TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
በደሴ ከተማ ተሰብስቦ ጫት መቃም እና ማስቃም ታገደ። የደሴ ከተማ አስተዳደር ለሀሰተኛ መረጃ መሰራጨት እና ለህዝቡ አለመረጋጋት ምክንያት እንደሆነ የገለፀውን ተሰብስቦ ጫት መቃም እና ማስቃም እንዲሁም ሺሻ ቤቶችን በይፋ ከልክሏል። ከትላንት ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገው ይህን ውሳኔ የተላለፈ አካል በህግ ተጠያቂ ይሆናል። የደሴ ከንቲባ አበበ ገ/መስቀል ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ፥ "ጫት ማስቃም እና ሺሻ ቤቶች…
"...ከዛሬ ጀምሮ በጎንደር ከተማ ጫት ከሌላ አካባቢ ማጓጓዝ ፣ መቸርቸር፣ ማከፋፈል፣ ማስቃምና መቃም ተከልክሏል" - ከጎንደር ከተማ የፀጥታ ም/ቤት

የጎንደር ከተማ የፀጥታ ም/ቤት ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ባስተላለፈው አስቸኳይ ውሳኔ ከዛሬ ነሃሴ 28 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በከተማዋ ጫት ከሌላ አካባቢ ማጓጓዝ፣ መቸርቸር ማከፋፈል፣ ማስቃምና መቃም መከልከሉን አሳውቋል።

ም/ቤቱ፥ ሽብረተኛ ድርጅት ተብሎ የተፈረጀው ህወሓት ከሌሎች ፅንፈኛ ፀረኢትዮጵያ ኃይሎች ጋር በመሆን በአማራ ክልል ወረራ በፈፀመባቸው አካባቢዎች ህዝቡ ላይ ሁሉንም አይነት ግፍ እየፈፀመ ነው፤ የበቀል በትሩንም ማሳረፍ ጀምሯል ብሏል።

ም/ ቤቱ ፤ "ወረራውን ሊመክት የሚችል የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት አስተማማኝ እንዲሆን የሚያደርግ መንፈሰ ጠንካራ ወጣት ሀይል በስነ ልቦና የተገነባ ትውልድ ደግሞ ሃገርን ከጥቃትና ከወረራ እንዲሁም ከጥፋት መታደግ የሚቻለው ከሱስ የፀዳ በስነ ምግባር የታነፀ በመሆኑ ይህንን ትውልድ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት መነሻ በማድረግ በከተማው በጫት አቅራቢዎች አጓጓዦች፣ አከፋፋዮች፣ ቸርቻሪዎች አስቃሚዎቾና ተጠቃሚዎች ላይ የክልከላ ውሳኔ ተላልፋል" ሲል አሳውቋል።

በመሆኑም ከነገ ጀምሮ ምክር ቤቱ ክልከላ ባደረገባቸው ተግባራት ላይ ሲሳተፍ የሚገኝ ተሽከርካሪ ግለሰብም ሆነ ድርጅት በህግ የሚጠየቅ መሆኑን ምክር ቤቱ አሳስቧል።

የተላለፈውን ክልከላ የከተማዎ የፀጥታ ሃይል ተከታትሎ እንዲያስፈፀም ታዟል ተብሏል።

በሌላ በኩል ፀጥታ ምክር ቤቱ በጎንደር ከተማ በጫት ንግድ የተሰማሩ የከተማው ህብረተሰብ ክፍሎች ዘርፍ ቀይረው በሌሎች የንግድ የአገልግሎትና ማኒፋክቸሪንግ ዘርፎች ለመሰማራት በተቋቋመው ግብረ ሃይል አማካኝነት አስፈላጊውን ጥረት እና እገዛ ይደረግላቸዋል ብሏል።

@tikvahethiopia
#GERD #FDREDefenseForce

ሀገር መከላከያ ሰራዊት፥ ኢትዮጵያ እየገነባች ያለውን ግዙፉን የታላቁ ሕዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን በአልምሃል ሰርጎ ለመግባት የሞከረውን የህወሓት ቅጥረኛ ሃይል ደመሰስኩኝ አለ።

የግድቡን ግንባታ ለማደናቀፍ ተልዕኮ ውስደው የተንቀሳቀሱና ሰራዊቱ የማያዳግም እርምጃ የወሰደባቸው ኃይሎች (የተገደሉ) በቁጥር 50 ሲሆኑ ፤ ከ70 በላይ የሚሆኑት ቁስለኛ ሆነዋል።

መከላከያ ሰራዊት ፥ እርምጃ የወሰደበት ኃይል የተለያዩ ፀረ ሰው እና ፀረ ተሽከርካሪ ፈንጂዎችን ለማጥመድ መሞከሩን ነገር ግን መቋቋም ተስኖት መበታተኑን አሳውቋል።

ይኸው ጥፋት ሊፈፅም የነበረው ኃይል ይጠቀምባቸው የነበሩ ቀላል እና ከባድ የቡድን መሳሪያዎች፣ ፈንጂዎች ወድመዋል ፤ የተቀሩትን ሰራዊቱ ተቆጣጥሯቸዋል።

የመተከል ዞን የተቀናጀ ግብረ ሃይል ኮማንድ ፖስት የኦፕሬሽን ዘርፍ አሰተባባሪ ኮ/ል ሰይፈ ኢንጊ ፣ "አሸባሪው ሕወሃት በግንባር ድል አልቀና ሲለው አብዛኝው ጦር ወደ ሰሜኑ ክፍል አቅንቷል በሚል ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ተቀናጅቶ የህዳሴ ግድባችንን ስራ ለማስተጓጎል ለማጥቃት ቢሞክርም አልተሳካለትም" ብለዋል።

በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሃይል፣ እግረኛና ሜካናይዝድ ክፍለጦሮች እንዲሁም የክልል ልዩ ኃይሎች አስፈላጊውን ዝግጁነት በማረጋገጥ ግዳጃቸውን እየፈፀሙ እንደሚገኙ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
#አሁን

"የኢትዮጵያ ዳር ድንበር ያልተቋጨ የቤት ሥራ" በሚል ርዕስ በዶክተር በለጠ በላቸው ይሁን ተፅፎ በ "ኢትዮጵያ አካዳሚክ ፕሬስ" የታተመ መፅሐፍ በሂልተን ሆቴል የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ፣ ሙሁራን ፣ የሚዲያ ባለሞያዎችና የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት በመመረቅ ላይ ይገኛል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ የመክፈቻና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት የተላለፈ ሲሆን በደንበር ጉዳዮች ዙርያ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች የሚመረምሩና የሚያጠኑ እንዲሁም በተግባር ስራ የሚሳተፉ ባለሞያዎች በመፅሐፉ ዙርያ ግመገማ ቀርቦ ውይይት በመከናዎን ላይ ይገኛል።

Via Bereket H.

@tikvahethiopia
#NewsAlert

የዋጋ ንረት በህብረተሰቡ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ ስንዴ ፣ ዘይት ፣ ስኳር እና ሩዝ ከቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆኑ ተወሰነ።

ፖስታ ፣ ማካሮኒ እና እንቁላል ደግሞ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንደተነሳላቸው የገንዘብ ሚኒስቴር ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

የቀረጥ እና የታክስ ማሻሻያው ላልተወሰነ ጊዜ እንደሚቆይ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የዋጋ ንረት በህብረተሰቡ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ ስንዴ ፣ ዘይት ፣ ስኳር እና ሩዝ ከቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆኑ ተወሰነ። ፖስታ ፣ ማካሮኒ እና እንቁላል ደግሞ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንደተነሳላቸው የገንዘብ ሚኒስቴር ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። የቀረጥ እና የታክስ ማሻሻያው ላልተወሰነ ጊዜ እንደሚቆይ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ዛሬ በሰጡት መግለጫ…
በመሰረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላይ የተፈረገው የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያ፦

የኢፌዴሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ከፊስካል ፖሊሲ አኳያ መሰረታዊ የምግብ ሸቀጦችን የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያ በማዘጋጀት ከነሐሴ 28/2013 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ በሚከተሉት መሰረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላይ የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያ እንዲደረግ ወስኗል።

• ስንዴ ከውጭ ሲገባ ከጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆን፣
• የምግብ ዘይት ከውጭ ሲገባም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጸምበት ከማንኛውም ቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆን
• ስኳር ከውጭ ሲገባም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጸምበት ከማንኛውም ቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆን
• ሩዝ ከውጭ ሲገባም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጸምበት ከማንኛውም ቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆን
• ፓስታ እና ማኮረኒ ከውጭ ሲገባም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጸምበት ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ እንዲሆን እንዲሁም
• የደሮ እንቁላል ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ እንዲሆን

ማሻሻው ተግባራዊ ሲደረግ መንግስት በብዙ ቢሊዮን የሚገመት ገቢ እንደሚያጣ በተደረገ ጥናት ተረጋግጧል።

የዋጋ ንረት በታክስ ብቻ የሚፈለገውን የዋጋ መቀነስ ስለማያመጣ አቅርቦትን ለመጨመር መንግስት በከፍተኛ ወጪ በመግዛት በዝቅተኛ ዋጋ ለህብረተሰቡ ከሚያቀርባቸው ከነዚህ መሰረታዊ የምግብ ሸቀጦች በተጨማሪ በሌሎች አካላት የሚገባውን በማከል አቅርቦቱ በከፍተኛ ደረጃ ይጨምር ዘንድ ለስድስት ወር ተፈቅዶ የነበረው ያለውጭ ምንዛሬ ሸቀጦችን የማስገባት አስራር ለሌላ ተጨማሪ 6 ወራት እንዲራዘም ተደርጓል።

ከዚህ ተጨማሪም መንግስት የዋጋ ግሽበቱን ለመቆጠር እና ገበያውን ለማረጋጋት ተጨማሪ የገንዘብ ፖሊሲን ጨምሮ ሌሎች የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይወስዳል።

#DrEyobTekalgn #MinistryofFinance

@tikvahethiopia
#Amhara #OCHA

የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ አገኘሁ ተሻገር ከተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UNOCHA) የኢትዮጵያ ኃላፊ ማርሲ ቪጎዳ ጋር ውይይት አድርገዋል።

አቶ አገኘሁ በሽብርተኛ ድርጅትነት የተፈረጀው "ህወሓት" በአማራ ክልል ወረራ ፈጽሞ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጥቃት እየፈጸመ መሆኑን ለማርሲ ቪጎዳ ገልፀዋል።

ቡድኑ ንጹሐን ዜጎችን በአስቃቂ ሁኔታ እየገደለና እያሳደደ መሆኑን የገለፁት ፕሬዜዳንቱ በክልሉ በከፈተው ጦርነት ከ550 ሺ በላይ ዜጎች መፈናቀላቸውን አመልክተዋል።

ቡድኑ ሀገር የማፍረስ ተግባር እና በዜጎች ላይ ያደረሰውን ጥቃት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል።

የሽብር ቡድኑ እያሳደዳቸውና እያፈናቀላቸው ላሉ ዜጎቻችን ሰብዓዊ ድጋፍ ከማቅረብ ጀምሮ አጋርነታቸውን በተግባር ማሳየት አለባቸው ብለዋል።

"እየተሳደዱ እየተጠቁ ላሉት ዜጎቻችን ድምጽ የሚሆኗቸውና ከጎናቸው የሚሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትን ማዬት እንሻለን" ያሉት አቶ አገኘሁ "የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮም የተፈናቀሉ ዜጎቻችንን ጉዳይ ተረድቶ ድጋፍ እንዲያደርግ እንፈልጋለን ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ የኢትዮጵያ ኀላፊ ማርሲ ቪጎዳ ተቋማቸው ለአማራ ክልል ለሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል 148 ሚሊዮን ብር መመደባቸውን ገልጸዋል፡፡

UNOCHA በፍትሐዊነት ላይ የተመሰረተ ድጋፍ የሚያደርግ በመሆኑ በቀጣይ ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን ለመርዳት ዝግጁ ነን ማለታቸውን ከአሚኮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
በቤንሻንጉል ጉሙዝ በሎ ጅጋንፎይ ወረዳ ነሃሴ 24 እና 25/2013 በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት ከ50 በላይ ሴቶች መገደላቸውን የክልሉ ፖሊስ ሪፖርት አደረገ።

የክልሉ ፖሊስ ም/ኮሚሽነር ምስጋናው ኢንጂፈታ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል፤ከ50 በላይ ሴቶችን በጅምላ የገደሉት የ 'ጉህዴን' ታጣቂዎች ናቸው ሲሉ ከሰዋል።

'ጉህዴን' ከዚህ ቀደም በአካባቢው እንደነበር አስታውሰው የሰላም ትግላቸውን ትተው በአፈሙዝ ጥቃት እየፈፀሙ ነው ብለዋል፤ ኃይሉ ከመተከል ዞን ባለፈም ወደካማሺ ዞን መግባቱን ጠቁመዋል።

አካባቢው ላይ በስፋት የጉምዝ ማህበረሰብ እንዳለ በማንሳት ነሃሴ 23 እና ነሃሴ 24 ቡድኑ ከ50 በላይ ሴቶችን በጅምላ መረሸኑን ገልፀዋል።

ም/ኮሚሽነሩ፤ አጠቃላይ የደረሰውን ጉዳት ለማወቅ እና አካባቢውን ከታጠቀው ኃይል ለማስለቀቅ ተጨማሪ ኃይል እየጠየቅን ነው ብለዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ የፀጥታ ኃይሎች በካማሺ 5 ወረዳዎች ከጉህዴን ታጣቂዎች ጋር ውጊያ እያካሄዱ መሆኑንም ም/ኮሚሽነሩ ገልፀዋል።

"እነዚህ ታጣቂዎች ጉምዝን ነፃ እናወጣለን፣ በመሰረተ ልማት ወደኃላ ቀርተናል፣ጉምዝ እራሱን በእራሱ ያስተዳደር የሚሉ...መዓት ነገር ነው የሚያነሱት ነገር ግን ጥያቄያቸውን በሰላም ከማቅረብ ይልቅ ኢ-ህገመንግስታዊ መንገድ ይዘው ነው የሚንቀሳቀሱት" ሲሉ አክለዋል።

ከቡድኑ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ የክልሉ ፖሊስ በርካታ ተጠርጣሪዎችን ማሰሩን ጠቁመዋል። 

ምክትል ኮሚሽነሩ በአካባቢው ባለው የታጣቂዎች እንቅስቃሴ የሱዳን እጅ በጣም ረጅም መሆኑን ያነሱ ሲሆን "በሱዳን አካባቢ የነበረው የፀረ ሰላም እንቅስቃሴ ከፍተኛ ነው፤ በመሳሪያ በሃሳብ፣ እዛ አካባቢ ያሉ ወጣቶችን መልምሎ ሱዳን አስቀምጦ የሚደግፉበትና ሽፋን የሚሰጡበት ሁኔታ አለ" ብለዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/BG-09-03

@tikvahethiopia
የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት በኢኮኖሚው ላይ :

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በይፋዊ የትዊተር ገፁ ዛሬ አመሻሽ ላይ ባሰራጨው አጭር ፅሁፍ ቀደም ብለው የተወሰዱ ርምጃዎች የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት በሀገሪቱ ምጣኔ ሃብት ላይ ከባድ ተጽዕኖ እንዳይፈጥር ማስቻሉን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ህዝብ ከፍተኛ የሰብዓዊ ዕርዳታ ወጭውን እየተጋራ መሆኑን ገልጿል።

እያጠናቀቅን ባለነው በዚህ ነሀሴ ወር ብቻ የኢትዮጵያ መንግሥት ለአስቸኳይ ዕርዳታ 9 ቢሊዮን ብር ወጭ ማድረጉን ጠ/ሚ ፅ/ቤት የገለፀ ሲሆን ውጪው በብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአስቸኳይ ጊዜ ሰብዓዊ አቅርቦት በኩል የወጣ መሆኑን ገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪ በሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ከ7 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶች መጎዳታቸውን በቅርቡ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁን የጠ/ሚር ፅህፈት ቤት አስታውሷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gambella በትላንትናው ዕለት ከጋምቤላ ከተማ 4 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከቀኑ 11 ሰዓት ከ30 አካባቢ ማንነታቸው ያልታወቁ 5 ግለሰቦች በከፈቱት ተኩስ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰው ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የጋምቤላ ክልል የሰላምና ፀጥታ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶማስ ቱት አስታወቁ። ጉዳቱን ተከትሎ በከተማው በተከሰተው ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉንና ሶስት ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት…
#Update

ከሰሞኑን በጋምቤላ ከተማ ተፈጥሮ ከነበረው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 30 ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር እንዳዋለ የክልሉ ፖሊስ ዛሬ አስታውቋል።

የክልሉ ፖሊስ ፥ "በከተማዋ ሽብር ለመፍጠር የተቀነባበረው ሴራ ከሽፎ የአካባቢው ሰላም ወደ ነበረበት ተመልሶ ነዋሪው የተለመደውን የዕለት ተለት ስራውን እያከናወነ ነው" ብሏል ለኢዜአ በሰጠው ቃል።

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት አቡላ ኡቦንግ በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች በሽብርተኝነት በተፈረጁት ህወሓት እና ሸኔ ተላላኪነት በከተማው የጸጥታ ችግር ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ የተጠረጠሩ ናቸው ብለዋል።

ከሰሞኑን ከጋምቤላ ከተማ 4 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ማንነታቸው ያልታወቁ 5 ግለሰቦች በከፈቱት ተኩስ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉ፤ ሁለት ሰው ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ይህን ጉዳቱን ተከትሎም በከተማው በተከሰተው ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉንና ሶስት ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ሪፖርት መደረጉ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 1,354 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ20 ሰዎች ህይወት አልፏል።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጤና ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው ሪፖርት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 6,954 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 1,354 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል። በተመሳሳይ በ24 ሰዓት ውስጥ 20 ዜጎች ህይወታቸው አልፏል።

የፅኑ ታማሚዎች ቁጥር እጅግ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ሲሆን የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 696 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ እና የጋና ፍልሚያ !

የሀገራችን የእግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ከደቂቃዎች በኃላ የጋና ብሄራዊ ቡድንን ይገጥማል።

ግጥሚያው ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ የሚደረግ #ማጣሪያ ሲሆን በጋና ኬፕ ኮስት በተባለው ስታዲየም ነው የሚደረገው።

በቋሚ አሰላለፍ ሀገራችን #ኢትዮጵያን የሚወክሉት ተጫዋቾች የታወቁ ሲሆን እነማን ናቸው የሚለውን በ https://yangx.top/tikvahethsport/20410 መመልከት ይቻላል።

የሀገራችን ብሄራዊ የእግር ኳስ ቡድን አረጓንዴ ቁምጣ ፣ ቢጫ ካሶተኒ ቀይ የሚለብሱ ሲሆን ተፋላሚያችን ጋና ሙሉ ነጭ መለያ ይለብሳል።

ጨዋታውን ጥሩ የኢንተርኔት ግንኙነት ያላችሁ በFIFA ይፋዊ የዩቲዩብ ገፅ በዚህ 👉 https://t.co/j55uaSRXkI መመልከት ትችላላችሁ።

@tikvahethsport ደግሞ የጨዋታውን ሁኔታ እየተከታተለ በፅሁፍ ያሳውቃል።

መልካም ዕድል ለኢትዮጵያችን !

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የኢትዮጵያ እና የጋና ፍልሚያ ! የሀገራችን የእግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ከደቂቃዎች በኃላ የጋና ብሄራዊ ቡድንን ይገጥማል። ግጥሚያው ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ የሚደረግ #ማጣሪያ ሲሆን በጋና ኬፕ ኮስት በተባለው ስታዲየም ነው የሚደረገው። በቋሚ አሰላለፍ ሀገራችን #ኢትዮጵያን የሚወክሉት ተጫዋቾች የታወቁ ሲሆን እነማን ናቸው የሚለውን በ https://yangx.top/tikvahethsport/20410 መመልከት ይቻላል።…
#Update

ለኳታሩ የዓለም ዋንጫ ለማለፍ የምድባቸውን የመጀመሪያ የማጣሪያ ጨዋታ ከጋና ብሄራዊ ቡድን ጋር ያደረጉት ዋልያዎቹ 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት ተሸንፈዋል።

ዋካሶ ብቸኛዋን የጋና ብሔራዊ ቡድን ጎል በመጀመሪያው አጋማሽ ማስቆጥር ችሏል።

ዋልያዎቹ በነገው ዕለት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ሲጠበቅ ወደ ባህር ዳር በዚሁ ዕለት የሚያቀኑ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በኋላ ማክሰኞ #ከዙምቧቡዌ አቻቸው ጋር በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ።

More : @tikvahethsport
#HappeningNow

የኢትዮጵያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት የሁርሶ የኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ምልምል አባላትን እያስመረቀ ይገኛል።

በሀገር መከላከያ ሚኒሰቴር የሰላም ማስከበር ማዕከል የሁርሶ የኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ዛሬ እያስመረቀ የሚገኘው ሶስተኛው ዙር በመሠረታዊ ወታደርነት ያሰለጠናቸውን ምልምል አባላትን ነው።

በምርቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተጨማሪ የመከላከያ ሰራዊት ኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሃኑ ጁላ እንዲሁም ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትእ አቶ ደመቀ መኮንን እንደሚገኙ ኢብኮ ዘግቧል።

@tikvahethiopia