#Attention
ከአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ (ፎርጅድ) እና መታወቂያ ለማይገባው ሰው የሰጠ ከ3 እስከ 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በተያያዘ በመታወቂያ አሰጣጥ ላይ ውይይት አድርጓል።
በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቀንአ ያደታ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሰረት በማድረግ የጊዜያዊ መታወቂያ አሰጣጥ መመሪያ መዘጋጀቱን ገልፀዋል።
መመሪያው ሰላማዊ እና ፀረ ሰላም ኃይሎችን ለመለየት፣ የሐሰት መታወቂያ የሚሰጡ ግለሰቦችንና ቡድኖችን ለመለየት እንዲሁም የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ሆነው ያለ አግባብ ጊዜያዊ መታወቂያ የሚሰጡትን ለመቆጣጠር ያግዛል ብለዋል።
ዶ/ር ቀነዓ እንዳሉት ከአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ (ፎርጅድ) እና መታወቂያ ለማይገባው ሰው የሰጠ ከ3 እስከ 10 ዓመት ያስቀጣል ያሉ ሱሆን ከህዳር 6 ቀን 2014 እስከ ህዳር 15/2014 በሚቆየው የጊዜያዊ መታወቂያ አሰጣጥ ሂደት ማህበረሰቡ መታወቂያ ማውጣት እንዳለበት ተናግረዋል።
የሎጂስቲክ እና የሰው ኃይል ቅድመ ዝግጅት ተካሂዶ አርብ ህዳር 10/2014 በየክፍለ ከተማው ጊዜያዊ መታወቂያ ለማህበረሰቡ ለመስጠት ዝግጅት መጀመሩም ተገልጿል።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
@tikvahethiopia
ከአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ (ፎርጅድ) እና መታወቂያ ለማይገባው ሰው የሰጠ ከ3 እስከ 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በተያያዘ በመታወቂያ አሰጣጥ ላይ ውይይት አድርጓል።
በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቀንአ ያደታ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሰረት በማድረግ የጊዜያዊ መታወቂያ አሰጣጥ መመሪያ መዘጋጀቱን ገልፀዋል።
መመሪያው ሰላማዊ እና ፀረ ሰላም ኃይሎችን ለመለየት፣ የሐሰት መታወቂያ የሚሰጡ ግለሰቦችንና ቡድኖችን ለመለየት እንዲሁም የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ሆነው ያለ አግባብ ጊዜያዊ መታወቂያ የሚሰጡትን ለመቆጣጠር ያግዛል ብለዋል።
ዶ/ር ቀነዓ እንዳሉት ከአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ (ፎርጅድ) እና መታወቂያ ለማይገባው ሰው የሰጠ ከ3 እስከ 10 ዓመት ያስቀጣል ያሉ ሱሆን ከህዳር 6 ቀን 2014 እስከ ህዳር 15/2014 በሚቆየው የጊዜያዊ መታወቂያ አሰጣጥ ሂደት ማህበረሰቡ መታወቂያ ማውጣት እንዳለበት ተናግረዋል።
የሎጂስቲክ እና የሰው ኃይል ቅድመ ዝግጅት ተካሂዶ አርብ ህዳር 10/2014 በየክፍለ ከተማው ጊዜያዊ መታወቂያ ለማህበረሰቡ ለመስጠት ዝግጅት መጀመሩም ተገልጿል።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
@tikvahethiopia
#Sidama
ከነገ ጀምሮ በሲዳማ ክልል የሰአት እላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ክልከላዎች ተላለፉ።
የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች ገደብ እና ክልከላዎችን ይፋ አድርጓል።
በዚህ መሰረት ፦
- ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክል (ታርጋ ያለው ብቻ) አንድ ሰው ጭኖ ከጠዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ ከጎንና ጎን ያለበሱትን ሸራ በማንሳትና ሶስት ሰው ብቻ በመጫን እስከ ምሽት ሁለት ሰዓት ፣ የህዝብ ትራንስፖርትና ታክሲዎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 2 ሰዓት ብቻ መንቀሳቀስ ይችላሉ።
- መታወቂያን በተመለከተ ፦ ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉ ሀላፊዎች መታወቂያ መስጠት የማይችሉና ማንነቱን የሚገልፅ መረጃ በመያዝ ግለሰቦች ከዛሬ ጀምሮ ጊዜያዊ መታወቂያ ማግኘት ይችላሉ።
- ከጦር መሳሪያ ጋር በተያያዘ፦ ከዚህ ቀደም ያስመዘገበም ያላስመዘገበም ከነገ ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት በአቅራቢያው በሚገኙ የፖሊስ ተቋማት ማስመዝገብና የፈቃድ ወረቀት መያዝ ይኖርበታል።
NB: ይህን ያላደረገና ያልተመዘገበ የጦር መሳሪያ ይዞ የተገኘ ማንኛውም አካል እንደ ወንጀለኛ የሚጠየቅ ይሆናል።
- ፋብሪካዎች፣ ኢንደስትሪ ፖርኮች፣ ሪዞርቶችና አለም አቀፍ ሆቴሎች የሰራተኛ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ከፖሊስ ኮሚሽኑ ፈቃድ ማግኘት ይችላሉ።
- ከሲዳማ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ወደ ክልሉ የሚገቡ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ መግባት አይችሉም። በእግረኞችና የቤት መኪኖች ላይ የሰዓት ገደብ ባይጣልም መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።
@tikvahethiopia
