TIKVAH-ETHIOPIA
#SUDAN : የሱዳን የፀጥታ ሀይሎች ተቃውሞዋቸውን በሰላማዊ መንገድ ለማሰማት አደባባይ በሚወጡ ዜጎች ላይ የሀይል እርምጃ እንዳይወስዱ አሜሪካና ብሪታኒያ አስጠነቀቁ። በዛሬው እለት የሱዳን ጦር በሲቪል አስተዳደሩ ላይ የወሰደውን እርምጃ በመቃወም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሲዳናውያን አደባባይ ወጥተው ተቃውሞዋችን እንደሚያሰሙ ይጠበቃል። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፤ የሱዳን የፀጥታ ሐይሎች…
ዛሬ የሱዳን ጦር 2 ሰልፈኞችን ገደለ።
በሱዳን የተካሄደውን ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በመቃወም በ100 ሺ የሚቆጠሩ ሱዳኒያውያን ዛሬ አደባባይ ወጥተው ነበር።
ሰልፉን ጠርተው የነበረው የዴሞክራሲ ተሟጋች ቡድኖች ናቸው።
በመላ ሀገሪቱ እንዲካሄድ ዛሬ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ የጀመረው ኦምዱርማን በተባለችው ከተማ ሲሆን ካርቱም ያሉ ሰልፈኞች ወዲያው ሰልፉን በመከተል የሲቪል አስተዳደሩ ወደ ቦታው እንዲመለስ ጠይቀዋል።
የሱዳን የሀኪሞች ህብረት እንዳስታወቀው አምዱርማን ከተማ ውስጥ 2 ሰዎች በጸጥታ ኃይሎች በጥይት ተገድለዋል።
የሱዳን የፀጥታ ሀይሎች ተቃውሞዋቸውን በሰላማዊ መንገድ ለማሰማት አደባባይ በሚወጡ ዜጎች ላይ የሀይል እርምጃ እንዳይወስዱ አሜሪካና ብሪታኒያ ማስጠንቀቃቸው አይዘነጋም።
Credit : DW/AFP/Al Jazeera
@tikvahethiopia
በሱዳን የተካሄደውን ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በመቃወም በ100 ሺ የሚቆጠሩ ሱዳኒያውያን ዛሬ አደባባይ ወጥተው ነበር።
ሰልፉን ጠርተው የነበረው የዴሞክራሲ ተሟጋች ቡድኖች ናቸው።
በመላ ሀገሪቱ እንዲካሄድ ዛሬ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ የጀመረው ኦምዱርማን በተባለችው ከተማ ሲሆን ካርቱም ያሉ ሰልፈኞች ወዲያው ሰልፉን በመከተል የሲቪል አስተዳደሩ ወደ ቦታው እንዲመለስ ጠይቀዋል።
የሱዳን የሀኪሞች ህብረት እንዳስታወቀው አምዱርማን ከተማ ውስጥ 2 ሰዎች በጸጥታ ኃይሎች በጥይት ተገድለዋል።
የሱዳን የፀጥታ ሀይሎች ተቃውሞዋቸውን በሰላማዊ መንገድ ለማሰማት አደባባይ በሚወጡ ዜጎች ላይ የሀይል እርምጃ እንዳይወስዱ አሜሪካና ብሪታኒያ ማስጠንቀቃቸው አይዘነጋም።
Credit : DW/AFP/Al Jazeera
@tikvahethiopia
ዕለታዊ የኮቪድ-19 ሪፖርት #Ethiopia ፦
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 14 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 7,458 የላብራቶሪ ምርመራ 384 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።
የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 425 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#ጥንቃቄ 😷 #TikvahFamily
@tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 14 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 7,458 የላብራቶሪ ምርመራ 384 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።
የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 425 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#ጥንቃቄ 😷 #TikvahFamily
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" እስካሁን ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል "- የአዲስ ከተማ ፖሊስ መምሪያ
መሳለሚያ እህል በረንዳ አካባቢ በአማኑኤል ህንፃ ላይ በተከሰተው የእሳት አደጋ እስካሁን 8 ሚሊዮን 370 ሺ 280 ብር የሚገመት ንብረት እንደወደመ የአዲስ ከተማ ፓሊስ መምሪያ አሳውቋል።
የእሳት አደጋውን መንስኤ እና ተያያዥ ጉዳዮች በተመለከተ በቀጣይ ምርመራ ተደርጎ ይገለፃል ተብሏል።
@tikvahethiopia
" እስካሁን ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል "- የአዲስ ከተማ ፖሊስ መምሪያ
