" የMokeypox በሽታ መስፋፋት ለኢትዮጵያም ስጋት ነው "
በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የቅድመ ማስጠንቀቂያ እና መረጃ ስርዓት አስተዳደር ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዘውዱ አሰፋ ለአል ዓይን ኒውስ በሰጡት ቃል የተናገሩት ፦
" ቫይረሱ ከዚህ በፊት ፈንጣጣ መሰሉ በሽታ ተጠቂ የሌለባቸው ሀገራት ሳይቀር እየተስፋፋ ነው፡፡
እንደማንኛውም ሀገር እኛም በቫይረሱ ስርጭት ስጋት አለን። በኢትዮጵያ የመግቢያ እና መውጫ በሮች ላይ የተለመደው ክትትል እየተደረገ ይገኛል።
በሀገሪቱ የየብስ እና የአየር ትራንስፖርት መግቢያ እና መውጫ ላይ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ እና ወደ ሌሎች ሀገራት እንዳይሄድ የተላላፊ በሽታዎች ክትትል እየተደረገ ነው።
የበሽታው ተጠቂ በኢትዮጵያ ቢገኝ ማድረግ ስለሚገባን ስራዎች፣ ለህብረተሰቡ መሰጠት ስለሚገባው የግንዛቤ ፈጠራ መልዕክት እና የህክምና ክትትል ስራዎችን ለመለየት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመሰራት ላይ ነው "
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የቅድመ ማስጠንቀቂያ እና መረጃ ስርዓት አስተዳደር ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዘውዱ አሰፋ ለአል ዓይን ኒውስ በሰጡት ቃል የተናገሩት ፦
" ቫይረሱ ከዚህ በፊት ፈንጣጣ መሰሉ በሽታ ተጠቂ የሌለባቸው ሀገራት ሳይቀር እየተስፋፋ ነው፡፡
እንደማንኛውም ሀገር እኛም በቫይረሱ ስርጭት ስጋት አለን። በኢትዮጵያ የመግቢያ እና መውጫ በሮች ላይ የተለመደው ክትትል እየተደረገ ይገኛል።
በሀገሪቱ የየብስ እና የአየር ትራንስፖርት መግቢያ እና መውጫ ላይ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ እና ወደ ሌሎች ሀገራት እንዳይሄድ የተላላፊ በሽታዎች ክትትል እየተደረገ ነው።
የበሽታው ተጠቂ በኢትዮጵያ ቢገኝ ማድረግ ስለሚገባን ስራዎች፣ ለህብረተሰቡ መሰጠት ስለሚገባው የግንዛቤ ፈጠራ መልዕክት እና የህክምና ክትትል ስራዎችን ለመለየት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመሰራት ላይ ነው "
@tikvahethiopia
#ኮሮጆ
ከቦታ ወደ ቦታ እየተንቀሳቀሱ የሚፈልጉትን እቃ መግዛት እጅግ አድካሚ ሆኗል። በተጨማሪም የሚፈልጉትን እቃ ማግኘት እንዲሁም በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እጅግ አዳጋች ነው። የግዢ ሂደትዎን በማዘመን ቤትዎ ውስጥ ሆነው ወይም ስራ ቦታ ስልክዎን ብቻ በመጠቀም Korojo መተግበሪያ ላይ የፈለጉትን ማማረጥና መሸመት ይችላሉ።
መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፤ የፈለጉትን ይሸምቱ። https://korojo.app/download
ከቦታ ወደ ቦታ እየተንቀሳቀሱ የሚፈልጉትን እቃ መግዛት እጅግ አድካሚ ሆኗል። በተጨማሪም የሚፈልጉትን እቃ ማግኘት እንዲሁም በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እጅግ አዳጋች ነው። የግዢ ሂደትዎን በማዘመን ቤትዎ ውስጥ ሆነው ወይም ስራ ቦታ ስልክዎን ብቻ በመጠቀም Korojo መተግበሪያ ላይ የፈለጉትን ማማረጥና መሸመት ይችላሉ።
መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፤ የፈለጉትን ይሸምቱ። https://korojo.app/download
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኮሎኔል_ገመቹ_አያና ➡️ " ኮሎኔል ገመቹ አያናን ከኦሮሚያ ፖሊስ በአደራ ከመቀበል ውጪ ምንም የወንጀል የምርመራ መዝገብ በስማቸው የለንም ፤... ኮለኔል ገመቹን ይዘን ወደ ኦሮሚያ ፖሊስ በመሔድ ተረከቡን ብለን ስንጠይቅ ኦሮሚያ ፖሊስ እኛ ጋር ጉዳይ የለውም የሚል ምላሽ ሰጥቶናል " - ኮማንደር ኤርትሮ ኦቦ ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ➡️ " ኮ/ል ገመቹ መታሰራቸውን አንፈልግም ቢለቀቁ አልቃወምም "…