ከነገ ጀምሮ በሲዳማ ክልል የሰአት እላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ክልከላዎች ተላለፉ።
የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች ገደብ እና ክልከላዎችን ይፋ አድርጓል።
በዚህ መሰረት ፦
- ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክል (ታርጋ ያለው ብቻ) አንድ ሰው ጭኖ ከጠዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ ከጎንና ጎን ያለበሱትን ሸራ በማንሳትና ሶስት ሰው ብቻ በመጫን እስከ ምሽት ሁለት ሰዓት ፣ የህዝብ ትራንስፖርትና ታክሲዎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 2 ሰዓት ብቻ መንቀሳቀስ ይችላሉ።
- መታወቂያን በተመለከተ ፦ ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉ ሀላፊዎች መታወቂያ መስጠት የማይችሉና ማንነቱን የሚገልፅ መረጃ በመያዝ ግለሰቦች ከዛሬ ጀምሮ ጊዜያዊ መታወቂያ ማግኘት ይችላሉ።
- ከጦር መሳሪያ ጋር በተያያዘ፦ ከዚህ ቀደም ያስመዘገበም ያላስመዘገበም ከነገ ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት በአቅራቢያው በሚገኙ የፖሊስ ተቋማት ማስመዝገብና የፈቃድ ወረቀት መያዝ ይኖርበታል።
NB: ይህን ያላደረገና ያልተመዘገበ የጦር መሳሪያ ይዞ የተገኘ ማንኛውም አካል እንደ ወንጀለኛ የሚጠየቅ ይሆናል።
- ፋብሪካዎች፣ ኢንደስትሪ ፖርኮች፣ ሪዞርቶችና አለም አቀፍ ሆቴሎች የሰራተኛ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ከፖሊስ ኮሚሽኑ ፈቃድ ማግኘት ይችላሉ።
- ከሲዳማ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ወደ ክልሉ የሚገቡ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ መግባት አይችሉም። በእግረኞችና የቤት መኪኖች ላይ የሰዓት ገደብ ባይጣልም መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
የኬንያው ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታን ጨምሮ የውጭ ልዑካን እና መሪዎች በሚያደርጉት ጥረት የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት የተኩስ አቁም ውሳኔ ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ኬንያ እምነት እንዳላት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አመለከቱ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሪቼል ኦሞሞ እና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር በጋራ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።
ሪቼል አሞሞ ኢትዮጵያ ለዚህ ቀውስ መፍትሄ የመፈለግ አቅም እንዳላት እና የተኩስ አቁም ሊደረግ እንደሚችል እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
ኦሞሞ በዚህ ንግግራቸው የገለጹት ተስፋ ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ እሁድ ዕለት ካደረጉት ድንገተኛ የኢትዮጵያ ጉብኝት ጋር ሊገናኝ እንደሚችል ዘገባዎች አመልክተዋል።
ብሊንከን በበኩላቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ ተኩስ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
የአፍሪካ ሕብረት በልዩ መልእክተኛው ኦሊሴንጎን ኦባሳንጆ አማካኝነት ኢትዮጵያ ላይ የጀመረውን የሰላም ጥረት እንደሚደግፉም መግለፃቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
ዛሬ ኬንያ የገቡት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከመግለጫው ቀደም ብሎ ከሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አሁሩ ኬንያታ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
@tikvahethiopia
የኬንያው ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታን ጨምሮ የውጭ ልዑካን እና መሪዎች በሚያደርጉት ጥረት የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት የተኩስ አቁም ውሳኔ ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ኬንያ እምነት እንዳላት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አመለከቱ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሪቼል ኦሞሞ እና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር በጋራ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።
ሪቼል አሞሞ ኢትዮጵያ ለዚህ ቀውስ መፍትሄ የመፈለግ አቅም እንዳላት እና የተኩስ አቁም ሊደረግ እንደሚችል እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
ኦሞሞ በዚህ ንግግራቸው የገለጹት ተስፋ ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ እሁድ ዕለት ካደረጉት ድንገተኛ የኢትዮጵያ ጉብኝት ጋር ሊገናኝ እንደሚችል ዘገባዎች አመልክተዋል።
ብሊንከን በበኩላቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ ተኩስ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
የአፍሪካ ሕብረት በልዩ መልእክተኛው ኦሊሴንጎን ኦባሳንጆ አማካኝነት ኢትዮጵያ ላይ የጀመረውን የሰላም ጥረት እንደሚደግፉም መግለፃቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
ዛሬ ኬንያ የገቡት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከመግለጫው ቀደም ብሎ ከሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አሁሩ ኬንያታ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
@tikvahethiopia
#Somali : የሶማሌ ክልል የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት በህብረተሰቡ መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የተንቀሳቀሱ ሚዲያዎች እና ግለሰቦች ላይ እርምጃ መውሰዱን ገለፀ።
የክልሉ መንግስት ኮሚዮኒኬሽን ቢሮ በህዝቡ መካከል የጥላቻ እና ሀሰተኛ መረጃዎችን የሚያሰራጩ አካላት ከዚህ በኋላ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሣስቧል።
የሶማሌ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አብዲቃድር ረሺድ ዱዓሌ ፥ " እነኚህ አካላት ለረዥም ዘመናት በመከባበርና አብሮ በኖሩ ማህበረሰብ መካከል የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃን በማሰራጨት ግጭት መቀስቀስን ዓላማቸው አድርገው ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል " ብለዋል።
የጥላቻ ንግግር እና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1185/2012 ተላልፈው በመገኘታቸው ምክንያት እነኚህን አካላት ለህግ ማቅረብ መቻሉን ኃላፊው አስታውቀዋል።
" እነኚህ አካላት ብሄርን ከብሄር ማጋጨት አላማቸው አድርገው ቢንቀሳቀሱም የሶማሌ ህዝብ ከመንግስት፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከሀይማኖት አባቶች እና ከጎሳ መሪዎች ጋር በጋራ የሚሰራ በመሆኑ የታሰበው ግጭት ሳይከሰት ቀርቷል " ሲሉ ሀላፊው አክለዋል።
ድርጊቱ በተለይ ሀገሪቷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ ባለችበት ሰዓት መፈፀሙ ደግሞ ጉዳዩን አሳሳቢ እንደሚያደርገው ገልፀው መንግስት ከዚህ በኋላ በመሰል ተግባር ተሰማርተው የሚንቀሳቀሱ አካላትን እንደማይታገስ ሀላፊው መናገራቸው የክልሉ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
የክልሉ ኮሚኒኬሽን እርምጃ ተውስዶባቸዋል ስለተባሉት ሚዲያዎች እና ግለሰቦች በግልፅ ያሰፈረው ነገር ያለው የለም።
@tikvahethiopia
የክልሉ መንግስት ኮሚዮኒኬሽን ቢሮ በህዝቡ መካከል የጥላቻ እና ሀሰተኛ መረጃዎችን የሚያሰራጩ አካላት ከዚህ በኋላ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሣስቧል።
የሶማሌ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አብዲቃድር ረሺድ ዱዓሌ ፥ " እነኚህ አካላት ለረዥም ዘመናት በመከባበርና አብሮ በኖሩ ማህበረሰብ መካከል የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃን በማሰራጨት ግጭት መቀስቀስን ዓላማቸው አድርገው ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል " ብለዋል።
የጥላቻ ንግግር እና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1185/2012 ተላልፈው በመገኘታቸው ምክንያት እነኚህን አካላት ለህግ ማቅረብ መቻሉን ኃላፊው አስታውቀዋል።
" እነኚህ አካላት ብሄርን ከብሄር ማጋጨት አላማቸው አድርገው ቢንቀሳቀሱም የሶማሌ ህዝብ ከመንግስት፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከሀይማኖት አባቶች እና ከጎሳ መሪዎች ጋር በጋራ የሚሰራ በመሆኑ የታሰበው ግጭት ሳይከሰት ቀርቷል " ሲሉ ሀላፊው አክለዋል።
ድርጊቱ በተለይ ሀገሪቷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ ባለችበት ሰዓት መፈፀሙ ደግሞ ጉዳዩን አሳሳቢ እንደሚያደርገው ገልፀው መንግስት ከዚህ በኋላ በመሰል ተግባር ተሰማርተው የሚንቀሳቀሱ አካላትን እንደማይታገስ ሀላፊው መናገራቸው የክልሉ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
የክልሉ ኮሚኒኬሽን እርምጃ ተውስዶባቸዋል ስለተባሉት ሚዲያዎች እና ግለሰቦች በግልፅ ያሰፈረው ነገር ያለው የለም።
@tikvahethiopia
ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽህፈት ቤት በዛሬው ዕለት አስታወቀ።
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ፥ የሲዳማ ጌዲዮ አማሮና ቡርጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለኢኦተቤ ቴሌቭዥን እንደገለጹት ብፁዕ አቡነ ባርናባስ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና ቀደም ሲል በማኅበራዊ ሚዲያ ሲባል እንደነበረው ክፉ እንዳልገጠማቸው አስታውቀዋል።
ምንጭ፦ EOTC
@tikvahethiopia
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ፥ የሲዳማ ጌዲዮ አማሮና ቡርጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለኢኦተቤ ቴሌቭዥን እንደገለጹት ብፁዕ አቡነ ባርናባስ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና ቀደም ሲል በማኅበራዊ ሚዲያ ሲባል እንደነበረው ክፉ እንዳልገጠማቸው አስታውቀዋል።
ምንጭ፦ EOTC
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Uganda: ዛሬ በኡጋንዳ በደረሱ 2 የሽብር አደጋዎች 3 ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ቆሰሉ፡፡ ካምፓላ ሁለት ቦታዎች በደረሱ የአጥፍቶ ጠፊዎች የሽብር ጥቃት ይ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የከተማይቱ ፖሊስ አስታቋል፡፡ በአደጋው ከቆሰሉት 33 ሰዎች ውስጥ አምስቱ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ተገልጿል፡፡ የተጎጂዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ ይችላል፡፡…
#UGANDA
የኢትዮጵያ መንግስት በዩጋንዳ መዲና ካማፓላ ከተማ የተፈጸመውን የሽብር ጥቃት አወገዘ፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ በትናንትናው ዕለት በካምፓላ ሁለት ቦታዎች ላይ በተፈጸመው የሽብር ጥቃት በንጹሃን ዜጎችና ፖሊስ ባልደረቦች ላይ በደረሰው የሞትና የአካል ጉዳት ማዘኑን ገልጿል፡፡
ኢትዮጵያ የተፈጸመውን የሽብር ጥቃት በጥብቅ እንደምታወግዝም ነው በመግለጫው የተመላከተው።
ኢትዮጵያና ዩጋንዳ በጋራ ሽብርተኝነትን የመዋጋት ልምድ እንዳላቸው በመጥቀስ ጥቃቱ ዩጋንዳም ሆነ ሌሎች የአፍሪካ አገራት ሽብርተኝነትን የበለጠ በቁርጠኝነት ከመዋጋት እንደማያግዳቸው የኢትዮጵያ መንግስት ገልጿል።
የኢትዮጵያ መንግስት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለኡጋንዳ ህዝብና መንግስት እንዲሁም ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
ምንጭ፦ ኤፍ ቢ ሲ/ የውጭ ጉዳዩ ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መንግስት በዩጋንዳ መዲና ካማፓላ ከተማ የተፈጸመውን የሽብር ጥቃት አወገዘ፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ በትናንትናው ዕለት በካምፓላ ሁለት ቦታዎች ላይ በተፈጸመው የሽብር ጥቃት በንጹሃን ዜጎችና ፖሊስ ባልደረቦች ላይ በደረሰው የሞትና የአካል ጉዳት ማዘኑን ገልጿል፡፡
ኢትዮጵያ የተፈጸመውን የሽብር ጥቃት በጥብቅ እንደምታወግዝም ነው በመግለጫው የተመላከተው።
ኢትዮጵያና ዩጋንዳ በጋራ ሽብርተኝነትን የመዋጋት ልምድ እንዳላቸው በመጥቀስ ጥቃቱ ዩጋንዳም ሆነ ሌሎች የአፍሪካ አገራት ሽብርተኝነትን የበለጠ በቁርጠኝነት ከመዋጋት እንደማያግዳቸው የኢትዮጵያ መንግስት ገልጿል።
የኢትዮጵያ መንግስት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለኡጋንዳ ህዝብና መንግስት እንዲሁም ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
ምንጭ፦ ኤፍ ቢ ሲ/ የውጭ ጉዳዩ ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Uganda: ዛሬ በኡጋንዳ በደረሱ 2 የሽብር አደጋዎች 3 ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ቆሰሉ፡፡ ካምፓላ ሁለት ቦታዎች በደረሱ የአጥፍቶ ጠፊዎች የሽብር ጥቃት ይ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የከተማይቱ ፖሊስ አስታቋል፡፡ በአደጋው ከቆሰሉት 33 ሰዎች ውስጥ አምስቱ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ተገልጿል፡፡ የተጎጂዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ ይችላል፡፡…
ኬንያ በተጠንቀቅ ላይ ናት።
ኬንያ፣ ትናንት በኡጋንዳ ሽብርተኞች ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ ዜጎቿ ሁኔታዎችን በንቃት እንዲከታተሉ አሳስባለች።
ናይሮቢ የትኛውንም ዐይነት የሽብር ጥቃት ለመከላከል በሚያስችል ተጠንቀቅ ላይ መሆኗን አስታውቃለች፡፡
በትናንቱ የካምፓላ ፍንዳታ አጥፍቶ ጠፊዎቹን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች ቆስለዋል፡፡
ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ ዝርዝር ማብራሪያን የሰጡት የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ካጉታ ሙሴቬኒ ጥቃቱ በሽብርተኝነት በተፈረጀው አሊያንስ ፎር ዴሞክራሲ (ADF) ሶስት አጥፍቶ ጠፊዎች መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡
የኬንያ መንግስት ቃል አቀባይ የሃገራቸው የጸጥታ አካላት በተጠንቀቅ ላይ መሆናቸውንና አጎራባች በሆኑ የድንበር አካባቢዎች ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ኬንያውያን ነቅተው አካባቢቺውን እንዲጠብቅና አዳዲስ ነገሮችን ሲመለከቱ ለፖሊስ እንዲያስታውቁም ኮሎኔል ሳይረስ ኦጉና በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አሳስበዋል፡፡
ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ
@tikvahethiopia
ኬንያ፣ ትናንት በኡጋንዳ ሽብርተኞች ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ ዜጎቿ ሁኔታዎችን በንቃት እንዲከታተሉ አሳስባለች።
ናይሮቢ የትኛውንም ዐይነት የሽብር ጥቃት ለመከላከል በሚያስችል ተጠንቀቅ ላይ መሆኗን አስታውቃለች፡፡
በትናንቱ የካምፓላ ፍንዳታ አጥፍቶ ጠፊዎቹን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች ቆስለዋል፡፡
ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ ዝርዝር ማብራሪያን የሰጡት የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ካጉታ ሙሴቬኒ ጥቃቱ በሽብርተኝነት በተፈረጀው አሊያንስ ፎር ዴሞክራሲ (ADF) ሶስት አጥፍቶ ጠፊዎች መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡
የኬንያ መንግስት ቃል አቀባይ የሃገራቸው የጸጥታ አካላት በተጠንቀቅ ላይ መሆናቸውንና አጎራባች በሆኑ የድንበር አካባቢዎች ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ኬንያውያን ነቅተው አካባቢቺውን እንዲጠብቅና አዳዲስ ነገሮችን ሲመለከቱ ለፖሊስ እንዲያስታውቁም ኮሎኔል ሳይረስ ኦጉና በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አሳስበዋል፡፡
ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ
@tikvahethiopia
Ethiopian Human Rights Commission - 1.pdf
265.7 KB
ኢሰመኮ፦
የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ ከአዋጁ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን አያያዝ የእስር ሁኔታና የታሳሪዎችን ሁኔታ ለመከታተል በሚያስችለው መልኩ መረጃ ማሰባበሰብ አለመቻሉን አሳውቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ እና በየካ ክ/ ከተሞች የሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎችንና ማቆያዎችን ጎብኝቷል፤ ታሳሪዎችንና ቤተሰቦቻቸውን አነጋግሯል፤ በክፍለ ከተማና በወረዳ ደረጃ ካሉ ከፖሊስ አባላት እና አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ መረጃዎችን አሰባስቧል፡፡
በአንጻሩ የአዲስ ከተማ፣ የልደታ፣ የጉለሌ፣ የቦሌ እና የአራዳ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች ከበላይ ትእዛዝ ካልመጣልን መረጃ አንሰጥም፣ እስረኛም መጎብኘት አትችሉም በማለታቸው ኮሚሽኑ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር እና ኃላፊነት እንዳይወጣ ምክንያት ሆነዋል፡፡
በኮሚሽኑ ክትትል የታሰሩ ሰዎችን ብዛት በሚመለከት የተሟላ መረጃ ለማግኘት እንዳልቻለ አሳውቋል።
ኮሚሽኑ በአንጻራዊነት የተሟላ መረጃ ያገኘው ከቂርቆስ ክ/ከተማ ሲሆን መረጃው በተሰጠበት ኅዳር 2/2014 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ 714 ሰዎች መታሰራቸውንና ከነዚህ ውስጥ 124ቱ ሴቶች እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።
በሌሎች ክ/ከተሞች በተመሳሳይ ሁኔታ እስሮች ሲከናወኑ ስለነበርና በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሂደት አሁንም የቀጠለ በመሆኑ በአዲስ አበባ ብቻ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መታሰራቸው ይገመታል።
በድሬዳዋ ደግሞ እስከ 300 የሚሆኑ ሰዎች ታስረዋል።
የተወሰኑ ሰዎች በሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት መረጃ መሰረት የሚታሰሩ ሲሆን አብዛኛዎቹ ግን ከህብረተሰቡ ተገኘ በተባለ ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር እንደሚውሉና ከመካከላቸው የትግራይ ተወላጆች የሆኑ ሰዎች ብዛት ከፍተኛ ነው።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል (PDF)
@tikvahethiopia
የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ ከአዋጁ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን አያያዝ የእስር ሁኔታና የታሳሪዎችን ሁኔታ ለመከታተል በሚያስችለው መልኩ መረጃ ማሰባበሰብ አለመቻሉን አሳውቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ እና በየካ ክ/ ከተሞች የሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎችንና ማቆያዎችን ጎብኝቷል፤ ታሳሪዎችንና ቤተሰቦቻቸውን አነጋግሯል፤ በክፍለ ከተማና በወረዳ ደረጃ ካሉ ከፖሊስ አባላት እና አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ መረጃዎችን አሰባስቧል፡፡
በአንጻሩ የአዲስ ከተማ፣ የልደታ፣ የጉለሌ፣ የቦሌ እና የአራዳ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች ከበላይ ትእዛዝ ካልመጣልን መረጃ አንሰጥም፣ እስረኛም መጎብኘት አትችሉም በማለታቸው ኮሚሽኑ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር እና ኃላፊነት እንዳይወጣ ምክንያት ሆነዋል፡፡
በኮሚሽኑ ክትትል የታሰሩ ሰዎችን ብዛት በሚመለከት የተሟላ መረጃ ለማግኘት እንዳልቻለ አሳውቋል።
ኮሚሽኑ በአንጻራዊነት የተሟላ መረጃ ያገኘው ከቂርቆስ ክ/ከተማ ሲሆን መረጃው በተሰጠበት ኅዳር 2/2014 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ 714 ሰዎች መታሰራቸውንና ከነዚህ ውስጥ 124ቱ ሴቶች እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።
በሌሎች ክ/ከተሞች በተመሳሳይ ሁኔታ እስሮች ሲከናወኑ ስለነበርና በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሂደት አሁንም የቀጠለ በመሆኑ በአዲስ አበባ ብቻ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መታሰራቸው ይገመታል።
በድሬዳዋ ደግሞ እስከ 300 የሚሆኑ ሰዎች ታስረዋል።
የተወሰኑ ሰዎች በሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት መረጃ መሰረት የሚታሰሩ ሲሆን አብዛኛዎቹ ግን ከህብረተሰቡ ተገኘ በተባለ ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር እንደሚውሉና ከመካከላቸው የትግራይ ተወላጆች የሆኑ ሰዎች ብዛት ከፍተኛ ነው።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል (PDF)
@tikvahethiopia
#Somalia #Ethiopia #Sudan #SouthSudan
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን እና የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ ባሉ አሁናዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ላይ ተወያይተዋል።
ውይይቱን በተመለከተ አንቶኒ ብሊንከን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ ፥ ውጤታማ ውይይት መደረጉን ገልፀዋል ።
ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በበኩላቸው ቀጠናዊ ሰላም እና ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በሌሎችም ቀጠናዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ከአንቶኒ ብሊንከን ጋር መወያየታቸውን በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ገልፀዋል።
ዶ/ር ወርቅነህ ፥ " በቀጣይም ከአሜሪካ ጋር በበርካታ ዘርፎች አብረን እንሰራለን " ያሉ ሲሆን " አሜሪካ የኢጋድ ወሳኝ አጋር ናት "ብለዋል።
Photo : Secretary Antony Blinken
@tikvahethiopia
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን እና የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ ባሉ አሁናዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ላይ ተወያይተዋል።
ውይይቱን በተመለከተ አንቶኒ ብሊንከን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ ፥ ውጤታማ ውይይት መደረጉን ገልፀዋል ።
ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በበኩላቸው ቀጠናዊ ሰላም እና ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በሌሎችም ቀጠናዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ከአንቶኒ ብሊንከን ጋር መወያየታቸውን በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ገልፀዋል።
ዶ/ር ወርቅነህ ፥ " በቀጣይም ከአሜሪካ ጋር በበርካታ ዘርፎች አብረን እንሰራለን " ያሉ ሲሆን " አሜሪካ የኢጋድ ወሳኝ አጋር ናት "ብለዋል።
Photo : Secretary Antony Blinken
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Attention ከአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ (ፎርጅድ) እና መታወቂያ ለማይገባው ሰው የሰጠ ከ3 እስከ 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በተያያዘ በመታወቂያ አሰጣጥ ላይ ውይይት አድርጓል። በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም እና…
#Attention
(ከአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የተላከ)
በህገ ወጥ መንገድ የተዘጋጀ ( #ፎርጅድ ) መታወቂያ ይዞ መንቀሳቀስ ከ3 - 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በላከልን የፁሁፍ መልዕክት አሳውቋል።
@tikvahethiopia
(ከአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የተላከ)
በህገ ወጥ መንገድ የተዘጋጀ ( #ፎርጅድ ) መታወቂያ ይዞ መንቀሳቀስ ከ3 - 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በላከልን የፁሁፍ መልዕክት አሳውቋል።
@tikvahethiopia
የልዩ ዕድል ሎተሪ የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች ፦
1ኛ. 20,000,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 1535477
2ኛ. 10,000,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0165840
3ኛ. 5,000,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0411256
4ኛ. 3,000,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1543809
5ኛ. 1,500,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 0503560
6ኛ. 750,000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 0837825
7ኛ. 300,000 ብር የሚያስገኘው የ7ኛ ዕጣ ቁጥር 1907437
8ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 20,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 30688
9ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 10,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 02294
10ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 5,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 96608
11ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 3696
12ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 5789
13ኛ. 2,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 500 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 846
14ኛ. 20,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 300 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 67
15ኛ. 200,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 4 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡
ምንጭ፦ ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር
@tikvahethiopia
1ኛ. 20,000,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 1535477
2ኛ. 10,000,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0165840
3ኛ. 5,000,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0411256
4ኛ. 3,000,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1543809
5ኛ. 1,500,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 0503560
6ኛ. 750,000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 0837825
7ኛ. 300,000 ብር የሚያስገኘው የ7ኛ ዕጣ ቁጥር 1907437
8ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 20,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 30688
9ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 10,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 02294
10ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 5,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 96608
11ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 3696
12ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 5789
13ኛ. 2,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 500 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 846
14ኛ. 20,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 300 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 67
15ኛ. 200,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 4 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡
ምንጭ፦ ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር
@tikvahethiopia