#HadiyaZone : አቶ ማቲዎስ ሎምበሶ በድጋሚ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ተሾሙ።
የሀዲያ ዞን ምክር ቤት እያካሄደ በሚገኘው 5ኛ ዙር 9ኛ ዓመት የስራ ዘመን 17ኛ መደበኛ ጉባኤ የቀረበለትን የዋና አስተዳዳሪ ሹመት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
በዚህም መሠረት አቶ ማቲዎስ ሎምበሶ በድጋሚ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል።
ሹመቱን ተከትሎ አቶ ማቲዎስ ሎምበሶ ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።
መረጃው የሀዲያ ዞን መ/ኮ/ጉ መምሪያ ነው።
@tikvahethiopia
የሀዲያ ዞን ምክር ቤት እያካሄደ በሚገኘው 5ኛ ዙር 9ኛ ዓመት የስራ ዘመን 17ኛ መደበኛ ጉባኤ የቀረበለትን የዋና አስተዳዳሪ ሹመት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
በዚህም መሠረት አቶ ማቲዎስ ሎምበሶ በድጋሚ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል።
ሹመቱን ተከትሎ አቶ ማቲዎስ ሎምበሶ ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።
መረጃው የሀዲያ ዞን መ/ኮ/ጉ መምሪያ ነው።
@tikvahethiopia
"... የፌዴራል መንግስት በልዩ ሁኔታ ካለው መጠባበቂያ በጀት ላይ ክልሉን እንዲያግዝ ጠይቀናል" - ዶ/ር ጥላሁን መሃሪ
የአማራ ክልል መንግስት ከፍተኛ የበጀት ጫና ውስጥ እንደሚገኝ የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮው ይህን ያሳወቀው ለሸገር ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።
ፌዴራል መንግስት ለክልሉ በሚደለድለው በጀት ውዝግብ ውስጥ እንደነበረ ያሳታወሰው ቢሮው በክልሉ ያጋጠመው ወቅታዊ ሁኔታ ተጨምሮ ችግሩ መበርታቱን ገልጿል።
የእንደ አማራ ክልል ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ መረጃ ዘንድሮ በጀት ሰማንያ ቢሊዬን አንድ መቶ አራት ሚሊዮን ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ሺ ሶስት መቶ ዘጠና ሰባት ብር ነው።
የክልሉ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጥላሁን መሃሪ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 በሰጡት ቃል በበጀት ዙሪያ ያለውን ቅሬታ እንደሚከተለው አብራርተዋል ፦
" መጀመሪያ በ1999 ዓ/ም የህዝብ እና ቤቶች ቆጠራ ተደርጎ መረጃ ሲወጣ ብዙ ክርክር የተደረገበት፣ ውዝግብም የነበረበት እንደሆነ ይታወቃል።
በወቅቱ የአማራ ህዝብ አመታዊ የእድገት ምጣኔ 1.7 ፐርሰንት ተብሎ ነበር የተሰላው፤ ይህም ከሁሉም የሀገሪቱ ክልል #የመጨረሻው ነው።
ይህ ግን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር ሲተያይ ብዙ አሳማኝ ያልሆኑ ነገሮች እንዳሉ ያመላክታል።
የአማራ ክልል ህዝብ ከሌላው ክልል ህዝብ የተለየ ባህሪ የለውም፤ የተለየ የእድገት ምጣኔ ሊኖረው የሚችልበት አሳማኝ ምክንያት የለውም።
ይሄ እንደገና መታየት አለበት በትክክል አልተሰራም ፣ ስህተቶች አሉ የሚል ቅሬታ ነበር በወቅቱ ፤ ይህን መሰረት ተደርጎ ኢንተርሴንሳል ሳምፕሊንግ መንገድ ተጠቅመው እንደገና የህዝብ እና ቤት ቆጠራ ይደረጋል በየክልሎቹ 2004 ዓ/ም 2005 ዓ/ም ይመስኛል ድጋሚ ቆጠራ ተደርጎ ሳምፕል ተወስዶ የእድገት ምጣኔው ወደ 2.34 ፐርሰንት አድጓል በሚል ማሻሻያ ተደርጎ ቀርቧል።