#Update
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራር የሆነት ኮነሌል ገመቹ አያና ከስር እንዲለቀቁ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 3ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት ወሰነ።
ኮነሌል ገመቹ አያና በግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ/ም በተከሰሱበት በሽብር ወንጀል በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረሽብርና የህገመንግክት ጉዳዮች ወንጀል ችሎች በነጻ ከተሰናበቱ በኋላ በነጋታው ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በር ላይ ሲወጡ በኦሮሚያ ፖሊስ ተይዘው ለ6 ወር በገላን ፓሊስ ጣቢያና በወታደራዊ ካንፕ እንዲሁም በአዋሽ መልካሳ በአንድ ጀነራል ዶሮ እርባታ ውስጥ ታስረው እንደነበርና ከህዳር 16 ጀምሮ ደግሞ በፌደራል ፖሊስ በስር ላይ እንደነበሩ ለፍርድ ቤት አስረድተው ነበር።
ኮነሌል ገመቹ አያናን በአደራ ከመቀበል ውጪ ምንም የወንጀል የምርመራ መዝገብ እንዳልተከፈተበት የፌደራል ፖሊስ ቀርቦ ማብራሪያ መስጠቱንም ይታወሳል።
ሰበር ሰሚ ችሎቱ የኦሮሚያ ፖሊስ ቀርቦ የኮነሌል ገመቹ የእስራት ሁኔታን እንዲያስረዳ ታዞ የነበረ ሲሆን ትላንት በነበረ ቀጠሮ ችሎት አልቀረበም።
ይህን ተከትሎ መርምሮ ትዛዝ ለመስጠት ችሎቱ ለዛሬ በይደረሰ ቀጥሮ የነበረ ሲሆን መርምሮ ኮነሌል ገመቹ አያና ከስር እንዲፈቱ ወስኗል።
ምንጭ ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራር የሆነት ኮነሌል ገመቹ አያና ከስር እንዲለቀቁ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 3ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት ወሰነ።
ኮነሌል ገመቹ አያና በግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ/ም በተከሰሱበት በሽብር ወንጀል በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረሽብርና የህገመንግክት ጉዳዮች ወንጀል ችሎች በነጻ ከተሰናበቱ በኋላ በነጋታው ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በር ላይ ሲወጡ በኦሮሚያ ፖሊስ ተይዘው ለ6 ወር በገላን ፓሊስ ጣቢያና በወታደራዊ ካንፕ እንዲሁም በአዋሽ መልካሳ በአንድ ጀነራል ዶሮ እርባታ ውስጥ ታስረው እንደነበርና ከህዳር 16 ጀምሮ ደግሞ በፌደራል ፖሊስ በስር ላይ እንደነበሩ ለፍርድ ቤት አስረድተው ነበር።
ኮነሌል ገመቹ አያናን በአደራ ከመቀበል ውጪ ምንም የወንጀል የምርመራ መዝገብ እንዳልተከፈተበት የፌደራል ፖሊስ ቀርቦ ማብራሪያ መስጠቱንም ይታወሳል።
ሰበር ሰሚ ችሎቱ የኦሮሚያ ፖሊስ ቀርቦ የኮነሌል ገመቹ የእስራት ሁኔታን እንዲያስረዳ ታዞ የነበረ ሲሆን ትላንት በነበረ ቀጠሮ ችሎት አልቀረበም።
ይህን ተከትሎ መርምሮ ትዛዝ ለመስጠት ችሎቱ ለዛሬ በይደረሰ ቀጥሮ የነበረ ሲሆን መርምሮ ኮነሌል ገመቹ አያና ከስር እንዲፈቱ ወስኗል።
ምንጭ ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
#ጥቆማ
መልቲቾይስ አፍሪካ/DSTV በየዓመቱ ለወጣት የፊልም ባለሙያዎች የአንድ ዓመት የፊልም ጥበብ ስኮላርሺፕ ይሰጣል።
የመልቲቾይስ ታለንት ፋክተሪ የስኮላርሺፕ ዕድል ወጣት ባለሙያዎችን ኬንያ በሚገኘው የመልቲቾይስ አካዳሚ የፊልም ጥበብ እውቀታቸውን የሚያጎለብቱበት ዕድል ይፈጥራል።
እድሚያችሁ ከ18-30 የሆነ ወጣቶች እስከ ግንቦት 26/2014 ዓ.ም ተከታዩን ሊንክ በመጠቀም ማመልከት ትችላላችሁ፦
www.multichoicetalentfactory.com
ለበለጠ መረጃ፦
https://cte.multichoicetalentfactory.com/Master/entrycriteria
