TIKVAH-ETHIOPIA
የአሜሪካ ድሮን ድብደባ ከአንድ ቤተሰብ የ9 ሰዎችን ህይወት አጠፋ። ትላንት አሜሪካ በካቡል የድሮን ጥቃት መፈፀሟን መረጃ መለዋወጣችን ይታወሳል፤ ጥቃቱ የነበረው በካቡል ኤርፖርት ጥቃት ሊፈፅሙ እየተዘጋጁ በነበሩ የአጥፍቶ ጠፊዎች ተሽከርካሪ ላይ ነበር። ከሐሚድ ካርዛይ ኤርፖርት በስተሰሜን በኩል በሚገኝ አንድ ሰፈር ውስጥ በተፈፀመው የድሮን ድብደባ ሰፈሩ በከፍተኛ ፍንዳታ ተናውጦ እንደነበር የአይን…
* KABUL
አሜሪካ በተፈፀመችው የድሮን ጥቃት ምክንያት በካቡል ከተማ የተገደሉ ንፁሃን 10 ሲሆኑ ስርዓተ ቀብራቸው በዛሬው ዕለት ተፈፅሟል።
ከሞቱት 10 ንፁሃን 7ቱ ህፃናት ናቸው።
ዛሬ በተካሄደው ስርዓተ ቀብር ላይ በርካታ ሰዎች የተገኙ ሲሆን በቦታው የነበረው ሁኔታ እጅግ ልብን የሚነካ እንደነበር የአይን እማኞች ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ዛሬ ምሽት ከታሊባን ምንጮች በተገኘ መረጃ የመጨረሻው የአሜሪካ ኃይሎችን የያዘው በረራ ከካቡል ተነስቷል።
በዚህም የአሜሪካ ጦር በአፍጋኒስታን የቆየበት 20 ዓመታት ጊዜ ማብቃቱ እውን ሆኗል።
@tikvahethiopia
አሜሪካ በተፈፀመችው የድሮን ጥቃት ምክንያት በካቡል ከተማ የተገደሉ ንፁሃን 10 ሲሆኑ ስርዓተ ቀብራቸው በዛሬው ዕለት ተፈፅሟል።
ከሞቱት 10 ንፁሃን 7ቱ ህፃናት ናቸው።
ዛሬ በተካሄደው ስርዓተ ቀብር ላይ በርካታ ሰዎች የተገኙ ሲሆን በቦታው የነበረው ሁኔታ እጅግ ልብን የሚነካ እንደነበር የአይን እማኞች ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ዛሬ ምሽት ከታሊባን ምንጮች በተገኘ መረጃ የመጨረሻው የአሜሪካ ኃይሎችን የያዘው በረራ ከካቡል ተነስቷል።
በዚህም የአሜሪካ ጦር በአፍጋኒስታን የቆየበት 20 ዓመታት ጊዜ ማብቃቱ እውን ሆኗል።
@tikvahethiopia
የጨጨሆ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ጉዳት ደረሰበት።
በህ/ተ/ም/ቤት ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው "ህወሓት" በታሪካዊው የጨጨሆ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰበት ዛሬ ሪፖርት ተደርጓል።
ይህን ያሳወቁት የጨጨሆ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ካቴድራል ገዳም ገንዘብ ያዥ መሪጌታ አብራራው መለሰ ናቸው።
ህወሓት ትናንት ምሽት በፈፀመው የከባድ መሳሪያ ጥቃት ቤተክርስቲያኑን መውደሙን ገልፀዋል።
በከባድ መሳሪያው ጥቃት የደረሰ ጉዳይ ዝርዝር ፦
- የቤተክርስቲያኑ 14 መስኮቶች፣ 5 በራፎች፣ ሕንጻውና ጣሪያው ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል።
- በግቢው ውስጥ የሚገኙ ዕጽዋት ወድመዋል።
- የገዳሙ ፍልፍል ዋሻ ፈርሷል።
ቤተክርስቲያኑ ወደነበረበት እንዲመለስ ርብርብ እንዲደረግ ተጠይቋል።
በአካባቢው ሆነው ቤተክርስቲያኑን ያስመቱ ግለሰቦች በጸጥታ አካላት ቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጋቸው ተገልጿል።
የፈለገ ፀሐይ በቅሎ አግት ጨጨሆ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በሦስተኛው ክፍለዘመን እንደተመሰረተ ይነገራል። #AMC
@tikvahethiopia
በህ/ተ/ም/ቤት ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው "ህወሓት" በታሪካዊው የጨጨሆ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰበት ዛሬ ሪፖርት ተደርጓል።
ይህን ያሳወቁት የጨጨሆ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ካቴድራል ገዳም ገንዘብ ያዥ መሪጌታ አብራራው መለሰ ናቸው።
ህወሓት ትናንት ምሽት በፈፀመው የከባድ መሳሪያ ጥቃት ቤተክርስቲያኑን መውደሙን ገልፀዋል።
በከባድ መሳሪያው ጥቃት የደረሰ ጉዳይ ዝርዝር ፦
- የቤተክርስቲያኑ 14 መስኮቶች፣ 5 በራፎች፣ ሕንጻውና ጣሪያው ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል።
- በግቢው ውስጥ የሚገኙ ዕጽዋት ወድመዋል።
- የገዳሙ ፍልፍል ዋሻ ፈርሷል።
ቤተክርስቲያኑ ወደነበረበት እንዲመለስ ርብርብ እንዲደረግ ተጠይቋል።
በአካባቢው ሆነው ቤተክርስቲያኑን ያስመቱ ግለሰቦች በጸጥታ አካላት ቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጋቸው ተገልጿል።
የፈለገ ፀሐይ በቅሎ አግት ጨጨሆ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በሦስተኛው ክፍለዘመን እንደተመሰረተ ይነገራል። #AMC
@tikvahethiopia
#ICRC
ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ አገራት ውስጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ደብዛቸው መጥፋቱ ተገለጸ።
ከ44 ሺህ በላይ ሰዎች በአሁኑ ወቅት በመላው አፍሪካ እንደጠፉ መረጋገጡን የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ (አይሲአርሲ) ዓለም አቀፉን የመጥፋት ቀንን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ከነዚህም ውስጥ 45 በመቶ የሚሆኑት ህፃናት ናቸው ብሏል።
ከነዚህ ከጠፉት 82 በመቶ ያህሉ በግጭት ከሚናጡ ከተባሉ ሰባት አገሮች ብቻ መሆናቸውን ድርጅቱ አስታውቋል።
በአፍሪካ ውስጥ ከጠፉት ሰዎች ጠቅላላ ቁጥር ከግማሽ በላይ ናይጄሪያውያን ናቸው። በአገሪቱ ውስጥ ወደ 24 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች መጥፋታቸው ተመዝግቧል።
በርካቶች የጠፉ ሰዎች ቁጥር የተመዘገበባቸው ሌሎች አገሮች ኢትዮጵያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ ሶማሊያ ፣ ሊቢያ ፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ እና ካሜሩን ይገኙበታል።
ድርጅቱ እንዳመለከተው ባለፈው ዓመት በተከሰቱ ግጭቶችና በሌሎች የጥቃት ዓይነቶች አህጉሪቱ የጠፉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጿል።
በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ወረርሽኝ ምክንያት በተጣሉ ገደቦች የጠፉ ተጎጂዎችን ለማግኘት እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማቀላቀል የሚደረገውን ጥረት እያደናቀፉ እንደሆነ ቢገልፅም የጠፉ ሰዎች የተረሱ ሰዎች አይደሉም ብሏል።
#ቢቢሲ
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ አገራት ውስጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ደብዛቸው መጥፋቱ ተገለጸ።
ከ44 ሺህ በላይ ሰዎች በአሁኑ ወቅት በመላው አፍሪካ እንደጠፉ መረጋገጡን የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ (አይሲአርሲ) ዓለም አቀፉን የመጥፋት ቀንን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ከነዚህም ውስጥ 45 በመቶ የሚሆኑት ህፃናት ናቸው ብሏል።
ከነዚህ ከጠፉት 82 በመቶ ያህሉ በግጭት ከሚናጡ ከተባሉ ሰባት አገሮች ብቻ መሆናቸውን ድርጅቱ አስታውቋል።
በአፍሪካ ውስጥ ከጠፉት ሰዎች ጠቅላላ ቁጥር ከግማሽ በላይ ናይጄሪያውያን ናቸው። በአገሪቱ ውስጥ ወደ 24 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች መጥፋታቸው ተመዝግቧል።
በርካቶች የጠፉ ሰዎች ቁጥር የተመዘገበባቸው ሌሎች አገሮች ኢትዮጵያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ ሶማሊያ ፣ ሊቢያ ፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ እና ካሜሩን ይገኙበታል።
ድርጅቱ እንዳመለከተው ባለፈው ዓመት በተከሰቱ ግጭቶችና በሌሎች የጥቃት ዓይነቶች አህጉሪቱ የጠፉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጿል።
በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ወረርሽኝ ምክንያት በተጣሉ ገደቦች የጠፉ ተጎጂዎችን ለማግኘት እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማቀላቀል የሚደረገውን ጥረት እያደናቀፉ እንደሆነ ቢገልፅም የጠፉ ሰዎች የተረሱ ሰዎች አይደሉም ብሏል።
#ቢቢሲ
@tikvahethiopia
#ALERT🚨
የጤና ሚኒስቴር ካለፉት ስምንት ሳምንታት ወዲህ በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሶስተኛ ማእበል በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋ መሆኑን አስታወቀ።
በጤና ሚኒስቴር የኮቪድ-19 ምላሽ አስተባባሪ አቶ መብራቱ ማሴቦ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናግሩት ፤ የኮቪድ -19 ወረርሽኝ ሶስተኛ ማእበል ላለፉት ስምንት ሳምንታት በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋ መጥቷል።
የወረርሽኙ ማዕበል በተለይ ደግሞ ከሀምሌ ወር የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ጀምሮ መጠነኛ መቀነስ አሳይቶ የነበረ ቢሆንም በነሐሴ ወር እንደ አዲስ ማገርሸቱንና በዚህም ከ600 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በፅኑ ህክምና ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
በቀን ውስጥ ተመርምረው ቫይረሱ እንዳለባቸው የሚረጋገጡ ሰዎች ቁጥር ሃያ በመቶ መድረሱን ያመለከቱት አቶ መብራቱ ፣ በአንድ ቀን ምርመራ ብቻ እስከ 2 ሺ የሚጠጉ ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸው እየታወቀ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በቫይረሱ የተያዙ፣ ምልክቱን ያላሳዩ፣ ያልተመረመሩ በርካታ ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉና የምርመራ አቅም ውስንነትን ከግምት ውስጥ በማስገባት በቀን በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችልም አስታውቀዋል። #ኢፕድ
@tikvahethiopia
የጤና ሚኒስቴር ካለፉት ስምንት ሳምንታት ወዲህ በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሶስተኛ ማእበል በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋ መሆኑን አስታወቀ።
በጤና ሚኒስቴር የኮቪድ-19 ምላሽ አስተባባሪ አቶ መብራቱ ማሴቦ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናግሩት ፤ የኮቪድ -19 ወረርሽኝ ሶስተኛ ማእበል ላለፉት ስምንት ሳምንታት በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋ መጥቷል።
የወረርሽኙ ማዕበል በተለይ ደግሞ ከሀምሌ ወር የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ጀምሮ መጠነኛ መቀነስ አሳይቶ የነበረ ቢሆንም በነሐሴ ወር እንደ አዲስ ማገርሸቱንና በዚህም ከ600 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በፅኑ ህክምና ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
በቀን ውስጥ ተመርምረው ቫይረሱ እንዳለባቸው የሚረጋገጡ ሰዎች ቁጥር ሃያ በመቶ መድረሱን ያመለከቱት አቶ መብራቱ ፣ በአንድ ቀን ምርመራ ብቻ እስከ 2 ሺ የሚጠጉ ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸው እየታወቀ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በቫይረሱ የተያዙ፣ ምልክቱን ያላሳዩ፣ ያልተመረመሩ በርካታ ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉና የምርመራ አቅም ውስንነትን ከግምት ውስጥ በማስገባት በቀን በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችልም አስታውቀዋል። #ኢፕድ
@tikvahethiopia
"...አዲስ ምዕራፍ ተጀምሯል፤ ወታደራዊ ተልዕኮው አልቋል፤ አዲስ ዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮ ተጀምሯል" - አንቶኒ ብሊንከን
20 ዓመታትን በአፍጋኒስታን የቆየችው አሜሪካ ከሀገሪቱ ጠቅልለ ወጥታለች። ትላንት የመጨረሻው የሃገሪቱ ወታደራዊ በረራ ከካቡል ተነስቷል።
የአካባቢው የአሜሪካ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ ጄኔራል ኬኔት ማኬንዚ እንዳሉት የመጨረሻው የሲ17 አውሮፕላን ማክሰኞ ከእኩለ ለሊት በኃላ የአሜሪካ አምባሳደርን ጭምር አሳፍሮ ከካቡል ወጥቷል ብለዋል።
ቀነ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት ከአፍጋኒስታን መውጣት ያልቻሉትን ለመርዳት የዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮው ይቀጥላል ሲሉም አክለዋል።
የመጨረሻው አውሮፕላን ከካቡል ከሄደ በኋላ ታሊባኖች በደስታ ተኩስ ከተማይቱን ሲንጧት ነው ያደሩት።
እስካሁን ባለው ሪፖርት ከ123 ሺህ በላይ ሰዎች ከአፍጋኒስታን ወጥተዋል።
ከመጨረሻው በረራ በኋላ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ባደረጉት ንግግር ፥ "ግዙፍ ወታደራዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ሰብዓዊ ተግባር" እና አሜሪካ እስካሁን ካከናወኗቸው በጣም ፈታኝ ጉዳዮች አንዱ ነው ብለዋል።
አክለውም ፥ "አዲስ ምዕራፍ ተጀምሯል። ወታደራዊ ተልዕኮው አልቋል። አዲስ ዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮ ተጀምሯል" ሲሉ ገልፀዋል።
ብሊንከን ፥ ታሊባን እውቅና ማግኘት እንዳለበትና ይህም የሚወሰነው የገባውን ቃል በመጠበቁና ግዴታዎቹን በመወጣቱ ነው ብለዋል።
በዚህም፦ የሲቪሎች በነጻነት ወደ ሃገሪቱ እንዲገቡ እና እንዲወጡ በመፍቀድ፣ የሴቶችን ጨምሮ የሁሉም አፍጋኒስታውያንን መብቶች መጠበቅ፣ የሽብር ቡድኖችን በመከልከል እንደሚወሰን ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ ፥ አሜሪካ በካቡል ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋሟን አቋርጣ ሥራዎችን ወደ ዶሃ አስተላልፋለች ማለታቸውን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
20 ዓመታትን በአፍጋኒስታን የቆየችው አሜሪካ ከሀገሪቱ ጠቅልለ ወጥታለች። ትላንት የመጨረሻው የሃገሪቱ ወታደራዊ በረራ ከካቡል ተነስቷል።
የአካባቢው የአሜሪካ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ ጄኔራል ኬኔት ማኬንዚ እንዳሉት የመጨረሻው የሲ17 አውሮፕላን ማክሰኞ ከእኩለ ለሊት በኃላ የአሜሪካ አምባሳደርን ጭምር አሳፍሮ ከካቡል ወጥቷል ብለዋል።
ቀነ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት ከአፍጋኒስታን መውጣት ያልቻሉትን ለመርዳት የዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮው ይቀጥላል ሲሉም አክለዋል።
የመጨረሻው አውሮፕላን ከካቡል ከሄደ በኋላ ታሊባኖች በደስታ ተኩስ ከተማይቱን ሲንጧት ነው ያደሩት።
እስካሁን ባለው ሪፖርት ከ123 ሺህ በላይ ሰዎች ከአፍጋኒስታን ወጥተዋል።
ከመጨረሻው በረራ በኋላ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ባደረጉት ንግግር ፥ "ግዙፍ ወታደራዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ሰብዓዊ ተግባር" እና አሜሪካ እስካሁን ካከናወኗቸው በጣም ፈታኝ ጉዳዮች አንዱ ነው ብለዋል።
አክለውም ፥ "አዲስ ምዕራፍ ተጀምሯል። ወታደራዊ ተልዕኮው አልቋል። አዲስ ዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮ ተጀምሯል" ሲሉ ገልፀዋል።
ብሊንከን ፥ ታሊባን እውቅና ማግኘት እንዳለበትና ይህም የሚወሰነው የገባውን ቃል በመጠበቁና ግዴታዎቹን በመወጣቱ ነው ብለዋል።
በዚህም፦ የሲቪሎች በነጻነት ወደ ሃገሪቱ እንዲገቡ እና እንዲወጡ በመፍቀድ፣ የሴቶችን ጨምሮ የሁሉም አፍጋኒስታውያንን መብቶች መጠበቅ፣ የሽብር ቡድኖችን በመከልከል እንደሚወሰን ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ ፥ አሜሪካ በካቡል ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋሟን አቋርጣ ሥራዎችን ወደ ዶሃ አስተላልፋለች ማለታቸውን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
"...አሜሪካ በአፍጋኒስታን ያደረገችውን ወታደራዊ ተልዕኮ አላሳካችም" - የታሊባን ቃል አቀባይ
ታሊባን የአሜሪካ ወታደሮች ከአፍጋኒስታን መውጣታቸው ሀገሪቱን ነጻ እና ሉዓላዊ እንዳደረጋት አስታውቋል።
የታሊባን ቃል አቀባይ ዛቢ ሁላህ ሙጃሂድ ፥ ከካቡል ሃሚድ ካርዛይ አውሮፕላን ማረፊያ ሆነው መግለጫ የሰጡ ሲሆን የቡድናቸው ድል የሁሉም ደስታ መሆኑን ገልፀዋል።
"አሁን ላይ እስላሚክ ኢሚሬትስ ኦፍ አፍጋኒስታን ነጻ እና ሉዓላዊት ሀገር መሆኗን አንጠራጠርም" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ዛቢ ሁላህ ሙጃሂድ በሰጡ መግለጫቸው ፥ አሜሪካ በአፍጋኒስታን ያደረገችውን ወታደራዊ ተልዕኮ አላሳካችም ያሉ ሲሆን አፍጋኒስታን ከምዕራባውያን ጋር የውጭ ግንኙነት ሥራ እንደምትጀምርም ተናግረዋል፡፡
ሀገሪቱ የውጭ ግንኙነት የምትጀምረው የአፍጋኒስታንን ነጻነት እና እስላማዊ እሴቶችን ከሚጠብቁ ሀገራት ጋር እንደሆነም ነው የጠቀሱት።
በሌላ በኩል ፥ የUN የጸጥታው ጥበቃ ም/ቤት ትናንትና ምሽት በአፍጋኒታን ጉዳይ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር፤ በዚህ ሰብሰባ ላይ ታሊባን አፍጋኒስታንን ለቀው መውጣት ለሚፈልጉ ዜጎች ምቹ የመተላለፊያ ሁኔታ እንዲፈጥር፤ ለሀገሪቱ የሰብዓዊ ድጋፍ እንዲዳረስ፤ የሴቶችንን እና ህጻናትን ጨምሮ ሁሉም ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ የውሳኔ ሃሳብ አቅርቧል፡፡
15 አምባሳደሮች ይህንን ውሳኔ ሃሳብ ሲደግፉ ቻይናና ሩሲያ ድጋፍም ተቃውሞም አለማቅረባቸው አላቀረቡም፤ የውሳኔ ሃሳቡ አፍጋኒስታን የሽብርተኝነት መደበቂያ መሆን እንደሌለባትም የሚገልጽ ይዘት እንዳለው ተገልጿል።
የመረጃ ባለቤት ፡ አል ዓይን ኒውስ
@tikvahethiopia
ታሊባን የአሜሪካ ወታደሮች ከአፍጋኒስታን መውጣታቸው ሀገሪቱን ነጻ እና ሉዓላዊ እንዳደረጋት አስታውቋል።
የታሊባን ቃል አቀባይ ዛቢ ሁላህ ሙጃሂድ ፥ ከካቡል ሃሚድ ካርዛይ አውሮፕላን ማረፊያ ሆነው መግለጫ የሰጡ ሲሆን የቡድናቸው ድል የሁሉም ደስታ መሆኑን ገልፀዋል።
"አሁን ላይ እስላሚክ ኢሚሬትስ ኦፍ አፍጋኒስታን ነጻ እና ሉዓላዊት ሀገር መሆኗን አንጠራጠርም" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ዛቢ ሁላህ ሙጃሂድ በሰጡ መግለጫቸው ፥ አሜሪካ በአፍጋኒስታን ያደረገችውን ወታደራዊ ተልዕኮ አላሳካችም ያሉ ሲሆን አፍጋኒስታን ከምዕራባውያን ጋር የውጭ ግንኙነት ሥራ እንደምትጀምርም ተናግረዋል፡፡
ሀገሪቱ የውጭ ግንኙነት የምትጀምረው የአፍጋኒስታንን ነጻነት እና እስላማዊ እሴቶችን ከሚጠብቁ ሀገራት ጋር እንደሆነም ነው የጠቀሱት።
በሌላ በኩል ፥ የUN የጸጥታው ጥበቃ ም/ቤት ትናንትና ምሽት በአፍጋኒታን ጉዳይ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር፤ በዚህ ሰብሰባ ላይ ታሊባን አፍጋኒስታንን ለቀው መውጣት ለሚፈልጉ ዜጎች ምቹ የመተላለፊያ ሁኔታ እንዲፈጥር፤ ለሀገሪቱ የሰብዓዊ ድጋፍ እንዲዳረስ፤ የሴቶችንን እና ህጻናትን ጨምሮ ሁሉም ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ የውሳኔ ሃሳብ አቅርቧል፡፡
15 አምባሳደሮች ይህንን ውሳኔ ሃሳብ ሲደግፉ ቻይናና ሩሲያ ድጋፍም ተቃውሞም አለማቅረባቸው አላቀረቡም፤ የውሳኔ ሃሳቡ አፍጋኒስታን የሽብርተኝነት መደበቂያ መሆን እንደሌለባትም የሚገልጽ ይዘት እንዳለው ተገልጿል።
የመረጃ ባለቤት ፡ አል ዓይን ኒውስ
@tikvahethiopia
#Gambella
በትላንትናው ዕለት ከጋምቤላ ከተማ 4 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከቀኑ 11 ሰዓት ከ30 አካባቢ ማንነታቸው ያልታወቁ 5 ግለሰቦች በከፈቱት ተኩስ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰው ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የጋምቤላ ክልል የሰላምና ፀጥታ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶማስ ቱት አስታወቁ።
ጉዳቱን ተከትሎ በከተማው በተከሰተው ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉንና ሶስት ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል።
በግጭቱ ባጠቃላይ የሶስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አምስት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሷል ብለዋል።
ጥፋተኞቹን ወደህግ ለማቅረብ የፀጥታ አካላት ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ሲሉ ገልፀዋል።
ከግጭቱ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ አስር የሚደርሱ ግለሰቦች ቀደም ብሎ በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ተገቢውን ማጣራት እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ግጭቱ በተፈጠረበት በጋምቤላ ከተማ ያለው ሰላም ወደ ነበረበት እየተመለሰ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ በመጠበቅ ከፀጥታ አካላት ጎን በመሆን አስፈላጊውን መረጃ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
ከጋምቤላ ከተማ ወደ ወረዳዎች የሚንቀሳቀሱ የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲገቡ ተደርጓል፤ ለጊዜው በፀጥታ አካላት እጀባ እንዲሄዱ እየተደረገ ነው ብለዋል።
መረጃው የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት ነው::
@tikvahethiopia
በትላንትናው ዕለት ከጋምቤላ ከተማ 4 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከቀኑ 11 ሰዓት ከ30 አካባቢ ማንነታቸው ያልታወቁ 5 ግለሰቦች በከፈቱት ተኩስ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰው ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የጋምቤላ ክልል የሰላምና ፀጥታ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶማስ ቱት አስታወቁ።
ጉዳቱን ተከትሎ በከተማው በተከሰተው ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉንና ሶስት ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል።
በግጭቱ ባጠቃላይ የሶስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አምስት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሷል ብለዋል።
ጥፋተኞቹን ወደህግ ለማቅረብ የፀጥታ አካላት ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ሲሉ ገልፀዋል።
ከግጭቱ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ አስር የሚደርሱ ግለሰቦች ቀደም ብሎ በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ተገቢውን ማጣራት እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ግጭቱ በተፈጠረበት በጋምቤላ ከተማ ያለው ሰላም ወደ ነበረበት እየተመለሰ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ በመጠበቅ ከፀጥታ አካላት ጎን በመሆን አስፈላጊውን መረጃ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
ከጋምቤላ ከተማ ወደ ወረዳዎች የሚንቀሳቀሱ የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲገቡ ተደርጓል፤ ለጊዜው በፀጥታ አካላት እጀባ እንዲሄዱ እየተደረገ ነው ብለዋል።
መረጃው የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት ነው::
@tikvahethiopia
ዛሬ በቡለን ወረዳ 5 ሚሊሻዎች ተገደሉ።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ስር ወዳለችው ቡለን ወረዳ ዛሬ ረፋዱን በባጃጅ ሲጓዙ የነበሩ 5 ሚሊሺያዎች በታጣቂዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
የክልሉ የሰላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት አልቦሮ፤ በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የጉሙዝ ታጣቂዎች አምስት ሚሊሺያዎችን መግደላቸውን አረጋግጠዋል።
ሚሊሺያዎቹ ጥቃቱ የተፈጸመባቸው “ለአካባቢ መጠበቂያ የሚሆን [ትጥቅ] ሊታጠቁ ወደ ከተማው ማዕከል በመጓዝ ላይ እያሉ” መሆኑን አቶ አብዮት ገልጸዋል።
በመተከል ዞን ከምትገኘው ዶቤ ቀበሌ እንደተነሱ የተነገረላቸው ሚሊሺያዎች፤ ወደ ቡለን ከተማ ሲጓዙ የነበረው በሶስት ባጃጆች ተሳፍረው ነበር ተብሏል።
ታጣቂዎቹ ጥቃቱን የሰነዘሩት በአንደኛው ባጃጅ ውስጥ በነበሩ ሰባት ሚሊሺያዎች ላይ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስረድተዋል።
በጥቃቱም አምስት ሚሊሺያዎች ሲገደሉ፤ ሁለቱ መቁሰላቸውን በቡለን ወረዳ የሚኖሩ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የመንግስት ሰራተኛ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘገባ በዚህ ይገኛል : https://telegra.ph/Ethiopia-Insider-08-31
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ስር ወዳለችው ቡለን ወረዳ ዛሬ ረፋዱን በባጃጅ ሲጓዙ የነበሩ 5 ሚሊሺያዎች በታጣቂዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
የክልሉ የሰላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት አልቦሮ፤ በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የጉሙዝ ታጣቂዎች አምስት ሚሊሺያዎችን መግደላቸውን አረጋግጠዋል።
ሚሊሺያዎቹ ጥቃቱ የተፈጸመባቸው “ለአካባቢ መጠበቂያ የሚሆን [ትጥቅ] ሊታጠቁ ወደ ከተማው ማዕከል በመጓዝ ላይ እያሉ” መሆኑን አቶ አብዮት ገልጸዋል።
በመተከል ዞን ከምትገኘው ዶቤ ቀበሌ እንደተነሱ የተነገረላቸው ሚሊሺያዎች፤ ወደ ቡለን ከተማ ሲጓዙ የነበረው በሶስት ባጃጆች ተሳፍረው ነበር ተብሏል።
ታጣቂዎቹ ጥቃቱን የሰነዘሩት በአንደኛው ባጃጅ ውስጥ በነበሩ ሰባት ሚሊሺያዎች ላይ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስረድተዋል።
በጥቃቱም አምስት ሚሊሺያዎች ሲገደሉ፤ ሁለቱ መቁሰላቸውን በቡለን ወረዳ የሚኖሩ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የመንግስት ሰራተኛ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘገባ በዚህ ይገኛል : https://telegra.ph/Ethiopia-Insider-08-31
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
#Ethiopia #Djibouti
ከሰሞኑን በዩጋንዳ እና ሩዋንዳ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉት እና ከሀገራቱ መሪዎች ጋር የመከሩት የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አሁን ደግሞ ከጎረቤት ሀገር ጅቡቲ ፕሬዜዳንታ ጋር በስልክ ተወያያተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኡመር ጌሌ ጋር የተወያዩት በተለያዩ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ነው። በውይይታቸው የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል ተብሏል።
ዶ/ር ዐቢይ እና ኢማኤል ኡመር ጌሌ በቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያም መክረዋል ፥ የሁለትዮሽ ተጠቃሚነትን በጠበቀ መልኩ የሁለትዮሽና የቀጠናዊ ግንኙነትን ለማጠናከር ተነጋግረዋል።
በጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እንደተገኘው መረጃ።
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን በዩጋንዳ እና ሩዋንዳ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉት እና ከሀገራቱ መሪዎች ጋር የመከሩት የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አሁን ደግሞ ከጎረቤት ሀገር ጅቡቲ ፕሬዜዳንታ ጋር በስልክ ተወያያተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኡመር ጌሌ ጋር የተወያዩት በተለያዩ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ነው። በውይይታቸው የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል ተብሏል።
ዶ/ር ዐቢይ እና ኢማኤል ኡመር ጌሌ በቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያም መክረዋል ፥ የሁለትዮሽ ተጠቃሚነትን በጠበቀ መልኩ የሁለትዮሽና የቀጠናዊ ግንኙነትን ለማጠናከር ተነጋግረዋል።
በጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እንደተገኘው መረጃ።
@tikvahethiopia
የመንግስት ምስረታ የሚካሄድበት ቀን ታወቀ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጪው መስከረም 24 ቀን 2014 ስድስተኛው ዙር የመንግስት ምስረታ እንደሚካሄድ ዛሬ አስታውቋል።
@tikvahethiopia
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጪው መስከረም 24 ቀን 2014 ስድስተኛው ዙር የመንግስት ምስረታ እንደሚካሄድ ዛሬ አስታውቋል።
@tikvahethiopia