በዛ ፐርሰንት ካደገ ከታች ጀምሮ 1999 ፣ 1998 ዓ/ም የነበረው ቤዙ በዛ ደረጃ ቢያንስ ሙሉ ይቆጠር የሚለውን ትተትን በዛ ብቻ መስተካከል ነበረበት ያ ስላልተስተካከለ አጠቃላይ ክልሉ ለበጀት ክፍፍል ታሳቢ የሚደረግበት የህዝብ ቁጥር እንዲያንስ ተደርጓል ፤ ብዙ የበጀት ማከፋፈያ ቀመሩ ላይ የተካተቱት ብዙ ፓራሜትሮች ደግሞ የህዝብ ቁጥርን መሰረት ያደረጉ ናቸው "
ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Sheger-FM-10-21-2
የአማራ ክልል መንግስት ከፍተኛ የበጀት ጫና ውስጥ እንደሚገኝ የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮው ይህን ያሳወቀው ለሸገር ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።
ፌዴራል መንግስት ለክልሉ በሚደለድለው በጀት ውዝግብ ውስጥ እንደነበረ ያሳታወሰው ቢሮው በክልሉ ያጋጠመው ወቅታዊ ሁኔታ ተጨምሮ ችግሩ መበርታቱን ገልጿል።
የእንደ አማራ ክልል ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ መረጃ ዘንድሮ በጀት ሰማንያ ቢሊዬን አንድ መቶ አራት ሚሊዮን ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ሺ ሶስት መቶ ዘጠና ሰባት ብር ነው።
የክልሉ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጥላሁን መሃሪ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 በሰጡት ቃል በበጀት ዙሪያ ያለውን ቅሬታ እንደሚከተለው አብራርተዋል ፦
" መጀመሪያ በ1999 ዓ/ም የህዝብ እና ቤቶች ቆጠራ ተደርጎ መረጃ ሲወጣ ብዙ ክርክር የተደረገበት፣ ውዝግብም የነበረበት እንደሆነ ይታወቃል።
በወቅቱ የአማራ ህዝብ አመታዊ የእድገት ምጣኔ 1.7 ፐርሰንት ተብሎ ነበር የተሰላው፤ ይህም ከሁሉም የሀገሪቱ ክልል #የመጨረሻው ነው።
ይህ ግን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር ሲተያይ ብዙ አሳማኝ ያልሆኑ ነገሮች እንዳሉ ያመላክታል።
የአማራ ክልል ህዝብ ከሌላው ክልል ህዝብ የተለየ ባህሪ የለውም፤ የተለየ የእድገት ምጣኔ ሊኖረው የሚችልበት አሳማኝ ምክንያት የለውም።
ይሄ እንደገና መታየት አለበት በትክክል አልተሰራም ፣ ስህተቶች አሉ የሚል ቅሬታ ነበር በወቅቱ ፤ ይህን መሰረት ተደርጎ ኢንተርሴንሳል ሳምፕሊንግ መንገድ ተጠቅመው እንደገና የህዝብ እና ቤት ቆጠራ ይደረጋል በየክልሎቹ 2004 ዓ/ም 2005 ዓ/ም ይመስኛል ድጋሚ ቆጠራ ተደርጎ ሳምፕል ተወስዶ የእድገት ምጣኔው ወደ 2.34 ፐርሰንት አድጓል በሚል ማሻሻያ ተደርጎ ቀርቧል።
በዛ ፐርሰንት ካደገ ከታች ጀምሮ 1999 ፣ 1998 ዓ/ም የነበረው ቤዙ በዛ ደረጃ ቢያንስ ሙሉ ይቆጠር የሚለውን ትተትን በዛ ብቻ መስተካከል ነበረበት ያ ስላልተስተካከለ አጠቃላይ ክልሉ ለበጀት ክፍፍል ታሳቢ የሚደረግበት የህዝብ ቁጥር እንዲያንስ ተደርጓል ፤ ብዙ የበጀት ማከፋፈያ ቀመሩ ላይ የተካተቱት ብዙ ፓራሜትሮች ደግሞ የህዝብ ቁጥርን መሰረት ያደረጉ ናቸው "
ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Sheger-FM-10-21-2
Telegraph
Sheger FM
