TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትኩረት የመተሐራ ቲክቫህ ቤተሰቦች በሚኖሩበት የመተሀራ አካባቢ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራበት እንደሚገባ በላኳቸው መልዕክቶች አስገንዝበዋል። ከዚህ ቀደም ወደ መተሀራ አካባቢ በርካታ ወጣቶች በመዝናኛ ቦታ እያሉ መገደላቸው በሚዲያዎችም ጭምር መገለፁ ይታወሳል። እዛው " መተሐራ " አካባቢ ከአምስት ቀናቶች በፊት አንድ የቀበሌ ሊቀመንበር ተገድሎ ነበር ፤ ከዚህ ግድያ በኃላም የአካባቢው…
#መተሐራ

ከጥቂት ቀናት በፊት በመተሐራ እና አካባቢው ያሉ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት እጅግ እየተደጋገመ የመጣው የታጣቂዎች ጥቃት የሰዎች ህይወት እየቀጠፈ መሆኑን ፤ በአጠቃላይ የደህንነት ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ስለመድረሱ በዝርዝር አመልክተው ነበር።

ዛሬ ከመተሐራ ቤተሰቦች የመጣው መልዕክት ፤ ትላንት ከጠዋቱ መተሐራ አባድር 2ተኛ ካምፕ በሚባል አካባቢ ታጣቂዎች ገብተው ከ10 በላይ ሰዎችን መገደላቸውን ፤ በዚህም ጥቃት ሳቢያ ደህንነታቸው አደጋ ላይ የወደቀባቸው ሰዎች መኖሪያቸውን ለቀው እንዲወጡ መገደዳቸውን ያመለክታል።

የሟቾች ስርዓተ ቀብርም ዛሬ ተፈፅሟል ብለዋል።

ትላንት መልዕክት እንዳይልኩ ኔትዎርክ እየሰራ እንዳልነበር ገልፀዋል።

ከዛው ከመተሐራ አንድ የቤተሰባችን አባል ፤ አባድር ሁለተኛ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በታጣቂዎች በተፈፀመው ጥቃት 12 ወጣቶች መገደላቸውን ገልጾ ነዋሪው ከቤት ንብረቱ ተፈናቅሏል ሲል አመልክቷል።

ተፈናቃዮችም በትምህርት ቤት ውስጥ እንደሚገኙ የገለፀው የቤተሰባችን አባል" ከወረዳውም ሆነ ከክልል በኩል እንዳች የተባለ ነገር የለም " ብሏል።

" ችግሩ አስከፊ እና አሳሳቢ ነው " ያለው ይኸው የቤተሰባችን አባል የህዝቡን ጩኸት የፌደራል መንግስትና ሌሎችም የሚመለከታቸው ሁሉ ሰምተው ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈልጉና አስተማማኝ ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲያደርጉ ጠይቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ከታሪፍ ውጪ አትክፈሉ !

" የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ላይ ምንም አይነት የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አልተደረገም " - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር

ከቀናት በፊት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ፤ የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ የሆኑ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች በሚጠቀሙት ነዳጅ ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አልተደረገም።

አነስተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በተዘረጋው ብሔራዊ የታለመ የነዳጅ ድጎማ አሠራር ታቅፈው ህዝቡን እንዲያገለግሉ የተመረጡት የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች በሚጠቀሙት ነዳጅ ላይ በ2ኛው ምዕራፍ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አልተደረገም።

ይህም ማለት ቀደም ሲል ይቀርብ በነበረበት የነጭ ናፍጣና ኬሮሲን ዋጋ ብር 40.86 ፣ የቢንዚን ብር 41.25 ነው እየቀረበ የሚገኘው።

#በታለመለት_የነዳጅ_ድጎማ_የታቀፉ_ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ቀደም ሲል በወጣላቸው ታሪፍ ሀብረተሰቡን እንዲያገለግሉ ማሳሰቢያ የተሰጠ ሲሆን ህብረተሰቡ ይህን አውቆ መንግስት ካስቀመጠው ታሪፍ ውጪ ባለመክፈል ተባባሪ እንዲሆን ተጠይቋል።

