#ውብ_አረቢያን_መጅሊስ
ከአውሮፓና ከእስያ በሚመረቱ ጥሬ እቃ በብቁ ባለሞያ በዘመነ ማሽን ውብ አረቢያን መጅሊስ የሚያመርታቸውን ውብ እና ማራኪ የሆኑ መጅሊሶቻችን እና ሶፋዎችን እንካቹ ስንል 👉 በ9 ቅርጫፎቻችን ስንጠበቅዎ በታላቅ ደስታ ነው 0910222244 / 0954111133 / 0954111100
ተጨማሪ ፎቶ ለመምረጥ ሊንኩን የጫኑት https://yangx.top/wubeare
ከአውሮፓና ከእስያ በሚመረቱ ጥሬ እቃ በብቁ ባለሞያ በዘመነ ማሽን ውብ አረቢያን መጅሊስ የሚያመርታቸውን ውብ እና ማራኪ የሆኑ መጅሊሶቻችን እና ሶፋዎችን እንካቹ ስንል 👉 በ9 ቅርጫፎቻችን ስንጠበቅዎ በታላቅ ደስታ ነው 0910222244 / 0954111133 / 0954111100
ተጨማሪ ፎቶ ለመምረጥ ሊንኩን የጫኑት https://yangx.top/wubeare
TIKVAH-ETHIOPIA
#Balderas የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ፕ/ት አቶ እስክንድር ነጋ ፤ በመንግስት ጫና በአባልነትም ሆነ በአመራርነት መስራት የማልችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸው አሳወቁ። አቶ እስክንድር ሀምሌ 16/2014 ዓ/ም ካሉበት ቦታ ሆነው ፃፉት በተባለውና በፓርቲው የፌስቡክ ገፅ ላይ…
#BALDERAS
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ባለፈው ሣምንት ከፕሬዝደንትነታቸው የለቀቁት አቶ እስክንድር ነጋ አሁንም የት እንዳሉ እንደማያውቅ ገልጿል።
የፓርቲው ኃላፊዎች ዛሬ ሰኞ በአዲስ አበባ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚህም ከሐምሌ 16 ቀን 2014 ጀምሮ አቶ እስክንድር ከባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ጽህፈት ቤት እና ከሥራ አስፈጻሚው ጋር ያላቸው ግንኙነት ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ገልጸዋል።
የፓርቲው ምክትል ፕሬዝደንት አቶ አምኃ ዳኘው ከተናገሩት ፦
" አቶ እስክንድር ምንም የነገረን ነገር ባለመኖሩ፤ የት እንደሔደ እና በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ባልታወቀበት ሁኔታ አድማጭን የሚያረካ መልስ መስጠት የሚቻልበት ሁኔታ አልነበረም።
በአሜሪካ ሀገር የሚገኙት የአቶ እስክንድር ባለቤት አልደነገጡም ፤ ከፓርቲው ሆነ በውጭ አገር ከሚገኘው የድጋፍ ኮሚቴ ማብራሪያ አልጠየቁም። በዚህ ምክንያት የመታፈን አደጋ እንዳልደረሰበት ገምተናል።
አቶ እስክንድር ያሉበትን ሁኔታ ያሳውቁናል ብለን በመጠባበቅ ላይ ሳለን ነው በአሜሪካ ከሚገኘው የድጋፍ ኮሚቴ በኩል የመልቀቂያ ደብዳቤው ይፋ የሆነው። "
የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የጽ/ቤቱ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ቀለብ ሥዩም ፦
" ከሐምሌ 16 ቀን 2014 ወዲህ አቶ እስክንድርን በስልክም ይሁን በአካል አግኝተናቸው አናውቅም።
መንግሥት አቶ እስክንድርን እንዳላፈናቸው እና እንዳላሰራቸው ፓርቲው ያምናል።
ከቤተሰቦቻቸው ደህና መሆናቸው ተገልጾልናል።
ይሁንና አቶ እስክንድር ከአሜሪካ ከተመለሱ በኋላ የተለያዩ የደህንነት መኪናዎች እና የተለያዩ ሰዎች ይከታተሏቸው ነበር። በዚህም ውጥረት እና ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ለመሆናቸው ምልክቶች እንደነበሩ እናውቃለን። "