(ዝርዝር መረጃ ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
መልቲቾይስ አፍሪካ/DSTV በየዓመቱ ለወጣት የፊልም ባለሙያዎች የአንድ ዓመት የፊልም ጥበብ ስኮላርሺፕ ይሰጣል።
የመልቲቾይስ ታለንት ፋክተሪ የስኮላርሺፕ ዕድል ወጣት ባለሙያዎችን ኬንያ በሚገኘው የመልቲቾይስ አካዳሚ የፊልም ጥበብ እውቀታቸውን የሚያጎለብቱበት ዕድል ይፈጥራል።
እድሚያችሁ ከ18-30 የሆነ ወጣቶች እስከ ግንቦት 26/2014 ዓ.ም ተከታዩን ሊንክ በመጠቀም ማመልከት ትችላላችሁ፦
www.multichoicetalentfactory.com
ለበለጠ መረጃ፦
https://cte.multichoicetalentfactory.com/Master/entrycriteria
(ዝርዝር መረጃ ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
#ሀሰት_ነው !
" ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ " በሚል የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
በ2014 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ማጠቃለያ ላይ ተማሪዎች ማጠቃለያ ፈተናዎችን ለመውስድ እየተዘጋጁ ይገኛሉ።
ነገር ግን ማህበራዊ ኃላፊነት በጎደላቸው አካላት ሆን ተብሎ ተማሪዎችን ለማዘናጋት በዘንድሮ ዓመት ከክፍል ወደ ክፍል መዘዋወር የለም ተብሎ በማህበራዊ የመገናኛ ዘዴዎች የሚናፈሰው ወሬ ፍፁም ከእውነት የራቀ መሆኑን ቢሮው ገልጿል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የወረደ አቅጣጫ የለም ያለው የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተማሪዎች " ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ" በሚል አሉባልታ ሳይምታቱ ለትምህርታቸው ትኩረት ስጥተዉ ለተሻለ ውጤት እንዲተጉ መልዕክት አስተላልፏል።
በተጨማሪ ⬇️
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚኒስቴሩን ስም እና አርማ በመጠቀም የተሳሳቱ እና የተዛቡ መረጃዎች እየተለቀቁ መሆኑን ገልጾ ተማሪዎች እና ወላጆች የሚሰረጩት መረጃዎች ከእውነት የራቁ መሆናቸውን በማወቅ በትኩረት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ አሳስቧል።
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
" ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ " በሚል የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
በ2014 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ማጠቃለያ ላይ ተማሪዎች ማጠቃለያ ፈተናዎችን ለመውስድ እየተዘጋጁ ይገኛሉ።
ነገር ግን ማህበራዊ ኃላፊነት በጎደላቸው አካላት ሆን ተብሎ ተማሪዎችን ለማዘናጋት በዘንድሮ ዓመት ከክፍል ወደ ክፍል መዘዋወር የለም ተብሎ በማህበራዊ የመገናኛ ዘዴዎች የሚናፈሰው ወሬ ፍፁም ከእውነት የራቀ መሆኑን ቢሮው ገልጿል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የወረደ አቅጣጫ የለም ያለው የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተማሪዎች " ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ" በሚል አሉባልታ ሳይምታቱ ለትምህርታቸው ትኩረት ስጥተዉ ለተሻለ ውጤት እንዲተጉ መልዕክት አስተላልፏል።
በተጨማሪ ⬇️
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚኒስቴሩን ስም እና አርማ በመጠቀም የተሳሳቱ እና የተዛቡ መረጃዎች እየተለቀቁ መሆኑን ገልጾ ተማሪዎች እና ወላጆች የሚሰረጩት መረጃዎች ከእውነት የራቁ መሆናቸውን በማወቅ በትኩረት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ አሳስቧል።
