አሜሪካ በኤርትራ ጦር አዛዥ ላይ ማዕቀብ ጣለች።
አሜሪካ የኤርትራ ጦር በትግራይ ክልል ፈጽሟል ባለችው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ምክንያት በጦሩ ዋና አዛዥ ላይ ማዕቀብ መጣሏን አስታወቀች።
ማዕቀቡ በኤርትራ ጦር ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሀንስ ላይ የተጣለ ነው፡፡
ማዕቀቡን የተጣለው በአሜሪካ የፌዴራል ግምጃ ቤት (ትሬዠሪ) በኩል ሲሆን አዛዡ በአሜሪካ ያላቸው ሀብት እንዲታገድ እንደተወሰነ ግምጃ ቤቱ በድረገጹ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
አሜሪካ በጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሀንስ የሚመራው የኤርትራ ጦር በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ፈጽሟል፤ ሴቶችን ደፍሯል እንዲሁም ወጣቶችን እና ንጹሀን ዜጎችን ቤት ለቤት በመግባት ገድሏል ስትል ከሳለች።
የኤርትራ ጦር የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት የተናጠል የተኩስ አቁም ካደረገ በኋላም ተመልሶ ወደ ትግራይ ክልል ገብቷል የሚለው የአሜሪካ ግምጃ ቤት ጦሩ በአስቸኳይ ወደ ኤርትራ እንዲመለስ ጠይቋል።
ውሳኔው አሜሪካ ለሰብአዊ መብት ጥበቃ ላላት ቁርጠኝነት ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚችልም ነው ግምጃ ቤቱ ያስታወቀው።
አሁንም ጦርነቱ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ነው የሚለው የህ ተቋም በቀጠለው ግጭት ምክንያት እርዳታ የሰብአዊ መብት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ማድረስ ባለመቻሉ ሁሉም አካላት ግጭቱን እንዲያስቆሙ ጠይቋል።
ኤርትራ ማዕቀቡን በተመለከተ እስካሁን የሰጠችው ምላሽ የለም፡፡
የመረጃ ባለቤት፦ አል አይን ኒውስ
@tikvhethiopia
አሜሪካ የኤርትራ ጦር በትግራይ ክልል ፈጽሟል ባለችው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ምክንያት በጦሩ ዋና አዛዥ ላይ ማዕቀብ መጣሏን አስታወቀች።
ማዕቀቡ በኤርትራ ጦር ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሀንስ ላይ የተጣለ ነው፡፡
ማዕቀቡን የተጣለው በአሜሪካ የፌዴራል ግምጃ ቤት (ትሬዠሪ) በኩል ሲሆን አዛዡ በአሜሪካ ያላቸው ሀብት እንዲታገድ እንደተወሰነ ግምጃ ቤቱ በድረገጹ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
አሜሪካ በጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሀንስ የሚመራው የኤርትራ ጦር በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ፈጽሟል፤ ሴቶችን ደፍሯል እንዲሁም ወጣቶችን እና ንጹሀን ዜጎችን ቤት ለቤት በመግባት ገድሏል ስትል ከሳለች።
የኤርትራ ጦር የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት የተናጠል የተኩስ አቁም ካደረገ በኋላም ተመልሶ ወደ ትግራይ ክልል ገብቷል የሚለው የአሜሪካ ግምጃ ቤት ጦሩ በአስቸኳይ ወደ ኤርትራ እንዲመለስ ጠይቋል።
ውሳኔው አሜሪካ ለሰብአዊ መብት ጥበቃ ላላት ቁርጠኝነት ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚችልም ነው ግምጃ ቤቱ ያስታወቀው።
አሁንም ጦርነቱ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ነው የሚለው የህ ተቋም በቀጠለው ግጭት ምክንያት እርዳታ የሰብአዊ መብት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ማድረስ ባለመቻሉ ሁሉም አካላት ግጭቱን እንዲያስቆሙ ጠይቋል።
ኤርትራ ማዕቀቡን በተመለከተ እስካሁን የሰጠችው ምላሽ የለም፡፡
የመረጃ ባለቤት፦ አል አይን ኒውስ
@tikvhethiopia
#መስከረም20
የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ህዝበ ውሳኔ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ/ም እንደሚከናወን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ አስታውቋል።
@tikvahethiopia
የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ህዝበ ውሳኔ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ/ም እንደሚከናወን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ አስታውቋል።
@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#BBC_HARDtalk
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከቢቢሲ ሀርድቶክ ፕሮግራም ጋር ሰኞ ዕለት ቆይታ አድርገው በትግራይ ከተከሰተው ጦርነት ጋር በተያያዘ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ትግራይ ውስጥ ተጀምሮ ሌሎች ክልሎች ስለተስፋፋው ጦርነት ፣ በትግራይ ስለተቋረጡት መሰረታዊ አገልግሎቶች፣ ሰለሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ ስለእርዳታ አቅርቦት እና ተያያዥ ጉዳዮች ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ከስቴፈን ሳከር ተወያይተዋል።
ዶ/ር ጌዲዮን በምን ጉዳዮች ላይ ምላሽ ሰጡ ?
- የሰብዓዊ እርዳታ ጉዳይ
- ሰላማዊ መፍትሔ
- የትግራይ ተወላጆች እስር
- የሰብዓዊ መብት ጥሰት ክሶች
- ስለመሠረታዊ አገልግሎቶች ... ሌሎችም።
ያንብቡ : telegra.ph/BBC-HardTalk-08-24 / ጥሩ የሆነ የኢንተርኔት ግንኙነት ማግኘት ከቻላችሁም ከላይ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Credit : BBC Amharic Service
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከቢቢሲ ሀርድቶክ ፕሮግራም ጋር ሰኞ ዕለት ቆይታ አድርገው በትግራይ ከተከሰተው ጦርነት ጋር በተያያዘ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ትግራይ ውስጥ ተጀምሮ ሌሎች ክልሎች ስለተስፋፋው ጦርነት ፣ በትግራይ ስለተቋረጡት መሰረታዊ አገልግሎቶች፣ ሰለሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ ስለእርዳታ አቅርቦት እና ተያያዥ ጉዳዮች ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ከስቴፈን ሳከር ተወያይተዋል።
ዶ/ር ጌዲዮን በምን ጉዳዮች ላይ ምላሽ ሰጡ ?
- የሰብዓዊ እርዳታ ጉዳይ
- ሰላማዊ መፍትሔ
- የትግራይ ተወላጆች እስር
- የሰብዓዊ መብት ጥሰት ክሶች
- ስለመሠረታዊ አገልግሎቶች ... ሌሎችም።
ያንብቡ : telegra.ph/BBC-HardTalk-08-24 / ጥሩ የሆነ የኢንተርኔት ግንኙነት ማግኘት ከቻላችሁም ከላይ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Credit : BBC Amharic Service
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አሜሪካ በኤርትራ ጦር አዛዥ ላይ ማዕቀብ ጣለች። አሜሪካ የኤርትራ ጦር በትግራይ ክልል ፈጽሟል ባለችው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ምክንያት በጦሩ ዋና አዛዥ ላይ ማዕቀብ መጣሏን አስታወቀች። ማዕቀቡ በኤርትራ ጦር ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሀንስ ላይ የተጣለ ነው፡፡ ማዕቀቡን የተጣለው በአሜሪካ የፌዴራል ግምጃ ቤት (ትሬዠሪ) በኩል ሲሆን አዛዡ በአሜሪካ ያላቸው ሀብት እንዲታገድ እንደተወሰነ…
#Eritrea
ኤርትራ፤ አሜሪካ በሀገሪቱ የጦር መሪ ጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሀንስ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ "መሠረተ ቢስ" ስትል ውድቅ አድርጋዋለች።
ኤርትራ "ህገ ወጥ" ያለችውን የአሜሪካን ማዕቀብ በተመለከተ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል መግለጫ አውጥታለች።
አሜሪካ በጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሀንስ ላይ "ተቀባይነት የሌላቸውን ክሶች ሰንዝሯል" ያለው መግለጫው የኤርትራ መንግስት የተቃጣበትን መሠረተ ቢስ ውንጀላና ክስ በደብዳቤም ሆነ በመንፈስ እንደማይቀበል አስታውቋል።
የአሜሪካ አስተዳደር እንዲህ ዐይነት መሠረተ ቢስ የውንጀላ ዘመቻዎችን በኤርትራ ላይ ሲያርግ የመጀመሪያው እንዳይደለም ሲል ጠቁሟል።
ባሳለፍነው መጋቢት መባቻ ላይ የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዑስማን ሳሌህ ለአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን "እንዳለመታደል ሆኖ በሚዲያዎች በሚነዙ ያልተረጋገጡ መረጃዎች ላይ ተመስርተው ማደማደሚያዎችን ይሰጣሉ" ሲሉ በጻፉት ደብዳቤ "ተከታታይ የአሜሪካ አስተዳደሮች ባለፉት 30 ዓመታት በኤርትራ ላይ ሲያራምዱት ወደነበረው ፖሊሲ የተመለሱ በሚያስመስለው ደብዳቤዎ አዝኛለሁ" ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸው እንደነበር አስታውሷል።
ሚኒስትሩ ወደ ዝርዝር ጉዳዮች አልገባም ባሉበት በዚህ ደብዳቤ መፍትሔዎች ሊኖሩ ይችላሉ በሚል ስለመግለጻቸው ነው የተጠቀሰው።
ኤርትራ ምክንያታዊ ያልሆኑ ተደጋጋሚ ክሶችን በዝምታ ልታልፍ እንደማትችልም ይጠቁማል። "ሃሰተኛ" ያለው ውንጀላ ሊጣራ የሚችል ነገር ካለው በገለልተኛ አካል እንዲጣራም ለአሜሪካ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።
የUN የጸጥታው ም/ቤት ተደጋጋሚ የዓለም አቀፍ ህግጋትና የሃገራትን የሉዓላዊነት ጥሰቶች በመግታትና መፈትሔ በመፈለግ ረገድ ኃላፊነቱን እንዲወጣም አሳስቧል።
(አል-ዓይን)
@tikvahethiopia
ኤርትራ፤ አሜሪካ በሀገሪቱ የጦር መሪ ጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሀንስ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ "መሠረተ ቢስ" ስትል ውድቅ አድርጋዋለች።
ኤርትራ "ህገ ወጥ" ያለችውን የአሜሪካን ማዕቀብ በተመለከተ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል መግለጫ አውጥታለች።
አሜሪካ በጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሀንስ ላይ "ተቀባይነት የሌላቸውን ክሶች ሰንዝሯል" ያለው መግለጫው የኤርትራ መንግስት የተቃጣበትን መሠረተ ቢስ ውንጀላና ክስ በደብዳቤም ሆነ በመንፈስ እንደማይቀበል አስታውቋል።
የአሜሪካ አስተዳደር እንዲህ ዐይነት መሠረተ ቢስ የውንጀላ ዘመቻዎችን በኤርትራ ላይ ሲያርግ የመጀመሪያው እንዳይደለም ሲል ጠቁሟል።
ባሳለፍነው መጋቢት መባቻ ላይ የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዑስማን ሳሌህ ለአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን "እንዳለመታደል ሆኖ በሚዲያዎች በሚነዙ ያልተረጋገጡ መረጃዎች ላይ ተመስርተው ማደማደሚያዎችን ይሰጣሉ" ሲሉ በጻፉት ደብዳቤ "ተከታታይ የአሜሪካ አስተዳደሮች ባለፉት 30 ዓመታት በኤርትራ ላይ ሲያራምዱት ወደነበረው ፖሊሲ የተመለሱ በሚያስመስለው ደብዳቤዎ አዝኛለሁ" ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸው እንደነበር አስታውሷል።
ሚኒስትሩ ወደ ዝርዝር ጉዳዮች አልገባም ባሉበት በዚህ ደብዳቤ መፍትሔዎች ሊኖሩ ይችላሉ በሚል ስለመግለጻቸው ነው የተጠቀሰው።
ኤርትራ ምክንያታዊ ያልሆኑ ተደጋጋሚ ክሶችን በዝምታ ልታልፍ እንደማትችልም ይጠቁማል። "ሃሰተኛ" ያለው ውንጀላ ሊጣራ የሚችል ነገር ካለው በገለልተኛ አካል እንዲጣራም ለአሜሪካ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።
የUN የጸጥታው ም/ቤት ተደጋጋሚ የዓለም አቀፍ ህግጋትና የሃገራትን የሉዓላዊነት ጥሰቶች በመግታትና መፈትሔ በመፈለግ ረገድ ኃላፊነቱን እንዲወጣም አሳስቧል።
(አል-ዓይን)
@tikvahethiopia
#Ethiopia
የዋጋ ንረቱ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ፤ የኑሮ ውድነቱ ከፍ እያለ የሰዎችን ኑሮ በእጅግ እየተፈታተነው ነው።
በተለይ ዝቅተኛ ደሞዝ የሚያገኘ ሰራተኞች ኑሮ ለመግፋት ፈተና እየሆነባቸው ነው፤ በየዕለቱ ሚጨምረው የዋጋ ንረት የኑሮውን ጫና መቋቋም ከማይቻልበት ደረጃ እየደረሰ ነው።
ቤት ኪራይ፣ ምግብ የልጆች ት/ቤት ክፍያ፣ የቀን ወጪ ..ሌሎችም ወጪዎች ሲጨምሩ እንጂ ሲቀንሱ አይታይም፤ የሚገኘው ደሞዝ እዛው ነው።
ከቅርብ ጊዜ በኃላ ደግሞ በኢትዮጵያ ሰሜናዊው ክፍል የተፈጠረውን ጦርነት እንደመልካም አጋጣሚ የተጠቀሙ ነጋዴዎች በተለላያዩ ምርቶች ላይ ያለአንዳች ምክንያት ዋጋ በመጨመር ዜጎችን ክፉኛ እያማረሩ ነው።
በተለያዩ ከተሞች ዋጋን በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ በመንግስት እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ሪፖርት የሚደረግ ቢሆንም አሁንም የሚቀረው ስራ ብዙ ነው።
በሀገሪቱ ውስጥ የሚሰሩ ኢኮሮሚያዊ አሻጥሮች ፣ ሆን ተብሎ ዜጎች እንዲማረሩ ለማድረግ የሚደረገው ሸር ነገ ሳይሆን ዛሬ አስሸኳይ መፍትሄ የሚፈልግ ነው።
የዋጋ ንረት እየፈጠሩ የዜጎችን ኑሮ የሚፈታተኑ ለሀገር ህልውና አደገኛ የሆኑ አካላት ላይ እርምጃ መውሰድ ካልተቻለ መዘዙ ከባድ ነው። ዜጎችም ነገ ኑሯቸውን የሚያከዱ ህገወጦችን ፣ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላትን ለሚመለከተው አካል በመጠቆም ዜግነታዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል።
Pic Credit : Addis Maleda
@tikvahethiopia
የዋጋ ንረቱ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ፤ የኑሮ ውድነቱ ከፍ እያለ የሰዎችን ኑሮ በእጅግ እየተፈታተነው ነው።
በተለይ ዝቅተኛ ደሞዝ የሚያገኘ ሰራተኞች ኑሮ ለመግፋት ፈተና እየሆነባቸው ነው፤ በየዕለቱ ሚጨምረው የዋጋ ንረት የኑሮውን ጫና መቋቋም ከማይቻልበት ደረጃ እየደረሰ ነው።
ቤት ኪራይ፣ ምግብ የልጆች ት/ቤት ክፍያ፣ የቀን ወጪ ..ሌሎችም ወጪዎች ሲጨምሩ እንጂ ሲቀንሱ አይታይም፤ የሚገኘው ደሞዝ እዛው ነው።
ከቅርብ ጊዜ በኃላ ደግሞ በኢትዮጵያ ሰሜናዊው ክፍል የተፈጠረውን ጦርነት እንደመልካም አጋጣሚ የተጠቀሙ ነጋዴዎች በተለላያዩ ምርቶች ላይ ያለአንዳች ምክንያት ዋጋ በመጨመር ዜጎችን ክፉኛ እያማረሩ ነው።
በተለያዩ ከተሞች ዋጋን በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ በመንግስት እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ሪፖርት የሚደረግ ቢሆንም አሁንም የሚቀረው ስራ ብዙ ነው።
በሀገሪቱ ውስጥ የሚሰሩ ኢኮሮሚያዊ አሻጥሮች ፣ ሆን ተብሎ ዜጎች እንዲማረሩ ለማድረግ የሚደረገው ሸር ነገ ሳይሆን ዛሬ አስሸኳይ መፍትሄ የሚፈልግ ነው።
የዋጋ ንረት እየፈጠሩ የዜጎችን ኑሮ የሚፈታተኑ ለሀገር ህልውና አደገኛ የሆኑ አካላት ላይ እርምጃ መውሰድ ካልተቻለ መዘዙ ከባድ ነው። ዜጎችም ነገ ኑሯቸውን የሚያከዱ ህገወጦችን ፣ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላትን ለሚመለከተው አካል በመጠቆም ዜግነታዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል።
Pic Credit : Addis Maleda
@tikvahethiopia
በድሬዳዋ የልኳንዳ ቤቶች ዋጋ ተተመነላቸው ...
ከዛሬ ነሐሴ 18 ጀምሮ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የልኳንዳ ቤቶች አንድ ኪሎ ስጋ መሸጫ ዋጋ ተተመነላቸው።
በዚህም መሰረት ፦
- በሆቴል ቤቶች ተጠብሶ የሚሸጥ የበሬ ስራ በኪሎ ግራም 420.00 ብር
- ጥሬ (ወደ ቤት የሚሄድ) የሚሸጥ የበሬ ስጋ በኪሎ ግራም 400.00 ብር
- በልኳንዳ ቤት የሚሸጥ የፍየል ስጋ በኪሎ ግራም 450.00 ብር
- የፍየል ጥሬ ስጋ (ወደ ቤት የሚሄድ) በኪሎ ግራም 430.00 ብር መሆኑ ተገልጿል።
ከላይ ከተተመነው ዋጋ ውጭ ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ነጋዴ ህጋዊ እርምጃ ይወሰድበታል ሲል የድሬዳዋ ከተማ ንግድ ፣ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስጠንቅቋል።
ውድ የድሬዳዋ ከተማ የቲክቫህ ኢትዮ. አባላት በከተማችሁ የከተማ አስተዳዳሩ በተመነው ዋጋ እየተሸጠ ስለመሆኑን በ @tikvahethiopiaBot አሳውቁን፤ በተተመነው ዋጋ የማይሸጥባቸው ቦታዎችንም እግረ መንገዳችሁን መጥቀስ እንዳትዘነጉ።
@tikvahethiopia
ከዛሬ ነሐሴ 18 ጀምሮ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የልኳንዳ ቤቶች አንድ ኪሎ ስጋ መሸጫ ዋጋ ተተመነላቸው።
በዚህም መሰረት ፦
- በሆቴል ቤቶች ተጠብሶ የሚሸጥ የበሬ ስራ በኪሎ ግራም 420.00 ብር
- ጥሬ (ወደ ቤት የሚሄድ) የሚሸጥ የበሬ ስጋ በኪሎ ግራም 400.00 ብር
- በልኳንዳ ቤት የሚሸጥ የፍየል ስጋ በኪሎ ግራም 450.00 ብር
- የፍየል ጥሬ ስጋ (ወደ ቤት የሚሄድ) በኪሎ ግራም 430.00 ብር መሆኑ ተገልጿል።
ከላይ ከተተመነው ዋጋ ውጭ ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ነጋዴ ህጋዊ እርምጃ ይወሰድበታል ሲል የድሬዳዋ ከተማ ንግድ ፣ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስጠንቅቋል።
ውድ የድሬዳዋ ከተማ የቲክቫህ ኢትዮ. አባላት በከተማችሁ የከተማ አስተዳዳሩ በተመነው ዋጋ እየተሸጠ ስለመሆኑን በ @tikvahethiopiaBot አሳውቁን፤ በተተመነው ዋጋ የማይሸጥባቸው ቦታዎችንም እግረ መንገዳችሁን መጥቀስ እንዳትዘነጉ።
@tikvahethiopia
#ALERT🚨
ሶስተኛው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰቱን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ተደሰ ገለጹ።
ዶክተር ሊያ በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ 5 ሺህ 547 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡
በአንድ ቀን ውስጥ ከ1ሺህ በላይ ሰዎች መያዛቸውን የገለጹት ሚኒስትሯ÷ የወረርሽኙ መጠን ከዚህ በፊት ካለው በእጅጉ መጨመሩን ተናግረዋል።
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በአሁኑ ሰአት ቫይረሱ የሚገኝበት ሰው ቁጥር ምጣኔ በእጅጉ መጨመሩ የሚያሳየው ሶስተኛው የኮቪድ 19 መረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰቱን እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
ማህበረሰቡም ከዚህ በፊት የሚያደርገውን ጥንቃቄ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ሚኒስትሯ አሳስበዋል። #ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
ሶስተኛው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰቱን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ተደሰ ገለጹ።
ዶክተር ሊያ በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ 5 ሺህ 547 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡
በአንድ ቀን ውስጥ ከ1ሺህ በላይ ሰዎች መያዛቸውን የገለጹት ሚኒስትሯ÷ የወረርሽኙ መጠን ከዚህ በፊት ካለው በእጅጉ መጨመሩን ተናግረዋል።
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በአሁኑ ሰአት ቫይረሱ የሚገኝበት ሰው ቁጥር ምጣኔ በእጅጉ መጨመሩ የሚያሳየው ሶስተኛው የኮቪድ 19 መረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰቱን እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
ማህበረሰቡም ከዚህ በፊት የሚያደርገውን ጥንቃቄ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ሚኒስትሯ አሳስበዋል። #ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ፥ "የዳቦ ዋጋን ተመን ለማውጣት የሚፈቅድ አሰራር የለንም" አለ።
ቢሮ ይህን ያለው ለአሀዱ ኤፍ ኤም 94.3 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ዳንኤል ሚኤሳ በሰጡት ቃል ፥ በመዲናዋ በርካታ ነዋሪዎች የዳቦ ዋጋ በእጅጉ መጨመሩን እንዲሁም የዳቦው መጠንና ዋጋው እንደማይመጣጠን ተደጋጋሚ ቅሬታ ያቀርባሉ ብለዋል።
በመዲናዋ ያሉ ከ 2 ሺህ በላይ ዳቦ ቤቶች ካለፈው 1 አመት ወዲህ ከንግድ ቢሮው ጋር የነበራቸውን ትስስር ያቋረጡ በመሆኑ አሁን ላይ ቢሮው የዋጋ ተመንን ለማውጣት የሚፈቅድ አሰራር እንደሌለው ተናግረዋል፡፡
መንግስት የስንዴ ድጎማውን ማቋረጡን ተከትሎም በመዲናዋ ያሉ ከ 2ሺ በላይ ዳቦ ቤቶች ትስስራቸውን ማቋረጣቸውንም አስረድተዋል፡፡
አቶ ዳንኤል ፥ "ምንም እንኳን በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች ቅሬታ ቢያቀርቡም አሁን ባለው የቢሮው አሰራር ዳቦ ቤቶቹ ባስቀመጡት የዳቦ ግራም እና ዋጋ በትክክል እየሸጡ መሆን አለመሆኑን ቁጥጥር ይደረጋል እንጂ ዋጋ በመተመን በገበያው ጣልቃ መግባት አይቻልም" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
አክለው በተያዘው አመት ባስቀመጡት የዳቦ ግራም መጠን ዋጋ ሲሸጡ ያልተገኙ ወደ 24 የሚጠጉ ዳቦ ቤቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል፡፡
መረጃው የአሀዱ ኤፍ ኤም 94.3 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ፥ "የዳቦ ዋጋን ተመን ለማውጣት የሚፈቅድ አሰራር የለንም" አለ።
ቢሮ ይህን ያለው ለአሀዱ ኤፍ ኤም 94.3 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ዳንኤል ሚኤሳ በሰጡት ቃል ፥ በመዲናዋ በርካታ ነዋሪዎች የዳቦ ዋጋ በእጅጉ መጨመሩን እንዲሁም የዳቦው መጠንና ዋጋው እንደማይመጣጠን ተደጋጋሚ ቅሬታ ያቀርባሉ ብለዋል።
በመዲናዋ ያሉ ከ 2 ሺህ በላይ ዳቦ ቤቶች ካለፈው 1 አመት ወዲህ ከንግድ ቢሮው ጋር የነበራቸውን ትስስር ያቋረጡ በመሆኑ አሁን ላይ ቢሮው የዋጋ ተመንን ለማውጣት የሚፈቅድ አሰራር እንደሌለው ተናግረዋል፡፡
መንግስት የስንዴ ድጎማውን ማቋረጡን ተከትሎም በመዲናዋ ያሉ ከ 2ሺ በላይ ዳቦ ቤቶች ትስስራቸውን ማቋረጣቸውንም አስረድተዋል፡፡
አቶ ዳንኤል ፥ "ምንም እንኳን በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች ቅሬታ ቢያቀርቡም አሁን ባለው የቢሮው አሰራር ዳቦ ቤቶቹ ባስቀመጡት የዳቦ ግራም እና ዋጋ በትክክል እየሸጡ መሆን አለመሆኑን ቁጥጥር ይደረጋል እንጂ ዋጋ በመተመን በገበያው ጣልቃ መግባት አይቻልም" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
አክለው በተያዘው አመት ባስቀመጡት የዳቦ ግራም መጠን ዋጋ ሲሸጡ ያልተገኙ ወደ 24 የሚጠጉ ዳቦ ቤቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል፡፡
መረጃው የአሀዱ ኤፍ ኤም 94.3 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
#አደይ
ልብ አንጠልጣዩ የቤተሰብ ድራማ ምዕራፍ 2
ከሰኞ - አርብ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ላይ በመታየት ላይ ይገኛል:
የሳምንቱን 5 ተከታታይ ክፍሎች እሁድ ከረፋዱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በአቦል ቻናል (146) ይመልከቱ!
#DStvየራሳችን
የዲኤስቲቪን ቤተሰብ ይቀላቀሉ!
https://bit.ly/3D2O1t4
ልብ አንጠልጣዩ የቤተሰብ ድራማ ምዕራፍ 2
ከሰኞ - አርብ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ላይ በመታየት ላይ ይገኛል:
የሳምንቱን 5 ተከታታይ ክፍሎች እሁድ ከረፋዱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በአቦል ቻናል (146) ይመልከቱ!
#DStvየራሳችን
የዲኤስቲቪን ቤተሰብ ይቀላቀሉ!
https://bit.ly/3D2O1t4
TIKVAH-ETHIOPIA
"...ጦሩ በፍጥነት አብዬን ለቆ እንዲወጣ እንፈልጋለን" - መሬም አልሳዲግ አልመሀዲ ዛሬ ሱዳን በአብዬ ግዛት የሚገኘው የኢትዮጵያ ሰላም አስካባሪ ኃይል ከቦታው ለቆ እንዲወጣ ተመድን መጠየቋን በይፋ አስታውቃለች፡፡ ሱዳን ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰቸው በኪንሻሳ የተካሄደው የግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ያለስምምነት መጠናቀቁን ተከትሎ ነው። የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል በተመድ ስር በመሆን በሱዳን እና…
#SUDAN
በአብዬ ግዛት የተሰማራው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር እንዲወጣ ያቀረበችውን ጥያቄ ተመድ እንደተቀበላት ሱዳን አስታወቀች፡፡
የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት መርያም አል ሳዲቅ አል መህዲ ከተመድ ዋና ጸሃፊ የምስራቅ አፍሪካ ልዩ መልዕክተኛ ፓርፊት አንያንጋ ጋር ትናንት ሰኞ ምሽት የበይነ መረብ ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይቱ የድርጅቱ የሰላም አስከባሪ ዋና ኃላፊ ዦን ፔሬ ላክሮይ እንዲሁም የኦፕሬሽን ዋና ኃላፊ አቱል ካሪ ተካፍለዋል፡፡
ውይይቱ በዋናነት በአብዬ ግዛት ስለተሰማራው የተመድ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነበር፡፡
የጸጥታ ኃይሉ አካል ሆኖ በስፍራው ሚገኘው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር በሱዳን ጥያቄ በቀጣዮቹ ሶስት ወራት ውስጥ ለቆ እንዲወጣ ስምምነት ስለተደረሰባቸው ሁኔታዎች በውይይቱ መነሳቱንም ነው የሃገሪቱ ዜና አገልግሎት (ሱና) የዘገበው፡፡
ተመድ የሱዳንን ሁኔታ ተረድቶ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር ወጥቶ በሌላ ይተካ የሚለውን ጥያቄ በመቀበሉ ያመሰገኑት መርያም አል ሳዲቅ ሃገራቸው ከደቡብ ሱዳን ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እንደምትሰራ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር በቶሎ ሊወጣ የሚችልበትን የተቀላጠፈ ሁኔታ ለማመቻቸትም እና ለተተኪው አቀባበል ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡
ሱዳን በጋራ የድንበር ጉዳዮች ላይ ያሉ ጋሬጣዎችን በማጽዳት የራሷን ሚና እንደምትጫወትም ነው ሚኒስትሯ የገለጹት፡፡
በአሀኑ ወቅት ከ3 ሺህ በላይ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሀይል በአብዬ ግዛት እንዳለ የመንግስታቱ ድርጅት ሪፖርት ያስረዳል።
ደቡብ ሱዳን ከሱዳን በህዝበ ውሳኔ ነጻ አገር ለመመስረት መወሰኗን ተከትሎ ነበር የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሀይል ወደ አብዬ ግዛት የተሰማራው።
(አል-ዓይን ኒውስ)
@tikvahethiopia
በአብዬ ግዛት የተሰማራው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር እንዲወጣ ያቀረበችውን ጥያቄ ተመድ እንደተቀበላት ሱዳን አስታወቀች፡፡
የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት መርያም አል ሳዲቅ አል መህዲ ከተመድ ዋና ጸሃፊ የምስራቅ አፍሪካ ልዩ መልዕክተኛ ፓርፊት አንያንጋ ጋር ትናንት ሰኞ ምሽት የበይነ መረብ ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይቱ የድርጅቱ የሰላም አስከባሪ ዋና ኃላፊ ዦን ፔሬ ላክሮይ እንዲሁም የኦፕሬሽን ዋና ኃላፊ አቱል ካሪ ተካፍለዋል፡፡
ውይይቱ በዋናነት በአብዬ ግዛት ስለተሰማራው የተመድ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነበር፡፡
የጸጥታ ኃይሉ አካል ሆኖ በስፍራው ሚገኘው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር በሱዳን ጥያቄ በቀጣዮቹ ሶስት ወራት ውስጥ ለቆ እንዲወጣ ስምምነት ስለተደረሰባቸው ሁኔታዎች በውይይቱ መነሳቱንም ነው የሃገሪቱ ዜና አገልግሎት (ሱና) የዘገበው፡፡
ተመድ የሱዳንን ሁኔታ ተረድቶ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር ወጥቶ በሌላ ይተካ የሚለውን ጥያቄ በመቀበሉ ያመሰገኑት መርያም አል ሳዲቅ ሃገራቸው ከደቡብ ሱዳን ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እንደምትሰራ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር በቶሎ ሊወጣ የሚችልበትን የተቀላጠፈ ሁኔታ ለማመቻቸትም እና ለተተኪው አቀባበል ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡
ሱዳን በጋራ የድንበር ጉዳዮች ላይ ያሉ ጋሬጣዎችን በማጽዳት የራሷን ሚና እንደምትጫወትም ነው ሚኒስትሯ የገለጹት፡፡
በአሀኑ ወቅት ከ3 ሺህ በላይ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሀይል በአብዬ ግዛት እንዳለ የመንግስታቱ ድርጅት ሪፖርት ያስረዳል።
ደቡብ ሱዳን ከሱዳን በህዝበ ውሳኔ ነጻ አገር ለመመስረት መወሰኗን ተከትሎ ነበር የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሀይል ወደ አብዬ ግዛት የተሰማራው።
(አል-ዓይን ኒውስ)
@tikvahethiopia
ችሎት !
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በዕግድ ላይ የሚገኘው የዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ አስተዳዳሪ እንዲሾም ውሳኔ ሰጠ፡፡
ዓቃቢ ህግ በአ/አ ከተማ የሚገኘው የዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ የማይቀሳቀስ ንብረት ኪራይ ለህውሐት ቡድን ለሽብር ተግባር እየዋለነው ብሎ ንብረቱን ማሳገዱ ይታወሳል፡፡
ይህ የታገደው የዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ የማይቀሳቀስ ንብረትን የሚያስተዳድር አካል ሊሾም ይገባል ሲል ዓቃቤ ህግ መከራከሪያ ነጥብ አንስቶ ተከራክሮ የነበረ ሲሆን በዶ/ር አዲስ አሌም ባሌማ በኩል ደግሞ የታገደው ንብረቴ ቤተሰቦቼ የሚተዳደሩበት በመሆኑ መተዳደር ያለበት በቤተሰቦቼ ነው ሲሉ መከራከሪያ ነጥብ አንስተው ተከራክረው ነበር፡፡
ክርክሩን የተከታተለው ፍርድ ቤቱ ዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ ንብረቴን ቤተሰቦቼ ናቸው ማስተዳደር ያለባቸው ሲሉ ያቀረቡትን መከራከሪያ ነጥብን ውድቅ አድርጎታል፡፡
ንብረቱን የሚያስተዳድር ሌላ አስተዳዳሪ አካል እንዲሾም ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
የመረጃ ባለቤት ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በዕግድ ላይ የሚገኘው የዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ አስተዳዳሪ እንዲሾም ውሳኔ ሰጠ፡፡
ዓቃቢ ህግ በአ/አ ከተማ የሚገኘው የዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ የማይቀሳቀስ ንብረት ኪራይ ለህውሐት ቡድን ለሽብር ተግባር እየዋለነው ብሎ ንብረቱን ማሳገዱ ይታወሳል፡፡
ይህ የታገደው የዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ የማይቀሳቀስ ንብረትን የሚያስተዳድር አካል ሊሾም ይገባል ሲል ዓቃቤ ህግ መከራከሪያ ነጥብ አንስቶ ተከራክሮ የነበረ ሲሆን በዶ/ር አዲስ አሌም ባሌማ በኩል ደግሞ የታገደው ንብረቴ ቤተሰቦቼ የሚተዳደሩበት በመሆኑ መተዳደር ያለበት በቤተሰቦቼ ነው ሲሉ መከራከሪያ ነጥብ አንስተው ተከራክረው ነበር፡፡
ክርክሩን የተከታተለው ፍርድ ቤቱ ዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ ንብረቴን ቤተሰቦቼ ናቸው ማስተዳደር ያለባቸው ሲሉ ያቀረቡትን መከራከሪያ ነጥብን ውድቅ አድርጎታል፡፡
ንብረቱን የሚያስተዳድር ሌላ አስተዳዳሪ አካል እንዲሾም ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
የመረጃ ባለቤት ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
#MinistryofPeace
የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከአፍሪካ ቀንድ ልዩ ተወካይ ዶክተር አኔቴ ዌበር ጋር ተወያይተዋል።
በውይይየታቸው ወ/ሮ ሙፈሪያት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ ልማት በተለያዩ መስኮች እያደረገ ለሚገኘው ድጋፍ አመስግነዋል።
ዶ/ር አኔቴ ዌበር በበኩላቸው፥የአውሮፓ ህብረት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ለረጅም ዘመናት የቆየውን መልካም የዲፕሎማሲያዊ እና የልማት ትብብር ለመቀጠል ያለውን ጠንካራ ፍላጎት መግለጻቸውን የሰላም ሚኒስቴር አሳውቋል።
@tikvahethiopia
የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከአፍሪካ ቀንድ ልዩ ተወካይ ዶክተር አኔቴ ዌበር ጋር ተወያይተዋል።
በውይይየታቸው ወ/ሮ ሙፈሪያት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ ልማት በተለያዩ መስኮች እያደረገ ለሚገኘው ድጋፍ አመስግነዋል።
ዶ/ር አኔቴ ዌበር በበኩላቸው፥የአውሮፓ ህብረት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ለረጅም ዘመናት የቆየውን መልካም የዲፕሎማሲያዊ እና የልማት ትብብር ለመቀጠል ያለውን ጠንካራ ፍላጎት መግለጻቸውን የሰላም ሚኒስቴር አሳውቋል።
@tikvahethiopia
ከባህር ዳር ተነስቶ አዲስ አበባ ሊገባ የነበረ የጦር መሳሪያ ተያዘ።
ከባህር ዳር ተነስቶ አዲስ አበባ ሊገባ የነበረ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ።
ሱሉልታ ከተማ በቁጥጥር ስር የዋለው መሳሪያ 83 ትንሿ ሽጉጥ፣ 199 ኤም ፎርቲን ጥይት እና 10 ሺህ 865 የሽጉጥ ጥይት መሆኑ ታውቋል።
የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና አዲስ አበባ ፖሊስ በጋራ ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል ተጠርጣሪ የሆኑት ሹፌሩና ረዳቱ ተይዘዋል።
#ኢፕድ
@tikvahethiopia
ከባህር ዳር ተነስቶ አዲስ አበባ ሊገባ የነበረ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ።
ሱሉልታ ከተማ በቁጥጥር ስር የዋለው መሳሪያ 83 ትንሿ ሽጉጥ፣ 199 ኤም ፎርቲን ጥይት እና 10 ሺህ 865 የሽጉጥ ጥይት መሆኑ ታውቋል።
የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና አዲስ አበባ ፖሊስ በጋራ ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል ተጠርጣሪ የሆኑት ሹፌሩና ረዳቱ ተይዘዋል።
#ኢፕድ
@tikvahethiopia
''ቱኒዚያ በድጋሜ ለተባበሩት የፀጥታው ምክር ቤት ለግብጽ ተገቢ ያልሆነ ድጋፍ ለማድረግ እየተዘጋጀች ነው'' - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን
ቱኒዚያ ድጋሚ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የግብፅን ሀሳብ ብቻ የሚደግፍ የውሳኔ ሀሳብ ለማቅረብ እየተዘጋጀች በመሆኑ አፍራሽ አካሔዷን ለመቀልበስ የላይኛው የናይል ተፋሰስ አባል ሀገራት በጋር መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገልጸዋል።
አምባሳደር ሬድዋን ይህን ያሉት ከላይኛው የናይል ተፋሰስ አባል ሐገራት አምባሳደሮች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው።
የላይኛው ተፋሰስ አገራት አምባሳደሮችም በበኩላቸው በቀረቡት ሃሳብ ላይ በመንተራስ ድንበር ተሻጋሪ ሃብቶችን ለጋራ ልማት ለማዋል የጋራ ትብብር እንደሚያስፈልግ እንዲሁም የአፍሪካን ጉዳይ በአፍሪካዊያን መፍታት እንደሚገባ አንስተዋል፡፡
ቱኒዚያ ለተባበሩት የፀጥታው ምክር ቤት ለግብጽ ተገቢ ያልሆነ ድጋፍ ለማድረግ ያቀረበችው የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ ቢደረግባትም በድጋሚ ለማቅረብ ዝግጅት ማድረጓን አንስተው፣ ይህ ውሳኔ ቢወሰን የሁሉም የላኛው ተፋሰስ አገራት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሊያስገባ እንደሚችልና ይህን ሃሳብ ለመቀልበስ በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግ ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል፡፡
አምባሳደር ሬድዋን የቱኒዚያ አካሄድ በአፍሪካ ህብረት እየተመራ ያለውን የሶስትዮሽ ድርድር ጥረት የሚያደናቅፍ መሆኑን ገልጸው፣ አገራቱ ኒውዮርክ ለሚገኙት ሚሲዮኖቻቸው ይህንኑ እንዲገልጹላቸው ጠይቀዋል።
መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ነው።
@tikvahethiopia
ቱኒዚያ ድጋሚ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የግብፅን ሀሳብ ብቻ የሚደግፍ የውሳኔ ሀሳብ ለማቅረብ እየተዘጋጀች በመሆኑ አፍራሽ አካሔዷን ለመቀልበስ የላይኛው የናይል ተፋሰስ አባል ሀገራት በጋር መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገልጸዋል።
አምባሳደር ሬድዋን ይህን ያሉት ከላይኛው የናይል ተፋሰስ አባል ሐገራት አምባሳደሮች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው።
የላይኛው ተፋሰስ አገራት አምባሳደሮችም በበኩላቸው በቀረቡት ሃሳብ ላይ በመንተራስ ድንበር ተሻጋሪ ሃብቶችን ለጋራ ልማት ለማዋል የጋራ ትብብር እንደሚያስፈልግ እንዲሁም የአፍሪካን ጉዳይ በአፍሪካዊያን መፍታት እንደሚገባ አንስተዋል፡፡
ቱኒዚያ ለተባበሩት የፀጥታው ምክር ቤት ለግብጽ ተገቢ ያልሆነ ድጋፍ ለማድረግ ያቀረበችው የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ ቢደረግባትም በድጋሚ ለማቅረብ ዝግጅት ማድረጓን አንስተው፣ ይህ ውሳኔ ቢወሰን የሁሉም የላኛው ተፋሰስ አገራት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሊያስገባ እንደሚችልና ይህን ሃሳብ ለመቀልበስ በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግ ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል፡፡
አምባሳደር ሬድዋን የቱኒዚያ አካሄድ በአፍሪካ ህብረት እየተመራ ያለውን የሶስትዮሽ ድርድር ጥረት የሚያደናቅፍ መሆኑን ገልጸው፣ አገራቱ ኒውዮርክ ለሚገኙት ሚሲዮኖቻቸው ይህንኑ እንዲገልጹላቸው ጠይቀዋል።
መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ነው።
@tikvahethiopia