(ከጀርመኝ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ)
@tikvahethiopia
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ባለፈው ሣምንት ከፕሬዝደንትነታቸው የለቀቁት አቶ እስክንድር ነጋ አሁንም የት እንዳሉ እንደማያውቅ ገልጿል።
የፓርቲው ኃላፊዎች ዛሬ ሰኞ በአዲስ አበባ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚህም ከሐምሌ 16 ቀን 2014 ጀምሮ አቶ እስክንድር ከባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ጽህፈት ቤት እና ከሥራ አስፈጻሚው ጋር ያላቸው ግንኙነት ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ገልጸዋል።
የፓርቲው ምክትል ፕሬዝደንት አቶ አምኃ ዳኘው ከተናገሩት ፦
" አቶ እስክንድር ምንም የነገረን ነገር ባለመኖሩ፤ የት እንደሔደ እና በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ባልታወቀበት ሁኔታ አድማጭን የሚያረካ መልስ መስጠት የሚቻልበት ሁኔታ አልነበረም።
በአሜሪካ ሀገር የሚገኙት የአቶ እስክንድር ባለቤት አልደነገጡም ፤ ከፓርቲው ሆነ በውጭ አገር ከሚገኘው የድጋፍ ኮሚቴ ማብራሪያ አልጠየቁም። በዚህ ምክንያት የመታፈን አደጋ እንዳልደረሰበት ገምተናል።
አቶ እስክንድር ያሉበትን ሁኔታ ያሳውቁናል ብለን በመጠባበቅ ላይ ሳለን ነው በአሜሪካ ከሚገኘው የድጋፍ ኮሚቴ በኩል የመልቀቂያ ደብዳቤው ይፋ የሆነው። "
የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የጽ/ቤቱ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ቀለብ ሥዩም ፦
" ከሐምሌ 16 ቀን 2014 ወዲህ አቶ እስክንድርን በስልክም ይሁን በአካል አግኝተናቸው አናውቅም።
መንግሥት አቶ እስክንድርን እንዳላፈናቸው እና እንዳላሰራቸው ፓርቲው ያምናል።
ከቤተሰቦቻቸው ደህና መሆናቸው ተገልጾልናል።
ይሁንና አቶ እስክንድር ከአሜሪካ ከተመለሱ በኋላ የተለያዩ የደህንነት መኪናዎች እና የተለያዩ ሰዎች ይከታተሏቸው ነበር። በዚህም ውጥረት እና ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ለመሆናቸው ምልክቶች እንደነበሩ እናውቃለን። "
(ከጀርመኝ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#የትምህርት_እድል ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ8ኛ ወደ 9ኛ ክፍል ያለፉ ተማሪዎች አወዳድሮ ለማስተማር እንደሚፈልግ ገልጿል። የምዝገባ መስፈርቶቹ ከታች የተዘረዘሩት ሲሆኑ መስፈርቶቹን የምታሟሉ ተማሪዎች ተመዝግባችሁ መወዳደር ትችላላችሁ። ሀ/ የውድድር መስፈርቶች 1ኛ. ክልላዊ የ8ኛ ክፍል አማካይ ውጤት (average) (ጥሬ ማርክ) ለወንድ…
#የተሻሻለ
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ8ኛ ወደ 9ኛ ክፍል ላለፉ ተማሪዎች አውጥቶ የነበረውን የትምህርት ዕድል ማስታወቂያ አሻሻለ።
ተቋሙ ማሻሻያውን ያደረገው የትምህርት ቢሮ ለምዝገባ የመቁረጫ ነጥብ በአዲስ መልኩ ስላሳወቀው መሆኑን ገልጿል።
በዚህም መሰረት የምዝገባ መስፈርቶች የሚከተሉት ናቸው።