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
#WorldCup
የኳታሩ አለም ዋንጫ ሊጀምር የወራቶች እድሜ ብቻ ሲቀሩት የአለም ዋንጫው በዛሬው ዕለት አስቀድሞ በተያዘለት ቀን #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ደርሷል።
ዛሬ ከሰዓት በኋላ በሸራተን ሆቴል በተደረገ ጋዜጣዊ መግለጫ የቀድሞ የባርሴሎና እና የቼልሲ የመስመር ተጫዋች ብራዚላዊው ጁሊያኖ ቤሌቲ እና የ ኮካ ኮላ ከፍተኛ ሀላፊዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
የአለም ዋንጫው በሀገራችን የሁለት ቀናት ቆይታ ሲኖረው በነገው ዕለት ከ ረፋዱ 4:30 ጀምሮ በመስቀል አደባባይ በመገኘት የስፖርት አፍቃሪው አብሮ ፎቶ መንሳት እንደሚችል ተገልጿል።
አስቀድሞ ዴቪድ ትሪዝጌት እንደሚመጣ ተገልፆ የነበረ ቢሆንም ተጫዋቹ ባጋጠመው ከአቅም በላይ የሆነ የግል ጉዳይ ሊገኝ አለመቻሉ ታውቋል።
Via @tikvahethsport (ቲክቫህ ስፖርት)
የኳታሩ አለም ዋንጫ ሊጀምር የወራቶች እድሜ ብቻ ሲቀሩት የአለም ዋንጫው በዛሬው ዕለት አስቀድሞ በተያዘለት ቀን #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ደርሷል።
ዛሬ ከሰዓት በኋላ በሸራተን ሆቴል በተደረገ ጋዜጣዊ መግለጫ የቀድሞ የባርሴሎና እና የቼልሲ የመስመር ተጫዋች ብራዚላዊው ጁሊያኖ ቤሌቲ እና የ ኮካ ኮላ ከፍተኛ ሀላፊዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
የአለም ዋንጫው በሀገራችን የሁለት ቀናት ቆይታ ሲኖረው በነገው ዕለት ከ ረፋዱ 4:30 ጀምሮ በመስቀል አደባባይ በመገኘት የስፖርት አፍቃሪው አብሮ ፎቶ መንሳት እንደሚችል ተገልጿል።
አስቀድሞ ዴቪድ ትሪዝጌት እንደሚመጣ ተገልፆ የነበረ ቢሆንም ተጫዋቹ ባጋጠመው ከአቅም በላይ የሆነ የግል ጉዳይ ሊገኝ አለመቻሉ ታውቋል።
Via @tikvahethsport (ቲክቫህ ስፖርት)
#NewsAlert
ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለማችንን ትልቁን የጤና ተቋም የዓለም የጤና ድርጅትን ለሁለተኛ ዙር እንዲመሩ ዳግም ተመረጡ።
የዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ብቸኛ ዕጩ ሆነው ዳግም መመረጣቸው የተረጋገጠው በጄኔቫ ላይ እየተካሄደ በሚገኘው 75ኛው የዓለም ጤና ድርጅት ጠቅላላ ጉብዔ ላይ ነው።
ዶክተር ቴድሮስ ያለተፎካካሪ በብቸኛ ዕጩነት በቀረቡበት መድረክ ላይ ከተለያዩ የድርጅቱ አባል አገራት ለዕጩነት ለተሰጣቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ተቋሙን በይፋ ከሰኔ ወር 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ለቀጣይ አምስት ዓመታት ለሁለተኛ ዙር መምራት ይጀምራሉ መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
@tikvahethiopia
ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለማችንን ትልቁን የጤና ተቋም የዓለም የጤና ድርጅትን ለሁለተኛ ዙር እንዲመሩ ዳግም ተመረጡ።
የዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ብቸኛ ዕጩ ሆነው ዳግም መመረጣቸው የተረጋገጠው በጄኔቫ ላይ እየተካሄደ በሚገኘው 75ኛው የዓለም ጤና ድርጅት ጠቅላላ ጉብዔ ላይ ነው።
ዶክተር ቴድሮስ ያለተፎካካሪ በብቸኛ ዕጩነት በቀረቡበት መድረክ ላይ ከተለያዩ የድርጅቱ አባል አገራት ለዕጩነት ለተሰጣቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ተቋሙን በይፋ ከሰኔ ወር 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ለቀጣይ አምስት ዓመታት ለሁለተኛ ዙር መምራት ይጀምራሉ መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
@tikvahethiopia
" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመኪና ስርቆት እየጨመረ በመምጣቱ ህብረተሰቡ አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዳይለየው " - የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት
የሰረቀውን መኪና ይዞ ለማምለጥ የሞከረው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን በአዲስ አበባ ከተማ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታወቀ።
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ሰርቆት የነበረውን መኪና እያሽከረከረ በመሸሽ ላይ የነበረ ተጠርጣሪ ግለሰብ ሲደረግበት ከነበረው ክትትል ለማምለጥ መኪናውን ከመብራት ፖል ጋር አጋጭቶ በግለሰቦች መኖሪያ ቤት ጣሪያ በመዝለል ለማምለጥ ያደረገው ሙከራ ሳይሳካ በአካባቢው ወጣቶችና ነዋሪዎች ርብርብ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሎ በፖሊስ ምርመራ እየተካሄደበት መሆኑን የገለፀድ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ከቅርብ ጊዜ ውዲህ የመኪና ስርቆት እየጨመረ በመምጣቱ ህብረተሰቡ አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዳይለየው አሳስቧል።
Via Mayor Office of AA
@tikvahethiopia
የሰረቀውን መኪና ይዞ ለማምለጥ የሞከረው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን በአዲስ አበባ ከተማ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታወቀ።
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ሰርቆት የነበረውን መኪና እያሽከረከረ በመሸሽ ላይ የነበረ ተጠርጣሪ ግለሰብ ሲደረግበት ከነበረው ክትትል ለማምለጥ መኪናውን ከመብራት ፖል ጋር አጋጭቶ በግለሰቦች መኖሪያ ቤት ጣሪያ በመዝለል ለማምለጥ ያደረገው ሙከራ ሳይሳካ በአካባቢው ወጣቶችና ነዋሪዎች ርብርብ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሎ በፖሊስ ምርመራ እየተካሄደበት መሆኑን የገለፀድ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ከቅርብ ጊዜ ውዲህ የመኪና ስርቆት እየጨመረ በመምጣቱ ህብረተሰቡ አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዳይለየው አሳስቧል።
Via Mayor Office of AA
@tikvahethiopia
#AGMAS
አግማስ የህክምና መገልገያ መሳርያዎች አስመጪ በእጆ ላይ ይገኛል፡፡ ቻናላችንን በመቀላቀል ስለእቃዎቻችን የዋጋ ቅናሾች ፡ የማጣርያ ሽያጮች እና ሌሎች ጠቃሚ መረጃዎችን ያግኙ፡፡
የምናስመጣቸው ምረቶች ፤ የተላዩ የኬምስትሪ ማሽኖች እና ሪኤጀንቶች፤ የራጅ እና የአልትራሳዉንድ ማሽኖች እንዲሁም ሌሎችም ይገኙበታል፡፡
ለበለጠ መረጃ በ +251-929 5003 77/ 78 +251-911 95 6626 ይደዉሉ
https://yangx.top/agmasmedical
አግማስ የህክምና መገልገያ መሳርያዎች አስመጪ በእጆ ላይ ይገኛል፡፡ ቻናላችንን በመቀላቀል ስለእቃዎቻችን የዋጋ ቅናሾች ፡ የማጣርያ ሽያጮች እና ሌሎች ጠቃሚ መረጃዎችን ያግኙ፡፡
የምናስመጣቸው ምረቶች ፤ የተላዩ የኬምስትሪ ማሽኖች እና ሪኤጀንቶች፤ የራጅ እና የአልትራሳዉንድ ማሽኖች እንዲሁም ሌሎችም ይገኙበታል፡፡
ለበለጠ መረጃ በ +251-929 5003 77/ 78 +251-911 95 6626 ይደዉሉ
https://yangx.top/agmasmedical
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ትላንት በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ መግለጫ አውጥቶ ነበር።