በተጨማሪም ኃላፊነታቸውን በተገቢው መንገድ የማይወጡ አሽከርካሪዎች ሲያጋጥሙ በየደረጃው ላሉ የፀጥታ አካላት #ጥቆማ በመስጠት ህብረተሰቡ መብቱን እንዲያስከብር በትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር መልዕክት ተላልፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ / ቪድዮ : የ2015 ዓ/ም የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል አከባበርን የሚያሳዩ ፎቶዎች እና ቪድዮዎች ከላይ ተያይዟል። ፎቶና ቪድዮው የተሰባሰበው ከተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ነው። @tikvahethiopia @tikvahethmagazine
ፎቶ : የ2015 የሆራ ሀርሰዴ በዓል በቢሾፍቱ ዛሬ ተከብሯል።

የበዓሉን ድባብ የሚያሳዩ ፎቶዎች ተያይዘዋል።

በዓሉ በሰላም መከበሩን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አሳውቋል።

የዘንድሮው 2015 ዓ/ም የ " ሆራ ፊንፊኔ " እና " ሆራ ሀረሰዴ " በዓል በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ ለአዲስ አበባ ህዝብ እና ለቢሾፍቱ ህዝብ ምስጋና ቀርቧል።

@tikvahethiopia
@tikvahethsport

ይህን ተጭነው ይገምቱ ፤ ይሸለሙ 👇
https://yangx.top/tikvahethsport/33477

ማንችስተር ሲቲ ከ ማንችስተር ዩናይትድ

(ቲክቫህ ስፖርት)

@tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
ከኢሰመኮ ሪፖርት ፦ " ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡00 ሰዓት በኋላ እንዲሁም ሰኔ 8 እና 9 ቀን 2014 ዓ.ም. በዋናነት በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች በተወሰዱ እርምጃዎች " የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እና መሣሪያ በቤታችሁ እንዳለ ተጠቁመናል፤ የደበቃችሁትን መሣሪያ አውጡ " በሚል ምክንያት ሴቶችና የአእምሮ ሕመምተኞችን ጨምሮ ቢያንስ 50 ሲቪል ሰዎች በተናጠል እና በጅምላ ከፍርድ ውጪ መገደላቸውን፣…
#ጋምቤላ

የጋምቤላ ክልል መንግስት የኢሰመኮን ሪፖርት "ለጠላት የወገነ ነው " ሲል ገልጾ ሪፖርቱን እንደማይቀበለውና እንደሚያወግዘው ገለፀ።

የጋምቤላ ክልል፤ "ኢሰመኮ ሰኔ 7/2014 ዓ.ም በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ ላይ ተፈጥሮ በነበረው ውጊያ ተከትሎ በክልሉ ልዩ ኃይሎች፣ ሚሊሽያ እና ተባባሪ ወጣቶችን ሲመሩ የነበሩ አመራሮች አማካይነት ደረሰ ባላቸው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ላይ ያወጣውን ሚዛናዊነት የጎደለውና የአንድ ክልል የፀጥታ ተቋምን ከተራ የአሸባሪ ቡድን ተላላኪ ጋር በአንድነት ያየ" ነው ሲል ገልጿል።

ሪፖርቱ "ከሁሉ በላይ በክልልና በአገር ላይ ይደርስ የነበረ ከፍተኛ ጥቃት በመቀልበስ ሂደት የህይወት መስዋዕትነት የከፈለውን የፀጥታ ተቋማችንን በጅምላ የፈረጀና የተገኘውንም ድል በዜሮ ያባዛ ሆኖ አግኝቶታል" ብሏል።

በዚህም የጋምቤላ ክልል መንግሥት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የምርመራ ሪፖርት እንደማይቀበለውና አጥብቆ እንደሚያወግዘው ገልጿል።

አክሎም "የክልሉ መንግሥት ምንም እንኳን አንድም የዜጋ ህይወት እንዲጠፋ የሚፈቅድ ባይሆንም በጥፋት ቡድኖቹ በተከፈተብን ጥቃት ከንፁሃን ዜጎች እንዲሁም የፀጥታ አካላት ህይወት መጥፋት ጋር ተያይዞ ኮምሽኑ ያወጣው የምርመራ ሪፖርት ግኝት እጅግ የተጋነነ እና በወቅቱ መሬት የነበረውን ጥሬ ሀቅ ያላገናዘበ" ነው ብሏል።

"የኢትዮጵያ ህዝቦች በጋምቤላ ከተማ ውስጥና ኦነግ ሸኔና ጋነግ የፈፀሙት ወረራና ጥቃት ብዥታ ተፈጥሮ የክልሉን መንግሥት እና ህዝብ በወቅቱ የተደረገውን ተጋድሎና ለዚህም የተከፈለውን መስዋዕትነት በዜሮ ያባዛ፤ ከሁሉ በላይ የክልሉን የፀጥታ ኃይል ሞራል የሚያዳክም፤ ፀረ-ሠላም ኃይሉንና መንግሥትን በአንድ ሚዛን ላይ አድርጎ ያየ በአጠቃላይ ለጠላት የወገነ ሪፖርት ሆኖ አግኝተነዋል" ሲል አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጋምቤላ የጋምቤላ ክልል መንግስት የኢሰመኮን ሪፖርት "ለጠላት የወገነ ነው " ሲል ገልጾ ሪፖርቱን እንደማይቀበለውና እንደሚያወግዘው ገለፀ። የጋምቤላ ክልል፤ "ኢሰመኮ ሰኔ 7/2014 ዓ.ም በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ ላይ ተፈጥሮ በነበረው ውጊያ ተከትሎ በክልሉ ልዩ ኃይሎች፣ ሚሊሽያ እና ተባባሪ ወጣቶችን ሲመሩ የነበሩ አመራሮች አማካይነት ደረሰ ባላቸው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ላይ ያወጣውን ሚዛናዊነት…
የጋምቤላ ክልል የኢሰመኮን ሪፖርት እንደማይቀበለው እና እንደሚያወግዝ በገለፀበት መግለጫ ምን አለ ?

- ሚዛናዊነት የጎደለው በመሆኑ ምርመራውን አልቀበለውም፤ በጥብቅም አወግዛለሁ።

- ሪፖርቱ የአንድ ክልል የፀጥታ ተቋምን ከተራ የአሸባሪ ቡድን ተላላኪ ጋር በአንድነት ያየ፤ በክልልና በአገር ላይ ይደርስ የነበረ ከፍተኛ ጥቃት በመቀልበስ ሂደት የህይወት መስዋዕትነት የከፈለውን የፀጥታ ተቋሙን በጅምላ የፈረጀ፤ የተገኘውንም ድል በዜሮ ያባዛ ነው።

- ሪፖርቱ የክልሉን የፀጥታ ኃይል ሞራል የሚያዳክም፤ ፀረ-ሠላም ኃይሉንና መንግሥትን በአንድ ሚዛን ላይ አድርጎ ያየ፤ በአጠቃላይ ለጠላት የወገነ ሪፖርት ነው።

- የመረጃ አሰባሰብና ምዘና ሥነ-ዘዴው ምክንያታዊ አሳማኝነት (Reasonable Grounds) ስልት ያልተከተለ ነው።

- መረጃው ከተወሰኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ማለትም ከኦነግ ሸኔና ህወኃት ደጋፊዎች እንዲሁም በተለያዩ ወንጀሎች ሲጠረጠሩ ከነበሩ ግለሰቦች የተወሰደና በአንድ አካባቢ የታጠረ ነው።

- ሪፖርቱ የጋምቤላን ነባር ብሔረሰቦች እና አብረዋቸው ለረዥም ዘመናት ከሚኖሩ ወንድምና እህት ኢትዮጵያዊያን ጋር እርስ በርስ ለማጋጨት #ሆን_ተብሎ የተዘጋጀ ሪፖርት ነው።

- በጋምቤላ ክልል የሚገኘው የኮሚሽኑ ጽ/ቤት ባልደረቦች ተቋሙ የተቋቋመለትን ዓላማና ተልዕኮ በቅጡ ያልተገነዘቡ፣ የግል ፍላጎታቸው የታየበት፣ የክልሉን ህዝብና መንግሥት አለያይቶ ለማጋጨት የተደረገ ሴራ ነው።

-  ሪፖርቱ የክልሉን መንግሥትና ህዝብ ስም ለማጥፋት ሆን ተብሎ በተለያዩ ሚዲያዎች የክልሉ መንግሥት የሰጠውን መግለጫዎችና ጥንቃቄ የጎደላቸው የግል ሃሳቦችን እንደ ማጣቀሻ በመጠቀም ስህተት ተኮር የሪፖርት ስልት የተከተለ ነው።

የኢሰመኮ ሪፖርት : t.me/tikvahethiopia/73948

@tikvahethiopia