" ከ3 ሳምንት ያላነሰ ጊዜ የሚፈልገውን ሥራ በአንድ ሳምንት ነው ያጠናቀቁት " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ጉዳት ደርሶበት የነበረው የወልዲያ አላማጣ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል።
ያለዕረፍት በተሰራ ሥራ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና እና የተሰበሩ ኢንሱሌተሮች ቅየራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ መስመሩን መፈተሽ እንደተገጀመረ ነው የተገለፀው።
በአንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የደረሰ ጉዳት በቀጣይ የሚጠገን ሲሆን የምሰሶው ጉዳት ግን መስመሩን ኃይል ከመስጠት የሚያግደው አይደለም ተብሏል።
በጥገና ሥራው ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎች ከሦስት ሳምንት ያላነሰ ጊዜ የሚፈልገውን ሥራ በአንድ ሳምንት እንዳጠናቀቁት ነው የተነገረው።
ከወልዲያ እስከ አላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ ያለው መስመር ጥገና መጠናቀቅ ከአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ በ66 ኪሎ ቮልት ኃይል ሲያገኙ የነበሩት ፦
- ላሊበላ፣
- ሰቆጣ
- ቆቦ እንዲሁም ማይጨው እና አካባቢያቸው ኃይል እንዲያገኙ ያስችላል።
መረጅው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ነው።
@tikvahethiopia
በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ጉዳት ደርሶበት የነበረው የወልዲያ አላማጣ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል።
ያለዕረፍት በተሰራ ሥራ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና እና የተሰበሩ ኢንሱሌተሮች ቅየራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ መስመሩን መፈተሽ እንደተገጀመረ ነው የተገለፀው።
በአንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የደረሰ ጉዳት በቀጣይ የሚጠገን ሲሆን የምሰሶው ጉዳት ግን መስመሩን ኃይል ከመስጠት የሚያግደው አይደለም ተብሏል።
በጥገና ሥራው ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎች ከሦስት ሳምንት ያላነሰ ጊዜ የሚፈልገውን ሥራ በአንድ ሳምንት እንዳጠናቀቁት ነው የተነገረው።
ከወልዲያ እስከ አላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ ያለው መስመር ጥገና መጠናቀቅ ከአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ በ66 ኪሎ ቮልት ኃይል ሲያገኙ የነበሩት ፦
- ላሊበላ፣
- ሰቆጣ
- ቆቦ እንዲሁም ማይጨው እና አካባቢያቸው ኃይል እንዲያገኙ ያስችላል።
መረጅው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#PeaceTalks የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ እና ፖለቲካዊ መፍትሄ ያገኝ ዘንድ በአፍሪካ ህበረት (AU) መሪነት በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ንግግር ዛሬ አራተኛ ቀኑን ይዟል። እስካሁን የንግግሮቹን ይዘት በተመለከተ ምንም አይነት መረጃ አልወጣም። በዛው ያሉ ሚዲያዎችም ስለ ሰላም ንግግሩ እና ስለሂደቱ መረጃ የሚያገኙበት መንገድ እንዳይኖር ተደርጓል።…
#PeaceTalks
ትላንት እሁድ ይጠናቀቃል ተብሎ ቀጠሮ የተያዘለት በደቡብ አፍሪካ እየተደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ንግግር ዛሬ ሰኞም እንደሚቀጥል ተሰምቷል።
ኤፒ አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ባለስልጣን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ከሆነ የሰላም ንግግሩ ዛሬም ይቀጥላል።
ከኤፒ በተጨማሪም " SA FM RADIO " የሰላም ንግግሩ ዛሬ እንደሚቀጥል ዘግቧል።
የሰላም ንግግሩን ይዘትና አጠቃላይ አሁን ላይ የደረሰበትን ሂደት በተመለከተ ምንም ይፋዊ መረጃ የለም። የሰላም ንግግሩ ሚዲያዎች መረጃ ሊያገኙበት በማይችል ሁኔታ እየተካሄደ ነው።
ለሰላም ንግግሩ ቅርብ የሆኑ አንድ ባለስልጣን ንግግሩ ምን እድገት እንዳሳየ ሲጠየቁ፤ " እሱን ጊዜ ብቻ ነው የሚነግረን " ሲሉ መልሰዋል።
ሌሎች ምንጮች ደግሞ የሰላም ንግግሩ ዝግ እያለ እየሄደ ቢሆንም በአካል ተገናኝቶ ፊት ለፊት መነጋገሩ ተቀባይነትን እንዳገኘ አመላክተዋል።
በግጭት ማቆም፣ በሰብአዊ ድጋፍ ተደራሽነት እና በወሳኝ መሰረታዊ አገልግሎቶች እንደገና መጀመር ላይ በተደረገ ንግግር "ትልቅ እድገት" ታይቷል ሲሉ እነዚህ ምንጮች ገልፀዋል።
የሰላም ንግግሩ " ወደ ተኩስ አቁም ይመራል " የሚል ተስፋ እንዳላቸው ሙሳ ፋኪ መሀመት ከቀናት በፊት ተናግረው እንደነበር ይታወሳል።
እስካሁን ከሰላም ንግግሩ አመቻቾች/ አዘጋጆች በኩል በቀጥታ የተሰጠ ይፋዊ መረጃ የለም፤ የሰላም ንግግሩ አዘጋጆች የንግግሮችን ይዘትና ሂደት በተመለከተ ከሚዲያዎች ርቀው ዝግ በሆነ መንገድ ነው እያስኬዱ የሚገኙት።
ውድ ቤተሰቦቻችን ከላይ ያነበባችሁት መረጃ የተሰባሰበው፦ ከ "The Star kenya" ጋዜጠኛው ኢሊዩድ ኪቢ፣ SA FM RADIO/SABC፣ ከDaily Maveric/South Africa/ እንዲሁም ከኤፒ ነው።
@tikvahethiopia
ትላንት እሁድ ይጠናቀቃል ተብሎ ቀጠሮ የተያዘለት በደቡብ አፍሪካ እየተደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ንግግር ዛሬ ሰኞም እንደሚቀጥል ተሰምቷል።
ኤፒ አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ባለስልጣን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ከሆነ የሰላም ንግግሩ ዛሬም ይቀጥላል።
ከኤፒ በተጨማሪም " SA FM RADIO " የሰላም ንግግሩ ዛሬ እንደሚቀጥል ዘግቧል።
የሰላም ንግግሩን ይዘትና አጠቃላይ አሁን ላይ የደረሰበትን ሂደት በተመለከተ ምንም ይፋዊ መረጃ የለም። የሰላም ንግግሩ ሚዲያዎች መረጃ ሊያገኙበት በማይችል ሁኔታ እየተካሄደ ነው።
ለሰላም ንግግሩ ቅርብ የሆኑ አንድ ባለስልጣን ንግግሩ ምን እድገት እንዳሳየ ሲጠየቁ፤ " እሱን ጊዜ ብቻ ነው የሚነግረን " ሲሉ መልሰዋል።
ሌሎች ምንጮች ደግሞ የሰላም ንግግሩ ዝግ እያለ እየሄደ ቢሆንም በአካል ተገናኝቶ ፊት ለፊት መነጋገሩ ተቀባይነትን እንዳገኘ አመላክተዋል።
በግጭት ማቆም፣ በሰብአዊ ድጋፍ ተደራሽነት እና በወሳኝ መሰረታዊ አገልግሎቶች እንደገና መጀመር ላይ በተደረገ ንግግር "ትልቅ እድገት" ታይቷል ሲሉ እነዚህ ምንጮች ገልፀዋል።
የሰላም ንግግሩ " ወደ ተኩስ አቁም ይመራል " የሚል ተስፋ እንዳላቸው ሙሳ ፋኪ መሀመት ከቀናት በፊት ተናግረው እንደነበር ይታወሳል።
እስካሁን ከሰላም ንግግሩ አመቻቾች/ አዘጋጆች በኩል በቀጥታ የተሰጠ ይፋዊ መረጃ የለም፤ የሰላም ንግግሩ አዘጋጆች የንግግሮችን ይዘትና ሂደት በተመለከተ ከሚዲያዎች ርቀው ዝግ በሆነ መንገድ ነው እያስኬዱ የሚገኙት።
ውድ ቤተሰቦቻችን ከላይ ያነበባችሁት መረጃ የተሰባሰበው፦ ከ "The Star kenya" ጋዜጠኛው ኢሊዩድ ኪቢ፣ SA FM RADIO/SABC፣ ከDaily Maveric/South Africa/ እንዲሁም ከኤፒ ነው።
@tikvahethiopia
3 የአልሸባብ አባላት በሞት ተቀጡ።
የጎረቤታችን ሶማሊያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት እ.ኤ.አ. በ2018-2020 መካከል ባለው ጊዜ የ15 ሰዎችን ህይወት በቀጠፉ ጥቃቶች ጥፋተኛ ናቸው የተባሉ 3 የአልሸባብ አባላትን በሞት ቀጣ።
ሰዎቹ የሞት ቅጣቱ የተፈፀመባቸው ሰኞ ማለዳ በሞቃዲሾ ውስጥ ነው ተብሏል።
ሶስቱ የአልሸባብ አባላት በ2019 የመንግስት ባለስልጣናት እና በርካታ ሲቪሎችን ህይወት የቀጠፉ የሽብር ጥቃቶችን መፈፀማቸው ተገልጿል።
በሌላ በኩል ፤ የሶማሊያ የሃይማኖት ሊቃውንት በይፋዊ መግለጫ ለ " አልሸባብ ገንዘብ መስጠት / መክፈል ሀራም ነው " ሲሉ አውጀዋል።
ቡድኑን ለመዋጋትም አንድነት እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል።
በሃይማኖት ሊቃውንቱ እና በፌዴራል እና በክልል የሃይማኖት ጉዳዮች ሚኒስቴር መካከል በተካሄደ ጉባኤ ማጠናቀቂያ ላይ መግለጫው የወጣው።
@tikvahethiopia
የጎረቤታችን ሶማሊያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት እ.ኤ.አ. በ2018-2020 መካከል ባለው ጊዜ የ15 ሰዎችን ህይወት በቀጠፉ ጥቃቶች ጥፋተኛ ናቸው የተባሉ 3 የአልሸባብ አባላትን በሞት ቀጣ።
ሰዎቹ የሞት ቅጣቱ የተፈፀመባቸው ሰኞ ማለዳ በሞቃዲሾ ውስጥ ነው ተብሏል።
ሶስቱ የአልሸባብ አባላት በ2019 የመንግስት ባለስልጣናት እና በርካታ ሲቪሎችን ህይወት የቀጠፉ የሽብር ጥቃቶችን መፈፀማቸው ተገልጿል።
በሌላ በኩል ፤ የሶማሊያ የሃይማኖት ሊቃውንት በይፋዊ መግለጫ ለ " አልሸባብ ገንዘብ መስጠት / መክፈል ሀራም ነው " ሲሉ አውጀዋል።
ቡድኑን ለመዋጋትም አንድነት እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል።
በሃይማኖት ሊቃውንቱ እና በፌዴራል እና በክልል የሃይማኖት ጉዳዮች ሚኒስቴር መካከል በተካሄደ ጉባኤ ማጠናቀቂያ ላይ መግለጫው የወጣው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#PeaceTalks ትላንት እሁድ ይጠናቀቃል ተብሎ ቀጠሮ የተያዘለት በደቡብ አፍሪካ እየተደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ንግግር ዛሬ ሰኞም እንደሚቀጥል ተሰምቷል። ኤፒ አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ባለስልጣን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ከሆነ የሰላም ንግግሩ ዛሬም ይቀጥላል። ከኤፒ በተጨማሪም " SA FM RADIO " የሰላም ንግግሩ ዛሬ እንደሚቀጥል ዘግቧል። የሰላም ንግግሩን…
#PeaceTalks
2 ዓመት ሊደፍን የተቃረበውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲያገኝ ለማድረግ በአፍሪካ ህብረት መሪነት በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ያለው የሰላም ንግግር ነገ ማክሰኞም ይቀጥላል ተብሏል።
ትላንት ይጠናቀቃል ተብሎ የነበረው ይኸው የሰላም ንግግር ተራዝሞ ዛሬም ቀጥሎ መዋሉና ነገም እንደሚካሄድ ተሰምቷል።
ከዚሁ የሰላም ንግግር ጋር በተያያዘ ፤ የአፍሪካ ህብረት ንግግሩ የሚጠናቀቅበት ቀነ ገደብ እንዳልተቀመጠ ለኤኤፍፒ በሰጠው ቃል ገልጿል።
የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት ቃል አቀባይ ኤባ ካሎንዶ ፤ " በንግግሩ (በሰላም ንግግሩ) ላይ ቀነ ገደብ አልተቀመጠም " ብለዋል።
አሁን ድረስ የንግግሩን ይዘት ፣ ስላለበት ደረጃ እና ተያያዥ ጉዳዮችን የተመለከተ ምንም አይነት ይፋዊ መረጃ ያልወጣና ሚዲያዎችንም የሰላም ንግግሩን በተመለከተ መረጃ የሚያገኙበት መንገድ ዝግ የተደረገ ሲሆን አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ዲፕሎማት የሰላም ንግግሩ አስተባባሪዎች ንግግሩን በጥብቅ ሚስጥር እንደያዙት ለኤኤፍፒ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
2 ዓመት ሊደፍን የተቃረበውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲያገኝ ለማድረግ በአፍሪካ ህብረት መሪነት በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ያለው የሰላም ንግግር ነገ ማክሰኞም ይቀጥላል ተብሏል።
ትላንት ይጠናቀቃል ተብሎ የነበረው ይኸው የሰላም ንግግር ተራዝሞ ዛሬም ቀጥሎ መዋሉና ነገም እንደሚካሄድ ተሰምቷል።
ከዚሁ የሰላም ንግግር ጋር በተያያዘ ፤ የአፍሪካ ህብረት ንግግሩ የሚጠናቀቅበት ቀነ ገደብ እንዳልተቀመጠ ለኤኤፍፒ በሰጠው ቃል ገልጿል።
የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት ቃል አቀባይ ኤባ ካሎንዶ ፤ " በንግግሩ (በሰላም ንግግሩ) ላይ ቀነ ገደብ አልተቀመጠም " ብለዋል።
አሁን ድረስ የንግግሩን ይዘት ፣ ስላለበት ደረጃ እና ተያያዥ ጉዳዮችን የተመለከተ ምንም አይነት ይፋዊ መረጃ ያልወጣና ሚዲያዎችንም የሰላም ንግግሩን በተመለከተ መረጃ የሚያገኙበት መንገድ ዝግ የተደረገ ሲሆን አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ዲፕሎማት የሰላም ንግግሩ አስተባባሪዎች ንግግሩን በጥብቅ ሚስጥር እንደያዙት ለኤኤፍፒ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
#EthiopianAirlines
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ50 ሚሊዮን ዶላር ዘመናዊ የኢ-ኮሜርስ የጭነት አገልግሎት ማዕከል እያስገነባ ሲሆን ይኸው ማዕከል በቅርቡ ስራ ይጀምራል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሰብሳቢ ግርማ ዋቄ ፤ አየር መንገዱ በካርጎ አገልግሎት ከአፍሪካ ትልቁና በዓለም ተወዳዳሪነቱን ለማስጠበቅ ዘመናዊ አሰራርን ይከተላል ብለዋል።
በዓለም ላይ የዲጂታል ግብይት እያደገ በመምጣቱ የመደበኛው ካርጎ አገልግሎት እየቀነሰ በአንጻሩ የኢ-ኮሜርስ የካርጎ አገልግሎት እየሰፋ መምጣቱን አንስተዋል።
አዲሱን የካርጎ አገልግሎት ማዕከል እውን ለማድረግ እውቀትና የአሰራር ስርዓት በአግባቡ ተዘርግቶለት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
አሰራሩ ከዚህ ቀደም ከነበረው የካርጎ አገልግሎት በእጅጉ የሚለይ ነው ያሉት የቦርድ ሰብሳቢው ዕቃ ከውጭ ተጭኖ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ይወስድ የነበረውን እስከ 7 ቀን በአዲሱ አሰራር እንደሚቀረፍ ተናግረዌ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እያስገነባ ያለው የኢ-ኮሜርስ ማዕከል በ15 ሺህ ስኩዌር ሜትር ላይ ሲሆን 50 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይሆንበታል።
ማዕከሉ በመጪው የፈረንጆቹ 2023 አጋማሽ ላይ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ኢዜአ አየር መንገዱን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ50 ሚሊዮን ዶላር ዘመናዊ የኢ-ኮሜርስ የጭነት አገልግሎት ማዕከል እያስገነባ ሲሆን ይኸው ማዕከል በቅርቡ ስራ ይጀምራል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሰብሳቢ ግርማ ዋቄ ፤ አየር መንገዱ በካርጎ አገልግሎት ከአፍሪካ ትልቁና በዓለም ተወዳዳሪነቱን ለማስጠበቅ ዘመናዊ አሰራርን ይከተላል ብለዋል።
በዓለም ላይ የዲጂታል ግብይት እያደገ በመምጣቱ የመደበኛው ካርጎ አገልግሎት እየቀነሰ በአንጻሩ የኢ-ኮሜርስ የካርጎ አገልግሎት እየሰፋ መምጣቱን አንስተዋል።
አዲሱን የካርጎ አገልግሎት ማዕከል እውን ለማድረግ እውቀትና የአሰራር ስርዓት በአግባቡ ተዘርግቶለት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
አሰራሩ ከዚህ ቀደም ከነበረው የካርጎ አገልግሎት በእጅጉ የሚለይ ነው ያሉት የቦርድ ሰብሳቢው ዕቃ ከውጭ ተጭኖ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ይወስድ የነበረውን እስከ 7 ቀን በአዲሱ አሰራር እንደሚቀረፍ ተናግረዌ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እያስገነባ ያለው የኢ-ኮሜርስ ማዕከል በ15 ሺህ ስኩዌር ሜትር ላይ ሲሆን 50 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይሆንበታል።
ማዕከሉ በመጪው የፈረንጆቹ 2023 አጋማሽ ላይ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ኢዜአ አየር መንገዱን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከ3 ሳምንት ያላነሰ ጊዜ የሚፈልገውን ሥራ በአንድ ሳምንት ነው ያጠናቀቁት " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ጉዳት ደርሶበት የነበረው የወልዲያ አላማጣ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል። ያለዕረፍት በተሰራ ሥራ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና እና የተሰበሩ ኢንሱሌተሮች…
#Update
ከአላማጣ እስከ ቆቦ የሚገኙ አካባቢዎች ዳግም #የኤሌክትሪክ_ኃይል ማግኘታቸው ተገልጿል።
የኤሌክትሪክ ኃይል ያገኙት ፦
- አላማጣ፣
- ኮረም፣
- ዋጃ፣
- ጥሙጋ እና ቆቦ ከተሞች ናቸው።
ከአላማጣ እስከ ላሊበላ የተዘረጋውን የ66 ኬ.ቪ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ በአካባቢው ያሉ ከተሞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።
@tikvahethiopia
ከአላማጣ እስከ ቆቦ የሚገኙ አካባቢዎች ዳግም #የኤሌክትሪክ_ኃይል ማግኘታቸው ተገልጿል።
የኤሌክትሪክ ኃይል ያገኙት ፦
- አላማጣ፣
- ኮረም፣
- ዋጃ፣
- ጥሙጋ እና ቆቦ ከተሞች ናቸው።
ከአላማጣ እስከ ላሊበላ የተዘረጋውን የ66 ኬ.ቪ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ በአካባቢው ያሉ ከተሞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
በዝርፊያ ምክንያት ኃይል ተቋርጧል።
ከጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ወደ ጃዊ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ የኤሌትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች #በሌቦች በመፈታታቸው ኃይል መቋረጡ ተገልጿል።
ይህንን ያሳወቀው የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ነው።
ዝርፊያው የተፈፀመው አይማ ገብርኤል ቀበሌ ጌሾ ወንዝ አካባቢ ነው።
ሦስት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በሌባ በመፈታታታቸው የወደቁ ሲሆን አንድ ተጨማሪ ምሰሶ በመሳሳብ ጉዳት ደርሶበት ወድቋል።
በዚህ የተነሳ ፦ ለበለስ ስኳር ፕሮጅክት፤ ለጃዊና አካባቢው የሚሰጠው የጃዊ ኤሌትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቱ ከጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተቋርጧል።
የወደቁትን ምሰሶዎች ለመጠገን የቴክኒክ ቡድን በሥፍራው ደርሶ ጥገና የጀመረ ሲሆን ጥገናውን ለማጠናቀቅ እስከ #አንድ_ሳምንት ሊፈጅ ይችላል ተብሏል።
ህብረተሰቡ የደረሰ ጉዳት እስኪጠገን በትዕግስት እንዲጠብቅ ዘራፊዎችን ለፀጥታ አካላት እንዲጠቁም ጥሪ ቀርቧል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
@tikvahethiopia
በዝርፊያ ምክንያት ኃይል ተቋርጧል።
ከጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ወደ ጃዊ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ የኤሌትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች #በሌቦች በመፈታታቸው ኃይል መቋረጡ ተገልጿል።
ይህንን ያሳወቀው የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ነው።
ዝርፊያው የተፈፀመው አይማ ገብርኤል ቀበሌ ጌሾ ወንዝ አካባቢ ነው።
ሦስት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በሌባ በመፈታታታቸው የወደቁ ሲሆን አንድ ተጨማሪ ምሰሶ በመሳሳብ ጉዳት ደርሶበት ወድቋል።
በዚህ የተነሳ ፦ ለበለስ ስኳር ፕሮጅክት፤ ለጃዊና አካባቢው የሚሰጠው የጃዊ ኤሌትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቱ ከጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተቋርጧል።
የወደቁትን ምሰሶዎች ለመጠገን የቴክኒክ ቡድን በሥፍራው ደርሶ ጥገና የጀመረ ሲሆን ጥገናውን ለማጠናቀቅ እስከ #አንድ_ሳምንት ሊፈጅ ይችላል ተብሏል።
ህብረተሰቡ የደረሰ ጉዳት እስኪጠገን በትዕግስት እንዲጠብቅ ዘራፊዎችን ለፀጥታ አካላት እንዲጠቁም ጥሪ ቀርቧል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
@tikvahethiopia
" ህብረተሰቡ የቤት ሠራተኞች ሲቀጥር በቂ ዋስትናም ማቅረብ እንዳለባቸው ጭምር #ሊያስገድድ ይገባል " - የአዲስ አበባ ፖሊስ
የአዲስ አበባ ፖሊስ የገዛ ቀጣሪዋን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለች ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል።
ወንጀሉ የተፈጸመው ጥቅምት 18 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 10:45 ሰዓት ሲሆን ቦታው በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ልዩ ቦታው " አስኮ ሊዝ ሰፈር " ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ መሆኑን የፖሊስ መረጃ ያሳያል።
ተከሳሽ በቤት ሠራተኝነት ተቀጥራ ከምትሠራበት ከወ/ሮ ፋሲካ ተሾመ ቤት ሲሆን በመሃላቸው በተፈጠረ አለመግባባት ሟችን በቡና ዘነዘና እና በስለት የተለያዩ የሰውነት አካላቸው ላይ ጉዳት በማድረስ የመግደል ወንጀል ፈጽማለች።
ፖሊስ መረጃው ከህብረተሰቡ ከደረሰው በኋላ ባደረገው ክትትልና ምርመራ ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን ከፈጸመች ከ3 ቀናት በኋላ በቁጥጥር ስር አውሏታል።
ህብረተሰቡ የቤት ሠራተኞችን ሲቀጥር በቂ ዋስትናም ማቅረብ እንዳለባቸው ጭምር ሊያስገድድ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ የገዛ ቀጣሪዋን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለች ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል።
ወንጀሉ የተፈጸመው ጥቅምት 18 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 10:45 ሰዓት ሲሆን ቦታው በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ልዩ ቦታው " አስኮ ሊዝ ሰፈር " ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ መሆኑን የፖሊስ መረጃ ያሳያል።
ተከሳሽ በቤት ሠራተኝነት ተቀጥራ ከምትሠራበት ከወ/ሮ ፋሲካ ተሾመ ቤት ሲሆን በመሃላቸው በተፈጠረ አለመግባባት ሟችን በቡና ዘነዘና እና በስለት የተለያዩ የሰውነት አካላቸው ላይ ጉዳት በማድረስ የመግደል ወንጀል ፈጽማለች።
ፖሊስ መረጃው ከህብረተሰቡ ከደረሰው በኋላ ባደረገው ክትትልና ምርመራ ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን ከፈጸመች ከ3 ቀናት በኋላ በቁጥጥር ስር አውሏታል።
ህብረተሰቡ የቤት ሠራተኞችን ሲቀጥር በቂ ዋስትናም ማቅረብ እንዳለባቸው ጭምር ሊያስገድድ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
#GebreGuracha
በ " ገብረ ጉራቻ " ከተማ በምድረ ገነት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ዲያቆን በታጣቂዎች ሲገደል ፤ 11 አገልጋዮች ደግሞ በታጣቂዎች መታገታቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቴሌቪዥን የማህበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎትን ዋቢ አድርጎ አሳወቀ።
የቤተክርስቲያኒቱ ቴሌቪዥን ፤ በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ገርበ ጉራቻ ከተማ በምትገኘው በምድረ ገነት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ጥቅምት 19/2015 ዓ.ም ሌሊት የማኅሌተ ጽጌ አገልግሎት ላይ በነበሩበት ወቅት #ታጣቂዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን በመግባት አንድ ዲያቆን በመግደል ሌሎች 11 አገልጋዮችን ማገታቸውን ገልጿል።
በአካባቢው ላይ ተደጋጋሚ ችግሮች በመከሰቱ ምእመናን ስጋት ላይ በመሆናቸው ለመንግስት አካላት የማሳወቅ ሥራ ቢሠራም መፍትሔ ማግኘት አልተቻለም ሲል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በይፋዊ #የተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል።
በሌላ በኩል ፤ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መምህር ሽፈራው ለተ.ሚ.ማ. በሰጡት ቃል የተፈጠረውን ጉዳይ እንደሰሙና ለዞኑ አስተዳደርና ለጸጥታ ዘርፉ ማሳወቃቸውን አስረድተዋል። በተለይ በቦታው ቅርብ ርቀት ላይ የመከላከያ ካምፕ መኖሩን ገልፀው ጉዳዩ ሲፈጠር የወሰዱት እርምጃ እንደሌለና ጉዳዩም አዲስ እንዳልሆነ ገልጸዋል።
ይህ ጉዳይ ከሀገረ ስብከቱ አቅም በላይ ስለሆነ ጉዳዩን ለቤተ ክህነት ማቅረባቸውን በአካባቢያው ለሚገኙ ቀሪ ምእመናን መፍትሔ እንዲሰጥ እንደጠየቁ እና ምላሽም እየተጠባበቁ ስለመሆኑ ለሚዲያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
በ " ገብረ ጉራቻ " ከተማ በምድረ ገነት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ዲያቆን በታጣቂዎች ሲገደል ፤ 11 አገልጋዮች ደግሞ በታጣቂዎች መታገታቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቴሌቪዥን የማህበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎትን ዋቢ አድርጎ አሳወቀ።
የቤተክርስቲያኒቱ ቴሌቪዥን ፤ በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ገርበ ጉራቻ ከተማ በምትገኘው በምድረ ገነት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ጥቅምት 19/2015 ዓ.ም ሌሊት የማኅሌተ ጽጌ አገልግሎት ላይ በነበሩበት ወቅት #ታጣቂዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን በመግባት አንድ ዲያቆን በመግደል ሌሎች 11 አገልጋዮችን ማገታቸውን ገልጿል።
በአካባቢው ላይ ተደጋጋሚ ችግሮች በመከሰቱ ምእመናን ስጋት ላይ በመሆናቸው ለመንግስት አካላት የማሳወቅ ሥራ ቢሠራም መፍትሔ ማግኘት አልተቻለም ሲል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በይፋዊ #የተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል።
በሌላ በኩል ፤ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መምህር ሽፈራው ለተ.ሚ.ማ. በሰጡት ቃል የተፈጠረውን ጉዳይ እንደሰሙና ለዞኑ አስተዳደርና ለጸጥታ ዘርፉ ማሳወቃቸውን አስረድተዋል። በተለይ በቦታው ቅርብ ርቀት ላይ የመከላከያ ካምፕ መኖሩን ገልፀው ጉዳዩ ሲፈጠር የወሰዱት እርምጃ እንደሌለና ጉዳዩም አዲስ እንዳልሆነ ገልጸዋል።
ይህ ጉዳይ ከሀገረ ስብከቱ አቅም በላይ ስለሆነ ጉዳዩን ለቤተ ክህነት ማቅረባቸውን በአካባቢያው ለሚገኙ ቀሪ ምእመናን መፍትሔ እንዲሰጥ እንደጠየቁ እና ምላሽም እየተጠባበቁ ስለመሆኑ ለሚዲያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
"ሀክ ተደርጌ ነው"
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ይፋዊ የተረጋገጠ የፌስቡክ ገፅ ላይ የተጋራው የአንድ ግለሰብ አካውንት መልዕክት በበርካቶች ዘንድ ውግዘት ያደረሰ ሲሆን የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ "ሀክ ተደርጌ ነው" ብሏል።
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ በፌስቡክ ገፁ ላይ ያጋራው ከላይ የተያያዘውን "Adisalem Desta" የተባለ ግለሰብ ፅሁፍ ሲሆን ፅሁፉ " የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ኃይሎች በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚቀርበውን ጥሪ ቸል በማለት የዘር ጭፍጨፋ ጦርነታቸውን እያባባሱ ነው / መላውን ትግራይ በመቆጣጠር የዚህን ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሚካሄደውን የሰላም ንግግር የትጥቅ ማስፈታት ስነስርዓት ለማድረግ ነው ። " የሚሉና ሌሎች ሀሳቦች የያዘ ነው።
ይኸው ፅሁፍ በገፁ ላይ ለ25 ደቂቃ ያህል የቆየ ሲሆን እጅግ በርካታ ሰዎች በአስተያየት መስጫው ላይ ከፍተኛ ውግዘት እና ተቃውሞ አሰምተዋል።
" ዓለም አቀፉ ተቋም የህወሓትን ቡድን ፕሮፖጋንዳ በግልፅ ማሰራጨቱን፣ ተቋሙ በሽብርተኝነት የተፈረጀውን ህወሓትን የመደገፍ አላማ እንዳለው፣ በዚህ ድርጊቱም ሊያፍር እንደሚገባ " በመግለፅ ድርጊቱን ኮንነዋል።
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ልዑክ በገፁ ላይ የነበረው ፅሁፍ የጠፋ ሲሆን ብዙም ሳይቆይ ገፁ " ተጠልፎ/ሀክ ተደርጎ " እንደነበር ገልጿል።
ልዑኩ፤ "ዛሬ አካውንታችን እንደተጠለፈ እና ፖስት እንደተደረገ ለማሳወቅ ይወዳል" ያለ ሲሆን "ይህ የአውሮፓ ህብረት / በኢትዮጵያ የአውሮፓ ልዑክ ይፋዊ መልዕክት አይደለም" ብሏል።
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ልዑክ አካውንቱን መልሶ መቆጣጠሩን አመልክቶ ከጠለፋው (ሀክ መደረጉ) ጋር በተያያዘ ያለውን ሁኔታ እየመረመረ መሆኑን ገልጿል።
"ሀክ ተደርጌ ነው" ባለበት ፅሁፉ የአስተያየት መስጫውን #ቆልፎታል።
@tikvahethiopia
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ይፋዊ የተረጋገጠ የፌስቡክ ገፅ ላይ የተጋራው የአንድ ግለሰብ አካውንት መልዕክት በበርካቶች ዘንድ ውግዘት ያደረሰ ሲሆን የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ "ሀክ ተደርጌ ነው" ብሏል።
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ በፌስቡክ ገፁ ላይ ያጋራው ከላይ የተያያዘውን "Adisalem Desta" የተባለ ግለሰብ ፅሁፍ ሲሆን ፅሁፉ " የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ኃይሎች በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚቀርበውን ጥሪ ቸል በማለት የዘር ጭፍጨፋ ጦርነታቸውን እያባባሱ ነው / መላውን ትግራይ በመቆጣጠር የዚህን ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሚካሄደውን የሰላም ንግግር የትጥቅ ማስፈታት ስነስርዓት ለማድረግ ነው ። " የሚሉና ሌሎች ሀሳቦች የያዘ ነው።
ይኸው ፅሁፍ በገፁ ላይ ለ25 ደቂቃ ያህል የቆየ ሲሆን እጅግ በርካታ ሰዎች በአስተያየት መስጫው ላይ ከፍተኛ ውግዘት እና ተቃውሞ አሰምተዋል።
" ዓለም አቀፉ ተቋም የህወሓትን ቡድን ፕሮፖጋንዳ በግልፅ ማሰራጨቱን፣ ተቋሙ በሽብርተኝነት የተፈረጀውን ህወሓትን የመደገፍ አላማ እንዳለው፣ በዚህ ድርጊቱም ሊያፍር እንደሚገባ " በመግለፅ ድርጊቱን ኮንነዋል።
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ልዑክ በገፁ ላይ የነበረው ፅሁፍ የጠፋ ሲሆን ብዙም ሳይቆይ ገፁ " ተጠልፎ/ሀክ ተደርጎ " እንደነበር ገልጿል።
ልዑኩ፤ "ዛሬ አካውንታችን እንደተጠለፈ እና ፖስት እንደተደረገ ለማሳወቅ ይወዳል" ያለ ሲሆን "ይህ የአውሮፓ ህብረት / በኢትዮጵያ የአውሮፓ ልዑክ ይፋዊ መልዕክት አይደለም" ብሏል።
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ልዑክ አካውንቱን መልሶ መቆጣጠሩን አመልክቶ ከጠለፋው (ሀክ መደረጉ) ጋር በተያያዘ ያለውን ሁኔታ እየመረመረ መሆኑን ገልጿል።
"ሀክ ተደርጌ ነው" ባለበት ፅሁፉ የአስተያየት መስጫውን #ቆልፎታል።
@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
" ... ህወሓቶች የሀገሪቱን ሕገ መንግስት እንዲያከብሩ ፤ እና እንደ ኢትዮጵያ አንድ #ክልል እንዲንቀሳቀሱ ለማሳመን እየሞከርን ነው " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመፍታት በሚካሄደው ሂደት ከባድ የውጭ ጣልቃ ገብነት እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ከCGTN ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ሰላምን ለማምጣት ባለው ሂደት " የውጪ ጣልቃ ገብነት " ቢኖርም የሰላም ስምምነት እንደሚደረስ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።
" በእርግጥ ከግራም ሆነ ከቀኝም በርካታ ጣልቃ ገብነቶች የሚኖሩ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ይሆናል " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ፤ " ኢትዮጵያውያን መረዳት ያለባቸው የራሳችንን ጉዳይ በራሳችን መፍታት አንደምንችል " ነው ሲሉ አክለዋል።
" ህወሓት የሀገሪቱን #ህገመንግስት እንዲያከብር ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ አንድ ክልል እንዲንቀሳቀስ ለማሳመን ጥረት እያደረገን ነው " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " ፍላጎታችንን መገንዘብ የሚችሉ ከሆነ እና የራሱን ህገመንግስት የሚያክብር እና በህጉ መሰረት የሚንቀሳቀስ ከሆነ ሰላም ይሰፍናል ብየ አስባሁ " ብለዋል።
(ሙሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመፍታት በሚካሄደው ሂደት ከባድ የውጭ ጣልቃ ገብነት እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ከCGTN ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ሰላምን ለማምጣት ባለው ሂደት " የውጪ ጣልቃ ገብነት " ቢኖርም የሰላም ስምምነት እንደሚደረስ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።
" በእርግጥ ከግራም ሆነ ከቀኝም በርካታ ጣልቃ ገብነቶች የሚኖሩ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ይሆናል " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ፤ " ኢትዮጵያውያን መረዳት ያለባቸው የራሳችንን ጉዳይ በራሳችን መፍታት አንደምንችል " ነው ሲሉ አክለዋል።
" ህወሓት የሀገሪቱን #ህገመንግስት እንዲያከብር ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ አንድ ክልል እንዲንቀሳቀስ ለማሳመን ጥረት እያደረገን ነው " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " ፍላጎታችንን መገንዘብ የሚችሉ ከሆነ እና የራሱን ህገመንግስት የሚያክብር እና በህጉ መሰረት የሚንቀሳቀስ ከሆነ ሰላም ይሰፍናል ብየ አስባሁ " ብለዋል።
(ሙሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DigitalLottery አድማስ ሎተሪ ወጣ ! የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር የአድማስ ሎተሪ ዕጣ ዛሬ መስከረም 11 ቀን 2015 ዓ/ም በብሔራዊ ሎተሪ የዕጣ ማውጫ አዳራሽ በሕዝብ ፊት መውጣቱን አሳውቋል። ዛሬ የወጣው ሁለተኛው ዙር ነው። 👉 የ1.5 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር ፦ 003111908205 👉 የ800 ሺህ ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር ፦ 003098506207…
#DigitalLottery
አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዛሬ ጥቅምት 22/205 ዓ/ም በብሄራዊ ሎተሪ የዕጣ ማውጫ አዳራሽ በህዝብ ፊት ወጥቷል።
1.5 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር 004159786369 ሆኖ ወጥቷል።
👉 1.5 ሚሊዮን ብር - 004159786369
👉 800 ሺህ ብር - 004412460260
👉 350 ሺህ ብር - 004223166354
👉 200 ሺህ ብር - 004429482613
👉 160 ሺህ ብር - 004095740673
👉 120 ሺህ ብር - 004374280736
(ተጨማሪ የዕጣ ቁጥሮች ከላይ ተያይዘዋል)
@tikvahethiopia
አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዛሬ ጥቅምት 22/205 ዓ/ም በብሄራዊ ሎተሪ የዕጣ ማውጫ አዳራሽ በህዝብ ፊት ወጥቷል።
1.5 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር 004159786369 ሆኖ ወጥቷል።
👉 1.5 ሚሊዮን ብር - 004159786369
👉 800 ሺህ ብር - 004412460260
👉 350 ሺህ ብር - 004223166354
👉 200 ሺህ ብር - 004429482613
👉 160 ሺህ ብር - 004095740673
👉 120 ሺህ ብር - 004374280736
(ተጨማሪ የዕጣ ቁጥሮች ከላይ ተያይዘዋል)
@tikvahethiopia