TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እንድታውቁት
ከአዲስ አበባ ፖሊስ ፦
1ኛ. በከተማ ደረጃ የደመራ ስነ-ሰርዓት ወደ ሚከናወንበት መስቀል አደባባይ ሆነ ሌሎች ተመሳሳይ ስፍራዎች የጦር መሳሪያ ፣ ስለታም ነገሮችን እና ህገወጥ ቁሳቁሶችን ይዞ መምጣት የተከለከ ነው።
2ኛ. ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ እንደሚኖር ሁሉም ህብረተሰብ ተገንዝቦ የተለመደ ትብብሩን ሊያደርግ ይገባል።
3ኛ. በመስቀል አደባባይ የሚካሄደው የደመራ ፕሮግራምን መጠናቀቅ ተከትሎ በከተማው በተለያዩ ደብሮች እና መንደሮች ደመራ የማብራት ስነ-ስርዓት የሚካሄድ ሲሆን በየአካባቢው ደመራ ሲበራ ህብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደረግ ይገባል። በማንኛውም ሁኔታ ርችት መተኮስ ፍፁም ክልክል ነው።
የፖሊስን አገልግሎት ለማግኘትም ሆነ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት መረጃ ለመስጠት 991 ወይም 816 ነፃ የስልክ መስመሮችን እንዲሁም 0111110111፣ 0111264359፣ 0111010297፣ መጠቀም ይቻላል።
የሚዘጉ መንገዶች #ማስታወሻ : https://yangx.top/tikvahethiopia/73882?single
#AddisAbabaPoliceCommission
@tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ ፖሊስ ፦
1ኛ. በከተማ ደረጃ የደመራ ስነ-ሰርዓት ወደ ሚከናወንበት መስቀል አደባባይ ሆነ ሌሎች ተመሳሳይ ስፍራዎች የጦር መሳሪያ ፣ ስለታም ነገሮችን እና ህገወጥ ቁሳቁሶችን ይዞ መምጣት የተከለከ ነው።
2ኛ. ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ እንደሚኖር ሁሉም ህብረተሰብ ተገንዝቦ የተለመደ ትብብሩን ሊያደርግ ይገባል።
3ኛ. በመስቀል አደባባይ የሚካሄደው የደመራ ፕሮግራምን መጠናቀቅ ተከትሎ በከተማው በተለያዩ ደብሮች እና መንደሮች ደመራ የማብራት ስነ-ስርዓት የሚካሄድ ሲሆን በየአካባቢው ደመራ ሲበራ ህብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደረግ ይገባል። በማንኛውም ሁኔታ ርችት መተኮስ ፍፁም ክልክል ነው።
የፖሊስን አገልግሎት ለማግኘትም ሆነ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት መረጃ ለመስጠት 991 ወይም 816 ነፃ የስልክ መስመሮችን እንዲሁም 0111110111፣ 0111264359፣ 0111010297፣ መጠቀም ይቻላል።
የሚዘጉ መንገዶች #ማስታወሻ : https://yangx.top/tikvahethiopia/73882?single
#AddisAbabaPoliceCommission
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#መልዕክት
የ " መስቀል ደመራ በዓል " አከባበርን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ መልዕክት ፦
- ሁከት ቀስሰቃሽ መልዕክቶችን በቲሸረሰቶች ላይም ሆነ በባነሮች ላይ በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ ይዞ መገኘት በፍፁም አይፈቀድም።
- በበዓሉ ላይ ህገ መንግስቱ የደነገገውን የኢትዮጵያን የፌዴራል ሰንደቅ ዓላማ #ወይም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የፀደቀውን የቤተክርስቲያን ዓርማን ብቻ መጠቀም ይገባል። ከዚህ ውጪ የሆነ ምንም ዓይነት አርማም ሆነ ሰንደቅ አላማ መያዝ በጥብቅ የተከለከለ ነው። የምንጠቀመው ሰንደቅ ዓላማ ሆነ የቤተክርስቲያን አርማ በግልፅ የሚታዩ በሁለቱም ፊት ዓርማዎቹ በትክክል የተቀመጡ መሆን አለባቸው።
- በቲሸርቶች ፣ በባነሮች እንዲሁም በትርኢቶች ላይ ሁሉ ሌሎች ወገኖችን የሚያስከፉ፣ መብትን የሚጋፉ ሁከት ቀስቃሽ የሆኑ ጥቅሶችን መጠቀም ከሥነ ምግባር ውጪ ከመሆኑም በላይ ለሁከትና ግርግር መፈጠር ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ በጥብቅ የተከለከለ ነው።
- ወደ መስቀል አደባባይ በሚደረግ ጉዞ #ተደጋጋሚ ፍተሻ ይደረጋል፤ የሚደረገው ፍተሻ ለደህንነታችን ተብሎ የሚደረግ ፍተሻ መሆኑን በመገንዘብ መላው ህዝበ ክርሰቲያን ራሱን ለፍተሻ ዝግጁ ማድረግና ፍጹም በሆነ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ለፍተሻ መተባበር እንደሚገባው በመረዳት የጸጥታ አካላትን መተባበር አለበት።
- በመስቀል አደባባይ እንዲሁም ደብረ ዕንቁ ቅድስት ልደታ ማርያም ጉዳይ የሚመለከተውን አካል በሕግ አግባብ መጠየቅ የሚገባና እና በጉዳዩ ዙሪያ ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጀምሮ ሁሉም የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ችግሩ የሚፈታበትን መንገድ ያከናውናሉ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች በዓሉ በሚከበርበት ወቅት ሊደረግ አይገባም።