ፓርቲው በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ ፤ " የሕግ የበላይነትን እና ሥርአትን ሕግን እየሸራረፉ እና መብቶችን እየጣሱ ማረገገጥ አይቻልም " ያለ ሲሆን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እያከናወነ ያለውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ በሕግ አግባብ ብቻ እንዲያከናውን አሳስቧል።
ክልሉ እያከናወናቸው ያሉት የጅምላ እስር ለብልሹ አሰራር እና ለዘፈቀደ ውሳኔ ተጋላጭ በመሆናቸው በአስቸኳይ እንዲቆሙ ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል ፤ የክልሉ መንግሥት እየወሰደ ባለው እርምጃ አብን አመራሮቹ እና አባላቱን ጨምሮ ባላቸው የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ምክንያት በግለሰቦች ላይ እየተፈጸመ ያለው እስር እንዲቆም እና በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት የታሰሩ ሰዎች ያላንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ጠይቋል።
በተጨማሪ አብን የክልሉ መንግስት እየወሰደው ባለው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ሂደት እየታዩ ያሉ ግልፅ ችግሮችን ሰበብ በማድረግ የአማራን ክልል የግጭት ማዕከል ለማድረግ እየሰሩ ያሉ ግለሰቦች እና ቡድኖችን በጽኑ አወግዛለሁ ያለ ሲሆን " ጠላት ጦርነት ለመክፈት በተዘጋጀበት ወቅት የአመጽ ጥሪ ማድረግ ያለንበትን አጠቃላይ የጸጥታ ከባቢያዊ ሁኔታ የዘነጋ እና ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ከመሆኑም በላይ ለጠላት የሚደረግ ስልታዊ ድጋፍ በመሆኑ የአመጽ ጥሪ የሚያደርጉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ሲል በመግለጫው አሳስቧል።
(አብን ትላንት ያወጣው መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ፓርቲው በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ ፤ " የሕግ የበላይነትን እና ሥርአትን ሕግን እየሸራረፉ እና መብቶችን እየጣሱ ማረገገጥ አይቻልም " ያለ ሲሆን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እያከናወነ ያለውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ በሕግ አግባብ ብቻ እንዲያከናውን አሳስቧል።
ክልሉ እያከናወናቸው ያሉት የጅምላ እስር ለብልሹ አሰራር እና ለዘፈቀደ ውሳኔ ተጋላጭ በመሆናቸው በአስቸኳይ እንዲቆሙ ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል ፤ የክልሉ መንግሥት እየወሰደ ባለው እርምጃ አብን አመራሮቹ እና አባላቱን ጨምሮ ባላቸው የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ምክንያት በግለሰቦች ላይ እየተፈጸመ ያለው እስር እንዲቆም እና በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት የታሰሩ ሰዎች ያላንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ጠይቋል።
በተጨማሪ አብን የክልሉ መንግስት እየወሰደው ባለው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ሂደት እየታዩ ያሉ ግልፅ ችግሮችን ሰበብ በማድረግ የአማራን ክልል የግጭት ማዕከል ለማድረግ እየሰሩ ያሉ ግለሰቦች እና ቡድኖችን በጽኑ አወግዛለሁ ያለ ሲሆን " ጠላት ጦርነት ለመክፈት በተዘጋጀበት ወቅት የአመጽ ጥሪ ማድረግ ያለንበትን አጠቃላይ የጸጥታ ከባቢያዊ ሁኔታ የዘነጋ እና ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ከመሆኑም በላይ ለጠላት የሚደረግ ስልታዊ ድጋፍ በመሆኑ የአመጽ ጥሪ የሚያደርጉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ሲል በመግለጫው አሳስቧል።
(አብን ትላንት ያወጣው መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia