TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል 42ቱን መለየቱን የም/ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ አሳውቀዋል። አቶ ታገሰ ፥ ከመላው የሀገሪቱ ክፍሎች 632 የእጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ መቅረባቸውንና አብዛኛዎቹ ስራውን ለመስራት የሚያስችል ልምድና ዕውቀት ያላቸው መሆኑን መገንዘብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ አዋጁ ለአፈ-ጉባኤውና ለአፈ…
#አሁን

በቅርቡ ለተሾሙ የሚሲዮን መሪዎች የተዘጋጀ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፤ በቅርቡ በተለያዩ ሀገራት ለተሾሙ የሚሲዮን መሪዎች እንዲሁም በዋናው መ/ቤት በተለያዩ የስራ ኃላፊነት ላይ ለተመደቡ የስራ ኃላፊዎች ያዘጋጀው ስልጠና ዛሬ መሰጠት መጀመሩን ገልጿል።

በቅርቡ ጄነራል ባጫ ደበሌ ፣ ጄነራል ሀሰን ኢብራሂም ፣ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ፣ አቶ ደሴ ዳልኬ እና አቶ ተፈራ ደርበውን ጨምሮ ሌሎችም ግለሰቦች የባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት ሹመት እንደተሰጣቸው እንዲሁም ሌሎችም ግለሰቦች በአምባሳደርነት ሹመት እንደተሰጣቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ? ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ከፓርላማ አባላት በርካታ ጥያቄ ተነስቶላቸው በአሁን ሰዓት ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። ከፓርላማ አባላት መካከል አቶ ክርስቲያን ታደለ መንግስት በእነ አቶ ስብሃት ነጋ ላይ የተነሰረተውን ክስ ያቋረጠው ከህግ አግባብና ከህገመንግስቱ በሚጣረስ መልኩ ስለሆነ ማስተካከያ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። አቶ ክርስቲያን ፥ " መንግስት መጀመሪያ ዜናውን…
ድርድርን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን አሉ ?

ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦

" እስካሁን የተደረገ ድርድር የለም፤ እስከዚህ ደቂቃ ድረስ ፤ ስለድርድር ብዙ ሲወራ ሰማለሁ ግን እስካሁን ድርድር አላደረግንም፤ አላደረግንም ማለት እስከነአካቴው ድርድር የሚባል ነገር አይኖርም ማለት አይደለም።

ድርድር ፣ ውይይት ማለት ችግር ተወግዷል ማለት ሳይሆን ችግር ለማስወገድ አማራጭ Alternative መንገድ አለው ወይ ብሎ ማየት ነው።

በድርድርም ኢትዮጵያን ነው የምናፀናው ፣በንትርክም ኢትዮጵያን ነው የምናፀናው በውጊያም ዋጋ የምንከፍለው ኢትዮጵያን ለማፅናት ነው። ኢትዮጵያን ለማፅናት ህይወታችንን ገንዘባችንን የምንገብር ከሆነ ኢትዮጵያን ለማፅናት ስሜቶቻችን አምቀን መነጋገር የሚቻል ከሆነ በደስታ ማየት ጥሩ ነው። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ድርድርን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን አሉ ? ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦ " እስካሁን የተደረገ ድርድር የለም፤ እስከዚህ ደቂቃ ድረስ ፤ ስለድርድር ብዙ ሲወራ ሰማለሁ ግን እስካሁን ድርድር አላደረግንም፤ አላደረግንም ማለት እስከነአካቴው ድርድር የሚባል ነገር አይኖርም ማለት አይደለም። ድርድር ፣ ውይይት ማለት ችግር ተወግዷል ማለት ሳይሆን ችግር ለማስወገድ አማራጭ Alternative መንገድ አለው…
#ተጨማሪ

ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ስለ ድርድር የተናገሩት ፦

" ... አንድ የእስራኤል ፕሬዜዳንት በአንድ ወቅት ያሉትን ማስታወስ ፈልጋለሁ፤ እኚህ ፕሬዜዳንይ እስራኤል እየተዋጉ ከሀማሶች ጋር ከሂዝቦላህ ጋር ይደራደራሉ።

በነገራችን ላይ TPLF ከኦነግ ጋር ይደራደር ነበር፣ ደርግ ከሻዕቢያ እና TPLF ጋር ይደራደር ነበር ድርድር ማለት እርቅ ማለት አይደለም። ድርድር ውስጥ ብዙ የሚገኙ ነገሮች አሉ። ከምሳሌ ... ምሳሌው ይቅርብኝ ግን አሉ ጥቅሞች።

እናም እኚህ የእስራኤል ፕሬዜዳንት በጦርነት ጊዜ ምንም የሰላም ጫላንጭል እንደሌለ ሰላም ተስፋ እንደሌለው አስበን ጨክነን እንዋጋለን ፤ በድርድር ጊዜ ተጋጭተን እንደማናውቅ ጦርነት የሚባል እንዳልነበር በሰከነ መንፈስ እንደራደራለን ሁለቱንም የምናደርገው ለእስራኤል ጥቅም ነው ብለዋል።

እኛ በውጊያው ጊዜ የነበረን አቋም እና ሂደት ለምክር ቤት መግለፅ አይጠበቅብኝም አቋማችን ግልፅ ነው። በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ምንም የማንደራደር መሆኑ ግልፅ ነው።

አሁንም የምናደርገው የዛ ተገላቢጦሽ ሆኖ መታየት አለበት። ታስታውሳላችሁ በዝግ ስንወያይ ኢትዮጵያን አፍርሰው እነዚህ ሰዎች አዲስ አበባ አይገቡም ብያቹ ነበር በቲቪ አልተላለፈም ያ ውይይት ነበራችሁ ብዙዎቻችሁ ያኔ የተወያየነው ነገር ነው ተፈፅሞ ያየነው።

አሁንም #በድርድር የሚባል ነገር ካለ በዛው sprint ማየት ጥሩ ነው። የሰላም አማራጭ ካለ ፤ TPLF ቀልብ ከገዛ በጦርነት እንደማያዋጣው እንደማያሸንፍ ከተገነዘበ እኛ በደስታ ነው የምናየው። "

@tikvahethiopia
" ወሬው ሀሰት ነው " - የአሜሪካ ኤምባሲ

የአሜሪካን ኤምባሲ በትግራይ ክልል መዲና መቐለ ጊዜያዊ የቆንፅላ ፅኅፈት ቤት ከፍቷል ተብሎ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው ሲል አሳውቋል።

ኤምባሲው ይህንን ያለው ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።

ከዛሬ ጥዋት ጀምሮ የአሜሪካ ኤምባሲ በ #መቐለ የቆንፅላ አገልግሎት የሚሰጥ ጊዜያዊ ቢሮ ከፍቷል የሚል ወሬ ሲሰራጭ ነበር።

የአሜሪካ ኤምባሲ ቃል አቀባይ ፅ/ቤት ወሬ ሀሰት ነው ሲል አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን አሁን ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የመጀመሪውን ዳታ ሴንተሩን አስመልክቶ ለሚዲያዎች ገለፃ ያደርጋል። በስፍራው የሚገኙ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ገለፃውን ተከታትለው ዝርዝር መረጃው ይልኩላችኃል። @tikvahethiopia
#Update

ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መግለጫ ፦

• ከፊታችን ሚያዝያ 1ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ የተመረጡ የቴሌኮም አገልግሎቶችን መስጠት ይጀምራል። ከሚጀመሩ አገልግሎቶች መካከል ፦
- የጽሁፍ አገልግሎት፣
- የዳታ፣
- የድምጽ በአገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ የቴሎኮም አገልግሎቶች ናቸው።

• ከሰኔ በኋላ ሁሉንም የቴሌኮም አገልግሎቶችን መስጠት ይጀመራል።

• አዲስ አበባ ፣ ባህርዳር ፣ ጎንደር ፣ ደሴ ኮምቦልቻ ፣ ሀረር ፣ ድሬዳዋና ጅግጅጋ አገልግሎቶቹ ከሚጀመርባቸው አካባቢዎች ዋነኞቹ ናቸው።

• በ07 መነሻ ኮድ አገልግሎት ይሰጣል።

• የኢትዮ ቴሌኮምን የቴሌኮሙንኬሽን መሰረተ ልማቶች ለመጠቀም ድርድሮች እየተደረጉ ነው።

• በያዝነው የፈረንጆቹ 2022 ዓመት ውስጥ 2 ተጨማሪ የመረጃ ማዕከላት በአዲስ አበባ እና አዳማ ከተሞች ይገነባል።

• በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የህዝብ ብዛት ውስጥ ለግማሹ ህዝብ የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት እቅድ አለው። በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ውስጥ 98% ለሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን አገልግሎት የመስጠት እቅድ ተይዟል።

