#Debark : የመስቀል በዓል በደባርቅ ተከበረ።
በበዓሉ የስሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኂሩያን እስጢፋኖስ ጥፍጤ፣ የደባርቅ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሰለሞን ተዘራ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ የሃይማኖቱ ተከታዮች በተገኙበት ነው የተከበረው።
የፀሎት ስነ ስርዓት ተካሂዶ ደመራው 5:30 በሀይማኖት አባቶች ፣ በሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ክቡር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ሰለሞን ተዘራና የባህል ቱሪዝም ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ችሎት ተቀባ በተገኙበት ተለኩሷል።
Credit : Debark Communication
@tikvahethiopia
በበዓሉ የስሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኂሩያን እስጢፋኖስ ጥፍጤ፣ የደባርቅ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሰለሞን ተዘራ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ የሃይማኖቱ ተከታዮች በተገኙበት ነው የተከበረው።
የፀሎት ስነ ስርዓት ተካሂዶ ደመራው 5:30 በሀይማኖት አባቶች ፣ በሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ክቡር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ሰለሞን ተዘራና የባህል ቱሪዝም ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ችሎት ተቀባ በተገኙበት ተለኩሷል።
Credit : Debark Communication
@tikvahethiopia
#Assosa : በአሶሳ ከተማ የጋሪ-ዎሮ የቦሮ-ሽናሻ የዘመን መለወጫ በዓል ተከበረ።
በበዓሉ የብሔረሰቡ ባህላዊ ቱፊቶች የሚንጸባረቁበት፣ አዛውንት እስከ ህጻናት በጋራ ተሰባስበው የሚያከብሩት በዓል ነው።
የብሔረሰቡ አባቶች መጪው ዘመን የሠላም፣ የጤና፣ የአብሮነትና የአንድነት ዘመን እንዲሆን መርቀዋል።
@tikvahethiopia
በበዓሉ የብሔረሰቡ ባህላዊ ቱፊቶች የሚንጸባረቁበት፣ አዛውንት እስከ ህጻናት በጋራ ተሰባስበው የሚያከብሩት በዓል ነው።
የብሔረሰቡ አባቶች መጪው ዘመን የሠላም፣ የጤና፣ የአብሮነትና የአንድነት ዘመን እንዲሆን መርቀዋል።
@tikvahethiopia
#Metekel : በሀገር መከላከያ እና ፌዴራል ፖሊስ ስልጠና የተሰጣቸው 265 ሚሊሻዎች ዛሬ ተመረቁ።
ዛሬ የተመረቁት ሚሊሻዎች የመተከልን ሰላም ለመመለስ ሲስለጥኑ የቆዩ እንደሆኑ ተገልጿል።
በአካባቢው የሚገኛው ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ኮ/ል መልካሙ በየነ ፥ መከላከያ ሰራዊት እና በፌዴራል ፖሊስ አማካኝነት ህብረተሰቡ ራሱን እንዲከላከል እና ፀረ ሰላም ሃይሎችን ለህግ አሳልፎ እንዲሰጥ አስፈላጊው ወታደራዊ ስልጠና ተሰጥቷል ማለታቸውን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ይፋ ባደረገው መረጃ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
ዛሬ የተመረቁት ሚሊሻዎች የመተከልን ሰላም ለመመለስ ሲስለጥኑ የቆዩ እንደሆኑ ተገልጿል።
በአካባቢው የሚገኛው ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ኮ/ል መልካሙ በየነ ፥ መከላከያ ሰራዊት እና በፌዴራል ፖሊስ አማካኝነት ህብረተሰቡ ራሱን እንዲከላከል እና ፀረ ሰላም ሃይሎችን ለህግ አሳልፎ እንዲሰጥ አስፈላጊው ወታደራዊ ስልጠና ተሰጥቷል ማለታቸውን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ይፋ ባደረገው መረጃ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#Syria : በርካታ የውጭ ኃይሎች እጃቸውን በከተቱበትና 10 ዓመታትን በዘለቀው የሶሪያ እርስ በእርስ ጦርነት ቢያንስ 350,209 ሰዎች እንደተገደሉ UN እአአ ከ2014 ወዲህ ባደረገው የመጀመሪያ ይፋዊ የሞት ቁጥር አስታውቋል።
ይህ ቁጥር ግን ድርጀቱ ማንነታቸው የለያቸው ሰዎች እንጂ በጦርነቱ የተገደሉ ሰዎችን ቁጥር በትክክል አያሳይም ተብሏል።
UN ከ2014 በኋላ የሟቾችን ቁጥር መመዝገብ በይፋ አቁሞ ነበር። ምክንያቱም ድርጅቱ መረጃው የተመሰረተው በሶሪያ ይንቀሳቀሱ የነበሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የነበሩ ሲሆን ከጦርነቱ መፋፋም ጋር ተያያዞ የድርጅቶቹ ቁጥር በመመናመኑ የተነሳ መሬት ላይ ያለውን የሟቾቹን ቁጥር በትክክለኛው የሚያሳይ መረጃም ለማግኘት ተቸግሮ ነበር።
ነገር ግን ጦርነቱ በዚህ አመት 10 አመት ማስቆጠሩን ተከትሎ UN የሰብዓዊ መብቶች ም/ቤት ለሰብዓዊ መብቶች ፅ/ቤት በአገሪቱ ውስጥ ምን ያህል ሰዎች እንደተገደሉ ለማወቅ እንዲሞክር ተጠይቋል።
ባለፈው ዓርብ ለም/ቤቱ ሪፖርት ያደረጉት የተመድ የሰብዓዊ መብት ኃላፊ ሚሸል ባችሌት "ውስብስብና አድካሚ ስራ" ያሉት ሲሆን ተለይተው የታወቁ ሟቾች ቁጥር 350,209 ነው ብለዋል።
ሟቾቹ የሲቪልና ተዋጊዎችን ቁጥር ያካተተ ሲሆን ጊዜው ከአውሮፓውያኑ 2011-2021 ነው።
የሰብዓዊ መብት ኃላፊዋ ከሟቾች ውስጥ እንደ የሴቶች ሟቾች አኃዝ ሁሉ የህፃናት ሟቾች ቁጥር 8 በመቶ ገደማ ነው።
በሶሪያ ጦርነት ከሀገሪቱ መንግስት እና ተቃዋሚዎች ውጪ የሩሲያ፣ አሜሪካ፣ ቱርክ፣ ኢራን ሌሎችም ኃይሎች እጅ ያለበት ሲሆን የውጭ ኃይሎቹ እንደግፈዋለን ለሚሉት አካል መሳሪያ በማቅረብ፣ ቢሊዮን ዶላሮችን በማፍሰስ፣ ወታደር በመላክ ፣ በማሰልጠን፣ የአየር ድብደባ በመፈፀም ተሳትፈዋል በሲቪሎች ግድያ ውስጥም እጃቸው አለበት።
@tikvahethiopia
ይህ ቁጥር ግን ድርጀቱ ማንነታቸው የለያቸው ሰዎች እንጂ በጦርነቱ የተገደሉ ሰዎችን ቁጥር በትክክል አያሳይም ተብሏል።
UN ከ2014 በኋላ የሟቾችን ቁጥር መመዝገብ በይፋ አቁሞ ነበር። ምክንያቱም ድርጅቱ መረጃው የተመሰረተው በሶሪያ ይንቀሳቀሱ የነበሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የነበሩ ሲሆን ከጦርነቱ መፋፋም ጋር ተያያዞ የድርጅቶቹ ቁጥር በመመናመኑ የተነሳ መሬት ላይ ያለውን የሟቾቹን ቁጥር በትክክለኛው የሚያሳይ መረጃም ለማግኘት ተቸግሮ ነበር።
ነገር ግን ጦርነቱ በዚህ አመት 10 አመት ማስቆጠሩን ተከትሎ UN የሰብዓዊ መብቶች ም/ቤት ለሰብዓዊ መብቶች ፅ/ቤት በአገሪቱ ውስጥ ምን ያህል ሰዎች እንደተገደሉ ለማወቅ እንዲሞክር ተጠይቋል።
ባለፈው ዓርብ ለም/ቤቱ ሪፖርት ያደረጉት የተመድ የሰብዓዊ መብት ኃላፊ ሚሸል ባችሌት "ውስብስብና አድካሚ ስራ" ያሉት ሲሆን ተለይተው የታወቁ ሟቾች ቁጥር 350,209 ነው ብለዋል።
ሟቾቹ የሲቪልና ተዋጊዎችን ቁጥር ያካተተ ሲሆን ጊዜው ከአውሮፓውያኑ 2011-2021 ነው።
የሰብዓዊ መብት ኃላፊዋ ከሟቾች ውስጥ እንደ የሴቶች ሟቾች አኃዝ ሁሉ የህፃናት ሟቾች ቁጥር 8 በመቶ ገደማ ነው።
በሶሪያ ጦርነት ከሀገሪቱ መንግስት እና ተቃዋሚዎች ውጪ የሩሲያ፣ አሜሪካ፣ ቱርክ፣ ኢራን ሌሎችም ኃይሎች እጅ ያለበት ሲሆን የውጭ ኃይሎቹ እንደግፈዋለን ለሚሉት አካል መሳሪያ በማቅረብ፣ ቢሊዮን ዶላሮችን በማፍሰስ፣ ወታደር በመላክ ፣ በማሰልጠን፣ የአየር ድብደባ በመፈፀም ተሳትፈዋል በሲቪሎች ግድያ ውስጥም እጃቸው አለበት።
@tikvahethiopia
"በጅማ ኤርፖርት ፍንዳታ አልደረሰም፤ በረራም አልቆመም" - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
በአንዳንድ የማህበራዊ ትስስር ገፆች በጅማ ኤርፖርት ፍንዳታ እንደደረሰና በረራም እንደቆመ ተደርጎ የሚናፈሰው ወሬ #ፍፁም_ሐሰት መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አረጋግጧል።
በአሁኑ ሰዓት በጅማ መደበኛ የኤርፖርት እና የበረራ ስራዎቻችን በተለመደው መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ ሲልም አየር መንገዱ አሳውቋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
@tikvahethiopia
በአንዳንድ የማህበራዊ ትስስር ገፆች በጅማ ኤርፖርት ፍንዳታ እንደደረሰና በረራም እንደቆመ ተደርጎ የሚናፈሰው ወሬ #ፍፁም_ሐሰት መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አረጋግጧል።
በአሁኑ ሰዓት በጅማ መደበኛ የኤርፖርት እና የበረራ ስራዎቻችን በተለመደው መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ ሲልም አየር መንገዱ አሳውቋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
@tikvahethiopia
ፎቶ : የጅማ ኤርፖርት መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው። ኤርፖርቱም አልተዘጋም።
በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በኤርፖርቱ ፍንዳታ እና አደጋ እንዳጋጠመ ፤ ኤርፖርቱም እንደተዘጋ የሚናፈሰው ወሬ ሀሰት ነው።
ጅማ ኤርፖት ፍንዳታ ደረሰ እያሉ ሲያሰራጩ ከነበሩት መካከል የውጭ ሀገራት ሚዲያዎች እንዲሁም ውጭ ሀገር ሆነው በኢትዮጵያ ጉዳይ የሚፅፉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ይገኙበታል።
ይህንን ሀሰተኛ መረጃ በርካቶች ሲያጋሩት ነበር።
የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ካሳሁን ጎፌ ድርጊቱ ከእውነት የራቀ እና የሃሰት ዜናዎችን በመዘገብ ህብረተስቡን ማሸበር እና ስጋት ማጫር የሚፈልጉ አካላት ሴራ ነው ያሉት ሲሆን ሁሉም አካል መደበኛ የትራንስፖርት እንቅስቃሴውን እንዳያስተጏጉል አሳስበዋል።
Photo Credit : Kominikeeshinii Magaalaa Jimmaa
@tikvahethiopia
በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በኤርፖርቱ ፍንዳታ እና አደጋ እንዳጋጠመ ፤ ኤርፖርቱም እንደተዘጋ የሚናፈሰው ወሬ ሀሰት ነው።
ጅማ ኤርፖት ፍንዳታ ደረሰ እያሉ ሲያሰራጩ ከነበሩት መካከል የውጭ ሀገራት ሚዲያዎች እንዲሁም ውጭ ሀገር ሆነው በኢትዮጵያ ጉዳይ የሚፅፉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ይገኙበታል።
ይህንን ሀሰተኛ መረጃ በርካቶች ሲያጋሩት ነበር።
የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ካሳሁን ጎፌ ድርጊቱ ከእውነት የራቀ እና የሃሰት ዜናዎችን በመዘገብ ህብረተስቡን ማሸበር እና ስጋት ማጫር የሚፈልጉ አካላት ሴራ ነው ያሉት ሲሆን ሁሉም አካል መደበኛ የትራንስፖርት እንቅስቃሴውን እንዳያስተጏጉል አሳስበዋል።
Photo Credit : Kominikeeshinii Magaalaa Jimmaa
@tikvahethiopia
#Gondar : ዛሬ በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ የመስቀል በዓል ተከብሯል።
በዓሉ በልዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ነው የተከበረው።
ፎቶ : HENA (Gondar Tikvah Family)
@tikvahethiopia
በዓሉ በልዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ነው የተከበረው።
ፎቶ : HENA (Gondar Tikvah Family)
@tikvahethiopia