ሀ/ የውድድር መስፈርቶች
1ኛ. ክልላዊ የ8ኛ ክፍል አማካይ ውጤት (average) (ጥሬ ማርክ) ለወንድ 80 እና ከዛ በላይ ለሴት 75 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገበ / ያስመዘገበች
2ኛ. ለተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርቶች ከፍተኛ ፍላጎት ያለው/ያላት 10ኛ ክፍል ካጠናቀቀ በኋላ በተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ መቀጠል የሚፈልግ/የምትፈልግ
ለ. ዝርዝር መረጃ
• የምዝገባ ቀን ከ10/12/14 - 16/12/14
• የምዘገባ ቦታ-በሳይንስ ሼርድ ካምፓስ፡ በቀድሞው ቀዳማዊ ምኒልክ የመጀመሪያ ት/ቤት፡፡ ከአራዳ ክ/ከተማ ፊት ለፊት
• የምዝገባ ሰዓት ከረፋዱ 3፡00 - ቀኑ 10:00
ሐ/ ተወዳዳሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ
• ክልላዊ የ8ኛ ክፍል ውጤት የሚገልጽ ዋናውንና 1 ፎቶ ኮፒ
• አንድ ክላሰር
መ. ተጨማሪ መረጃ
• የጽሑፍ ፈተና የሚሰጥበት ቀን 18/12/14 ከቀኑ 7፡30 - 10፡30
ት/ቤቱ ጎበዝ ተማሪዎች በማፍራት በሀገሪቱ ውስጥ አሉ ከሚባሉና በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናዎችም እጅግ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ያፈራ ት/ቤት ነው።
ለአብነት በ2013 ዓ/ም ብሄራዊ ፈተና 78 ተማሪዎችን አስፈትኖ 42 ተማሪዎች ከ600 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።
በኢትዮጵያ ትልቁ ውጤት የመጣውም 659 ከዚሁ ት/ቤት ነበር።
@tikvahethiopia
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ8ኛ ወደ 9ኛ ክፍል ላለፉ ተማሪዎች አውጥቶ የነበረውን የትምህርት ዕድል ማስታወቂያ አሻሻለ።
ተቋሙ ማሻሻያውን ያደረገው የትምህርት ቢሮ ለምዝገባ የመቁረጫ ነጥብ በአዲስ መልኩ ስላሳወቀው መሆኑን ገልጿል።
በዚህም መሰረት የምዝገባ መስፈርቶች የሚከተሉት ናቸው።
ሀ/ የውድድር መስፈርቶች
1ኛ. ክልላዊ የ8ኛ ክፍል አማካይ ውጤት (average) (ጥሬ ማርክ) ለወንድ 80 እና ከዛ በላይ ለሴት 75 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገበ / ያስመዘገበች
2ኛ. ለተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርቶች ከፍተኛ ፍላጎት ያለው/ያላት 10ኛ ክፍል ካጠናቀቀ በኋላ በተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ መቀጠል የሚፈልግ/የምትፈልግ
ለ. ዝርዝር መረጃ
• የምዝገባ ቀን ከ10/12/14 - 16/12/14
• የምዘገባ ቦታ-በሳይንስ ሼርድ ካምፓስ፡ በቀድሞው ቀዳማዊ ምኒልክ የመጀመሪያ ት/ቤት፡፡ ከአራዳ ክ/ከተማ ፊት ለፊት
• የምዝገባ ሰዓት ከረፋዱ 3፡00 - ቀኑ 10:00
ሐ/ ተወዳዳሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ
• ክልላዊ የ8ኛ ክፍል ውጤት የሚገልጽ ዋናውንና 1 ፎቶ ኮፒ
• አንድ ክላሰር
መ. ተጨማሪ መረጃ
• የጽሑፍ ፈተና የሚሰጥበት ቀን 18/12/14 ከቀኑ 7፡30 - 10፡30
ት/ቤቱ ጎበዝ ተማሪዎች በማፍራት በሀገሪቱ ውስጥ አሉ ከሚባሉና በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናዎችም እጅግ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ያፈራ ት/ቤት ነው።
ለአብነት በ2013 ዓ/ም ብሄራዊ ፈተና 78 ተማሪዎችን አስፈትኖ 42 ተማሪዎች ከ600 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።
በኢትዮጵያ ትልቁ ውጤት የመጣውም 659 ከዚሁ ት/ቤት ነበር።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኬንያ
የኬንያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ እስካሁን ድረስ ይፋ አልሆነም።
ከሰዓታት በፊት ይፋ ይደረጋል ቢባልም እስካሁን ኮሚሽኑ የምርጫውን ውጤት ሊያሳውቅ አልቻልም።
ውጤት በሚገለፅበት ቦማስ የድምፅ ቆጠራ ማዕከልም እስከ መደባደብ የደረሰ አለመግባባት ተፈጥሯል።
በጎረቤታችን ኬንያ እየሆነ ስላለው ጉዳይ ተከታትለን እናሳውቃለን።
@tikvahethiopia
የኬንያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ እስካሁን ድረስ ይፋ አልሆነም።
ከሰዓታት በፊት ይፋ ይደረጋል ቢባልም እስካሁን ኮሚሽኑ የምርጫውን ውጤት ሊያሳውቅ አልቻልም።
ውጤት በሚገለፅበት ቦማስ የድምፅ ቆጠራ ማዕከልም እስከ መደባደብ የደረሰ አለመግባባት ተፈጥሯል።
በጎረቤታችን ኬንያ እየሆነ ስላለው ጉዳይ ተከታትለን እናሳውቃለን።
@tikvahethiopia
#Sport
ተጋጣሚውን 9 ለ 0 ያሸነፈው የኢትዮጵያ ክለብ !
ከደቂቃዎች በፊት በተጠናቀቀው በ #CECAFA ሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ የኢትዮጵያው ንግድ ባንክ ቡድን ተጋጣሚውን ዋሪየርስ ኩዊን በሰፊ የግብ ልዩነት 9 ለ 0 አሸንፏል።
መዲና አዎል 4 ግቦችን እንዲሁም ሎዛ አበራ 5 ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል ።
More : @tikvahethsport
ተጋጣሚውን 9 ለ 0 ያሸነፈው የኢትዮጵያ ክለብ !
ከደቂቃዎች በፊት በተጠናቀቀው በ #CECAFA ሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ የኢትዮጵያው ንግድ ባንክ ቡድን ተጋጣሚውን ዋሪየርስ ኩዊን በሰፊ የግብ ልዩነት 9 ለ 0 አሸንፏል።
መዲና አዎል 4 ግቦችን እንዲሁም ሎዛ አበራ 5 ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል ።
More : @tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኬንያ የኬንያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ እስካሁን ድረስ ይፋ አልሆነም። ከሰዓታት በፊት ይፋ ይደረጋል ቢባልም እስካሁን ኮሚሽኑ የምርጫውን ውጤት ሊያሳውቅ አልቻልም። ውጤት በሚገለፅበት ቦማስ የድምፅ ቆጠራ ማዕከልም እስከ መደባደብ የደረሰ አለመግባባት ተፈጥሯል። በጎረቤታችን ኬንያ እየሆነ ስላለው ጉዳይ ተከታትለን እናሳውቃለን። @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ኬንያ
በኬንያ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ዛሬ ሰኞ ከሰዓት በኋላ ይፋ ይደረጋል ተብሎ እየተጠበቀ ባለበት ጊዜ አለመግባባት እና ውዝግብ ተፈጥሯል።
የፕሬዝዳንታዊ ምርጫውን ውጤት ያሳውቃሉ ተብለው በሚጠበቁት የኮሚሽኑ ባለሥልጣንት መካከል ክፍፍል መፈጠሩ ነው የተነገረው።
በዚህም 4 የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በይፋ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ውጤት ከሚነገርበት ማዕከል ውጪ መሃል ናይሮቢ በሚገኘው ሴሬና ሆቴል ውስጥ ሂደቱን ጥያቄ ላይ በሚጥል ሁኔታ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም ከ6ቱ ኮሚሽነሮች አራቱ በሰጡት መግለጫ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ውጤት አያያዝ “ግልጽነት የጎደለው በመሆኑ፣ ውጤቱን በኃላፊነት ለመውሰድ አንችልም” በማለት ገልጸዋል።
ውጤት በኮሚሽነሩ ዋፉላ ቺቡካቲ አማካይነት ይፋ ይደረግበታል በተባለው የቦማስ ማዕከል ውዝግብና ግብግብ ተፈጥሮ ታይቷል።
ለደቂቃዎች በአዳራሹ የነበረ ውጥረት ረግቦ በአሁን ሰዓት በአዳራሹ መርሀግብሩ ቀጥሏል። በአዳራሹ ውስጥ ሩቶ ቢገኙም ዋነኛ ተፎካካሪው ራይላ ኦዲንጋ የሉም።
በተለያዩ የኬንያ አካባቢዎች ላይ ውጥረት መንገሱም ተነግሯል።
Via BBC
Video Credit : CitizenTV
@tikvahethiopia
በኬንያ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ዛሬ ሰኞ ከሰዓት በኋላ ይፋ ይደረጋል ተብሎ እየተጠበቀ ባለበት ጊዜ አለመግባባት እና ውዝግብ ተፈጥሯል።
የፕሬዝዳንታዊ ምርጫውን ውጤት ያሳውቃሉ ተብለው በሚጠበቁት የኮሚሽኑ ባለሥልጣንት መካከል ክፍፍል መፈጠሩ ነው የተነገረው።
በዚህም 4 የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በይፋ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ውጤት ከሚነገርበት ማዕከል ውጪ መሃል ናይሮቢ በሚገኘው ሴሬና ሆቴል ውስጥ ሂደቱን ጥያቄ ላይ በሚጥል ሁኔታ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም ከ6ቱ ኮሚሽነሮች አራቱ በሰጡት መግለጫ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ውጤት አያያዝ “ግልጽነት የጎደለው በመሆኑ፣ ውጤቱን በኃላፊነት ለመውሰድ አንችልም” በማለት ገልጸዋል።
ውጤት በኮሚሽነሩ ዋፉላ ቺቡካቲ አማካይነት ይፋ ይደረግበታል በተባለው የቦማስ ማዕከል ውዝግብና ግብግብ ተፈጥሮ ታይቷል።
ለደቂቃዎች በአዳራሹ የነበረ ውጥረት ረግቦ በአሁን ሰዓት በአዳራሹ መርሀግብሩ ቀጥሏል። በአዳራሹ ውስጥ ሩቶ ቢገኙም ዋነኛ ተፎካካሪው ራይላ ኦዲንጋ የሉም።
በተለያዩ የኬንያ አካባቢዎች ላይ ውጥረት መንገሱም ተነግሯል።
Via BBC
Video Credit : CitizenTV
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኬንያ በኬንያ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ዛሬ ሰኞ ከሰዓት በኋላ ይፋ ይደረጋል ተብሎ እየተጠበቀ ባለበት ጊዜ አለመግባባት እና ውዝግብ ተፈጥሯል። የፕሬዝዳንታዊ ምርጫውን ውጤት ያሳውቃሉ ተብለው በሚጠበቁት የኮሚሽኑ ባለሥልጣንት መካከል ክፍፍል መፈጠሩ ነው የተነገረው። በዚህም 4 የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በይፋ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ውጤት ከሚነገርበት ማዕከል ውጪ መሃል ናይሮቢ በሚገኘው ሴሬና…
#BREAKING
ዊሊያም ሩቶ የኬንያን ምርጫ ማሸነፋቸው ይፋ ሆነ።
የኬንያ ምርጫ ኮሚሽን በቦማስ ማዕከል ዊልያም ሩቶ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን ማሸነፋቸውን ይፋ አድርጓል።
ዊልያም ሩቶ እና ራይላ ኦዲንጋ በተቀራራቢ ውጤት አንገት ለአንገት ተናንቀው እስከ አሁኗ የውጤት መግለጫ ሰዓት የደረሱ ሲሆን በመጨረሻም የፕሬዜደንታዊ ምርጫው አሸናፊ ዊሊያም ሩቶ መሆናቸውን በቦማስ ማዕከል ባለው ኮሚሽን ተገልጿል።
ሩቶ ያሸነፉት ከተሰጠው ጠቅላላ ድምፅ 50.49% በማግኘት ሲሆን ራይላ ኦዲንጋ 48.8% ድምፅ አግኝተዋል።
@tikvahethiopia
ዊሊያም ሩቶ የኬንያን ምርጫ ማሸነፋቸው ይፋ ሆነ።
የኬንያ ምርጫ ኮሚሽን በቦማስ ማዕከል ዊልያም ሩቶ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን ማሸነፋቸውን ይፋ አድርጓል።
ዊልያም ሩቶ እና ራይላ ኦዲንጋ በተቀራራቢ ውጤት አንገት ለአንገት ተናንቀው እስከ አሁኗ የውጤት መግለጫ ሰዓት የደረሱ ሲሆን በመጨረሻም የፕሬዜደንታዊ ምርጫው አሸናፊ ዊሊያም ሩቶ መሆናቸውን በቦማስ ማዕከል ባለው ኮሚሽን ተገልጿል።
ሩቶ ያሸነፉት ከተሰጠው ጠቅላላ ድምፅ 50.49% በማግኘት ሲሆን ራይላ ኦዲንጋ 48.8% ድምፅ አግኝተዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING ዊሊያም ሩቶ የኬንያን ምርጫ ማሸነፋቸው ይፋ ሆነ። የኬንያ ምርጫ ኮሚሽን በቦማስ ማዕከል ዊልያም ሩቶ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን ማሸነፋቸውን ይፋ አድርጓል። ዊልያም ሩቶ እና ራይላ ኦዲንጋ በተቀራራቢ ውጤት አንገት ለአንገት ተናንቀው እስከ አሁኗ የውጤት መግለጫ ሰዓት የደረሱ ሲሆን በመጨረሻም የፕሬዜደንታዊ ምርጫው አሸናፊ ዊሊያም ሩቶ መሆናቸውን በቦማስ ማዕከል ባለው ኮሚሽን ተገልጿል። …
#ኬንያ
የሀገራችን ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና የዝምባብዌው ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ የኬንያ ምርጫ ውጤት ይፋ መደረጉን ተከትሎ ለዊልያም ሩቶ የ " እንኳን ደስ አልዎት " መልዕክት ያስተለለፉ የመጀመሪያዎቹ የዓለም ሀገራት መሪዎች ሆነዋል።
@tikvahethiopia
የሀገራችን ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና የዝምባብዌው ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ የኬንያ ምርጫ ውጤት ይፋ መደረጉን ተከትሎ ለዊልያም ሩቶ የ " እንኳን ደስ አልዎት " መልዕክት ያስተለለፉ የመጀመሪያዎቹ የዓለም ሀገራት መሪዎች ሆነዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING ዊሊያም ሩቶ የኬንያን ምርጫ ማሸነፋቸው ይፋ ሆነ። የኬንያ ምርጫ ኮሚሽን በቦማስ ማዕከል ዊልያም ሩቶ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን ማሸነፋቸውን ይፋ አድርጓል። ዊልያም ሩቶ እና ራይላ ኦዲንጋ በተቀራራቢ ውጤት አንገት ለአንገት ተናንቀው እስከ አሁኗ የውጤት መግለጫ ሰዓት የደረሱ ሲሆን በመጨረሻም የፕሬዜደንታዊ ምርጫው አሸናፊ ዊሊያም ሩቶ መሆናቸውን በቦማስ ማዕከል ባለው ኮሚሽን ተገልጿል። …
ተቃውሞ እና ደስታ በጎረቤት ኬንያ !
ዛሬ በኬንያ የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ይፋ መደረጉን ተከትሎ ውጤቱን እንደማይቀበሉ የገለፁ የራይላ ኦዲንጋ ደጋፊዎች ተቃውሞ ማሰማት መጀመራቸው ፤ በአንዳንድ ቦታዎችም አመፅ መቀስቀሳቸው ተሰምቷል።
ከዚህ በተቃራኒው በጠባብ ውጤት እንዳሸነፉ የተነገረላቸው የዊሊያም ሩቶ ደጋፊዎች አደባባይ በመውጣት ደስታቸውን እየጨፈሩ በመግለፅ ላይ ናቸው።
የራይላ ደጋፊዎች በተለይም በኪሱሙ መንገድ በመዝጋት ፣ ጎማዎችን በማቃጠል የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበሉት ገልፀዋል። ደጋፊዎቹ ሰዎች ላይ ድንጋይ ሲወረውሩም እንደነበር ታይቷል።
የፀጥታ ኃይሎች ሁኔታውን ለመቆጣጠር አስለቃሽ ጭስ እስከመተኮስ መድረሳቸውም ተሰምቷል።
ኪሱሙ የራይላ ኦዲንጋ ደጋፊዎች በብዛት ያሉበት ነው።
በሌላ በኩል በኪቤራ የራይላ ኦዲንጋ ደጋፊዎች " ራይላ ከሌለ ሰላም የለም " እያሉ ጎማ በማቃጠል የምርጫው ውጤት መጭበርበሩን በመግለፅ እንደማይቀበሉት አሳውቀዋል።
ከዚህ በተቃራኒ በተለያዩ ከተሞች የዊሊያም ሩቶ ደጋፊዎች በውጤቱ ደስታቸውን በተለያየ መንገድ እየገለፁ ይገኛሉ።
@tikvahethiopia
ዛሬ በኬንያ የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ይፋ መደረጉን ተከትሎ ውጤቱን እንደማይቀበሉ የገለፁ የራይላ ኦዲንጋ ደጋፊዎች ተቃውሞ ማሰማት መጀመራቸው ፤ በአንዳንድ ቦታዎችም አመፅ መቀስቀሳቸው ተሰምቷል።
ከዚህ በተቃራኒው በጠባብ ውጤት እንዳሸነፉ የተነገረላቸው የዊሊያም ሩቶ ደጋፊዎች አደባባይ በመውጣት ደስታቸውን እየጨፈሩ በመግለፅ ላይ ናቸው።
የራይላ ደጋፊዎች በተለይም በኪሱሙ መንገድ በመዝጋት ፣ ጎማዎችን በማቃጠል የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበሉት ገልፀዋል። ደጋፊዎቹ ሰዎች ላይ ድንጋይ ሲወረውሩም እንደነበር ታይቷል።
የፀጥታ ኃይሎች ሁኔታውን ለመቆጣጠር አስለቃሽ ጭስ እስከመተኮስ መድረሳቸውም ተሰምቷል።
ኪሱሙ የራይላ ኦዲንጋ ደጋፊዎች በብዛት ያሉበት ነው።
በሌላ በኩል በኪቤራ የራይላ ኦዲንጋ ደጋፊዎች " ራይላ ከሌለ ሰላም የለም " እያሉ ጎማ በማቃጠል የምርጫው ውጤት መጭበርበሩን በመግለፅ እንደማይቀበሉት አሳውቀዋል።
ከዚህ በተቃራኒ በተለያዩ ከተሞች የዊሊያም ሩቶ ደጋፊዎች በውጤቱ ደስታቸውን በተለያየ መንገድ እየገለፁ ይገኛሉ።
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አፍሪካ ቀንድ 🇸🇴🇪🇹🇰🇪
እንደ ዓለም ምግብ ፕሮግራም መረጃ በአፍሪካ ቀንድ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች #በድርቅ ፣ #በግጭት እና #በምግብ_ውድነት ምክንያት አስከፊ ለሆነ ረሃብ ተጋልጠዋል።
የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሶማሊያ ላሉ ቤተሰቦች እገዛ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል።
#ShareTheMeal (በUN | WFP ስር ያለ) በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ቤተሰቦች የድንገተኛ ጊዜ የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን ለዚሁ ስራ የሚውልን ገንዘብ ከለጋሾች በመተግበሪያው እንዲሁም በድረገፁ በኩል እያሰባሰበ ይገኛል። https://t.co/rjY1JlrJTl
@tikvahethiopia
እንደ ዓለም ምግብ ፕሮግራም መረጃ በአፍሪካ ቀንድ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች #በድርቅ ፣ #በግጭት እና #በምግብ_ውድነት ምክንያት አስከፊ ለሆነ ረሃብ ተጋልጠዋል።
የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሶማሊያ ላሉ ቤተሰቦች እገዛ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል።
#ShareTheMeal (በUN | WFP ስር ያለ) በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ቤተሰቦች የድንገተኛ ጊዜ የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን ለዚሁ ስራ የሚውልን ገንዘብ ከለጋሾች በመተግበሪያው እንዲሁም በድረገፁ በኩል እያሰባሰበ ይገኛል። https://t.co/rjY1JlrJTl
@tikvahethiopia
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር ፤ በአዲሱ ረቂቅ የትምህርት እና ጥናት ፖሊሲ ከቅድመ አንደኛ እስከ ስምንተኛ ከፍል የሚሰጥ ትምህርት #ነፃ እና #አስገዳጅ እንደሚሆን አስታውቋል።
በሚኒስቴሩ የስርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ ክፍል ኃላፊ ዶ/ር ቴዎድሮስ ሸዋረገድ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል " በአዲሱ የትምህርት ፍኖታ ካርታ ግኝት መሰረት ዜጎች ከቅድመ አንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል በግዴታ እንዲማሩ ለማስቻልና የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱን የተሳለጠ ለማድረግ አጠቃላይ የትምህርት ረቂቅ አዋጅ ተግባራዊ ይደረጋል " ብለዋል።
ፍኖተ ካርታውን ለማዘጋጀት ሲሞከር የትምህርት ዘርፉ ያለበትን ሁኔታ ሊያሳይ የሚያስችል ጥናት መደረጉን ገልፀው መንግስት ለትምህርት ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ጥራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በአዲስ መልክ ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ገብቷል ሲሉ አስረድተዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/MoE-08-16 (ኢቢሲ)
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር ፤ በአዲሱ ረቂቅ የትምህርት እና ጥናት ፖሊሲ ከቅድመ አንደኛ እስከ ስምንተኛ ከፍል የሚሰጥ ትምህርት #ነፃ እና #አስገዳጅ እንደሚሆን አስታውቋል።
በሚኒስቴሩ የስርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ ክፍል ኃላፊ ዶ/ር ቴዎድሮስ ሸዋረገድ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል " በአዲሱ የትምህርት ፍኖታ ካርታ ግኝት መሰረት ዜጎች ከቅድመ አንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል በግዴታ እንዲማሩ ለማስቻልና የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱን የተሳለጠ ለማድረግ አጠቃላይ የትምህርት ረቂቅ አዋጅ ተግባራዊ ይደረጋል " ብለዋል።
ፍኖተ ካርታውን ለማዘጋጀት ሲሞከር የትምህርት ዘርፉ ያለበትን ሁኔታ ሊያሳይ የሚያስችል ጥናት መደረጉን ገልፀው መንግስት ለትምህርት ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ጥራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በአዲስ መልክ ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ገብቷል ሲሉ አስረድተዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/MoE-08-16 (ኢቢሲ)
@tikvahethiopia