#አልዓይን

ፎቶ ፦ ከቲክቫህ ቤተሰብ አባላት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ? ኡስታዝ ከሚል ሸምሱ ፦ " እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ ሀገራችን ከሌሎች ሀገራት ያላትን ዲፕሎማሲ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለማሻሻል እና ዲፕሎማሲውም የሀገራትን የጋራ ጥቅም ያስጠበቀ እንዲሁም የሀገሩን ክብር እና ሉዓላዊነት በጠበቀ መልኩ እንዲጎለበት ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ። ሆኖም ግን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የሀገራትን የፖለቲካ አስተላለፍ በመከተል ወዳጅ የነበሩ ሀገራት ጎራቸውን…
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በሳዑዲ ስላሉ ዜጎች ጉዳይ የተናገሩት ፦

" ... ባለፉት ወራት ችግር ውስጥ እያለንም ቢሆን በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር መልሰናል ከሳዑዲ።

አሁን ችግሩ ምንድነው ሳዑዲ አረቢያ እንደመንግስት ሪፎርም እየሰሩ ነው። የሀገሬው ዜጋ ስራ እንዲሰራ ፣ እና ኢኮኖሚያቸውን ለማሻሻል ከውጭ የመጡ ሰዎች ከዚህ ቀደም የሚሰሯቸውን ስራዎች በራሳቸው ለመስራት እና ለመቀነስ ፍላጎት አላቸው። መብታቸውም ነው ትክክልም ናቸው፤ ተገቢ ነው ከእነሱ አንፃር።

ከእኛ አንፃር ፈተና አለብን። ፈተናው ምንድነው ሰዎቹ illegal /በህገወጥ/ የሄዱ ናቸው። ሁሉም ፓስፖርት ያለው አይደለም፤ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለመሆኑ እርግጠኛ አይደለሁም፤ ሁሉም ከዚህ ሳዑዲ የሄደ መሆኑን ማወቅ ያስቸግራል፤ የሰለጠኑ ገዳዮች አሉበት ይባላል ብዙ ጉዳይ ነው የሚወራው ቁጥሩ ግን ከፍተኛ ነው መቶ ሺዎች ነው።

ዝም ብለም ብናመጣ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደተለመደው የራሱን ዜጎች ተቸግሮም ቢሆን ቂጣም ጎመኑንም ተካፍሎ ይኖራል የሚለው ጠፍቶን ሳይሆን መከራ አብሮ እንዳይነጣ ቆም ብሎ ማጥናት ማስላት ስለሚፈልግ ነው።

ከሳዑዲ አረቢያ መንግስት ጋር በቅርበት እየሰራን ነው። Delegation ሄዷል በቅርቡ ሚኒስትሪያል ኮሚቴ በክቡር ምክትል ጠ/ሚ ሚመራ ተቋቁሟል በደንብ አጥንተን ዜጎቻንን እንመልሳለን።

ስንመልስ ጥፋት የሚያስከትሉ ሰዎች ካሉ ጥንቃቄ እናደርጋለን ፣ እንደዛ አይነት ምልክቶች ስላሉ ስጋት ስላለብን ነው ነገሩን ያዝ አድርገን ቆም አድርገን እየሰራን ያልነው። ንፁሃን አሉ የሚጎዱ ለምሳሌ መቶ ሰዎች አብሯቸው አስር ሰዎች ካሉ አብረው ከመጡ በኃላ የሚደርሰው ጥፋት እና አደጋ በተለይ በነበርንበት ሁኔታ አደገኛ ነበር ለዛ ነው ትንሽ የተቸገርነው። እያየን መስመር የሚይዝ ይሆናል። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጨማሪ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ስለ ድርድር የተናገሩት ፦ " ... አንድ የእስራኤል ፕሬዜዳንት በአንድ ወቅት ያሉትን ማስታወስ ፈልጋለሁ፤ እኚህ ፕሬዜዳንይ እስራኤል እየተዋጉ ከሀማሶች ጋር ከሂዝቦላህ ጋር ይደራደራሉ። በነገራችን ላይ TPLF ከኦነግ ጋር ይደራደር ነበር፣ ደርግ ከሻዕቢያ እና TPLF ጋር ይደራደር ነበር ድርድር ማለት እርቅ ማለት አይደለም። ድርድር ውስጥ ብዙ የሚገኙ ነገሮች አሉ።…
#የተጠቃለለ

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የሰጧቸው ምላሾች [ የተጠቃለለ ] በአጭሩ ቀርበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለም/ቤት አባላቱ ምላሽ ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል የኢኮኖሚ ሁኔታ ፣ የዋጋ ግሽበት / የኑሮ ውድነት፣ ሙስና ፣ የተፈቱ እስረኞችን በተመለከተ ፣ አፋርን በተመለከተ፣ ኦነግ ሸኔን በተመለከተ ፣ የልዩ ሀይሎች ጉዳይ ፣ ድርቅን በተመለከተ ፣ የዲፕሎማሲ ምደባ ይገኙበታል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/Dr-Abiy-Ahmed-02-22
#ታላቁ_የኢድ_ስግደት !

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ የተናገሩት ፦

" ... ከፊታችን ረመዳን እየመጣ ነው። ያው እንደምታውቁት የመጀመሪያው ሂጅራ የሚባለው ፣ የመጀመሪያው የእስልምና እንቅስቃሴ የተጀመረው ኢትዮጵያ ውስጥ ነው / የነበረው እንቅስቃሴ የመጣው ወደ ኢትዮጵያ ነው።

የሚቀጥለው ረመዳን ኢድ ታላቁ የኢድ ስግደት በኢትዮጵያ ይደረጋል። ይሄንን ታላቁን የኢድ ስግደት ከሁሉም ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን መጥተው ድምቀት እንዲሰጡት ይጠበቃል።

ብዙ የአረብ ሀገራት በቂ ሙስሊም ያለን አይመስላቸውም። ግማሽ የሚያህለው ሙስሊም ያለበት ሀገር እናም በእምነቱ ጠንካራ Values ያለው ህዝብ መሆኑን ለዓለም ለማሳየት እስካሁን የነበረው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ አሁን ሰፋ ባለ ደረጃ የሚታሰብ ነገር አለ።

ዳያስፖራ መጥቶ ኢድን ከእኛ ጋር እንዲያከብር ሀገር ውስጥ ያላችሁ ሙስሊም ወንድሞቻችን በየሀገሩ ያሉ ኢትዮጵያውያን መጥተው ከእኛ ጋር በጋራ ኢድን እንዲያከብሩ ብታደርጉ በጣም ጠቃሚ ይሆናል "

@tikvahethiopia
#CHINA

ሹዌ ቢንግ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው ተሾሙ።

#ቻይና በአሁኑ ወቅት በግጭት እየታመሰ ላለው የአፍሪካ ቀንድ ሹዌ ቢንግን ልዩ መልዕክተኛ አድርጋ መሾሟ ታውቋል።

ሹዌ ቢንግ ቀደም ሲል በፓፑዋ ኒው ጊኒ የቻይና አምባሳደር በመሆን አገልግለዋል። በአፍሪካ፣ በአሜሪካ እና በኦሺንያ የመሥራት ልምድ እንዳላቸው የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ዛሬ ማክሰኞ አስታውቋል።

@tikvahethiopia
ፕ/ር ካሣሁን ብርሀኑ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም ዐቀፍ ግንኙነት (PSIR) ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ የነበሩት ፕ/ር ካሣሁን ብርሀኑ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ፕ/ር ካሣሁን በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ የካቲት 15/2014 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አሳውቋል።

ፕ/ር ካሣሁን ላለፉት 36 ዓመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነትና ተመራማሪነት እንዲሁም በልዩ ልዩ ከፍተኛ የኃላፊነት ዕርከኖች አገልግለዋል።

በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ የተለያዩ ማኅበራዊ አገልግሎቶችን በማበርከትም ይታወቁ ነበር፡፡

የቀብር ስነ ስርዓታቸው ነገ የካቲት 16 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 በየካ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት ይፈፀማል፡፡

ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የሚመሩ 11 ኮሚሽነሮችን ሹመት በ5 ድምፀ ታአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል። በዚህ መሰረት ፦ 1ኛ. ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ (ሰብሳቢ) 2ኛ. ወ/ሮ ሂሩት ገብረስላሴ (ምክትል ሰብሳቢ) 3ኛ. ዶ/ር አይሮሪት መሐመድ 4ኛ. ዶ/ር ተገኝወርቅ ጌቱ 5ኛ. ዶ/ር ዮናስ አዳዬ 6ኛ. ዶ/ር አምባዬ ኦጋቶ 7ኛ. አምባሳደር…
የኮሚሽነሮቹ ጉዳይ ?

የኢፌዴሪ የህ/ተ/ም/ቤት የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽንን 11 ኮሚሽነሮችን ትላንት ማስፅደቁ ይታወሳል።

ም/ቤቱ ዛሬ ባወጣው ዝርዝር ማብራሪያ ከመጨረሻዎቹ 42 እጩ ኮሚሽነሮች ዝርዝር ውስጥ ያልተካተቱ እጩዎች ኮሚሽነር ሆነው ተሰይመዋል ተብሎ እየተሰራጨ ያለው መረጃ ትክክል አይደለም ብሏል።

ም/ቤቱ 632 ጥቆማዎች መቀበሉ የገለፀ ሲሆን ከነዚህ መካከል 42 በአንደኛ ደረጃ እና 75 በሁለተኛ ደረጃ ምድብ ለማደራጀት መቻሉን አስረድቷል።

42 እጩዎች ከተለዩ በኋላ ከሲቪክ ማህበራት ፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ፣ ከሀይማኖት ተቋማት፣ ከሀገር ሽማግሌዎች የተውጣጡ ተወካዮች በእጩዎቹ ላይ የተለያዩ አስተያየቶች እንዲሰጡ መደረጉን ገልጿል።

በም/ቤቱ ድረ ገጽ እና የፌስ ቡክ ገፁ የተደራጀ የእጩዎች ፕሮፋይል በማስቀመጥ ለሁለት ሳምንታት የህዝብ አስተያየቶች መሰባሰቡን አስታውሷል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ሰብሰቢና ም/ ሰብሳቢን የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ ቢሯ ቸው በመጥራት በ42ቱ እጩዎች ላይ ያላቸውን ሀሳብና አስተያየት እንዲቀርቡ ተደርጓል ብሏል።

በተለያ መንገድ የተሰበሰቡ 2,890 አስተያየቶች በማደራጀት የእጮዎችን ሁኔታ እንደገና ለማየት እንደ ግብአት ተጠቅመና ያለው ም/ቤቱ በዚሁ መሰረት ብዝሃነትን ፤ጾታን እና አድሜን መሰረት ያደረገ ማስተካከያ ተደርጓል ብሏል።

አንዳንዶቹ በዜግነት ኢትዮጵያ ያለመሆናቸው በመረጋገጡ እና አንዳንድ እጩዎች ፍላጎት እንደሌላቸው በመግለጻቸው ከ42ቱ የእጩዎች ዝርዝር እንዲሰረዙና በምትካቸው በ2ኛ ደረጃ ከተለዩት መካከል ወደ 42ቱ ተካተው በድጋሜ ለህዝብ አስተያየት በድረ ገፁ ላይ ለህዝብ አስተያየት ይፋ መደረጉን ገልጿል።

ከአስተያየቶቹ በኋላ አስራ አንዱ ኮሚሽነሮች ተለይተው በህ/ተ/ምክር ቤት ተሰይመዋል ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መግለጫ ፦ • ከፊታችን ሚያዝያ 1ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ የተመረጡ የቴሌኮም አገልግሎቶችን መስጠት ይጀምራል። ከሚጀመሩ አገልግሎቶች መካከል ፦ - የጽሁፍ አገልግሎት፣ - የዳታ፣ - የድምጽ በአገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ የቴሎኮም አገልግሎቶች ናቸው። • ከሰኔ በኋላ ሁሉንም የቴሌኮም አገልግሎቶችን መስጠት ይጀመራል። • አዲስ አበባ ፣ ባህርዳር ፣ ጎንደር ፣…
#SafaricomEthiopia

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ቃሊቲ አካባቢ በ100 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የገነባውን የዳታ ማዕከል አስጎብኝቷል።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላትም በስፍራ ተገኝተው ማዕከሉን ተመልክተዋል።

የዳታ ማዕከሉ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የደንበኞቹን መረጃዎች የሚይዝበት ሲሆን የኢትዮጵያ ደንበኞቹ መረጃቸው በዚሁ በኢትዮጵያ ውስጥ ይቀመጣል።

ሳፋሪኮም ፤ የሙከራ የድምጽ ፣ የአጭር ጹሑፍ (SMS) እንዲሁም የዳታ ሙከራዎች አሁን ላይ በገነባቸው መሰረተ ልማቶች መሳካታቸውን ማረጋገጡን አሳይቷል።

ድርጅቱ አገልግሎቱን ሲጀምር የዳታ አገልግሎቱን በ #4G የሚያስጀምር ሲሆን #3G እንዲሁም #2G መጠቀምም ያስችላል።

#5G የኢንተርኔት አገልግሎትም ለመስጠት ከወዲሁ እየሰራ ነው።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዛሬ ያስጎበኘውን የዳታ ማዕከል በፎቶ ከተጨማሪ መረጃዎች ጋር በዚህ ያንብቡ : telegra.ph/SafaricomEthiopia-02-22

@tikvahethiopia
#PP

የገዢው ብልፅግና ፓርቲ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በአሁን ሰዓት ስብሰባውን እያካሄደ ነው።

ስብሰባው በዐበይት ሀገራዊ ጉዳዮችና በልዩ ልዩ የፓርቲ አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ የፓርቲው ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ገልፀዋል።

@tikvahethiopia