት ተቀብለዋል።
አዲሱን ዓመት 2023 ከተቀበሉ ሀገራት መካከል ጎረቤት ሀገር ኬንያ ፣ ግብፅ፣ ፈረንሳይ፣ አሜሪካ፣ ዩናይትድ ኪንግደም ፣ ህንድ ፣ ፓኪስታን ፣ አይቮሪ ኮስት እጅግ በጥቂቱ ይጠቀሳሉ።
ከዓለማችን ሀገራት መካከል የራሷ የሆነ የዘመን አቆጣጠር ያላት #ኢትዮጵያ በግንባር ቀደምትነት የምትነሳ ሲሆን ሀገራችን የአውሮፓውያን ቀን አቆጣጠርን አትጠቀምም።
የ13 ወራት ፀጋ ባለቤቷ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት የዘመን አቆጣጠሯ መለየቱ ብቻ ሳይሆን የራሷ የሆኑ ባህሎች፣ ቋንቋዎች ፣ ፊደል፣ ጥበብ ያለባት ሀገር ናት።
@tikvahethiopia
የግሪጎሪያን ቀን አቆጣጠርን የሚከተሉት እጅግ በርካታ የዓለማችን ሀገራት አዲሱን 2023 ዓመት ተቀብለዋል።
አዲሱን ዓመት 2023 ከተቀበሉ ሀገራት መካከል ጎረቤት ሀገር ኬንያ ፣ ግብፅ፣ ፈረንሳይ፣ አሜሪካ፣ ዩናይትድ ኪንግደም ፣ ህንድ ፣ ፓኪስታን ፣ አይቮሪ ኮስት እጅግ በጥቂቱ ይጠቀሳሉ።
ከዓለማችን ሀገራት መካከል የራሷ የሆነ የዘመን አቆጣጠር ያላት #ኢትዮጵያ በግንባር ቀደምትነት የምትነሳ ሲሆን ሀገራችን የአውሮፓውያን ቀን አቆጣጠርን አትጠቀምም።
የ13 ወራት ፀጋ ባለቤቷ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት የዘመን አቆጣጠሯ መለየቱ ብቻ ሳይሆን የራሷ የሆኑ ባህሎች፣ ቋንቋዎች ፣ ፊደል፣ ጥበብ ያለባት ሀገር ናት።
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA
ከሰሞኑን የፌዴራሉ መንግስት የ #ሰላም_ስምምነቱን በተመለከተ ከ50 በላይ ለማሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማብራሪያ ሰጥቶ ነበር።
ማብራሪያውን ከሰጡት መካከል የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ሬድዋን ሁሴን (አምባሳደር) ነበሩ።
በወቅቱ ፤ የመድረኩ ተሳታፊ የነበሩት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጠንከር ያሉ ጥያቄዎችን አቅርበው ነበር።
ምን ተጠየቀ ? ምንስ ምላሽ ተሰጠ ?
- ስለወልቃይት ባለቤትነት፣
- ስለኤርትራ ወታደሮች፣
- ስለሰላም ስምምነቱ ግልጽነትና የመረጃ አሰጣጥ፣
- ስለሰላም ስምምነቱ ተደራዳሪዎች ጥያቄዎች ቀርበው ነበር።
የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ (የኢሶዴፓ) ምክትል ፕሬዚዳንት ራሔል ባፌ (ዶ/ር) ፦
" ከወልቃይት ጋር እየተነሳ ያለው ጉዳይ፣ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ በአንድ በኩል የባህር በር ስታጣ በሌላ በኩል ደግሞ ወልቃይትን በመቀማት አገሪቱ ከሌላ አገር ጋር እንዳትገናኝ ለመዝጋት የተደረገ እንቅስቃሴ በመሆኑ መንግሥት ጉዳዩን እንዴት እየተከታተለው ነው ? "
የኢዜማ ተወካይ ጫኔ ከበደ (ዶ/ር) ፦
" በሰላም ስምምነቱ ትግራይ ክልል ከአማራና ከአፋር ክልሎች ጋር በሚዋሰንባቸው አካባቢዎች የሚነሱ ጉዳዮችን በተመለከተ ስምምነቱ ምን ይላል ? በዚህ የተዳፈነ እሳት ላይ የታሰበ ነገር ካለ ቢነገረን ? "
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) አመራር አባል አቶ ሙላቱ ገመቹ ፦
" የኤርትራ ሠራዊት ከትግራይ ክልል አልፎ በቤኒሻንጉል ጉሙዝና በኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ነው። መንግሥት ለምን ዝምታን መረጠ ? "
የእናት ፓርቲ ፕሬዚዳንት ሰይፈ ሥላሴ አያሌው (ዶ/ር) ፦
" የሰላም ስምምነት ለአገር ተሰፋ የፈነጠቀ ቢሆንም፣ ድርድሩ ሲካሄድ የተሳተፉ የብልፅግና እና የሕወሓት ሰዎች ብቻ መሆናቸው ቅሬታ ፈጥሮብናል።
በጦርነቱ ውስጥ ዋነኛ ሰለባና ገፈት ቀማሽ የነበሩት የአማራና የአፋር ክልሎች ሕዝቦች ለምን እንዲሳተፉ አልተደረገም ?
በተጨማሪም እየተከናወኑ ያሉ ውይይቶችና ድርድሮች ለሕዝብ እየተነገሩ አይደለም።
ሲዋጋ፣ ሲሞትና ሲቆስል የነበረው ሕዝብ በመጨረሻ ስለተደረሰበት ስምምነት መንግሥት መረጃ ሊሰጠው የገባል።
ከአራት ዓመት በፊት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከነበረበት ኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ እንዲገባ ሲደረግ መንግሥት ፈጸምኳቸው ያላቸውን ስምምነቶች በርካታ ቢሆኑም፣ ለሕዝብ ግልጽ ሳይደረጉ አሁን የሚታየው ጥፋት ተከስቷል። "
የጠ/ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ምን ምላሽ ሰጡ ?
አምባደር ሬድዋን ሁሴን ፦
ወልቃይት ...
" የወልቃይት ጉዳይ በ #ሕገ_መንግሥቱ መሠረት ይፈታል።
ከጅምሩ የጦርነቱ ዓላማ ወልቃይትን ማስመለስ እና ሕወሓትን ማጥፋት አልነበረም።
የጦርነቱ ዋና ዓላማ የነበረው የአገሪቱን ሉዓላዊነት ማስከበርና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ማስፈን ነው
ሕወሓትን እንደ ፖለቲካ ኃይል የማጥፋት ዓላማ ያለው ሰው ይኖራል፣ ነገር ግን የፌዴራል መንግሥቱ ዓላማ አይደለም።
ወልቃይት በአማራ እና በትግራይ ክልሎች መካከል ያለ ፀብ ነው፣ በሁለት ክልሎች መካከል ያለው ፀብ ደግሞ የሚፈታው የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሚመራው ሥርዓት።
የፌዴራል መንግሥት አቋም ተራ በተራ ጡንቻ እየተፈታተን አንዳችን ሌላችንን ማንበርከክ ይቁም የሚል ነው።
ወልቃይትን ከዚህ ቀደም ሕወሓት ጡንቻ ስለነበረው በጉልበት ወስዷል፣ አሁን ደግሞ ሕወሓት ሸብረክ ሲል ጡንቻ ያለው አካል ይውሰድ ካልን መጪው ትውልድ 20 ዓመታትን ጠብቆ ድንገት ጡንቻ ካገኘ ይወስደዋል ፤ ስለዚህም ዘላቂው መፍትሔ ጡንቻ ሳይሆን ሕግና ሥርዓት ነው።
አንድ ሰው ትግራይን ሲወድ ካርታውን ብቻ ሳይሆን ሕዝቡን ነው፣ ነገር ግን ካርታውን ወዶ ሕዝቡን መጥላት አይቻልም።
ቲፎዞና ደም መርጠን መለቃቀስ ይቅር፣ የትም ቦታ ሰው ሲሞት ሁላችንም ሊሰማን ይገባል። "
ኤትራን በተመለከተ ...
" የእኛ ወገን ናቸው የምንላቸው የሕወሓት ሰዎች ለ30 ዓመታት ታገልኩለት ያሉትን ሕዝብ ለ30 ዓመታት እየቀለበ፣ እየጠበቀ፣ አብሮ እየሠራና እያረሰ የኖረውን ሠራዊት ከጀርባው አርደው ሜዳ ላይ ሲጥሉት የታደጉት እነዚህ ሰዎች ናቸው፡፡ ለአጭር ጊዜም ቢሆን ውለታን መርሳት ነውር ነው።
በሦስተኛው ዙር አገሪቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለማፍረስ በተካሄደው ጦርነት የፌዴራል መንግሥት በቆቦ በኩል ባለው ዳገት ወደ ላይ መውጣት ላዳገተው፣ ሕወሓት ያለውን መልክዓ ምድራዊ ጠቀሜታ ተጠቅሞ ቆቦን ተቆጣጥሮ ነበር።
ወቅቱ ክረምት ስለነበር በምዕራብ በኩል ተከዜን ሠራዊቱ ማቋረጥ ባለመቻሉ ፣ #በዛላምበሳ እና #በአዲግራት ለመምጣት ተከዜን መሻገር የኤርትራ መንግሥት በመፍቀዱ ጦርነቱ ሊቀለበስ ችሏል።
ለአጭር ጊዜም ቢሆን በራቸውን ባይፈቅዱልን ኖሮ ይኼንን ጦርነት መቀልበስ አይቻልም ነበር፡፡ እንደ አገር ከባድ ፈተና ውስጥ እንወድቅ ነበር።
የኤርትራ መንግሥት ይኼን ያደረገው ሕወሓት በዚያ ጊዜ የጋራ ጠላታችን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ሕወሓት የጋራ ጠላት የሚሆነው ትጥቁን እስኪፈታ ነው። ትጥቁ ከሌለ አደጋ አይሆንም።
በፖለቲካ መጠላላት እና መለያየት ሲኖር ያለ ሦስተኛ ወገን በራችንን ዘግተን መነጋገር እንችላለን። "
የኤርትራ ሰራዊት ጉዳይ ...
" ' የኤርትራ ሠራዊት ከኢትዮጵያ ይውጣ ' የሚሉት አካላት ለኢትዮጵያ አዝነው አይደለም። ኤርትራ ይውጣ የሚሉ አካላት ሱዳን 50 ኪሎ ሜትር አልፎ ድንበር ወሮ በነበረበት ወቅት አፋቸውን ዘግተው ነበር።
በተመሳሳይ #ግብፅ በሚሊዮን በሚቆጠር ገንዘብ መድባ ወደ ኢትዮጵያ መሣሪያ እያስገባች በጋምቤላ ለኦነግ ሸኔና ለሕወሓት ጭምር በአየር እና መሬት ላይ ስታስታጥቅ፣ እነዚህ ምንም አላሉም ፤ ይህ የሚያሳየው መንግሥትን የሚያዳክም ሲሆን ዝምታ፣ መንግሥትን የሚያግዝ ሲሆን ደግሞ ጩኸት ማብዛት የሚወዱ በመኖራቸው ነው።
በመሆኑም ኤርትራ እኛን አስቸገረን ካላልን ምን አሳሰባቸው ? ኤርትራ ባስቸገረን ጊዜ እኛ ራሳችን በቃን እንላለን፡፡
የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ካሳሰባችሁ ሱዳን ትውጣ ብላችሁ መግለጫ አውጡ፡፡ ከዚያ ኤርትራ ትውጣ ብትሉ እኛ መረዳት እችላለን።
በሌላ በኩል በእኛ አስታኮ የኤርትራ መንግሥትን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም፡፡ ቢያንስ ከተፈጠረው የሰላም ስምምነት አንፃር እኛ እንዳንፈርስ አግዘውናል፡፡
የጋራ ጠላት የነበረን ቢሆንም ትጥቁን የፈታ የሕወሓት ታጣቂ ግን ኢትዮጵያዊ ነው። ስለዚህ አቅማችን ባለበት እስኪጠናከር ሕወሓት መጀመሪያ ትጥቁን መፍታት ይጀምርና እንደማንወጋ ስናረጋግጥ፣ ከጀርባችን ያለው አካል ማንም ይሁን ማን ይውጣልን ማለት እንችላለን። "
ምንጭ፦ www.ethiopiareporter.com
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን የፌዴራሉ መንግስት የ #ሰላም_ስምምነቱን በተመለከተ ከ50 በላይ ለማሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማብራሪያ ሰጥቶ ነበር።
ማብራሪያውን ከሰጡት መካከል የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ሬድዋን ሁሴን (አምባሳደር) ነበሩ።
በወቅቱ ፤ የመድረኩ ተሳታፊ የነበሩት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጠንከር ያሉ ጥያቄዎችን አቅርበው ነበር።
ምን ተጠየቀ ? ምንስ ምላሽ ተሰጠ ?
- ስለወልቃይት ባለቤትነት፣
- ስለኤርትራ ወታደሮች፣
- ስለሰላም ስምምነቱ ግልጽነትና የመረጃ አሰጣጥ፣
- ስለሰላም ስምምነቱ ተደራዳሪዎች ጥያቄዎች ቀርበው ነበር።
የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ (የኢሶዴፓ) ምክትል ፕሬዚዳንት ራሔል ባፌ (ዶ/ር) ፦
" ከወልቃይት ጋር እየተነሳ ያለው ጉዳይ፣ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ በአንድ በኩል የባህር በር ስታጣ በሌላ በኩል ደግሞ ወልቃይትን በመቀማት አገሪቱ ከሌላ አገር ጋር እንዳትገናኝ ለመዝጋት የተደረገ እንቅስቃሴ በመሆኑ መንግሥት ጉዳዩን እንዴት እየተከታተለው ነው ? "
የኢዜማ ተወካይ ጫኔ ከበደ (ዶ/ር) ፦
" በሰላም ስምምነቱ ትግራይ ክልል ከአማራና ከአፋር ክልሎች ጋር በሚዋሰንባቸው አካባቢዎች የሚነሱ ጉዳዮችን በተመለከተ ስምምነቱ ምን ይላል ? በዚህ የተዳፈነ እሳት ላይ የታሰበ ነገር ካለ ቢነገረን ? "
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) አመራር አባል አቶ ሙላቱ ገመቹ ፦
" የኤርትራ ሠራዊት ከትግራይ ክልል አልፎ በቤኒሻንጉል ጉሙዝና በኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ነው። መንግሥት ለምን ዝምታን መረጠ ? "
የእናት ፓርቲ ፕሬዚዳንት ሰይፈ ሥላሴ አያሌው (ዶ/ር) ፦
" የሰላም ስምምነት ለአገር ተሰፋ የፈነጠቀ ቢሆንም፣ ድርድሩ ሲካሄድ የተሳተፉ የብልፅግና እና የሕወሓት ሰዎች ብቻ መሆናቸው ቅሬታ ፈጥሮብናል።
በጦርነቱ ውስጥ ዋነኛ ሰለባና ገፈት ቀማሽ የነበሩት የአማራና የአፋር ክልሎች ሕዝቦች ለምን እንዲሳተፉ አልተደረገም ?
በተጨማሪም እየተከናወኑ ያሉ ውይይቶችና ድርድሮች ለሕዝብ እየተነገሩ አይደለም።
ሲዋጋ፣ ሲሞትና ሲቆስል የነበረው ሕዝብ በመጨረሻ ስለተደረሰበት ስምምነት መንግሥት መረጃ ሊሰጠው የገባል።
ከአራት ዓመት በፊት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከነበረበት ኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ እንዲገባ ሲደረግ መንግሥት ፈጸምኳቸው ያላቸውን ስምምነቶች በርካታ ቢሆኑም፣ ለሕዝብ ግልጽ ሳይደረጉ አሁን የሚታየው ጥፋት ተከስቷል። "
የጠ/ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ምን ምላሽ ሰጡ ?
አምባደር ሬድዋን ሁሴን ፦
ወልቃይት ...
" የወልቃይት ጉዳይ በ #ሕገ_መንግሥቱ መሠረት ይፈታል።
ከጅምሩ የጦርነቱ ዓላማ ወልቃይትን ማስመለስ እና ሕወሓትን ማጥፋት አልነበረም።
የጦርነቱ ዋና ዓላማ የነበረው የአገሪቱን ሉዓላዊነት ማስከበርና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ማስፈን ነው
ሕወሓትን እንደ ፖለቲካ ኃይል የማጥፋት ዓላማ ያለው ሰው ይኖራል፣ ነገር ግን የፌዴራል መንግሥቱ ዓላማ አይደለም።
ወልቃይት በአማራ እና በትግራይ ክልሎች መካከል ያለ ፀብ ነው፣ በሁለት ክልሎች መካከል ያለው ፀብ ደግሞ የሚፈታው የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሚመራው ሥርዓት።
የፌዴራል መንግሥት አቋም ተራ በተራ ጡንቻ እየተፈታተን አንዳችን ሌላችንን ማንበርከክ ይቁም የሚል ነው።
ወልቃይትን ከዚህ ቀደም ሕወሓት ጡንቻ ስለነበረው በጉልበት ወስዷል፣ አሁን ደግሞ ሕወሓት ሸብረክ ሲል ጡንቻ ያለው አካል ይውሰድ ካልን መጪው ትውልድ 20 ዓመታትን ጠብቆ ድንገት ጡንቻ ካገኘ ይወስደዋል ፤ ስለዚህም ዘላቂው መፍትሔ ጡንቻ ሳይሆን ሕግና ሥርዓት ነው።
አንድ ሰው ትግራይን ሲወድ ካርታውን ብቻ ሳይሆን ሕዝቡን ነው፣ ነገር ግን ካርታውን ወዶ ሕዝቡን መጥላት አይቻልም።
ቲፎዞና ደም መርጠን መለቃቀስ ይቅር፣ የትም ቦታ ሰው ሲሞት ሁላችንም ሊሰማን ይገባል። "
ኤትራን በተመለከተ ...
" የእኛ ወገን ናቸው የምንላቸው የሕወሓት ሰዎች ለ30 ዓመታት ታገልኩለት ያሉትን ሕዝብ ለ30 ዓመታት እየቀለበ፣ እየጠበቀ፣ አብሮ እየሠራና እያረሰ የኖረውን ሠራዊት ከጀርባው አርደው ሜዳ ላይ ሲጥሉት የታደጉት እነዚህ ሰዎች ናቸው፡፡ ለአጭር ጊዜም ቢሆን ውለታን መርሳት ነውር ነው።
በሦስተኛው ዙር አገሪቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለማፍረስ በተካሄደው ጦርነት የፌዴራል መንግሥት በቆቦ በኩል ባለው ዳገት ወደ ላይ መውጣት ላዳገተው፣ ሕወሓት ያለውን መልክዓ ምድራዊ ጠቀሜታ ተጠቅሞ ቆቦን ተቆጣጥሮ ነበር።
ወቅቱ ክረምት ስለነበር በምዕራብ በኩል ተከዜን ሠራዊቱ ማቋረጥ ባለመቻሉ ፣ #በዛላምበሳ እና #በአዲግራት ለመምጣት ተከዜን መሻገር የኤርትራ መንግሥት በመፍቀዱ ጦርነቱ ሊቀለበስ ችሏል።
ለአጭር ጊዜም ቢሆን በራቸውን ባይፈቅዱልን ኖሮ ይኼንን ጦርነት መቀልበስ አይቻልም ነበር፡፡ እንደ አገር ከባድ ፈተና ውስጥ እንወድቅ ነበር።
የኤርትራ መንግሥት ይኼን ያደረገው ሕወሓት በዚያ ጊዜ የጋራ ጠላታችን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ሕወሓት የጋራ ጠላት የሚሆነው ትጥቁን እስኪፈታ ነው። ትጥቁ ከሌለ አደጋ አይሆንም።
በፖለቲካ መጠላላት እና መለያየት ሲኖር ያለ ሦስተኛ ወገን በራችንን ዘግተን መነጋገር እንችላለን። "
የኤርትራ ሰራዊት ጉዳይ ...
" ' የኤርትራ ሠራዊት ከኢትዮጵያ ይውጣ ' የሚሉት አካላት ለኢትዮጵያ አዝነው አይደለም። ኤርትራ ይውጣ የሚሉ አካላት ሱዳን 50 ኪሎ ሜትር አልፎ ድንበር ወሮ በነበረበት ወቅት አፋቸውን ዘግተው ነበር።
በተመሳሳይ #ግብፅ በሚሊዮን በሚቆጠር ገንዘብ መድባ ወደ ኢትዮጵያ መሣሪያ እያስገባች በጋምቤላ ለኦነግ ሸኔና ለሕወሓት ጭምር በአየር እና መሬት ላይ ስታስታጥቅ፣ እነዚህ ምንም አላሉም ፤ ይህ የሚያሳየው መንግሥትን የሚያዳክም ሲሆን ዝምታ፣ መንግሥትን የሚያግዝ ሲሆን ደግሞ ጩኸት ማብዛት የሚወዱ በመኖራቸው ነው።
በመሆኑም ኤርትራ እኛን አስቸገረን ካላልን ምን አሳሰባቸው ? ኤርትራ ባስቸገረን ጊዜ እኛ ራሳችን በቃን እንላለን፡፡
የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ካሳሰባችሁ ሱዳን ትውጣ ብላችሁ መግለጫ አውጡ፡፡ ከዚያ ኤርትራ ትውጣ ብትሉ እኛ መረዳት እችላለን።
በሌላ በኩል በእኛ አስታኮ የኤርትራ መንግሥትን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም፡፡ ቢያንስ ከተፈጠረው የሰላም ስምምነት አንፃር እኛ እንዳንፈርስ አግዘውናል፡፡
የጋራ ጠላት የነበረን ቢሆንም ትጥቁን የፈታ የሕወሓት ታጣቂ ግን ኢትዮጵያዊ ነው። ስለዚህ አቅማችን ባለበት እስኪጠናከር ሕወሓት መጀመሪያ ትጥቁን መፍታት ይጀምርና እንደማንወጋ ስናረጋግጥ፣ ከጀርባችን ያለው አካል ማንም ይሁን ማን ይውጣልን ማለት እንችላለን። "
ምንጭ፦ www.ethiopiareporter.com
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የጤና ሚኒስቴር፤ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምላሽና ለመደበኛ አገልግሎት #በኮንትራት ተቀጥረው የነበሩ የጤና ባለሙያዎችን በተመከለተ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ከመግለጫው የተወሰደ፦ " የባለሙያዎቹ ኮንትራት ለ6 ዙር (በአጠቃላይ ለሶስት አመት) በየ6 ወሩ በተደጋጋሚ እየታደሰ እንዲሰሩ የተደረገ ሲሆን ካለዉ የሀብት ዉስንነትና የወረርሽኙ ትርጉም ባለዉ ደረጃ መቀነስ ጋር ተያይዞ በዚህ ወረርሽኝ…
የኢትዮጵያ ጤና ባለሞያዎች ማህበር የኮቪድ-19 ኮንትራት ተቀጣሪዎችን በተመለከተ ካወጣው መግለጫ ፦
" በቅርቡ ጤና ሚኒስቴር በኮቪድ 19 የኮንትራት ተቀጣሪዎች ላይ የወሰደዉ አላግባብ ከስራ የማሰናበት እርምጃ ሃላፊነት የጎደለዉ ተግባር መሆኑን ማህበሩ ያምናል።
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ አለምን በአስጨነቀበት በዛ ወቅት ለአንድ ህይወታቸዉ ሳይሳሱ ፣ እጅግ አስቸጋሪዉን የስራ ሁኔታ ተቋቁመዉ ወረርሽኙን ግንባር ቀደም ሁነዉ የተፋለሙ ጤና ባለሙያዎች የጀግና ሽልማት መሸለም ሲገባቸዉ ሃላፊነት በጎደለዉ መልኩ ከስራ ገበታቸዉ መባረራቸዉን የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማህበር በፅኑ ይቃወማል።
ድርጊቱ በድጋሚ ታይቶ የእርምት እርምጃ እንዲሰጠዉ የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማህበር ይጠይቃል።
ሚኒስቴር መስርያ ቤቱ የኮቪድ 19 የሶስት አመት ያህል የኮንትራት ተቀጣሪዎችን በሚመለከት የሰጠዉ መግለጫም የጤና ባለሙያዎችን አሁናዊ ሁኔታ ያላገናዘበና ጤና ባለሙያዎችን በበላይነት ከሚያስተዳድር ተቋም የማይጠበቅ ተግባር ነው። "
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
" በቅርቡ ጤና ሚኒስቴር በኮቪድ 19 የኮንትራት ተቀጣሪዎች ላይ የወሰደዉ አላግባብ ከስራ የማሰናበት እርምጃ ሃላፊነት የጎደለዉ ተግባር መሆኑን ማህበሩ ያምናል።
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ አለምን በአስጨነቀበት በዛ ወቅት ለአንድ ህይወታቸዉ ሳይሳሱ ፣ እጅግ አስቸጋሪዉን የስራ ሁኔታ ተቋቁመዉ ወረርሽኙን ግንባር ቀደም ሁነዉ የተፋለሙ ጤና ባለሙያዎች የጀግና ሽልማት መሸለም ሲገባቸዉ ሃላፊነት በጎደለዉ መልኩ ከስራ ገበታቸዉ መባረራቸዉን የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማህበር በፅኑ ይቃወማል።
ድርጊቱ በድጋሚ ታይቶ የእርምት እርምጃ እንዲሰጠዉ የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማህበር ይጠይቃል።
ሚኒስቴር መስርያ ቤቱ የኮቪድ 19 የሶስት አመት ያህል የኮንትራት ተቀጣሪዎችን በሚመለከት የሰጠዉ መግለጫም የጤና ባለሙያዎችን አሁናዊ ሁኔታ ያላገናዘበና ጤና ባለሙያዎችን በበላይነት ከሚያስተዳድር ተቋም የማይጠበቅ ተግባር ነው። "
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
በተጋጋሚ የታረመው /edit/ የተደረገው የመንግስት ሰራተኛው ህልፈተ ህይወት !
የአብክመ መሬት ቢሮ ባልደረባ የሆነ ወጣት ባየ በዛ ትናንት ምሸት ታህሳስ 22/2015 ባህር ዳር ውስጥ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የሰራተኛውን ህልፈት በተመለከተ ግን የሚሰራበት ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ያሰራጨው መረጃ አወዛጋቢ ሆኖ ተገኝቷል።
ቢሮው በቅድሚያ ባልደረባው " ባልታወቀ ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " ብሎ የገለፀ ሲሆን በኃላ ቆየት ብሎ " ባልታወቁ አካላት ጥቃት በደረሰበት ጥቃት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " ሲል አስተካክሏል።
ቆየት ብሎ ቢሮው ባልደረባው "በደረሰበት የትራፊክ አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " ብሏል። ከዚህ ማስተካከያ በኃላም " የትራፊክ አድራሹ መሰወሩን ተሽከርካሪው በቁጥጥር ስር ውሎ ባህር ዳር 9ኛ ፖሊስ ጣቢያ ምርመራ እየተካሄደ ነው ብሏል።
በ45 ደቂቃዎች በፊት ደግሞ በአስተያት መስጫው ላይ ቢሮው ባልደረባው በትራፊክ አደጋ መሞቱን አረጋግጣለሁ ሲል ፅፏል።
በመጨረሻም ቢሮው መረጃውን ከገፁ ላይ ሙሉ በሙሉ አጥፍቶታል።
እንዴት አንድ ተቋም የራሱ የባልደረባውን ህልፈት በተመለከት አጠራጣሪ እና ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ለህዝብ ያሰራጫል ?
@tikvahethiopia
የአብክመ መሬት ቢሮ ባልደረባ የሆነ ወጣት ባየ በዛ ትናንት ምሸት ታህሳስ 22/2015 ባህር ዳር ውስጥ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የሰራተኛውን ህልፈት በተመለከተ ግን የሚሰራበት ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ያሰራጨው መረጃ አወዛጋቢ ሆኖ ተገኝቷል።
ቢሮው በቅድሚያ ባልደረባው " ባልታወቀ ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " ብሎ የገለፀ ሲሆን በኃላ ቆየት ብሎ " ባልታወቁ አካላት ጥቃት በደረሰበት ጥቃት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " ሲል አስተካክሏል።
ቆየት ብሎ ቢሮው ባልደረባው "በደረሰበት የትራፊክ አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " ብሏል። ከዚህ ማስተካከያ በኃላም " የትራፊክ አድራሹ መሰወሩን ተሽከርካሪው በቁጥጥር ስር ውሎ ባህር ዳር 9ኛ ፖሊስ ጣቢያ ምርመራ እየተካሄደ ነው ብሏል።
በ45 ደቂቃዎች በፊት ደግሞ በአስተያት መስጫው ላይ ቢሮው ባልደረባው በትራፊክ አደጋ መሞቱን አረጋግጣለሁ ሲል ፅፏል።
በመጨረሻም ቢሮው መረጃውን ከገፁ ላይ ሙሉ በሙሉ አጥፍቶታል።
እንዴት አንድ ተቋም የራሱ የባልደረባውን ህልፈት በተመለከት አጠራጣሪ እና ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ለህዝብ ያሰራጫል ?
@tikvahethiopia