"... የፌዴራል መንግስት በልዩ ሁኔታ ካለው መጠባበቂያ በጀት ላይ ክልሉን እንዲያግዝ ጠይቀናል" - ዶ/ር ጥላሁን መሃሪ የአማራ ክልል መንግስት ከፍተኛ የበጀት ጫና ውስጥ እንደሚገኝ የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አሳውቋል። ቢሮው ይህን ያሳወቀው ለሸገር ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው። ፌዴራል መንግስት ለክልሉ በሚደለድለው በጀት ውዝግብ ውስጥ እንደነበረ ያሳታወሰው ቢሮው በክልሉ ያጋጠመው ወቅታዊ ሁኔታ…
#Balderas : አቶ እስክንድር ነጋ ማረሚያ ቤት ውስጥ ድብደባ እንደተፈፀመባቸው ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ገለፀ።
አቶ እስክንድር በተፈፀማባቸው ድብደባ ምክንያት ጉልበታቸው መቁሰሉን ዋና ሳጅን መስፍን ይልማ (የቂሊንጦ ወህኒ ቤት የፈረቃ ሓላፊ) ለፍርድ ቤት መናገራቸውን ፓርቲው ገልጿል።
አቶ እስክንድር ዛሬ ችሎት መቅረብ እንዳልቻሉ ተገልጿል።
በዚህም ምክንያት በተከታታይ ምስክር የመስማት ቀጠሮ ተሰርዞ ፤ ለፊታችን ሰኞ ጥቅምት 15 ቀን 2014 ዓ.ም መዘዋወሩን ባልደራስ አሳውቋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ችሎት ለመታደም የተገኙ በጅምላ ታፍሰው ልደታ ፖሊስ ጣቢያ መምሪያ ተወስደዋል ሲል ፓርቲው በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
አቶ እስክንድር በተፈፀማባቸው ድብደባ ምክንያት ጉልበታቸው መቁሰሉን ዋና ሳጅን መስፍን ይልማ (የቂሊንጦ ወህኒ ቤት የፈረቃ ሓላፊ) ለፍርድ ቤት መናገራቸውን ፓርቲው ገልጿል።
አቶ እስክንድር ዛሬ ችሎት መቅረብ እንዳልቻሉ ተገልጿል።
በዚህም ምክንያት በተከታታይ ምስክር የመስማት ቀጠሮ ተሰርዞ ፤ ለፊታችን ሰኞ ጥቅምት 15 ቀን 2014 ዓ.ም መዘዋወሩን ባልደራስ አሳውቋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ችሎት ለመታደም የተገኙ በጅምላ ታፍሰው ልደታ ፖሊስ ጣቢያ መምሪያ ተወስደዋል ሲል ፓርቲው በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ እና በኬንያ ድንበር አካባቢዎች የእንስሳት ክትባት ዘመቻ እየተካሄደ ነው።
የኢትዮጵያ ግብርና ሚኒስቴር ድንበር ተሻጋሪ ተዛማች የእንስሳት በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በኬንያ እና ኢትዮጵያ ድንበር አካባቢዎች የእንስሳት ክትባት ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑን አሳውቋል።
ለክትባት ዘመቻው ድጋፍ ያደረገው የክፍለ አህጉራዊ የአርብቶአደር ኑሮ ማቋቋሚያ ፕሮጀክት (RPLRP) መሆኑ የተገለፀ ሲሆን እኤአ ከ2018 ጀምሮ 8 ሚሊዮን እንስሳትን እንዲከተቡ በማድረግ ረገድ 300 ሺህ አባወራዎችንና እማወራዎችን ተጠቃሚ አድርጓጋ።
የክትባት ዘመቻው ዛሬ በኢትዮጵያ በኩል በቦረና ዞን ሞያሌ ወረዳ የተለያዩ እንስሳትን በመከተብ የተጀመረ ሲሆን በነገው ዕለት ደግሞ በኬንያ በኩል እንደሚካሄድ የሚኒስቴሩ መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ግብርና ሚኒስቴር ድንበር ተሻጋሪ ተዛማች የእንስሳት በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በኬንያ እና ኢትዮጵያ ድንበር አካባቢዎች የእንስሳት ክትባት ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑን አሳውቋል።
ለክትባት ዘመቻው ድጋፍ ያደረገው የክፍለ አህጉራዊ የአርብቶአደር ኑሮ ማቋቋሚያ ፕሮጀክት (RPLRP) መሆኑ የተገለፀ ሲሆን እኤአ ከ2018 ጀምሮ 8 ሚሊዮን እንስሳትን እንዲከተቡ በማድረግ ረገድ 300 ሺህ አባወራዎችንና እማወራዎችን ተጠቃሚ አድርጓጋ።
የክትባት ዘመቻው ዛሬ በኢትዮጵያ በኩል በቦረና ዞን ሞያሌ ወረዳ የተለያዩ እንስሳትን በመከተብ የተጀመረ ሲሆን በነገው ዕለት ደግሞ በኬንያ በኩል እንደሚካሄድ የሚኒስቴሩ መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
#HappeningNow : የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት 2ኛ ዙር የጸረ ሽምቅ ፖሊስ በባምባሲ ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ እያስመረቀ ይገኛል።
Photo Credit : BGMMA
@tikvahethiopia
Photo Credit : BGMMA
@tikvahethiopia
#Sudan : ሱዳን በወረራ በያዘችው በኢትዮጵያ ግዛት ስር በነበረው " አልፋሽቃ " ከ25 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ142 ሺህ 800 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የተዘራ ሰብል ሰበሰብኩ አለች።
ይህ አካባቢ ሱዳን ባሳለፍነው ዓመት በወረራ መያዟ ይታወቃል።
በምስራቅ ሱዳን የሚገኘው የገዳሪፍ ክልል የግብርና ቢሮ ተጠባባቂ ሚኒስትር አህመድ ሃሳ አሎባ በሰጡት መግለጫ፤ “ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት አልፋሽቃ ስኬታማ የግብርና ስራ አከናውናለች” ብለዋል።
“በአሁኑ የእርሻ ወቅት በአልፋሽቃ ምንም አይነት የፀጥታ ችግር አልነበረም” ያሉት አህመድ ሃሳ አሎባ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ባለው የድንበር ውዝግብ ምክንያት የእርሻ ስራው የፀጥታ ስጋት ባለባቸው ስፍራዎች በሀገሪቱ ታጣቂ ሀይሎች መከናወኑንም አስታውቀዋል።
በዘንድሮው የእርሻ ወቅት በአልፋሽቃ በ142 ሺ 800 ሄክታር መሬት ላይ በተከናወነው ስራ ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ እና ማሽላ በስፋት መመረቱን ያስታወቁት ተጠባባቂ ሚኒስትሩ፤ የሱፍ አበባን ጨምሮ ሌሎችም የቅባት እህሎች መሰብሰባቸውን ገልፀዋል።
አልፋሽቃ ላለፉት 25 ዓመታት በኢትዮጵያ ግዛት ስር የነበረ ሲሆን፤ ኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የተለያዩ የእርሻ ስራዎችን ሲያከናውኑበት ነበረ።
ይህን አካባቢ ካለፈው አመት አንስቶ የሱዳን ጦር በወረራ ይዞታል።
ኢትዮጵያ የሱዳን ጦር ከያዛቸው ሉዓላዊ የኢትዮጵያ መሬቶች ለቆ እንዲወጣ እና ከአሁን ቀደም የተጀመሩ ድርድሮች እንዲቀጥሉ፤ በእነዚህ አካባቢዎች ድልድይና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን መገንባቱን እንዲያቆም ጭምር አሳስባ እንደነበር አይዘነጋም።
Credit : አል ዓይን
@tikvahethiopia
ይህ አካባቢ ሱዳን ባሳለፍነው ዓመት በወረራ መያዟ ይታወቃል።
በምስራቅ ሱዳን የሚገኘው የገዳሪፍ ክልል የግብርና ቢሮ ተጠባባቂ ሚኒስትር አህመድ ሃሳ አሎባ በሰጡት መግለጫ፤ “ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት አልፋሽቃ ስኬታማ የግብርና ስራ አከናውናለች” ብለዋል።
“በአሁኑ የእርሻ ወቅት በአልፋሽቃ ምንም አይነት የፀጥታ ችግር አልነበረም” ያሉት አህመድ ሃሳ አሎባ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ባለው የድንበር ውዝግብ ምክንያት የእርሻ ስራው የፀጥታ ስጋት ባለባቸው ስፍራዎች በሀገሪቱ ታጣቂ ሀይሎች መከናወኑንም አስታውቀዋል።
በዘንድሮው የእርሻ ወቅት በአልፋሽቃ በ142 ሺ 800 ሄክታር መሬት ላይ በተከናወነው ስራ ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ እና ማሽላ በስፋት መመረቱን ያስታወቁት ተጠባባቂ ሚኒስትሩ፤ የሱፍ አበባን ጨምሮ ሌሎችም የቅባት እህሎች መሰብሰባቸውን ገልፀዋል።
አልፋሽቃ ላለፉት 25 ዓመታት በኢትዮጵያ ግዛት ስር የነበረ ሲሆን፤ ኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የተለያዩ የእርሻ ስራዎችን ሲያከናውኑበት ነበረ።
ይህን አካባቢ ካለፈው አመት አንስቶ የሱዳን ጦር በወረራ ይዞታል።
ኢትዮጵያ የሱዳን ጦር ከያዛቸው ሉዓላዊ የኢትዮጵያ መሬቶች ለቆ እንዲወጣ እና ከአሁን ቀደም የተጀመሩ ድርድሮች እንዲቀጥሉ፤ በእነዚህ አካባቢዎች ድልድይና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን መገንባቱን እንዲያቆም ጭምር አሳስባ እንደነበር አይዘነጋም።
Credit : አል ዓይን
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Mekelle : በትግራይ ክልል መዲና መቐለ ዛሬ ጥዋት የአየር ጥቃት መፈፀሙን ሮይተርስ የክልሉን ቴሌቪዥን ዋቢ አደርጎ ዘግቧል። አጃንስ ፍራንስ ፕሬስም በመቐለ የአየር ጥቃት መፈፀሙን የረድኤት ተቋማት ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። የዛሬ ጥዋቱ ጥቃት በዚህ ሳምንት ሁለተኛው ነው ተብሏል። የጥዋቱ የአየር ድብዳ መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ በተባለው ተቋም ኢላማ ያደረገ እንደነበርም ተሰምቷል።…
#Mekelle : በዛሬው ዕለት በትግራይ ክልል መዲና መቐለ የአየር ጥቃት መፈፀሙን ሮይተርስ ዘግቧል።
የዛሬው ጥቃት በአራት ቀናት ውስጥ ለ3ኛ ጊዜ የተፈፀመ ነው።
የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ዛሬ ሐሙስ የአየር ጥቃት መፈጸሙን አረጋግጠዋል።
የዛሬው የአየር ድብደባ ኢላማ ያደረገው የቀድሞ የኢትዮጵያ ሠራዊት ይዞታ የነበረ (ሰሜን ዕዝ)ና በአሁኑ ጊዜ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር /TPLF/ የማሰልጠኛ ማዕከል መሆኑን ዶ/ር ለገሰ ለሮይተርስ ተናግረዋል።
ዶክተር ለገሰ ፥ የአየር ድብደባው የተፈፀመው በወታደራዊ ስፍራ ስለሆነ ምንም የሲቪሎች ጉዳት አልደረሰም ብለዋል።
የዛሬው ጥቃት ከሰዓት ከ9 ሰዓት በኋላ የተፈጸመ መሆኑን ተገልጿል።
@tikvahethiopia
የዛሬው ጥቃት በአራት ቀናት ውስጥ ለ3ኛ ጊዜ የተፈፀመ ነው።
የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ዛሬ ሐሙስ የአየር ጥቃት መፈጸሙን አረጋግጠዋል።
የዛሬው የአየር ድብደባ ኢላማ ያደረገው የቀድሞ የኢትዮጵያ ሠራዊት ይዞታ የነበረ (ሰሜን ዕዝ)ና በአሁኑ ጊዜ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር /TPLF/ የማሰልጠኛ ማዕከል መሆኑን ዶ/ር ለገሰ ለሮይተርስ ተናግረዋል።
ዶክተር ለገሰ ፥ የአየር ድብደባው የተፈፀመው በወታደራዊ ስፍራ ስለሆነ ምንም የሲቪሎች ጉዳት አልደረሰም ብለዋል።
የዛሬው ጥቃት ከሰዓት ከ9 ሰዓት በኋላ የተፈጸመ መሆኑን ተገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን እና የጋና ጨዋታ በደቡብ አፍሪካ ኦርላዶ ስታዲየም እንዲካሄድ #ኢትዮጵያ መርጣለች።
የባሕር ዳር ስታዲየም በካፍ ከታገደ በኋላ ኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታውን ከሀገር ውጭ ለማድረግ በመገደዱ፤ የኢ.እ.ፌ በአማራጭነት ኬንያ፣ ዚምቧቤን እና ደቡብ አፍሪካን መርጧል።
ሶስቱም ሀገራት ይህንን ጨዋታ ለማስተናገድ ፈቃደኝነታቸውን የገለጹ ሲሆን፤ የዚምቧቤ ስታዲየም የዚምቧቤን እና የኢትዮጵያን ጨዋታ ብቻ እንዲያስተናግድ በገደብ የተፈቀደለት እንጂ ሌላ ጨዋታ ማካሄድ እንደማይችል ካፍ በማረጋገጡ፤ ኬንያ ፈቃደኝነቷን የገለጸች ቢሆንም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ ዚምቧቤ ለመጨረሻ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታው ማቅናቱ ስለማይቀር፤ በአንድ የአውሮፕላን ጉዞ እና መጠነኛ ወጪ ጨዋታውን በደቡብ አፍሪካ ለማድረግ ወስኗል።
በመሆኑም ጨዋታው ፊፋ በሚያስቀምጠው ቀን በደቡብ አፍሪካ ኦርላዶ ስታዲየም ለማድረግ የኢ.እ.ፌ ከደቡብ አፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር ተስማምቷል።
Credit : EFF
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን እና የጋና ጨዋታ በደቡብ አፍሪካ ኦርላዶ ስታዲየም እንዲካሄድ #ኢትዮጵያ መርጣለች።
የባሕር ዳር ስታዲየም በካፍ ከታገደ በኋላ ኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታውን ከሀገር ውጭ ለማድረግ በመገደዱ፤ የኢ.እ.ፌ በአማራጭነት ኬንያ፣ ዚምቧቤን እና ደቡብ አፍሪካን መርጧል።
ሶስቱም ሀገራት ይህንን ጨዋታ ለማስተናገድ ፈቃደኝነታቸውን የገለጹ ሲሆን፤ የዚምቧቤ ስታዲየም የዚምቧቤን እና የኢትዮጵያን ጨዋታ ብቻ እንዲያስተናግድ በገደብ የተፈቀደለት እንጂ ሌላ ጨዋታ ማካሄድ እንደማይችል ካፍ በማረጋገጡ፤ ኬንያ ፈቃደኝነቷን የገለጸች ቢሆንም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ ዚምቧቤ ለመጨረሻ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታው ማቅናቱ ስለማይቀር፤ በአንድ የአውሮፕላን ጉዞ እና መጠነኛ ወጪ ጨዋታውን በደቡብ አፍሪካ ለማድረግ ወስኗል።
በመሆኑም ጨዋታው ፊፋ በሚያስቀምጠው ቀን በደቡብ አፍሪካ ኦርላዶ ስታዲየም ለማድረግ የኢ.እ.ፌ ከደቡብ አፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር ተስማምቷል።
Credit : EFF
@tikvahethiopia
ዛሬ 3ኛው ዙር ከፍተኛ የፌደራል ግብር ከፋዮች የእውቅና ስነስርዓት ጠ/ሚ ዶ/ት ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ተከናውኗል።
ስነ ስርዓቱ በአንድነት ፓርክ የተከናወነው ሲሆን የአሠራር ሂደታቸውን ኃላፊነት በተሞላው መንገድ ላከናወኑ እና በወቅቱ ግብር ለከፈሉ 300 የንግድ አካላት እውቅና ተሰጥቷል።
እውቅና የተሰጣቸው አካላት ብዛት ካለፈው ዓመት ሲነጻጸር በ100 ብልጫን ማሳየቱ አበረታች መሆኑም ተገልጿል።
በተጨማሪ ፦
• ኸርበርግ ሮስ ኃ.የተ.የግ.ማ፣
• አርዱነጃ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ፣
• አፐር ናይል ትሬዲንግ የተሰኙት 3 ተቋማት ኃላፊዎች ሙስናን በማጋለጥ ልዩ ተሸላሚዎች ሆነዋል፡፡
ይህ ዓመታዊ የእውቅና መርኃ ግብር መላው የንግድ ማኅበረሰብ ሕግን አክብሮ ሁሉን የሚጠቅም ሥራን እንዲከውን ለማበረታታት የታለመ መሆኑን ከጠ/ሚ ፅ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
ስነ ስርዓቱ በአንድነት ፓርክ የተከናወነው ሲሆን የአሠራር ሂደታቸውን ኃላፊነት በተሞላው መንገድ ላከናወኑ እና በወቅቱ ግብር ለከፈሉ 300 የንግድ አካላት እውቅና ተሰጥቷል።
እውቅና የተሰጣቸው አካላት ብዛት ካለፈው ዓመት ሲነጻጸር በ100 ብልጫን ማሳየቱ አበረታች መሆኑም ተገልጿል።
በተጨማሪ ፦
• ኸርበርግ ሮስ ኃ.የተ.የግ.ማ፣
• አርዱነጃ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ፣
• አፐር ናይል ትሬዲንግ የተሰኙት 3 ተቋማት ኃላፊዎች ሙስናን በማጋለጥ ልዩ ተሸላሚዎች ሆነዋል፡፡
ይህ ዓመታዊ የእውቅና መርኃ ግብር መላው የንግድ ማኅበረሰብ ሕግን አክብሮ ሁሉን የሚጠቅም ሥራን እንዲከውን ለማበረታታት የታለመ መሆኑን ከጠ/ሚ ፅ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
#NewsAlert : የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ለተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ሹመት መስጠቱን አሳወቀ።
የክልሉ ፕሬዜዳንት አቶ አሻድሊ ሃሰን ፥ ዛሬ የተሰጠው ሹመት 6ኛው ጠቅላላ ምርጫ በክልሉ ሙሉ በሙሉ ተካሂዶ መንግስት እስኪመሰረት ድረስ የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ነው ብለዋል።
በዚህም መሰረት ፦
- ከቤኒሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ (ቤህነን) አቶ አብዱሠላም ሸንገል የክልሉ መንገድ እና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ፣
- ከቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ቦዴፓ) አቶ አመንቴ ገሺ የክልሉ መሬት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ጽህፈት ቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።
በተጨማሪ ፦
-ከቤህነን ፓርቲ አቶ መርቀኔ አዙቤር የክልሉ ዳያስፖራ ጽህፈት ቤት ሃላፊ እና አቶ መሃመድ እስማኤል ደግሞ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ፣
- ከቦዴፓ ፓርቲ አቶ መልካሙ ጅራ የመተከል ዞን ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።
Credit : ENA
@tikvahethiopia
የክልሉ ፕሬዜዳንት አቶ አሻድሊ ሃሰን ፥ ዛሬ የተሰጠው ሹመት 6ኛው ጠቅላላ ምርጫ በክልሉ ሙሉ በሙሉ ተካሂዶ መንግስት እስኪመሰረት ድረስ የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ነው ብለዋል።
በዚህም መሰረት ፦
- ከቤኒሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ (ቤህነን) አቶ አብዱሠላም ሸንገል የክልሉ መንገድ እና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ፣
- ከቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ቦዴፓ) አቶ አመንቴ ገሺ የክልሉ መሬት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ጽህፈት ቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።
በተጨማሪ ፦
-ከቤህነን ፓርቲ አቶ መርቀኔ አዙቤር የክልሉ ዳያስፖራ ጽህፈት ቤት ሃላፊ እና አቶ መሃመድ እስማኤል ደግሞ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ፣
- ከቦዴፓ ፓርቲ አቶ መልካሙ ጅራ የመተከል ዞን ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።
Credit : ENA
@tikvahethiopia