መሳለሚያ እህል በረንዳ አካባቢ በአማኑኤል ህንፃ ላይ በተከሰተው የእሳት አደጋ እስካሁን 8 ሚሊዮን 370 ሺ 280 ብር የሚገመት ንብረት እንደወደመ የአዲስ ከተማ ፓሊስ መምሪያ አሳውቋል።
የእሳት አደጋውን መንስኤ እና ተያያዥ ጉዳዮች በተመለከተ በቀጣይ ምርመራ ተደርጎ ይገለፃል ተብሏል።
@tikvahethiopia
#ጥቅምት24
የኢትዮጵያ የመንግስት ጥቅምት 24 የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) በሰሜን እዝ ላይ የተፈፀመው ጥቃት ታስቦ እንደሚውል አሳውቋል።
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ዕለቱ “አልረሳውም፥ እኔም የኢትዮጵያ ሰራዊት ነኝ” በሚል መሪ ቃል ታስቦ እንደሚውል አሳውቋል።
ዕለቱ የሀገር መከላከያ ሰራዊቱ እየከፈለ ያለውን መስዋዕትነት ለማሰብ፣ ሁሉም ህዝብ የሀገሩ ጠባቂ እና ሰራዊት መሆኑን እንዲሁም ከመከላከያ ጎን መሆኑን የሚያሳይበት ይሆናል ተብሏል።
በተጨማሪ ፤ " ጥቅምት 24 በሚኖረው ስነ ስርዓት መስዋዕት የሆኑ የሰራዊት አባላትን እና የቡድኑን ክህደት ለማስታወስ በዕለቱ ጠዋት 3 ሰዓት ጀምሮ ሁሉም ህዝብ ለ45 ሰኮንዶች እጃቸውን ደረታቸው ላይ በማድረግ ይቆያሉ " የመንግስት ኮሚኒኬሽን ገልጿል።
የሻማ ማብራትና ደሙን እየገበረ ላለው ሰራዊት የደም ልገሳ መረሃ ግብር ይከናወናል ተብሏል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የመንግስት ጥቅምት 24 የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) በሰሜን እዝ ላይ የተፈፀመው ጥቃት ታስቦ እንደሚውል አሳውቋል።
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ዕለቱ “አልረሳውም፥ እኔም የኢትዮጵያ ሰራዊት ነኝ” በሚል መሪ ቃል ታስቦ እንደሚውል አሳውቋል።
ዕለቱ የሀገር መከላከያ ሰራዊቱ እየከፈለ ያለውን መስዋዕትነት ለማሰብ፣ ሁሉም ህዝብ የሀገሩ ጠባቂ እና ሰራዊት መሆኑን እንዲሁም ከመከላከያ ጎን መሆኑን የሚያሳይበት ይሆናል ተብሏል።
በተጨማሪ ፤ " ጥቅምት 24 በሚኖረው ስነ ስርዓት መስዋዕት የሆኑ የሰራዊት አባላትን እና የቡድኑን ክህደት ለማስታወስ በዕለቱ ጠዋት 3 ሰዓት ጀምሮ ሁሉም ህዝብ ለ45 ሰኮንዶች እጃቸውን ደረታቸው ላይ በማድረግ ይቆያሉ " የመንግስት ኮሚኒኬሽን ገልጿል።
የሻማ ማብራትና ደሙን እየገበረ ላለው ሰራዊት የደም ልገሳ መረሃ ግብር ይከናወናል ተብሏል።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba : የኑሮ ዉድነትን ለመቀነስ "የእሁድ ገበያን" በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች መጀመራቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳውቀዋል።
ገበያዎቹ በየሳምንቱ እሁድ የተለያዩ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦችን ለከተማው ነዋሪ በአነስተኛ ዋጋ አንደሚቀርቡም ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል ።
በዚህም በአምራቾችና በሸማቾች መካከል ቀጥተኛ እና አጭር የግብኝት ግንኙነት እንዲኖር ማድረግ ይቻላል ያሉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዋናነትም ህገ ወጥ የዋጋ ጭማሪና ሰዉ ሰራሽ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር አስቀድሞ መከላከል ያስችላል ብለዋል ።
በሁሉም የከተማው አቅጣጫ የሚገኙ ነዋሪዎች በእረፍት ቀናቸው በአቅራቢያቸድ ወዳሉት የእሁድ ገበያዎች በመሄድ መገበያየት እንደሚችሉ ወ/ሮ አዳነች አሳውቀዋል።
Credit : AAPS
@tikvahethiopia
ገበያዎቹ በየሳምንቱ እሁድ የተለያዩ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦችን ለከተማው ነዋሪ በአነስተኛ ዋጋ አንደሚቀርቡም ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል ።
በዚህም በአምራቾችና በሸማቾች መካከል ቀጥተኛ እና አጭር የግብኝት ግንኙነት እንዲኖር ማድረግ ይቻላል ያሉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዋናነትም ህገ ወጥ የዋጋ ጭማሪና ሰዉ ሰራሽ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር አስቀድሞ መከላከል ያስችላል ብለዋል ።
በሁሉም የከተማው አቅጣጫ የሚገኙ ነዋሪዎች በእረፍት ቀናቸው በአቅራቢያቸድ ወዳሉት የእሁድ ገበያዎች በመሄድ መገበያየት እንደሚችሉ ወ/ሮ አዳነች አሳውቀዋል።
Credit : AAPS
@tikvahethiopia
#ItsMyDam🇪🇹
" የተርባይኖቹ ሃይል ማመንጨት ተከዜና ጣና በለስ ግድቦችን በአንድ ጊዜ የማጠናቀቅ ያህል ነው " - ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ
የታላቁ የህዳሴ ግድብ 2 ተርባይኖች ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት መጀመር ተከዜንና ጣና በለስ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድቦችን በአንድ ጊዜ የማጠናቀቅ ያህል መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ተደራዳሪ አባል ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ ገለጹ።
ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፥ በጣና በለስና በተከዜ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድቦች የሚመረተው የኤሌክትሪክ ሃይል የህዳሴው ግድብ ሁለቱ ተርባይኖች ከሚመነጩት ኤሌክትሪክ ሃይል እኩል ነው ብለዋል።
ሁለቱ ተርባይኖች ተጠናቀው ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት መጀመር ሁለት ግዙፍ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክቶች በአንድ ጊዜ እንደማጠናቀቅ ይቆጠራል ሲሉም ገልፀዋል።
ፕሮፌሰሩ ፥ ጣና በለስና ተከዜ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድቦች እንደቅደም ተከተላቸው 460ና 300 ሜጋ ዋት ሃይል እንደሚያመነጩ አውስተው፤ የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሃይል ማመንጫ ግድብ ሁለት ተርባይኖች ስራ መጀመር 750 ሜጋ ዋት ሃይል ስለሚያመነጩ ሁለት ትልልቅ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድቦችን የማጠናቀቅ ያህል ነው ብለዋል።
Credit : EPA
@tikvahethiopia
" የተርባይኖቹ ሃይል ማመንጨት ተከዜና ጣና በለስ ግድቦችን በአንድ ጊዜ የማጠናቀቅ ያህል ነው " - ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ
የታላቁ የህዳሴ ግድብ 2 ተርባይኖች ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት መጀመር ተከዜንና ጣና በለስ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድቦችን በአንድ ጊዜ የማጠናቀቅ ያህል መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ተደራዳሪ አባል ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ ገለጹ።
ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፥ በጣና በለስና በተከዜ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድቦች የሚመረተው የኤሌክትሪክ ሃይል የህዳሴው ግድብ ሁለቱ ተርባይኖች ከሚመነጩት ኤሌክትሪክ ሃይል እኩል ነው ብለዋል።
ሁለቱ ተርባይኖች ተጠናቀው ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት መጀመር ሁለት ግዙፍ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክቶች በአንድ ጊዜ እንደማጠናቀቅ ይቆጠራል ሲሉም ገልፀዋል።
ፕሮፌሰሩ ፥ ጣና በለስና ተከዜ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድቦች እንደቅደም ተከተላቸው 460ና 300 ሜጋ ዋት ሃይል እንደሚያመነጩ አውስተው፤ የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሃይል ማመንጫ ግድብ ሁለት ተርባይኖች ስራ መጀመር 750 ሜጋ ዋት ሃይል ስለሚያመነጩ ሁለት ትልልቅ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድቦችን የማጠናቀቅ ያህል ነው ብለዋል።
Credit : EPA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba : የኑሮ ዉድነትን ለመቀነስ "የእሁድ ገበያን" በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች መጀመራቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳውቀዋል። ገበያዎቹ በየሳምንቱ እሁድ የተለያዩ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦችን ለከተማው ነዋሪ በአነስተኛ ዋጋ አንደሚቀርቡም ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል ። በዚህም በአምራቾችና በሸማቾች መካከል ቀጥተኛ እና አጭር የግብኝት ግንኙነት እንዲኖር ማድረግ ይቻላል ያሉት ከንቲባ…
ፎቶ ፦ በአዲስ አበባ በተመረጡ ቦታዎች የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበ ይገኛል።
ዛሬ ፦
- በንፋስ ስልክ ላፍቶ ጀሞ 67 ቁጥር ማዞሪያ፣
- በመገናኛ፣
- በፒያሳ፣
- በሜክሲኮ አደባባይ እና በቃሊቲ መናኸሪያ በርካታ ነዋሪዎች የተለያዩ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በመገበያየት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የሸማቾች ኅብረት ስራ ማኅበራት፣ የሰብልና አትክልት አቅራቢዎች ፣የጅምላ ነጋዴዎች እና በምግብ ማቀነባበር የተሰማሩ ፋብሪካዎች እንዲሁም በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የሚገኙ የኅብረት ስራ ማህበራትና አምራች አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል ።
ለህብረተሰቡ እየቀረበ ካለው የግብርና ምርቶች መካከል ፦
- የጤፍ፣
- የስንዴ ዱቄት፣
- የአትክልትና ፍራፍሬ ይገኝበታል።
ከኢንዱስትሪ ምርቶች ደግሞ ዘይት፣ ማካሮኒና ፓስታ እንዲሁም የባልትና ውጤቶች ቀርበዋል እንደ አዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬተሪያት መረጃ።
@tikvahethiopia
ዛሬ ፦
- በንፋስ ስልክ ላፍቶ ጀሞ 67 ቁጥር ማዞሪያ፣
- በመገናኛ፣
- በፒያሳ፣
- በሜክሲኮ አደባባይ እና በቃሊቲ መናኸሪያ በርካታ ነዋሪዎች የተለያዩ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በመገበያየት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የሸማቾች ኅብረት ስራ ማኅበራት፣ የሰብልና አትክልት አቅራቢዎች ፣የጅምላ ነጋዴዎች እና በምግብ ማቀነባበር የተሰማሩ ፋብሪካዎች እንዲሁም በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የሚገኙ የኅብረት ስራ ማህበራትና አምራች አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል ።
ለህብረተሰቡ እየቀረበ ካለው የግብርና ምርቶች መካከል ፦
- የጤፍ፣
- የስንዴ ዱቄት፣
- የአትክልትና ፍራፍሬ ይገኝበታል።
ከኢንዱስትሪ ምርቶች ደግሞ ዘይት፣ ማካሮኒና ፓስታ እንዲሁም የባልትና ውጤቶች ቀርበዋል እንደ አዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬተሪያት መረጃ።
@tikvahethiopia
#Aykel : የሠላም ምክክር መድረክ በአይከል !
በዛሬው ዕለት የአማራና ቅማንት ህዝቦች የሠላም ምክክር መድረክ በአይከል ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በሠላም ምክክር መድረኩ ከሶስቱ የጎንደር ዞኖች የተሰባሰቡ የሃይማኖት አባቶች፣ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የመከላከያ ሰራዊትና የአማራ ልዩ ሃይል አባላት፣ የአካባቢው የጸጥታ አካላትና ነዋሪዎች መገኘታቸው ተገልጿል።
በዚህ መድረክ የአይከል ከተማ ተወካይ ከንቲባ አቶ ለገሰ ብርቄ ÷ በአሁኑ ሰአት በአካባቢው የሚታየው የሰላም እጦት፣ የሰዎች እገታና ዘረፋ መሠረቱ ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴና የሰዎች ዝውውር ነው ብለዋል።
አቶ ለገሰ ፥ " ድርጊቱ በአሸባሪው ህወሓትና በቅማንት ጽንፈኛ ቡድን ሴራ ለዓመታት ሲተገበር ቆይቷል" ሲሉ ገልፀዋል።
እጩ ዶ/ር ያሬድ ደበበ የጠገዴ አርማጭሆና አካባቢው በጎ አድራጎት ማህበር አባል የመወያያ ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን " የዜጎች ሰላም መደፍረስና የሀገር ህልውና አደጋ ላይ የወደቀው አሁን ሳይሆን አሸባሪው ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
አክለውም ፤ " አሁን ላይ አሸባሪ ቡድኑ በጥቅም የሚገዙ የአማራ እና ቅማንት ሰዎችን አሰማርቶ የጥፋት ስራውን ቀጥሎበታል " ብለዋል።
" በግጭት ውስጥ የሚያተርፉ በርካታ ሰዎች አሉ " ያሉት እጩ ዶ/ር ያሬድ ÷ " በአማራና ቅማንት ህዝቦች መካከል የሚፈጥረውን ግጭት ለማስቀጠል በርካታ ጥረቶችን እያደረገ ቆይቷል " ሲሉ ተናግረዋል።
በአንድ ሀገር ላይ የሚኖሩ ሰዎች ሰላማቸውን ማረጋገጥ ይገባል ፤ የሁለቱ ብሔሮች ህዝቦችም ይህንን በትኩረት ሊሰሩበት ይገባልም ሲሉ ገልፀዋል።
telegra.ph/AYKEL-10-31 (ኤፍቢሲ)
@tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት የአማራና ቅማንት ህዝቦች የሠላም ምክክር መድረክ በአይከል ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በሠላም ምክክር መድረኩ ከሶስቱ የጎንደር ዞኖች የተሰባሰቡ የሃይማኖት አባቶች፣ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የመከላከያ ሰራዊትና የአማራ ልዩ ሃይል አባላት፣ የአካባቢው የጸጥታ አካላትና ነዋሪዎች መገኘታቸው ተገልጿል።
በዚህ መድረክ የአይከል ከተማ ተወካይ ከንቲባ አቶ ለገሰ ብርቄ ÷ በአሁኑ ሰአት በአካባቢው የሚታየው የሰላም እጦት፣ የሰዎች እገታና ዘረፋ መሠረቱ ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴና የሰዎች ዝውውር ነው ብለዋል።
አቶ ለገሰ ፥ " ድርጊቱ በአሸባሪው ህወሓትና በቅማንት ጽንፈኛ ቡድን ሴራ ለዓመታት ሲተገበር ቆይቷል" ሲሉ ገልፀዋል።
እጩ ዶ/ር ያሬድ ደበበ የጠገዴ አርማጭሆና አካባቢው በጎ አድራጎት ማህበር አባል የመወያያ ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን " የዜጎች ሰላም መደፍረስና የሀገር ህልውና አደጋ ላይ የወደቀው አሁን ሳይሆን አሸባሪው ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
አክለውም ፤ " አሁን ላይ አሸባሪ ቡድኑ በጥቅም የሚገዙ የአማራ እና ቅማንት ሰዎችን አሰማርቶ የጥፋት ስራውን ቀጥሎበታል " ብለዋል።
" በግጭት ውስጥ የሚያተርፉ በርካታ ሰዎች አሉ " ያሉት እጩ ዶ/ር ያሬድ ÷ " በአማራና ቅማንት ህዝቦች መካከል የሚፈጥረውን ግጭት ለማስቀጠል በርካታ ጥረቶችን እያደረገ ቆይቷል " ሲሉ ተናግረዋል።
በአንድ ሀገር ላይ የሚኖሩ ሰዎች ሰላማቸውን ማረጋገጥ ይገባል ፤ የሁለቱ ብሔሮች ህዝቦችም ይህንን በትኩረት ሊሰሩበት ይገባልም ሲሉ ገልፀዋል።
telegra.ph/AYKEL-10-31 (ኤፍቢሲ)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የመምህራን ጉዳይ ! " በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችና የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ጊዚያዊ ምደባ ይሰጣቸዋል " - ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ በትግራይ ክልል የሚገኙ 4 ዩኒቨርሲቲዎች እና የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ጉዳይን በተመለከተ ለትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተ-ልማት ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ጠይቀናል። የትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች እና የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ…
#Update
ትምህርት ሚኒስቴር ፦
• በመቐለ ፣
• በዓዲግራት፣
• በአክሱም ፣
• በራያ እና በወልድያ ዩኒቨርስቲዎች ሲያስተምሩ የነበሩ መምህራን በሙሉ ወደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች ጊዜያዊ ምደባ ለመመደብ እንዲያስችል መምህራን በሚከተለው ሊንክ https://forms.gle/uEmVwqqDFQ7dFk5dA ተጠቅመው ከነገ ጀምሮ እስከ እሮብ 24/2/2014 ዓ.ም እንዲመዘገቡ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር ፦
• በመቐለ ፣
• በዓዲግራት፣
• በአክሱም ፣
• በራያ እና በወልድያ ዩኒቨርስቲዎች ሲያስተምሩ የነበሩ መምህራን በሙሉ ወደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች ጊዜያዊ ምደባ ለመመደብ እንዲያስችል መምህራን በሚከተለው ሊንክ https://forms.gle/uEmVwqqDFQ7dFk5dA ተጠቅመው ከነገ ጀምሮ እስከ እሮብ 24/2/2014 ዓ.ም እንዲመዘገቡ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia