TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#EMA

የኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ትላንት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ "አሸባሪዎችን ከእነአስተሳሰባቸው ቀብረን ኢትዮዽያን እናስቀጥላለን" በሚል ርዕስ ያሰፈሩትን ጹሑፍ ተንተርሶ አዲስ ስታንደርድ ሚዲያ ወደ እንግሊዝኛ ሲተረጉመው በዋና ዳይሬክተሩ ያልተባለ እና ከፍተኛ የደኅንነት አንድምታ ያለው መልዕክት ጨምሮ መዘገቡን የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን ገልጿል።

ባለሥልጣኑ ለጃክሊን ፐብሊኬሽን (አዲስ ስታንዳርድ) በጻፈው ደብዳቤ

''...ነውረኛ ድርጊቶች እንኳን ሊገስፁ ቀርቶ እንዲያውም ቀለብ ከመስፈር ጀምሮ የህክምና መድሀኒቶችና የመገናኛ መሳሪያዎችን እያመቻቹ መገኘታቸው ሳያንስ መንግስትን ሲተቹ፤ ሲጎነትሉና ሲያስፈራሩ ማየት ልብን ያደማል፤ ጨጏራ ይመልጣል፤ ቆሽትን ያሳርራል።'' የሚለውን የዋና ዳይሬክተሩን ጹሑፍ

“Let alone condemning, these countries are helping the T.P.L.F. including feeding it, providing medicine, communication equipment and providing arms ” በሚል መተርጎሙ ሀሰተኛ ያልተባለና የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም የሚጎዳ እንደሆነ ያነሳል።

ባለሥልጣኑ ሚዲያው አንባቢውን እና የደኅንነት ተቋሙን ይቅርታ እንዲጠይቅና ለፈጸመው ከባድ ጥፋትም በአስቸኳይ እርማት እንዲያደርግ ያዛል።

አዲስ ስታንደርድ በድረገጹ ላይ ዘገባው ላይ ለነበረው የትርጉም ስህተት በኤዲተሮቹ በኩል ይቅርታ ጠይቋል።

ስህተቱ ''በትርጉም ወቅት የተፈጸመ ስህተት መሆኑን እና የዋና ዳይሬክተሩን መግለጫ በተሳሳተ መንገድ ለማቅረብ የተደረገ ሙከራ አለመሆኑን ለአንባቢዎቻችን ማረጋገጥ እንፈልጋለን'' ብሏል።

telegra.ph/EBA-08-26

@tikvahethiopia
"...በግድ የለሽነት በሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች ላይ የሚደረግ አሉታዊ ፍረጃ ተገቢ አይደለም" - ኢመብባ

በግድ የለሽነት በሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች ላይ የሚደረግ አሉታዊ ፍረጃ ተገቢ አይደለም ሲል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙህኃን ባለስልጣን አሳወቀ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን በቅርቡ ከሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ በህዝብና በንግድ መገናኛ ብዙኋን የተስተዋለው የዘገባ ሽፋን ሙያዊ መርኅን በበቂ ሁኔታ የማያሟላ ነው ሲል ገልጿል።

''በግድ የለሽነት በሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች ላይ የሚደረግ አሉታዊ ፍረጃ ለተጎዱ ዜጎቻችን በትጋት ሰብዓዊ እርዳታ የሚሰጡ በርካቶችን የሚጎዳ ነው። የጅምላ ፍረጃው የማይገመት አደጋ የሚያስከትልም ነው። ሚዛናዊ የአዘጋገብ መርኅም አይደለም።'' ሲል መግለጫው ጠቅሷል።

የመገናኛ ብዙኀን ባለሞያዎች በዜና አዘጋገባቸው ከስሜት ቆስቋሽ ዘገባ ተቆጥበው የላቀ ፍትሐዊና ሚዛናዊ አዘጋገብን ለማረጋገጥ ንቁና ጠንቃቃ እንዲሆኑ በሚያሳስበው በዚሁ የባለሥልጣኑ መግለጫ የግጭት ወቅት ዘገባ ከባድ ኃላፊነት የሚጠይቅ መሆኑን በመጥቀስ ማንኛውም ዋጋ ተከፍሎም ቢሆን ጉዳት ለመቀነስ መሰራት እንዳለበት ጠቁሟል።

ከሰሞኑ የሀገሪቱን ህግና ሥርዓት ባለማክበራቸው ምክንያት የተወሰኑ የሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች በሚመለከተው አካል አስተዳደራዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸውና መገናኛ ብዙኀንም ሁነቱን የተመለከቱ ዘገባዎችን መስራታቸውን ያስታወሰው ባለሥልጣን መስሪያቤቱ ''የመገናኛ ብዙኃን በመረጃ ላይ ተመርኩዘው በተለያዩ አካላት ላይ ምርመራ በማካሄድ እና በማጋለጥ ስህተትን የመግለጥ የጋዜጠኝነት ሞያዊ ሀላፊነታቸውን በመወጣታቸው ሙሉ ለሙሉ እውቅና እየሰጠ ያበረታታል'' ሲል አክሎ ገልጿል።

@tikvahethiopia
"...የእሳት ቃጠሎውን በቀላሉ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል" - አዲስ አበባ ፖሊስ

ዛሬ ነሀሴ 20 ቀን 2013 ዓ/ም ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ፖሊስ በአንድ የአባላት ማረፊያ ክፍል ውስጥ የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ነበር።

የአዲስ አበባ ፖሊስ የተነሳው ቃጠሎ መጠነኛ እንደነበር ገልጾ ፤ ቃጠሎውን በእሳት አደጋ ሰራተኞች እና በፖሊስ አመራርና አባላት ትብብር በቀላሉ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል ሲል ሪፖርት አድርጓል።

የእሳቱ መነሻ መንስኤ እየተጣራ መሆኑን ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TerrorThreat ከቀናት በፊት በአፍጋኒስታን " ካቡል ኤርፖርት " አካባቢ ISIS የሽብር ጥቃት ሊያደርስ መሆኑን መረጃዎች መውጣታቸው ተከትሎ አካባቢው ላይ ውጥረት ስለመንገሱ ሪፖርት መደረጉ ይታወሳል። በወቅቱ የአሜሪካ ኤምባሲ የደህንነት ስጋት እንዳለ ተናግሮ ነገር ግን ስጋቱ ምን እንደሆነ ሳይጠቅስ ከአፍጋኒስታን የሚወጡ የአሜሪካ ዜጎች እና ሌሎችም ወደ አካባቢው እንዳይሄዱ አስጠንቅቆ ነበር።…
#ካቡል

በአፍጋኒስታን ካቡል ኤርፖርት ውጭ ፍንዳታ ተከሰተ።

አሜሪካ፣ ዩናይትስ ኪንግደም፣ አውስትራሊያ ለዜጎቻቸው ማስጠንቀቂያ በሰጡ በሰዓታት ውስጥ በኤርፖርቱ በ "አቤይ መግቢያ" ውጭ በኩል ፍንዳታ ተከስቷል።

ሀገራቱ ጥቃት ሊፈፀም ስለሚችል ከኤርፖርት በውጭ በኩል ያሉ ሰዎች ከአካባቢው በአቸኳይ እንዲርቁ አስጠንቅቀው ነበር።

ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ስለተከሰተው ፍንዳታ የአሜሪካ ባለስልጣናት አረጋግጠዋል፤ ፍንዳታ የቦንብ እንደሆነም ጠቁመዋል።

እስካሁን ምን ያህል ሰው እንደተጎዳ ወይም እንደሞተ ተጨባጭ መረጃ ማግኘት አልተቻለም።

ትላንትና ምሽት ላይ ወደኤርፖርት ለመግባት በአቤይ መግቢያ በኩል 5,000 የሚደርሱ አፍጋናውያን እንዲሁም ምናልባትም የተወሰኑ አሜሪካውያን እንደነበሩ ተነግሯል።

Photo Credit : Zee

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ካቡል በአፍጋኒስታን ካቡል ኤርፖርት ውጭ ፍንዳታ ተከሰተ። አሜሪካ፣ ዩናይትስ ኪንግደም፣ አውስትራሊያ ለዜጎቻቸው ማስጠንቀቂያ በሰጡ በሰዓታት ውስጥ በኤርፖርቱ በ "አቤይ መግቢያ" ውጭ በኩል ፍንዳታ ተከስቷል። ሀገራቱ ጥቃት ሊፈፀም ስለሚችል ከኤርፖርት በውጭ በኩል ያሉ ሰዎች ከአካባቢው በአቸኳይ እንዲርቁ አስጠንቅቀው ነበር። ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ስለተከሰተው ፍንዳታ የአሜሪካ ባለስልጣናት አረጋግጠዋል፤…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update

አሁን ይፋ በሆነ ሪፖርት ከካቡል ኤርፖርት ውጭ በደረሰው ፍንዳታ ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች የተጎዱ ሲሆን ከጎጂዎቹ መካከል የአሜሪካ ሰዎች እንዳሉበት CNN ዘግቧል።

በሌላ በኩል ደግሞ ቃላቸውን ለአልጀዚራ የሰጡ አንድ በታሊባን ቡድን ውስጥ በኃላፊነት ደረጃ ላይ የሚገኙ ግለሰብ ከ " ካቡል ኤርፖርት " ውጭ በደረሰው ፍንዳታ 11 ሰዎች (ህፃናት ልጆችን ጨምሮ) መገደላቸውን ሪፖርት አድርገዋል።

Video Credit : ASVAKA

@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce

የደቡብ ዕዝ ቀዳማዊ የጦር ፍርድ ቤት በሀገር እና በሀገሪቱ ሰራዊት ላይ ክህደት በመፈፀም ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ባላቸው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ እስከ 18 ዓመት የሚደርስ የፅኑ እስራት ቅጣት አስተላልፎባቸዋል።

ተጠርጣሪዎቹ የተከሰሱበት ክስ ዋና ጭብጥ ምንድናቸው ?

- ከሀገር አፍራሽ አሸባሪዎች ጋር ሚስጥራዊ ግንኙነት በመፍጠር የሀገር ደህንነት አደጋ ላይ በመጣል፣
- ክህደት በመፈፀም ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀውን የህወሓት ቡድን ለመቀላቀል በማሴር፣
- ሽብርተኛ ተብሎ ለተፈረጀው የ "ሸኔ" ቡድን መረጃ ማቀበል፣
- ከግዳጅ ቀጠና በመሸሽ የወገን ጦርን ለአደጋ ማጋለጥ፣
- ያለ በቂ ምክንያት ሲቪሎችን በመግደል፣
- የበላይን ትዕዛዝ ችላ በማለት ለንፁሐን ሞት ምክንያት መሆን
- የመንግሥትና የህዝብን ወታደራዊ ንብረትን ይዞ ለመሸሽ ሙከራ ማድረግ የሚሉ ክሶች ዋነኛ ጭብጥ ሆነው ቀርቧል፡፡

ወታደራዊ ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን ሲመረምር ቆይቶ ተከሳሾች እራሳቸውን መከላከል ባለመቻላው የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

በዚህ መሰረት፡-

1. ሻለቃ ክፍሌ ካሳይ በ17 አመት ፅኑ እስራት
2. ኮሎኔል ክፍሌ ፍሰሃዬ በ14 ከ 2 ወር ፅኑ እስራት
3. ሀምሳ አለቃ መብራቱ ጥላዬ በ18 አመት ፅኑ እስራት
4. መሰረታዊ ወታደር መኮንን ክንፈ በ13 አመት ፅኑ እስራት
5. ሀምሳ አለቃ ፈረደ ይባስ በ11 አመት እስራት
6. ምክትል አስር አለቃ ሀጎስ በርሄ በ11 አመት ፅኑ እስራት
7. ምክትል ክፍሌ ንጉስ በ9 አመት ፅኑ እስራት
8. ኮሎኔል ካሱ ሀብቱ በ11 አመት ከ2 ወር
9. ኮሎኔል ሀጎስ አሰፋ በ8 አመት ፅኑ እስራት
10. ሌተናል ኮሎኔል ሀይላይ ገብሩ በ10 አመት ከ2 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወታደራዊ ፍ/ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡

@tikvahethiopia
#ውድ_ቤተሰቦቻችን_ጥንቃቄያችሁን_አጠናክሩ

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 1,621 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ13 ሰዎች ህይወት ደግሞ ጠፍቷል።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጤና ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው ሪፖርት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 10,620 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 1,621 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓታት ውስጥ 13 ዜጎች ህይወታቸው አልፏል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ በ #ኢትዮጵያ ጉዳይ ፦

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ም/ቤት (UNSC) በትግራይ ክልል ግጭት ዙሪያ ትላንት ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ የድርጅቱ ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬስ የተገኙ ሲሆን፤ በጦርነቱ የተካፈሉ አካላት በሙሉ የተኩስ አቁም እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ምንም እንኳን የኢትዮጵያ መንግስት የተናጥል ተኩስ አቁም በማወጅ ከትግራይ ቢወጣም የህወሓት ሀይሎች ወደ ጎረቤት አፋር እና አማራ ክልሎች ጥቃት በመክፈታቸው አጠቃላይ የተኩስ አቁም ላይ መደረስ እንደልተቻለ ገልጸዋል።

ከወራት በፊት በትግራይ ክልል የተከሰተው ግጭት አሁን ላይ እየተስፋፋ መሆኑን እና በርካታ ሰብአዊ ኪሳራዎች እያስከተለ መሆኑን ተናግረዋል።

በጦርነቱ ሳቢያ፦
- የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር በየእለቱ እያሻቀበ መሆኑን
- ከ2 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን ግጭቱን ተከትሎ መፈናቀላቸውን
- ከትግራይ ክልል በተጨማሪም ወደ አማራ እና አፋር ክልል በተስፋፋው ግጭት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን፤
- ከሰብአዊ ቀውስ በተጨማሪም የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ክፉኛ እየተጎዳ መሆኑን
- የበሀገሪቱ የብድር ጣራ እየጨመረ መሆኑን
- ሀገሪቱ እዳ የመክፈል አቅሟ እየተዳከመ መምጣቱን፣
- የኑሮ ውድነቱ በከፍተኛ ሁኔታ እያሸቀበ መምጣቱን ገልፀዋል።

ገተሬስ ፥ የኢትዮጵያ አንድነት እና የቀጠናው መረጋጋት ወሰሳኝ ናቸው ያሉ ሲሆን አሁን ላለው ሁኔታ ወታደራዊ መፍትሄ የለም ሲሉ ተናረዋል።

በጦርነቱ የተካፈሉ አካት በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም እንዲያድርጉ፣ የውጭ ሀገራት ሀይሎች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ፣ ለሰብአዊ ድጋች መተላለፊያ መንገዶች እንዲከፈቱ እና ችግሩን ለመቅረፍ #በኢትዮጵያ_የሚመራና ሁሉንም አካታች የሆነ ውይይት እንዲካሄድ ጥሪ አቅርበዋል።

#Al_AIN

@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሀገራት በፀጥታው ም/ቤት ምን አሉ?

#Russia

በUN ፀጥታ ም/ቤት የሩሲያ ተወካይ የኢትዮጵያ መንግስት ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ ያወጀው የተናጥል የተኩስ አቁም በህወሓት ሀይሎች መጣሱ አሳዛኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የህወሓት ሀይሎች ከትግራይ ውጪ ወደ አማራና አፋር ክልሎች ጥቃት መክፈታውን፤የሀገር ውስጥ ፈናቃዮች ቁጥር በእጥፍ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል።

“የሰብአዊ ድጋፍ ጉዳይን ፖለቲካዊ ማድረግ ተገቢ አይደለም፣ በሚዲያ የሚካሄደው መርዛማ አካሄድ የመሳካት እድሉ አነስተኛ ነው” ብለዋል፤ሰብአዊ ድጋፍ ሲቀርቡ ለትግራይ ብቻ ተብሎ ሳይሆን፤ለአማራ፣ አፋር፣ ሶማሌና ኦሮሚያም ክልሎችም መሆን አለበት ሲሉ ተናግረዋል።

“በኢትዮጵየ ፖለቲካው ውይይት እንደጀመር እንደግፋለን፤ ነገር ግን ውይይቱ ያለማንም ጣልቃ ገብነት #በኢትዮጵያውያን መሪነት ሊካሄድ ይገባል" ብለዋል።

ለኢትዮጵያ ሚደረጉ ድጋፎች የሀገሪቱን ሉአላዊነት እና አንድነት ባስጠበቀ መልኩ ሊካሄድ ይገባል ያሉ ሲሆን፤ ሰኔ ወር በተካሄደው ምርጫ ኢትዮጵያውያን የመረጡት መንግስት ሀገሪቱን ወደቀድሞ መስመር የመመለስ አቅም እንዳለው የሩሲያ መንግስት ያምናል ሲሉ ተግረዋል።

#China

የቻይና ተወካይ በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ ሁሉም አካላት በራሳቸው መንግድ በሚያድርጉት የፖለቲካ ውይይት ልዩነቶቻቸውን እንደሚፈቱ ቻይና ታምለች ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የሰብአዊ ድጋፍ ሰጪ ድርጅቶች ስራቸውን በሚሰሩበት ጊዜ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት ባከበረ መልኩ መሆን ይገባል ብለዋል። ለኢትዮጵያ ሚደረገው የሰብአዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። በሰብአዊ መብትና በሰብዓዊ ድጋፍ ስም በኢትዮጵየ የውስጥ ጉዳይ ላይ የሚደረጉ ጣልቃ ገብነቶችን ቻይና አጥብቃ ትቃወማለች ብለዋል።

ያንብቡ፦ telegra.ph/UNSC-08-27

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በፀጥታው ም/ቤት ስብሰባ የኢትዮጵያ ተወካይ ምን አሉ ?

በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልእክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ፤ የህወሓትን ጸብ አጫሪነት ለምክር ቤቱ ያብራሩ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግሰት ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ ተኩስ አቁም አውጆ መውጣቱ በአካባቢው ለሰብአዊ እንቅቃሴ እንዲሁም ሰላም እና መረጋጋትን ለማምጣት ነበር ብለዋል።

ሆኖም ግን ህወሓት ወደ ተኩስ አቁም የመምጣት ፍላጎት የላቸውም፤ ይባስ ብሎም ህጻናትን ወደ ውትድርና እያስገቡ ነው፤ ወላጆች ልጆቻውን ለውትድርና እንዲሰጡ እርዳታ እህልን እንደ ማስፈራሪያ እየተጠቀሙ ነው ብለዋል።

ህወሓት በአማራ እና በአፋር ክልሎች ላይ በከፈተው ጥቃት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀለቸውን እንዲሁም በህወሓት ተግባር ከትግራይ ክልል በተጨማሪ በአማራ እና አፋር ክልሎች የሚገኙ አርሶ አደሮች የግብርና ስራ መስራ እንዳልቻሉም አስረድተዋል።

ቡድኑ የእርዳታ እህሎች እንቅስቃሴን እያስተጓጎለ መሆኑን በመጥቀስ፤ ሀገሪቱ እንዳትረጋጋ ከተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀይሎች ጋር ጥምረት እየፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ግብ ሰላም ነው፤ ነገር ግን ህወሓት በኢትዮጵያና በሰላም መካከል እንቅፋት ሆኖ ቆሟል ሲሉም ተናግረዋል።

ሁሉም አካል የህወሓት ቡድን ከዚህ ተግባሩ እንዲታቀብ ጫና እንዲፈጥሩ ጥሪ ያቀረቡት አማባሳደር ታዬ ፤ ሁሉም የም/ቤቱ አባላት እውነታ ላይ የተመሰረተ መረጃ ብቻ እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ በልዩነት ውስጥ አንደነትን መፍጠር የቻለች ሀገር ነች፤ አሁን በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለው ለውጥም መድሎን ሳይሆን አንድነትን ማጠናከር ላይ የሚሰራ ነው ብለዋል።

#አልአይን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የደ/ሱዳን ፕሬዚዳንት አዲስ አበባ ገቡ። የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፣ የሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልና የመከለከያ ሚኒስትር ዶክተር ቀነዓ ያደታን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል ተብሏል። በኢትዮጵያ ቆይታቸው…
#Ethiopia #SouthSudan

ወደኢትዮጵያ ለስራ ጉብኝት የመጡት የጎረቤት ሀገር ደ/ሱዳን ፕሬዜዳንት ፥ "ኢትዮጵያ ነጻነቷን እና ሉአላዊነቷን ለማስጠበቅ በምታደርገው የህልውና ዘመቻ እየደረሰባት ያለውን የውጭ ጣልቃ ገብነት አንቀበለም" ማለታቸው ተሰምቷል።

የጠ/ሚ ፅ/ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢልለኔ ስዩም፥ ሳልቫ ኪር ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ጋር በትላንትና እለት ከተወያዩ በኋላ ህወሃት እያደረሰ ያለውን ጥቃት ኮንነዋል ብለዋል።

“የጉብኝቱ ትኩረት ቁልፍ በሆኑ የሁለትዮሽ እና የክልል ጉዳዮች ላይ በጋራ መነጋገር ነበር” ሲሉም አክለዋል፡፡

ኪር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቢትሪስ ዋኒ-ኖህን ጨምሮ ወደ ኢትዮጵያ የመጣው የልዑካን ቡድን ጉብኝት ላይ “በተለይ ትኩረት የሰጠው ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶችን እና የጋራ የመሠረተ ልማት ግንባታን ማጠናከር ነበር” ማለታቸውን ሱዳን ፖስት ዘግቧል፡፡

ፕሬዜዳንት ሳልቫኪየር ፥ ህወሃትን በተመለከተ "ከኢትዮጵያ ጎን እንቆማለን" ስለማለታቸው የተገለፀ ሲሆን በሰኔ ወር የተከናወነው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት መጠናቁንና በአባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተመለከተ ለዶ/ር ዐቢይ አህመድ እንኳን ደስ አለዎት ሰሉ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

መረጃው የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopoa
TIKVAH-ETHIOPIA
#update አሁን ይፋ በሆነ ሪፖርት ከካቡል ኤርፖርት ውጭ በደረሰው ፍንዳታ ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች የተጎዱ ሲሆን ከጎጂዎቹ መካከል የአሜሪካ ሰዎች እንዳሉበት CNN ዘግቧል። በሌላ በኩል ደግሞ ቃላቸውን ለአልጀዚራ የሰጡ አንድ በታሊባን ቡድን ውስጥ በኃላፊነት ደረጃ ላይ የሚገኙ ግለሰብ ከ " ካቡል ኤርፖርት " ውጭ በደረሰው ፍንዳታ 11 ሰዎች (ህፃናት ልጆችን ጨምሮ) መገደላቸውን ሪፖርት አድርገዋል።…
#Kabul

ትላንትና ከካቡል ኤርፖርት ውጭ በተፈፀመው አጥፍቶ ጠፊ የፈንጂ ጥቃት የሟቾች ቁጥር 60 መድረሱ ሪፖርት ተደርጓል።

ከ60 ሟቾች መካከብ 13ቱ የአሜሪካ ወታደሮች ናቸው።

በጥቃቱ የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር በመቶዎች ናቸው።

ለጥቃቱ አፍጋኒስታን የሚገኘውና የISIS የአፍጋን ቅርጫፍ ኃላፊነቱን ወስዷል። ይህ የሽብር ቡድን እጅግ ወግ አጥባቂው የታሊባን ቡድን መለሳለስ የሚታይበት ለዘብተኛ ነው የሚል ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ሌሎች የግድያ ጥቃቶችን የፈጸመ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kabul ትላንትና ከካቡል ኤርፖርት ውጭ በተፈፀመው አጥፍቶ ጠፊ የፈንጂ ጥቃት የሟቾች ቁጥር 60 መድረሱ ሪፖርት ተደርጓል። ከ60 ሟቾች መካከብ 13ቱ የአሜሪካ ወታደሮች ናቸው። በጥቃቱ የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር በመቶዎች ናቸው። ለጥቃቱ አፍጋኒስታን የሚገኘውና የISIS የአፍጋን ቅርጫፍ ኃላፊነቱን ወስዷል። ይህ የሽብር ቡድን እጅግ ወግ አጥባቂው የታሊባን ቡድን መለሳለስ የሚታይበት ለዘብተኛ ነው…
"...ምህረት አይኖረንም፤ አንረሳውምም፤ የገባችሁበት ገብተን እናድናችኋለን፤ ዋጋ እንድትከፍሉም እናደርጋለን" - ጆ ባይደን

የአሜሪካ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን ትላንት በካቡል ከተፈፀመው ጥቃት ጋር በተያያዘ ንግግር አድርገዋል።

የሽብር ጥቃቱን ለፈጸሙትም ሆነ አሜሪካን ለመጉዳት የሚመኙ አካላትን ጠንከር ባለ ንግግራቸው አስጠንቅቀዋል።

ባይደን ፥ "ምህረት አይኖረንም፤ አንረሳውምም፤ የገባችሁበት ገብተን እናድናችኋለን፤ ዋጋ እንድትከፍሉም እናደርጋለን" ሲሉ ዝተዋል።

አሜሪካ እና አፍጋኒስታንን የሚቆጣጠረው ታሊባን ቀደም ሲል በደረሱት ስምምነት መሳረት የአሜሪካ ወታደሮች እና ተልዕኮ ከ4 ቀናት በኋላ የፊታችን ረቡዕ ያበቃል።

የአሜሪካ መከላከያ ሚንስትር ፔንታጎን ተጨማሪ የሽብር ጥቃት ሊኖር ይችላል ሲል ስጋቱን በመግለጥ ጥንቃቄ እንዲደረግ ከወዲሁ አሳስቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ፦ አፍጋኒስታን ውስጥ አሜሪካንን ሲያግዙ ከነበሩ የውጭ ኃይሎች መካከል የጀርመን ወታደሮች ሙሉ በሙሉ ያለምንም ጉዳት ወደ ጀርመን መመለሳቸው ተጠቅሷል።

Source : #DeutscheWelle (DW)

@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የሐዋሳ ሀይቅን የማስዋብ ፕሮጄክትን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል አካባቢን ነፃ ማድረግ ስራ መጀመሩን ከተማ አስተዳደሩ ዛሬ አሳውቋል።

የሐዋሳ ሀይቅ የማስዋብ ስራ በከተማዋ በ2014 በጀት አመት በይፋ ከሚጀመሩ ፕሮጄክቶች መካከል አንዱ እንደሆነ ተገልጿል።

ፕሮጄክቱ ሲጠናቀቅ የሐዋሳን ሀይቅ ለዘርፈ ብዙ የቱሪዝም መስህብነት ብቁ የሚያደርገው ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሐ/ከ/አስ/የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ ገልጿል።

@tikvahethiopia