- በቤተክርስቲያን ማዕከላዊ አስተዳደርና በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ተዘጋጅቶ ከሚሰራጨው መጽሔት እና ብሮሸር ውጪ ምንም ዓይነት የህትመት ውጤት ስለማይሰራጭ ከእነዚህ ውጪ የሆኑ የህትመት ውጤቶችንና በራሪ ወረቀቶችን ይዞ መገኘት በጥብቅ የተከለከለ ነው። ይዞ የተገኘም በህግ ተጠያቂ ይሆናል።
- ከመስቀል አደባባይ ውጪ በአድባራትና ገዳማት በሚከበሩ የመስቀል ደመራ በዓላት ሁሉም ህዝበ ክርስቲያን ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር እና በመረዳዳት መሥራት የሚገባ ሲሆን ሁከት ቀስቃሽ ከሆኑ መልዕክቶች በመታቀብና ህጋዊ ያልሆኑ ሰንደቅ ዓላማዎችን ባለመጠቀም የበዓሉን ሰላማዊነትና የመስቀሉን ዓላማ መሰረት ያደረጉ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባርን የተላበሱ እንቅስቃሴዎች ሊደረጉ ይገባል።
- ማንኛውም አጠራጣሪ እና ለጸጥታ ስጋት የሚሆኑ ነገሮች ሲያጋጥም በቦታው ለተመደቡ የሥነሥርዓትና የጸጥታ አስከባሪ አባላት / ለፖሊስ አካላት መጠቆም ይገባል።
(የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን)
@tikvahethiopia
የ " መስቀል ደመራ በዓል " አከባበርን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ መልዕክት ፦
- ሁከት ቀስሰቃሽ መልዕክቶችን በቲሸረሰቶች ላይም ሆነ በባነሮች ላይ በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ ይዞ መገኘት በፍፁም አይፈቀድም።
- በበዓሉ ላይ ህገ መንግስቱ የደነገገውን የኢትዮጵያን የፌዴራል ሰንደቅ ዓላማ #ወይም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የፀደቀውን የቤተክርስቲያን ዓርማን ብቻ መጠቀም ይገባል። ከዚህ ውጪ የሆነ ምንም ዓይነት አርማም ሆነ ሰንደቅ አላማ መያዝ በጥብቅ የተከለከለ ነው። የምንጠቀመው ሰንደቅ ዓላማ ሆነ የቤተክርስቲያን አርማ በግልፅ የሚታዩ በሁለቱም ፊት ዓርማዎቹ በትክክል የተቀመጡ መሆን አለባቸው።
- በቲሸርቶች ፣ በባነሮች እንዲሁም በትርኢቶች ላይ ሁሉ ሌሎች ወገኖችን የሚያስከፉ፣ መብትን የሚጋፉ ሁከት ቀስቃሽ የሆኑ ጥቅሶችን መጠቀም ከሥነ ምግባር ውጪ ከመሆኑም በላይ ለሁከትና ግርግር መፈጠር ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ በጥብቅ የተከለከለ ነው።
- ወደ መስቀል አደባባይ በሚደረግ ጉዞ #ተደጋጋሚ ፍተሻ ይደረጋል፤ የሚደረገው ፍተሻ ለደህንነታችን ተብሎ የሚደረግ ፍተሻ መሆኑን በመገንዘብ መላው ህዝበ ክርሰቲያን ራሱን ለፍተሻ ዝግጁ ማድረግና ፍጹም በሆነ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ለፍተሻ መተባበር እንደሚገባው በመረዳት የጸጥታ አካላትን መተባበር አለበት።
- በመስቀል አደባባይ እንዲሁም ደብረ ዕንቁ ቅድስት ልደታ ማርያም ጉዳይ የሚመለከተውን አካል በሕግ አግባብ መጠየቅ የሚገባና እና በጉዳዩ ዙሪያ ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጀምሮ ሁሉም የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ችግሩ የሚፈታበትን መንገድ ያከናውናሉ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች በዓሉ በሚከበርበት ወቅት ሊደረግ አይገባም።
- በቤተክርስቲያን ማዕከላዊ አስተዳደርና በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ተዘጋጅቶ ከሚሰራጨው መጽሔት እና ብሮሸር ውጪ ምንም ዓይነት የህትመት ውጤት ስለማይሰራጭ ከእነዚህ ውጪ የሆኑ የህትመት ውጤቶችንና በራሪ ወረቀቶችን ይዞ መገኘት በጥብቅ የተከለከለ ነው። ይዞ የተገኘም በህግ ተጠያቂ ይሆናል።
- ከመስቀል አደባባይ ውጪ በአድባራትና ገዳማት በሚከበሩ የመስቀል ደመራ በዓላት ሁሉም ህዝበ ክርስቲያን ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር እና በመረዳዳት መሥራት የሚገባ ሲሆን ሁከት ቀስቃሽ ከሆኑ መልዕክቶች በመታቀብና ህጋዊ ያልሆኑ ሰንደቅ ዓላማዎችን ባለመጠቀም የበዓሉን ሰላማዊነትና የመስቀሉን ዓላማ መሰረት ያደረጉ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባርን የተላበሱ እንቅስቃሴዎች ሊደረጉ ይገባል።
- ማንኛውም አጠራጣሪ እና ለጸጥታ ስጋት የሚሆኑ ነገሮች ሲያጋጥም በቦታው ለተመደቡ የሥነሥርዓትና የጸጥታ አስከባሪ አባላት / ለፖሊስ አካላት መጠቆም ይገባል።
(የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በአዲስ አበባ 49,203 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ ተመዝግበዋል " - የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ፈተናው ከሚሰጥባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራሮች ጋር ውይይት አካሂዷል። ዘንድሮ ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሚሰጥ…
#ብሔራዊ_ፈተና
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ኮማንድ ፖስት በፈተናው ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።
በውይይቱ ፦
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ፣
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኔጅመንት አባላት ፣
• የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣
• የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፣
• የኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣
• የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
• የፌደራል ቴክኒክና እልጠና ኢንስቲትዩት ሀላፊዎች እና የክ/ከተማ የትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከመስከረም 30 ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሚሰጥ ቀደም ብሎ በትምህርት ሚኒስቴር የተገለጸ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፈተናውን ፦
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤
- ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤
- ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፣
- አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
- ፌደራል ቴክኒክና እልጠና ኢንስቲትዩት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ በውይይቱ ላይ ተገልጻል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅት እና አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ የተፈታኞችን መብትና ግዴታዎች አቅርበዋል።
#የተፈታኞች_መብቶች_የሆኑት፡-
➭ ከፈተና ጥያቄ ውጪ ማንኛውንም ያልተረዳውን ነገር ጠይቆ የመረዳት መብት አላቸው።
➭ በየኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ምግብ፣ የህክምና አገልግሎት፣ የማደሪያ ክፍል፣ ፍራሽና ትራስ የማግኘት መብት አላቸው።
➭ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን የቤተ መጽሐፍት፣ የመጸዳጃ ቤቶች፣ የሻወር፣ የካፍቴሪያዎች፣ የሚኒ ሱፐር ማርኬቶች፣ የተለያዩ ሱቆች፣ የመናፈሻና መዝናኛ አገልግሎቶችን የመጠቀም መብት አላቸው።
➭ የኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የጋራ የደህንነት ጥበቃ የማግኘት መብት አላቸው።
➭ በፈተና ሰዓት መፈተኛ ክፍል ገብቶ ብርሃናማ የመፈተኛ ቦታ፣ ወንበር፣ መጻፊያ ጠረጴዛ የማግኘት መብት አላቸው።
➭ ፈተና ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀድሞ ስለፈተናው ገለጻ (ኦሬንቴሽን) የማግኘት መብት አላቸው።
#የተፈታኞች_ግዴታ_የሆኑት፡-
➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከልም ይሁን መፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ የመገኘት ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ የትምህርት ቤት #ወይም የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊትና ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባቱ በፊት ሙሉ አካላዊ ፍተሻ የመፈተሽ ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢና በመፈተኛ ክፍል የተከለከሉ ቁሳቁሶችን/ዕቃዎችን መያዝ የለበትም።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ ይዞ መገኘት አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብን የማክበር ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከል ውስጥና በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የፈተና አስፈጻሚዎች የፈተና አስተዳደር ሥራን ውጤታማ ለማድረግና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የሚያደርጉትን ጥረት የመተባበር ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከመጀመሩ በፊት መፈተኛ ክፍል የመገኘት ግዴታ አለበት።
➤ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ለፈታኙ የማሰረከብ ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ አንሶላ፣ ብርድልብስና የትራስ ጨርቅ ይዞ የመምጣት ግዴታ አለበት።
➤ #ዩኒፎርም ለብሶ መገኘት አለበት።
#ለተፈታኞች_የተፈቀዱ_ነገሮች ፦
➣ አዲስ ወይም ቀድሞ ለመማር እና ለማጥናት ሲጠቀሙበት የነበሩ ማስተወሻ ደብተር ፣ የትምህርት መጽሐፍ፣ መንፈሳዊ/ኃይማኖታዊ መጽሐፍት፣ ባዶ ወረቀት
➣ ደረቅ ምግቦች ወይም ሰንዱች ምግቦች (ጩኮ፣ በሶ፣ ዳቦ ቆሎ፣ ቆሎ….)
➣ ገንዘብ (ብር)
➣ የልብስ ወይም የእጅ ቦርሳ፣ የግል ልብስ፣ ጫማ
➣ የግል ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ (ሳሙና፣ ሞዴስ፣ የጥርስ ብሩሽ፣ የጥርስ ሳሙና፣ የገላ ማድረቂያ ፎጣ፣ ሶፍት፣ ሻምፖ፣ ኮንዲሽነር፣ ሎሽን፣ ቻፕስቲክ፣ የጸጉር ቅባት፣ የፊት ቅባት)
#ለተፈታኞች_የተከለከሉ_ነገሮች ፦
⮕ ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውንም ዓይነት ስለት እና ሹልነት ያላቸውን ብረታ ብረቶችና ጠንካራ ፕላስትኮች ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው።
⮕ ማንኛውም ድምጽ የሚቀዳ፣ ፎቶ የሚያነሳ፣ ቪዲዮ የሚቀርጽ፣ ከቴሌ መስመርም ሆነ ከቴሌ መስመር ውጭ መልዕክት በዲጂታል መንገድ የሚሰጥ ወይም የሚቀበል የግል ዕቃ/መሳሪያ /ቴክኖሎጂ ውጤት፣ ስልክ፣ አይ-ፓድ፣ ታብሌት፣ ኮምፕዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ሰዓት፣ ማጂክ ብዕር/እስክሪብቶ፣ ማጂክ ኮት/ጃኬት እና ሌሎች ማንኛቸውም ፎቶ፣ ምስል እና ድምጽ የሚቀርጹ የኤሌክትሮኖክስ መሣሪያዎችን በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ ዙሪያ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት የግል ፍላሽ ዲስክ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ሲዲ፣ ሚሞሪ፣ ሚሞሪ ሪደር፣ ኦ-ቲጂ ኮንቨርተርና መሰል ዕቃዎችን ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውም አደንዛዥ እጾች (ጫት፣ ሲጋራ፣ በሓኪም ማዘዣ የሌለው መድኃኒት (በሽሮፕም ይሁን በታብሌት፣ ህክምና መስጫ መርፌ)) መያዝ ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውም ዓይነት የአልኮል መጠጥ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውም ዓይነት የአንገት ሐብል፣ የጸጉር ጌጥ፣ የጆሮ ጌጥ፣ የጣት ቀለበት፣ የእጅ አንባር፣ አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡ (ከልሙጥ የጋብቻ ቀለበት በስተቀረ)
⮕ ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል መግባት እና ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ከፈተና ክፍል መውጣት የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ይዞ መውጣት ተከለከለ ነው፡፡
⮕ በፈተና ሰዓት በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ማስቲካ መያዝም ሆነ መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በግልም ሆነ በቡድን መጮህ ወይም በጣም ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት የተከለከለ ነው፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 49,203 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ የተመዘገቡ ሲሆን ፈተናው ከመስከረም 30 ጀምሮ በቅድሚያ የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች ተፈትነው ሲጨርሱ የናቹራል ሳይንስ ተማሪዎች ቀጥለው ይፈተናሉ ፤ ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ወቅት የምግብና የመኝታ አገልግሎቶችን በየተቋማቱ ያገኛሉ።
(የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ)
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ኮማንድ ፖስት በፈተናው ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።
በውይይቱ ፦
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ፣
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኔጅመንት አባላት ፣
• የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣
• የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፣
• የኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣
• የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
• የፌደራል ቴክኒክና እልጠና ኢንስቲትዩት ሀላፊዎች እና የክ/ከተማ የትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከመስከረም 30 ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሚሰጥ ቀደም ብሎ በትምህርት ሚኒስቴር የተገለጸ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፈተናውን ፦
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤
- ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤
- ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፣
- አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
- ፌደራል ቴክኒክና እልጠና ኢንስቲትዩት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ በውይይቱ ላይ ተገልጻል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅት እና አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ የተፈታኞችን መብትና ግዴታዎች አቅርበዋል።
#የተፈታኞች_መብቶች_የሆኑት፡-
➭ ከፈተና ጥያቄ ውጪ ማንኛውንም ያልተረዳውን ነገር ጠይቆ የመረዳት መብት አላቸው።
➭ በየኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ምግብ፣ የህክምና አገልግሎት፣ የማደሪያ ክፍል፣ ፍራሽና ትራስ የማግኘት መብት አላቸው።
➭ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን የቤተ መጽሐፍት፣ የመጸዳጃ ቤቶች፣ የሻወር፣ የካፍቴሪያዎች፣ የሚኒ ሱፐር ማርኬቶች፣ የተለያዩ ሱቆች፣ የመናፈሻና መዝናኛ አገልግሎቶችን የመጠቀም መብት አላቸው።
➭ የኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የጋራ የደህንነት ጥበቃ የማግኘት መብት አላቸው።
➭ በፈተና ሰዓት መፈተኛ ክፍል ገብቶ ብርሃናማ የመፈተኛ ቦታ፣ ወንበር፣ መጻፊያ ጠረጴዛ የማግኘት መብት አላቸው።
➭ ፈተና ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀድሞ ስለፈተናው ገለጻ (ኦሬንቴሽን) የማግኘት መብት አላቸው።
#የተፈታኞች_ግዴታ_የሆኑት፡-
➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከልም ይሁን መፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ የመገኘት ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ የትምህርት ቤት #ወይም የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊትና ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባቱ በፊት ሙሉ አካላዊ ፍተሻ የመፈተሽ ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢና በመፈተኛ ክፍል የተከለከሉ ቁሳቁሶችን/ዕቃዎችን መያዝ የለበትም።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ ይዞ መገኘት አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብን የማክበር ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከል ውስጥና በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የፈተና አስፈጻሚዎች የፈተና አስተዳደር ሥራን ውጤታማ ለማድረግና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የሚያደርጉትን ጥረት የመተባበር ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከመጀመሩ በፊት መፈተኛ ክፍል የመገኘት ግዴታ አለበት።
➤ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ለፈታኙ የማሰረከብ ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ አንሶላ፣ ብርድልብስና የትራስ ጨርቅ ይዞ የመምጣት ግዴታ አለበት።
➤ #ዩኒፎርም ለብሶ መገኘት አለበት።
#ለተፈታኞች_የተፈቀዱ_ነገሮች ፦
➣ አዲስ ወይም ቀድሞ ለመማር እና ለማጥናት ሲጠቀሙበት የነበሩ ማስተወሻ ደብተር ፣ የትምህርት መጽሐፍ፣ መንፈሳዊ/ኃይማኖታዊ መጽሐፍት፣ ባዶ ወረቀት
➣ ደረቅ ምግቦች ወይም ሰንዱች ምግቦች (ጩኮ፣ በሶ፣ ዳቦ ቆሎ፣ ቆሎ….)
➣ ገንዘብ (ብር)
➣ የልብስ ወይም የእጅ ቦርሳ፣ የግል ልብስ፣ ጫማ
➣ የግል ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ (ሳሙና፣ ሞዴስ፣ የጥርስ ብሩሽ፣ የጥርስ ሳሙና፣ የገላ ማድረቂያ ፎጣ፣ ሶፍት፣ ሻምፖ፣ ኮንዲሽነር፣ ሎሽን፣ ቻፕስቲክ፣ የጸጉር ቅባት፣ የፊት ቅባት)
#ለተፈታኞች_የተከለከሉ_ነገሮች ፦
⮕ ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውንም ዓይነት ስለት እና ሹልነት ያላቸውን ብረታ ብረቶችና ጠንካራ ፕላስትኮች ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው።
⮕ ማንኛውም ድምጽ የሚቀዳ፣ ፎቶ የሚያነሳ፣ ቪዲዮ የሚቀርጽ፣ ከቴሌ መስመርም ሆነ ከቴሌ መስመር ውጭ መልዕክት በዲጂታል መንገድ የሚሰጥ ወይም የሚቀበል የግል ዕቃ/መሳሪያ /ቴክኖሎጂ ውጤት፣ ስልክ፣ አይ-ፓድ፣ ታብሌት፣ ኮምፕዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ሰዓት፣ ማጂክ ብዕር/እስክሪብቶ፣ ማጂክ ኮት/ጃኬት እና ሌሎች ማንኛቸውም ፎቶ፣ ምስል እና ድምጽ የሚቀርጹ የኤሌክትሮኖክስ መሣሪያዎችን በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ ዙሪያ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት የግል ፍላሽ ዲስክ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ሲዲ፣ ሚሞሪ፣ ሚሞሪ ሪደር፣ ኦ-ቲጂ ኮንቨርተርና መሰል ዕቃዎችን ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውም አደንዛዥ እጾች (ጫት፣ ሲጋራ፣ በሓኪም ማዘዣ የሌለው መድኃኒት (በሽሮፕም ይሁን በታብሌት፣ ህክምና መስጫ መርፌ)) መያዝ ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውም ዓይነት የአልኮል መጠጥ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውም ዓይነት የአንገት ሐብል፣ የጸጉር ጌጥ፣ የጆሮ ጌጥ፣ የጣት ቀለበት፣ የእጅ አንባር፣ አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡ (ከልሙጥ የጋብቻ ቀለበት በስተቀረ)
⮕ ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል መግባት እና ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ከፈተና ክፍል መውጣት የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ይዞ መውጣት ተከለከለ ነው፡፡
⮕ በፈተና ሰዓት በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ማስቲካ መያዝም ሆነ መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በግልም ሆነ በቡድን መጮህ ወይም በጣም ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት የተከለከለ ነው፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 49,203 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ የተመዘገቡ ሲሆን ፈተናው ከመስከረም 30 ጀምሮ በቅድሚያ የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች ተፈትነው ሲጨርሱ የናቹራል ሳይንስ ተማሪዎች ቀጥለው ይፈተናሉ ፤ ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ወቅት የምግብና የመኝታ አገልግሎቶችን በየተቋማቱ ያገኛሉ።
(የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#መልዕክት የ " መስቀል ደመራ በዓል " አከባበርን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ መልዕክት ፦ - ሁከት ቀስሰቃሽ መልዕክቶችን በቲሸረሰቶች ላይም ሆነ በባነሮች ላይ በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ ይዞ መገኘት በፍፁም አይፈቀድም። - በበዓሉ ላይ ህገ መንግስቱ የደነገገውን የኢትዮጵያን የፌዴራል ሰንደቅ ዓላማ #ወይም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የፀደቀውን የቤተክርስቲያን…
ፎቶ / ቪድዮ : የመስቀል ደመራ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን (አዲስ አበባ - መስቀል አደባባይ)
ፎቶ / ቪድዮ - የቲክቫህ አዲስ አበባ አባላት
በተለያዩ ከተሞች የነበረውን የበዓሉን አከባበር ፎቶዎች በ @tikvahethmagazine ላይ ያገኛሉ።
@tikvahethiopia
ፎቶ / ቪድዮ - የቲክቫህ አዲስ አበባ አባላት
በተለያዩ ከተሞች የነበረውን የበዓሉን አከባበር ፎቶዎች በ @tikvahethmagazine ላይ ያገኛሉ።
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ፤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በጽዮን ማርያም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን
ፎቶ : ጽዮን ማርያም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን
@tikvahethiopia @tikvahethmagazine
ፎቶ : ጽዮን ማርያም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን
@tikvahethiopia @tikvahethmagazine
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ / ቪድዮ : የመስቀል ደመራ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን (አዲስ አበባ - መስቀል አደባባይ) ፎቶ / ቪድዮ - የቲክቫህ አዲስ አበባ አባላት በተለያዩ ከተሞች የነበረውን የበዓሉን አከባበር ፎቶዎች በ @tikvahethmagazine ላይ ያገኛሉ። @tikvahethiopia
" በዓሉ በሰላም ተከብሮ ተጠናቋል "
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በዓል ሃይማኖታዊ ስርዓቱን ፣ ትውፊቱንና እሴቱን ጠብቆ ባማረና በደመቀ ሁኔታ በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን አሳውቋል።
ከተማ አስተዳደሩ ለአዲስ አበባ ህዝብ ፣ ለእምነት አባቶች ፣ ምእመናን ፣ ወጣቶች፣ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች፣ የፀጥታ ሃይሎች፣ ለከተማው የሰላም ሰራዊት አባላት እና የደንብ ማስከበር አገልግሎት ምስጋና አቅርቧል።
Video : Hena (Tikvah Family)
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በዓል ሃይማኖታዊ ስርዓቱን ፣ ትውፊቱንና እሴቱን ጠብቆ ባማረና በደመቀ ሁኔታ በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን አሳውቋል።
ከተማ አስተዳደሩ ለአዲስ አበባ ህዝብ ፣ ለእምነት አባቶች ፣ ምእመናን ፣ ወጣቶች፣ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች፣ የፀጥታ ሃይሎች፣ ለከተማው የሰላም ሰራዊት አባላት እና የደንብ ማስከበር አገልግሎት ምስጋና አቅርቧል።
Video : Hena (Tikvah Family)
@tikvahethiopia
ቅዱስ ፓትርያርኩ ምን አሉ ?
" አለመግባባትን በዕርቅ ዘግቶ በፍቅርና በሰላም ከመኖር የተሻለ ሌላ አማራጭ የለም። " ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ገለጹ፡፡
ቅዱስነታቸው የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ በተከበረበት ወቅት ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት " የምናከናውነው ተግባር በሙሉ የእግዚአብሔርን ፈቃድና የመስቀሉን ምሥጢር የጠበቀ ሊሆን ይገባል " ብለዋል።
ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ ፍጥረታት በሙሉ እርስ በእርስ ሲጣሉና ሲተረማመሱ ማየት ቀዋሚ ትዕይንት ሆኖ እንደሚገኝ የገለጹት ቅዱስነታቸው ምንም እንኳ ችግሩ በፍጥረታት ሁሉ ላይ ሰፍኖ ቢገኝም መፍትሔ የሌለው ችግር ግን አይደለም ብለዋል።
" በየጊዜው በተግባር የተፈተነ ጠንካራና የማያወላውል መፍትሔው ይቅርታና ዕርቅ ነው " ያሉት ቅዱስ ፓትርፓርኩ " የሰው ልጅ አለመግባባትን በዕርቅ ዘግቶ ሰላምንና አንድነትን መሥርቶ በመከባበርና በመተሳሰብ፣ በመተዛዘንና በመተጋገዝ፣ በመረዳዳትና በመቻቻል፣ በፍቅርና በሰላም ከመኖር የተሻለ ሌላ አማራጭ የለውም ብለዋል። "
ይህም እውን ሊሆን የሚችለው፥ ለወንድሜና ለእኅቴ የሚል ቅን ሀሳብና ለሁላችንም የሚል የጋራ አስተሳሰብ በሰዎች ልቡና የበላይነት ሲያገኝ ነው ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ቅዱስ ፓትርያርኩ " እግዚአብሔር ግጭቱን አስወግዶ ሰላሙን ፍቅሩን፣ አንድነቱንና ስምምነቱን እንዲያመጣልን፤ እኛም የዕርቅና የይቅርታ ሰዎች ሆነን እንገኝ ዘንድ በርትተን እንፀልይ " ሲሉ አባታዊና መንፈሳዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ምንጭ፦ telegra.ph/EOTC-09-26
@tikvahethiopia
" አለመግባባትን በዕርቅ ዘግቶ በፍቅርና በሰላም ከመኖር የተሻለ ሌላ አማራጭ የለም። " ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ገለጹ፡፡
ቅዱስነታቸው የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ በተከበረበት ወቅት ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት " የምናከናውነው ተግባር በሙሉ የእግዚአብሔርን ፈቃድና የመስቀሉን ምሥጢር የጠበቀ ሊሆን ይገባል " ብለዋል።
ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ ፍጥረታት በሙሉ እርስ በእርስ ሲጣሉና ሲተረማመሱ ማየት ቀዋሚ ትዕይንት ሆኖ እንደሚገኝ የገለጹት ቅዱስነታቸው ምንም እንኳ ችግሩ በፍጥረታት ሁሉ ላይ ሰፍኖ ቢገኝም መፍትሔ የሌለው ችግር ግን አይደለም ብለዋል።
" በየጊዜው በተግባር የተፈተነ ጠንካራና የማያወላውል መፍትሔው ይቅርታና ዕርቅ ነው " ያሉት ቅዱስ ፓትርፓርኩ " የሰው ልጅ አለመግባባትን በዕርቅ ዘግቶ ሰላምንና አንድነትን መሥርቶ በመከባበርና በመተሳሰብ፣ በመተዛዘንና በመተጋገዝ፣ በመረዳዳትና በመቻቻል፣ በፍቅርና በሰላም ከመኖር የተሻለ ሌላ አማራጭ የለውም ብለዋል። "
ይህም እውን ሊሆን የሚችለው፥ ለወንድሜና ለእኅቴ የሚል ቅን ሀሳብና ለሁላችንም የሚል የጋራ አስተሳሰብ በሰዎች ልቡና የበላይነት ሲያገኝ ነው ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ቅዱስ ፓትርያርኩ " እግዚአብሔር ግጭቱን አስወግዶ ሰላሙን ፍቅሩን፣ አንድነቱንና ስምምነቱን እንዲያመጣልን፤ እኛም የዕርቅና የይቅርታ ሰዎች ሆነን እንገኝ ዘንድ በርትተን እንፀልይ " ሲሉ አባታዊና መንፈሳዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ምንጭ፦ telegra.ph/EOTC-09-26
@tikvahethiopia
#DrAlQaradawi
የሙስሊም ምሁራን ፌዴሬሽን መስራችና ፌዴሬሽኑን ለ14 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት የመሩት እውቁ የእስልምና ምሁር ግብፃዊ ዶክተር ሼክ ዩሱፍ አል ቃራዳዊ በ96 ዓመታቸው ህይወታቸው አልፏል።
ህልፈታቸውን ልጃቸው አብዱል ራህማን ዩሱፍ አል ቃራዳዊ አረጋግጠዋል።
ዶ/ር አልቃራዳዊ ህይወታቸው ያለፈው ኳታር፤ ዶሃ ውስጥ ነው።
እኤአ 2004 የተቋቋመውን (እሳቸው መስራች ነበሩ) ዓለም አቀፉ የሙስሊም ምሁራን ፌዴሬሽን ከተቋቋመበተ ጊዜ አንስቶ ለ14 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት መርተዋል።
ዶ/ር አልቃራዳዊ ከሙስሊም ወንድማማቾች ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሲሆን የኳታር ዜግነት ተሰጥቷቸው ህይወታቸው እስክታለፍ ድረስ ኑሯቸውን በኳታር፣ዶሃ አድርገው ነበር።
አልቃራዳዊ በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ወቅት በግብፅ በ1926 ነበር የተወለዱት።
ገና በለጋ እድሜያቸው እስላማዊ ትምህርትን መከታተል የጀመሩት አልቃራዳዊ በፀረ ቅኝ አገዛዛ ላይ እንቅስቃሴ ያደርጉ ነበር። በ1950 ዎቹ ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴና ከሙስሊም ወንድማማቾች ንቅናቄ ጋር በተገናኘ ብዙ ጊዜ ለእስር ተዳርገው ነበር።
ከ120 በላይ መፅሀፍትን ያሳተሙት ዶ/ር አል ቃራዳዊ ለእስልምና ባበረከቱት አስተዋፆ 8 ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን መሸለም እንደቻሉ ተገልጿል።
ዶ/ር አል ቃራዳዊ በክፈለ ዘመኑ በጣም ታዋቂ ከሆኑ የእስልምና ሊቃውንት አንዱ እንደነበሩ ተዘግቧል።
በህይወት በነበሩበት ወቅት በተለያዩ ሚዲያዎች በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ አመለካከታቸውን ሲያጋሩ የነበረ ሲሆን በሚያነሷቸው ሀሳቦች የሚደግፏቸው እንዳሉ ሁሉ ሀሳባቸውን የሚቃወሙም ነበሩ።
የዶ/ር አልቃራዳዊን ህልፈት ተከትሎ ፤ የተርክዬ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለልጃቸው አብዱል ራህማን በመደወል የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው አፅናንተዋል።
@tikvahethiopia
የሙስሊም ምሁራን ፌዴሬሽን መስራችና ፌዴሬሽኑን ለ14 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት የመሩት እውቁ የእስልምና ምሁር ግብፃዊ ዶክተር ሼክ ዩሱፍ አል ቃራዳዊ በ96 ዓመታቸው ህይወታቸው አልፏል።
ህልፈታቸውን ልጃቸው አብዱል ራህማን ዩሱፍ አል ቃራዳዊ አረጋግጠዋል።
ዶ/ር አልቃራዳዊ ህይወታቸው ያለፈው ኳታር፤ ዶሃ ውስጥ ነው።
እኤአ 2004 የተቋቋመውን (እሳቸው መስራች ነበሩ) ዓለም አቀፉ የሙስሊም ምሁራን ፌዴሬሽን ከተቋቋመበተ ጊዜ አንስቶ ለ14 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት መርተዋል።
ዶ/ር አልቃራዳዊ ከሙስሊም ወንድማማቾች ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሲሆን የኳታር ዜግነት ተሰጥቷቸው ህይወታቸው እስክታለፍ ድረስ ኑሯቸውን በኳታር፣ዶሃ አድርገው ነበር።
አልቃራዳዊ በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ወቅት በግብፅ በ1926 ነበር የተወለዱት።
ገና በለጋ እድሜያቸው እስላማዊ ትምህርትን መከታተል የጀመሩት አልቃራዳዊ በፀረ ቅኝ አገዛዛ ላይ እንቅስቃሴ ያደርጉ ነበር። በ1950 ዎቹ ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴና ከሙስሊም ወንድማማቾች ንቅናቄ ጋር በተገናኘ ብዙ ጊዜ ለእስር ተዳርገው ነበር።
ከ120 በላይ መፅሀፍትን ያሳተሙት ዶ/ር አል ቃራዳዊ ለእስልምና ባበረከቱት አስተዋፆ 8 ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን መሸለም እንደቻሉ ተገልጿል።
ዶ/ር አል ቃራዳዊ በክፈለ ዘመኑ በጣም ታዋቂ ከሆኑ የእስልምና ሊቃውንት አንዱ እንደነበሩ ተዘግቧል።
በህይወት በነበሩበት ወቅት በተለያዩ ሚዲያዎች በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ አመለካከታቸውን ሲያጋሩ የነበረ ሲሆን በሚያነሷቸው ሀሳቦች የሚደግፏቸው እንዳሉ ሁሉ ሀሳባቸውን የሚቃወሙም ነበሩ።
የዶ/ር አልቃራዳዊን ህልፈት ተከትሎ ፤ የተርክዬ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለልጃቸው አብዱል ራህማን በመደወል የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው አፅናንተዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#EHRC
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጳጉሜ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል፣ ሆሮጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በሲቪል ሰዎች ላይ የደረሰን ግድያ አስመልከቶ ባወጣው መግለጫ በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ተጨማሪ የጸጥታ ሥጋቶች በመኖራቸው በታጠቁ ቡድኖች በሲቪል ሰዎች ላይ ብሔርን መሰረት ያደረጉ ተጨማሪ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ለመከላከል በትኩረት እንዲሠራ ማሳሰቡን ይታወሳል።
ኢሰመኮ በአካባቢው ሲቪል ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች አሁንም ተሰፋፍተው መቀጠላቸው ገልጾ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን አስገንዝቧል።
በዞኑ በአሙሩ፣ በሆሮ ቡልቅ እና በጃርደጋ ጃርቴ ወረዳዎች ከነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት ሦስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሽኔ)፣ በአማራ ኢመደበኛ ታጣቂ ኃይሎች እና ግለሰቦች በተከታታይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ከ100 በላይ ሲቪል ሰዎች የተገደሉ መሆኑ ታወቋል ሲል ኢስመኮ ገልጿል።
እንዲሁም የግል ንበረት እና የቁም ከብቶች መዘረፋቸውን ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ያለበቂ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የሚገኙ መሆኑን ኮሚሽኑ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ ከአካባቢው የፍትሕና የአስተዳደር አካላት እንዲሁም በአካባቢው ከሚንቀሳቀሱ የእርዳታ ድርጅቶች ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች እና ማስረጃዎች ያሳያሉ ብሏል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ " የክልሉ አና የፌዴራል መንግሥታት በአካባቢው ብሔርን መሰረት አድርገው የሚፈጸመው ጥቃቶችን ለመከላከል በመወሰድ ላይ የሚገኙትን እርምጃ ችግሩን በሚመጥን ደረጃ በማሳደግ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል" ሲሉ በድጋሚ አሳስበዋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጳጉሜ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል፣ ሆሮጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በሲቪል ሰዎች ላይ የደረሰን ግድያ አስመልከቶ ባወጣው መግለጫ በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ተጨማሪ የጸጥታ ሥጋቶች በመኖራቸው በታጠቁ ቡድኖች በሲቪል ሰዎች ላይ ብሔርን መሰረት ያደረጉ ተጨማሪ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ለመከላከል በትኩረት እንዲሠራ ማሳሰቡን ይታወሳል።
ኢሰመኮ በአካባቢው ሲቪል ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች አሁንም ተሰፋፍተው መቀጠላቸው ገልጾ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን አስገንዝቧል።
በዞኑ በአሙሩ፣ በሆሮ ቡልቅ እና በጃርደጋ ጃርቴ ወረዳዎች ከነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት ሦስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሽኔ)፣ በአማራ ኢመደበኛ ታጣቂ ኃይሎች እና ግለሰቦች በተከታታይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ከ100 በላይ ሲቪል ሰዎች የተገደሉ መሆኑ ታወቋል ሲል ኢስመኮ ገልጿል።
እንዲሁም የግል ንበረት እና የቁም ከብቶች መዘረፋቸውን ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ያለበቂ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የሚገኙ መሆኑን ኮሚሽኑ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ ከአካባቢው የፍትሕና የአስተዳደር አካላት እንዲሁም በአካባቢው ከሚንቀሳቀሱ የእርዳታ ድርጅቶች ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች እና ማስረጃዎች ያሳያሉ ብሏል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ " የክልሉ አና የፌዴራል መንግሥታት በአካባቢው ብሔርን መሰረት አድርገው የሚፈጸመው ጥቃቶችን ለመከላከል በመወሰድ ላይ የሚገኙትን እርምጃ ችግሩን በሚመጥን ደረጃ በማሳደግ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል" ሲሉ በድጋሚ አሳስበዋል።
@tikvahethiopia