ከጤና ተቋማት ተምረውና ተመርቀው የሚወጡ የጤና ባለሙያዎችን ወደሥራ ለማስገባት አማራጭ መንገዶች መለየታቸው ተገለፀ !
የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ፥ ከተለያዩ የጤና ተቋማት ተምረውና ተመርቀው የሚወጡ ባለሙያዎችን ወደሥራ ለማሰማራትና ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ለማስገባት ሶስት ዋና ዋና አማራጭ መንገዶች መለየታቸውን አሳወቁ።
ዶ/ር ሊያ ይህን ያሳወቁት ዛሬ ጤና ሚኒስቴር ከሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ጋር የመግባቢያ ሰነድ በተፈራረመበት ወቅት ነው።
ከተለያዩ የጤና ተቋማት ተምረውና ተመርቀው የሚወጡ ባለሙያዎችን ፦
- በአገር ውስጥ ሥራ ማስያዝ፣
- የውጭ ሀገራት የሥራ ዕድሎችንና አማራጮችን ማመቻቸት - አዳዲስ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ሞዴሎች ላይ መሰማራት እንዲችሉ የማመቻቸት ሥራዎችን በመሥራት ባለሞያዎች በተናጠል ሆነ በጋራ ተቋም መስርተው እንዲሰሩ ማድረግ ዋና ዋና አማራጭ ተብለው የተጠቀሱ ናቸው።
አዳዲስ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ሞዴሎች እንዲፈቀዱ በማድረግ ለመተግበር እንዲቻል የተለያዩ አገራትን ልምድ በመቀመር የጤና ባለሞያዎች በተናጠል ሆነ በጋራ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ የሚያስችሉ መመሪያዎች የማዘጋጀት ሥራ የተጠናቀቀ መሆኑን ዶ/ር ሊያ አሳውቀዋል።
የቤት ውስጥ የጤና አገልግሎት (Homebased Care) እና በስልክ ጥሪ የሚደረጉ የጤና ድጋፎች (Telemedicine) መመሪያ ክለሳ መደረጉን ገልፀዋል።
@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ፥ ከተለያዩ የጤና ተቋማት ተምረውና ተመርቀው የሚወጡ ባለሙያዎችን ወደሥራ ለማሰማራትና ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ለማስገባት ሶስት ዋና ዋና አማራጭ መንገዶች መለየታቸውን አሳወቁ።
ዶ/ር ሊያ ይህን ያሳወቁት ዛሬ ጤና ሚኒስቴር ከሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ጋር የመግባቢያ ሰነድ በተፈራረመበት ወቅት ነው።
ከተለያዩ የጤና ተቋማት ተምረውና ተመርቀው የሚወጡ ባለሙያዎችን ፦
- በአገር ውስጥ ሥራ ማስያዝ፣
- የውጭ ሀገራት የሥራ ዕድሎችንና አማራጮችን ማመቻቸት - አዳዲስ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ሞዴሎች ላይ መሰማራት እንዲችሉ የማመቻቸት ሥራዎችን በመሥራት ባለሞያዎች በተናጠል ሆነ በጋራ ተቋም መስርተው እንዲሰሩ ማድረግ ዋና ዋና አማራጭ ተብለው የተጠቀሱ ናቸው።
አዳዲስ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ሞዴሎች እንዲፈቀዱ በማድረግ ለመተግበር እንዲቻል የተለያዩ አገራትን ልምድ በመቀመር የጤና ባለሞያዎች በተናጠል ሆነ በጋራ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ የሚያስችሉ መመሪያዎች የማዘጋጀት ሥራ የተጠናቀቀ መሆኑን ዶ/ር ሊያ አሳውቀዋል።
የቤት ውስጥ የጤና አገልግሎት (Homebased Care) እና በስልክ ጥሪ የሚደረጉ የጤና ድጋፎች (Telemedicine) መመሪያ ክለሳ መደረጉን ገልፀዋል።
@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
"...ይህ ሁሉ ውድመት ሲከሰት የጸጥታ ኃይላችን የት ነበር ? የመረጃ እና የደኀንነት መዋቅራችን የት ነበር ? የሚለውን እያጣራን ነው" - አቶ አገኘሁ ተሻገር
የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ሰሞኑን በኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን እና በሰሜን ሸዋ ዞን በደረሰው ጥፋት ጥቃት ፈፃሚዎችን ለሕግ ለማቅረብ ከፌዴራል የጸጥታ ኀይል ጋር በጋራ እየተሠራ ነው ብለዋል።
አቶ አገኘሁ ይህን ያሉት ዛሬ ማምሻውን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
ፕሬዝዳንቱ ፥ በሁለቱ ዞኖች በተፈፀመው ጥቃት የመንግሥት መዋቅር ጭምር መሳተፉን ገልፀዋል።
"እኛም መዋቅራችንን እየፈተሽን ነው ፣ ይህ ሁሉ ውድመት ሲከሰት የጸጥታ ኀይላችን የት ነበር፣ የመረጃ እና የደኀንነት መዋቅራችን የት ነበር የሚለውን እያጣራን ነው" ብለዋል።
አቶ አገኘሁ ፥ ማንነትን መሰረት አድርጎ እየተፈፀመ ያለውን ጥቃት በሰላማዊ እና በሰለጠ መንገድ መግለጹ ተገቢ መሆኑን ተናግረው፤ ሰላማዊ ሰልፎች በአብዛኛው ሰላማዊ እንደነበሩ ተናግረዋል።
ሰልፎቹ ላይ ግን የተሳሳተ መልዕክት ለማስተላለፍ ጥረት መደረገን ዛሬ ደግሞ በባህር ዳር ከተማ የዝርፊያ እና የንግድ ተቋማትን የመዝጋት ሙከራዎች እንደነበሩ አንስተዋል።
አሁን ላይ የከተማዋ እንቅስቃሴ ወደነበረበት እንደተመለሰ ነው ብለዋል።
More : https://telegra.ph/AMC-04-22
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ሰሞኑን በኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን እና በሰሜን ሸዋ ዞን በደረሰው ጥፋት ጥቃት ፈፃሚዎችን ለሕግ ለማቅረብ ከፌዴራል የጸጥታ ኀይል ጋር በጋራ እየተሠራ ነው ብለዋል።
አቶ አገኘሁ ይህን ያሉት ዛሬ ማምሻውን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
ፕሬዝዳንቱ ፥ በሁለቱ ዞኖች በተፈፀመው ጥቃት የመንግሥት መዋቅር ጭምር መሳተፉን ገልፀዋል።
"እኛም መዋቅራችንን እየፈተሽን ነው ፣ ይህ ሁሉ ውድመት ሲከሰት የጸጥታ ኀይላችን የት ነበር፣ የመረጃ እና የደኀንነት መዋቅራችን የት ነበር የሚለውን እያጣራን ነው" ብለዋል።
አቶ አገኘሁ ፥ ማንነትን መሰረት አድርጎ እየተፈፀመ ያለውን ጥቃት በሰላማዊ እና በሰለጠ መንገድ መግለጹ ተገቢ መሆኑን ተናግረው፤ ሰላማዊ ሰልፎች በአብዛኛው ሰላማዊ እንደነበሩ ተናግረዋል።
ሰልፎቹ ላይ ግን የተሳሳተ መልዕክት ለማስተላለፍ ጥረት መደረገን ዛሬ ደግሞ በባህር ዳር ከተማ የዝርፊያ እና የንግድ ተቋማትን የመዝጋት ሙከራዎች እንደነበሩ አንስተዋል።
አሁን ላይ የከተማዋ እንቅስቃሴ ወደነበረበት እንደተመለሰ ነው ብለዋል።
More : https://telegra.ph/AMC-04-22
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Ethiopia😷
ባለፉት 24 ሰዓት 22 ሰዎች በኮቪድ-19 መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።
በተመሳሳይ ከተደረገው 7,041 የላብራቶሪ ምርመራ 1,505 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ትላንት 1,175 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 247,989 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 3,496 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 185,107 ሰዎች አገግመዋል።
አሁን ላይ 999 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose
@tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት 22 ሰዎች በኮቪድ-19 መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።
በተመሳሳይ ከተደረገው 7,041 የላብራቶሪ ምርመራ 1,505 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ትላንት 1,175 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 247,989 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 3,496 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 185,107 ሰዎች አገግመዋል።
አሁን ላይ 999 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
"ሙሃመድ ዴክሲሶ በአፋጣኝ ከእስር ሊለቀቅ ይገባል" - ኢሰመኮ ከየካቲት 6 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ በጅማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ወረዳ 1 ፖሊስ ጣቢያ በእስር ላይ የሚገኘውን ሙሃመድ ዴክሲሶ በተመለከተ የጅማ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት የካቲት 16 ቀን 2013 ዓ.ም. በዋስ እንዲለቀቅ ያሳለፈውን ውሳኔ በመተላለፍ ከእስር አለመለቀቁ እንዳሳሰበው ገልጾ፣ ሙሃመድ ዴክሲሶን ጨምሮ ሌሎችም በፍርድ ቤት የዋስትና…
'መሀመድ ዴክሲሶ ያለበት አይታወቅም'
• "...የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ነው ስድስት ሆነው መጥተው ነው በፓትሮል የወሰዱት ከዛ ቀን ጀምሮ እዚህ ነው የሚል ተጨባጭ መረጃ የለንም።" - አቶ ሱልጣን ዴክሲሶ
• "... እኛም ያለበትን ቦታ ማወቅ አልቻልንም" - ኢሰመኮ
የካቲት 6/2013 ዓ/ም ጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በሚያስመርቅበት መድረክ ላይ እነ አቶ ጃዋር መሃመድን ጨምሮ ሌሎች እስረኞች ከእስር እንዲፈቱ የጠየቀው መሃመድ ዴክሲሶ በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥሯል በሚል በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ክስ ከተመሰረተበት ወዲህ ከእስር አልተለቀም።
የመሀመድ ቤተሰቦች ፥ ፍርድ ቤት ከአንድም ሁለት ጊዜ ቢያሰናብተውም እስካሁን ሳይለቀቅ ቀርቷል ብለዋል።
የመሀመድ ዴክሲሶ ወንድም አቶ ሱልጣን ዴክሲሶ ለጀርመን ድምፅ እንደተናገሩት ከሆነ ፥ አሁን ላይ መሀመድ ዴክሲሶ ያለበትን ቤተሰቦቹ አያውቁም።
አቶ ሱልጣን ፥ " ... በምርቃት ቀኑ እዛው በመድረክ ላይ ድምፁን ካሰማ በኃላ ነው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለው፤ ከዛም ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው የተወሰደው ፤ ከዛ ፍርድ ቀርቦ ነበር፤ ከዛ በኃላ ባልታወቀ ምክንያት ልዩ ኃይል በሚባለው ተወሰደ ፤ ከተወሰደ ወዲህ ዛሬ 3 ሳምንት አልፎታል ፤ እዚህ ነው ያለው፤ በዚህ ሁኔታ ነው ያለው የሚለውን እንደቤተሰብ እኛ ምንም የምናውቀው ነገር የለም" ብለዋል።
በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢስመኮ) የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ አማካሪ ኢማድ አብዱልፈታህ እንደተናገሩት፥ መሀመድ ዴክሲሶ አሁን ያለበትን ስፍራ ለማወቅ የተለያዩ የመንግስት መዋቅሮችን ጠይቆ ለመረዳት ቢሞከርም ይህ ከኮሚሽኑ አቅም በላይ መሆኑን ነው የገለፁት።
ያንብቡ : telegra.ph/Mohaammad-Deeksisoo-04-22
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
• "...የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ነው ስድስት ሆነው መጥተው ነው በፓትሮል የወሰዱት ከዛ ቀን ጀምሮ እዚህ ነው የሚል ተጨባጭ መረጃ የለንም።" - አቶ ሱልጣን ዴክሲሶ
• "... እኛም ያለበትን ቦታ ማወቅ አልቻልንም" - ኢሰመኮ
የካቲት 6/2013 ዓ/ም ጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በሚያስመርቅበት መድረክ ላይ እነ አቶ ጃዋር መሃመድን ጨምሮ ሌሎች እስረኞች ከእስር እንዲፈቱ የጠየቀው መሃመድ ዴክሲሶ በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥሯል በሚል በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ክስ ከተመሰረተበት ወዲህ ከእስር አልተለቀም።
የመሀመድ ቤተሰቦች ፥ ፍርድ ቤት ከአንድም ሁለት ጊዜ ቢያሰናብተውም እስካሁን ሳይለቀቅ ቀርቷል ብለዋል።
የመሀመድ ዴክሲሶ ወንድም አቶ ሱልጣን ዴክሲሶ ለጀርመን ድምፅ እንደተናገሩት ከሆነ ፥ አሁን ላይ መሀመድ ዴክሲሶ ያለበትን ቤተሰቦቹ አያውቁም።
አቶ ሱልጣን ፥ " ... በምርቃት ቀኑ እዛው በመድረክ ላይ ድምፁን ካሰማ በኃላ ነው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለው፤ ከዛም ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው የተወሰደው ፤ ከዛ ፍርድ ቀርቦ ነበር፤ ከዛ በኃላ ባልታወቀ ምክንያት ልዩ ኃይል በሚባለው ተወሰደ ፤ ከተወሰደ ወዲህ ዛሬ 3 ሳምንት አልፎታል ፤ እዚህ ነው ያለው፤ በዚህ ሁኔታ ነው ያለው የሚለውን እንደቤተሰብ እኛ ምንም የምናውቀው ነገር የለም" ብለዋል።
በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢስመኮ) የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ አማካሪ ኢማድ አብዱልፈታህ እንደተናገሩት፥ መሀመድ ዴክሲሶ አሁን ያለበትን ስፍራ ለማወቅ የተለያዩ የመንግስት መዋቅሮችን ጠይቆ ለመረዳት ቢሞከርም ይህ ከኮሚሽኑ አቅም በላይ መሆኑን ነው የገለፁት።
ያንብቡ : telegra.ph/Mohaammad-Deeksisoo-04-22
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የፀጥታው ምክር ቤት መግለጫ :
የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ም/ቤት በኢትዮጵያ የትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ ፣ በክልሉ ላለው ቀውስ እልባት ለመስጠት የኢትዮጵያ መንግስት እያከናወነ ያለውን ተግባር አድንቋል፡፡
መግለጫው እንደሚገልፀው ፣ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት የኢትዮጵያ መንግስት ሰብዓዊ ዕርዳታን ለማቅረብ እና ሰብዓዊ ተደራሽነትን ከፍ ለማድረግ እያደረገ ላለው ጥረት እውቅና ሰጥተዋል፡፡
ነገር ግን የምክር ቤቱ አባላት የሰብዓዊ ችግሮች አሁንም መኖራቸውን እንደሚገነዘቡ እና በክልሉ ያለው ሰብዓዊ ሁኔታ እንደሚያሳስባቸውም ነው መግለጫው ያመለከተው፡፡
ከምግብ ዋስትና ጋር በተያያዘ የሚደረገው የሰብዓዊ ድጋፍ መጨመር እንዳለበት እና ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ ለሁሉም የተቸገሩ ወገኖች ተደራሽ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።
ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ አስቸኳይ እርዳታ መርሆዎች ጋር በሚጣጣም መልኩ ሰብዓዊነትን ፣ ገለልተኛነትን እና ነፃነትን መሰረት በማድረግ የሚከናወኑ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቶች እንዲቀጥሉ የፀጥታው ም / ቤት አባላት ጥሪ አቅርበዋል።
በትግራይ የተፈጠረው ፀጥታ ችግር ለቀጣይ የሰብአዊ አገልግሎቶች እንቅፋት መሆኑን በመግለጽ መደበኛ ሁኔታው እንዲመለስም አባላቱ መጠየቃቸው በመግለጫው ተካቷል ፡፡
ያንብቡ : https://telegra.ph/UNSC-04-23
ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ም/ቤት በኢትዮጵያ የትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ ፣ በክልሉ ላለው ቀውስ እልባት ለመስጠት የኢትዮጵያ መንግስት እያከናወነ ያለውን ተግባር አድንቋል፡፡
መግለጫው እንደሚገልፀው ፣ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት የኢትዮጵያ መንግስት ሰብዓዊ ዕርዳታን ለማቅረብ እና ሰብዓዊ ተደራሽነትን ከፍ ለማድረግ እያደረገ ላለው ጥረት እውቅና ሰጥተዋል፡፡
ነገር ግን የምክር ቤቱ አባላት የሰብዓዊ ችግሮች አሁንም መኖራቸውን እንደሚገነዘቡ እና በክልሉ ያለው ሰብዓዊ ሁኔታ እንደሚያሳስባቸውም ነው መግለጫው ያመለከተው፡፡
ከምግብ ዋስትና ጋር በተያያዘ የሚደረገው የሰብዓዊ ድጋፍ መጨመር እንዳለበት እና ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ ለሁሉም የተቸገሩ ወገኖች ተደራሽ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።
ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ አስቸኳይ እርዳታ መርሆዎች ጋር በሚጣጣም መልኩ ሰብዓዊነትን ፣ ገለልተኛነትን እና ነፃነትን መሰረት በማድረግ የሚከናወኑ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቶች እንዲቀጥሉ የፀጥታው ም / ቤት አባላት ጥሪ አቅርበዋል።
በትግራይ የተፈጠረው ፀጥታ ችግር ለቀጣይ የሰብአዊ አገልግሎቶች እንቅፋት መሆኑን በመግለጽ መደበኛ ሁኔታው እንዲመለስም አባላቱ መጠየቃቸው በመግለጫው ተካቷል ፡፡
ያንብቡ : https://telegra.ph/UNSC-04-23
ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#UNHCR
የተመድ የስደተኞች ተቋም (UNHCR)፥ ከስድስት ወር በፊት በትግራይ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ በክልሉ የነበሩ 2 የስደተኞች ጣቢያዎች ከአገልገሎት ውጪ መሆናቸውን ተከትሎ በአማራ ክልል ደባርቅ ከተማ የስደተኞች መጠለያ ሊገነባ መሆኑን ለቢቢሲ አስታውቋል።
ተመድ (UNHCR) ከስደተኞችና የስደት ተመላሾች ኤጀንሲ ጋር በመሆን በትግራይ ክልል እንዲዘጉ በተደረጉት ሁለት የመጠለያ ጣብያዎች ምትክ በአማራ ክልል ደባርቅ ከተማ ለመገንባት ቦታ የመለየት ስራ መከናወኑን ገልጿል።
ተመድ በስፍራው ላይ ለኤርትራውያን ስደተኞች መጠለያ ለመገንባት ሕጋዊ ሰነዶች እስኪሟሉ እየጠበቀ ነው።
እንደ ድርጅቱ መረጃ ከሆነ የክረምቱ ወራት ከመጀመሩ በፊት ግንባታውን ለማካሄድ እና ስደተኞቹን በቦታው ለማስፈር እቅድ መያዙን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የተመድ የስደተኞች ተቋም (UNHCR)፥ ከስድስት ወር በፊት በትግራይ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ በክልሉ የነበሩ 2 የስደተኞች ጣቢያዎች ከአገልገሎት ውጪ መሆናቸውን ተከትሎ በአማራ ክልል ደባርቅ ከተማ የስደተኞች መጠለያ ሊገነባ መሆኑን ለቢቢሲ አስታውቋል።
ተመድ (UNHCR) ከስደተኞችና የስደት ተመላሾች ኤጀንሲ ጋር በመሆን በትግራይ ክልል እንዲዘጉ በተደረጉት ሁለት የመጠለያ ጣብያዎች ምትክ በአማራ ክልል ደባርቅ ከተማ ለመገንባት ቦታ የመለየት ስራ መከናወኑን ገልጿል።
ተመድ በስፍራው ላይ ለኤርትራውያን ስደተኞች መጠለያ ለመገንባት ሕጋዊ ሰነዶች እስኪሟሉ እየጠበቀ ነው።
እንደ ድርጅቱ መረጃ ከሆነ የክረምቱ ወራት ከመጀመሩ በፊት ግንባታውን ለማካሄድ እና ስደተኞቹን በቦታው ለማስፈር እቅድ መያዙን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
የፀጥታው ምክር ቤት መግለጫ : የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ም/ቤት በኢትዮጵያ የትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ ፣ በክልሉ ላለው ቀውስ እልባት ለመስጠት የኢትዮጵያ መንግስት እያከናወነ ያለውን ተግባር አድንቋል፡፡ መግለጫው እንደሚገልፀው ፣ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት የኢትዮጵያ መንግስት ሰብዓዊ ዕርዳታን ለማቅረብ እና ሰብዓዊ ተደራሽነትን ከፍ ለማድረግ እያደረገ…
የUN የፀጥታው ም/ቤት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ያወጣውን የፕሬስ መግለጫ በተመለከተ በተመድ የኢፌድሪ ቋሚ መልዕክተኛ ጽህፈ ቤት መግለጫ ሰጠ።
* ሙሉ የመግለጫው ሀሳብ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
* ሙሉ የመግለጫው ሀሳብ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Bahirdar
ባህር ዳር ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
የከተማው ኮሚኒኬሽን ቢሮ፥ "ከተማችን ሰላም ናት ወደመደበኛ እንቅስቃሴዋ ተመልሳለች" ነው ያለው።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ባህር ዳር ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
የከተማው ኮሚኒኬሽን ቢሮ፥ "ከተማችን ሰላም ናት ወደመደበኛ እንቅስቃሴዋ ተመልሳለች" ነው ያለው።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በአሶሳ አንድ ተሣቢ መኪና ሙሉ የጦር መሣሪያ ተይዟል ?
ትናንት በአሶሳ ከተማ "ባለቤቱ ያለታወቀ አንድ ተሣቢ መኪና የጦር መሣሪያ ተይዟል" በሚል ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የተናፈሰው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ።
"በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጨው መረጃ ማንነታቸውን በደበቁ እና ድብቅ አጀንዳ ባነገቡ አካላት ነው" ያለው ፖሊስ ህብረተሰቡን በማደናገር እና በከተማው ያልተፈለገ ግርግር ለመፍጠር የታሰበ እንደሆነ ተረድቻለሁ ብሏል።
ወደ ከተማው ገባ የተባለው ተሽከርካሪ የንብረቱ ባለቤቶች ባሉበት ፍተሻ ሲያደርግ በመኪናው ውስጥ የነበረው በህጋዊ መንገድ እና ህጋዊ ሰውነት በፌደራል ተሰጥቶት የገባ የ"ወርቅ ማሽን" ነው ፤ ግለሰቦቹ የማሽኑን ህጋዊነት የሚያሳይ ሰነድ ይዘው መገኘታቸውም ተረጋግጧል ሲል አሳውቋል።
ህብረተሰቡ ምንጩ የማይታወቅ እና ያልተረጋገጠ መረጃዎች ይዘው ለማወናበድና የከተማውን ነዋሪ ወደ አልተፈለገ ሽብር ለመውሰድ የሚንቀሳቀሱ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎችን በመለየት እራሱን እንዲጠብቅ ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ አሳስቧል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ትናንት በአሶሳ ከተማ "ባለቤቱ ያለታወቀ አንድ ተሣቢ መኪና የጦር መሣሪያ ተይዟል" በሚል ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የተናፈሰው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ።
"በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጨው መረጃ ማንነታቸውን በደበቁ እና ድብቅ አጀንዳ ባነገቡ አካላት ነው" ያለው ፖሊስ ህብረተሰቡን በማደናገር እና በከተማው ያልተፈለገ ግርግር ለመፍጠር የታሰበ እንደሆነ ተረድቻለሁ ብሏል።
ወደ ከተማው ገባ የተባለው ተሽከርካሪ የንብረቱ ባለቤቶች ባሉበት ፍተሻ ሲያደርግ በመኪናው ውስጥ የነበረው በህጋዊ መንገድ እና ህጋዊ ሰውነት በፌደራል ተሰጥቶት የገባ የ"ወርቅ ማሽን" ነው ፤ ግለሰቦቹ የማሽኑን ህጋዊነት የሚያሳይ ሰነድ ይዘው መገኘታቸውም ተረጋግጧል ሲል አሳውቋል።
ህብረተሰቡ ምንጩ የማይታወቅ እና ያልተረጋገጠ መረጃዎች ይዘው ለማወናበድና የከተማውን ነዋሪ ወደ አልተፈለገ ሽብር ለመውሰድ የሚንቀሳቀሱ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎችን በመለየት እራሱን እንዲጠብቅ ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ አሳስቧል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#WorldBank
የአለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሚተገበሩ ሶስት ፕሮጀክቶች የሚውል የ907 ሚሊዮን ዶላር የልማት ድጋፍ አድርጓል።
ዛሬ አርብ በገንዘብ ሚኒሰቴር በተደረገ የፊርማ ስነ-ሰርዓት በኢትዮጰያ መንግስት እና በዓለም ባንክ የ907 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈርሟል።
ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ እና የዓለም ባንክ ግሩፕ የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ሚ/ር ኦስማን ዲዮን ናቸው የፈረሙት።
ስምምነቱ ሶስት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ ይወላል ተብሏል ፦
- የ200 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በኢትዮጵያ ውስጥ በአነስተኛ እና ጥቃቅን ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሚውል ነው።
- የ500 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በሀገሪቱ ለሚከናወን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ካፒታል ተሳትፎንና ዘላቂ የፋይናንስ አማራጮችን ለማምጣት የሚያስችል ነው ፤ ከዚህ ውስጥ 100 ሚሊዮን ዶላር የሚውለው የግሉ ዘርፍ በኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጥ እና አቅርቦት ተሳትፎ እንዲኖረው ለማስቻል ነው፡፡
- የ207 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በኢትዮጵያ ውስጥ የኮቪድ - 19 ወረርሽኝ የሚያስከተለውን ጉዳት ለመቀነስ እና የበሽታው መከላከያ ክትባቶችን ውጤታማ እና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲዳረስ ለማድረግ የሚውል ነው።
Via Ministry of Finance -Ethiopia
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የአለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሚተገበሩ ሶስት ፕሮጀክቶች የሚውል የ907 ሚሊዮን ዶላር የልማት ድጋፍ አድርጓል።
ዛሬ አርብ በገንዘብ ሚኒሰቴር በተደረገ የፊርማ ስነ-ሰርዓት በኢትዮጰያ መንግስት እና በዓለም ባንክ የ907 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈርሟል።
ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ እና የዓለም ባንክ ግሩፕ የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ሚ/ር ኦስማን ዲዮን ናቸው የፈረሙት።
ስምምነቱ ሶስት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ ይወላል ተብሏል ፦
- የ200 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በኢትዮጵያ ውስጥ በአነስተኛ እና ጥቃቅን ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሚውል ነው።
- የ500 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በሀገሪቱ ለሚከናወን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ካፒታል ተሳትፎንና ዘላቂ የፋይናንስ አማራጮችን ለማምጣት የሚያስችል ነው ፤ ከዚህ ውስጥ 100 ሚሊዮን ዶላር የሚውለው የግሉ ዘርፍ በኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጥ እና አቅርቦት ተሳትፎ እንዲኖረው ለማስቻል ነው፡፡
- የ207 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በኢትዮጵያ ውስጥ የኮቪድ - 19 ወረርሽኝ የሚያስከተለውን ጉዳት ለመቀነስ እና የበሽታው መከላከያ ክትባቶችን ውጤታማ እና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲዳረስ ለማድረግ የሚውል ነው።
Via Ministry of Finance -Ethiopia
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ከተማ በግንባታ ላይ ያለ ህንጻ ተደርምሶ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ !
ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ካዛንቺስ አካባቢ በግንባታ ላይ የነበረ አንድ ህንፃ ተደርምሶ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ።
በክፍለ ከተማው ወረዳ 8 ካዛንቺስ ጁፒተር ሆቴል ፊት ለፊት በግንባታ ላይ የነበረ ህንፃ በመደርመሱ ነው የሶስት ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ አልፏል።
የአዲስ አበባ አተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የኮሚኒኬሽን ቡድን መሪ አቶ ጉልላት ጌታነህ ፥ ከሟቾች በተጨማሪ በአደጋው ሶሰት ሰዎች ቀላል አንድ ሰው ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብለዋል።
አደጋው የተከሰተው ዛሬ ከጠዋቱ 5 ሰዓት አካባቢ ሲሆን በግንባታ ላይ የነበረ አንድ ህንፃ በመደርመሱ መሆኑንም ተናግረዋል።
በወቅቱ ከአደጋው ሰዎችን ለመታደግ 35 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ፣ 3 ከባድና 4 ቀላል ተሽከርካሪዎች እንዲሁም 3 አምቡላንሶች መሰማራታቸውን ገልጸዋል፡፡
በወቅቱ በቦታው ስራ ላይ የነበሩ 109 ሰዎችን ከአደጋው መታደግ መቻሉን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBOT
ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ካዛንቺስ አካባቢ በግንባታ ላይ የነበረ አንድ ህንፃ ተደርምሶ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ።
በክፍለ ከተማው ወረዳ 8 ካዛንቺስ ጁፒተር ሆቴል ፊት ለፊት በግንባታ ላይ የነበረ ህንፃ በመደርመሱ ነው የሶስት ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ አልፏል።
የአዲስ አበባ አተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የኮሚኒኬሽን ቡድን መሪ አቶ ጉልላት ጌታነህ ፥ ከሟቾች በተጨማሪ በአደጋው ሶሰት ሰዎች ቀላል አንድ ሰው ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብለዋል።
አደጋው የተከሰተው ዛሬ ከጠዋቱ 5 ሰዓት አካባቢ ሲሆን በግንባታ ላይ የነበረ አንድ ህንፃ በመደርመሱ መሆኑንም ተናግረዋል።
በወቅቱ ከአደጋው ሰዎችን ለመታደግ 35 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ፣ 3 ከባድና 4 ቀላል ተሽከርካሪዎች እንዲሁም 3 አምቡላንሶች መሰማራታቸውን ገልጸዋል፡፡
በወቅቱ በቦታው ስራ ላይ የነበሩ 109 ሰዎችን ከአደጋው መታደግ መቻሉን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የቻድ ፕሬዜዳንት ተገደሉ። ላለፉት 30 ዓመታት ቻድን የመሩት ፕሬዝደንት ኢድሪስ ዴቢ በአማጺ ኃይሎች መገደላቸውን የሀገሪቱ መከላከያ ማስታወቁን አል ዓይን ዘግቧል። ፕሬዝደንቱ የመንግስት ኃይሎች ከአማጺያን ጋር እያደረጉ ባለው ጦርነት ተመተው መገደላቸውን ነው መከላከያ ሠራዊቱ በሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ይፋ ያደረገው፡፡ ፕሬዝደንቱ በውጊያው ከቆሰሉ ከጥቂት ቆይታ በኋላ ነው ህይወታቸው…
#update
“...ቻድን ማንም እንዲያስፈራራት አልፈቅድም” - የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት
የቀድሞ የቻድ ፕሬዝዳንት ኢድሪስ ዴቢ ቀብር ስነስርዓት ዛሬ በትውልድ አካባቢያቸው አቅራቢያ ተፈፀመ።
የቀብር ስነስርዓቱ በትውልድ አካባቢያቸው ከመፈፀሙ ቀደም ብሎ በኒጃሚን በነበረ ስነስርዓት የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ የኮንጎ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ቺሲዲኬ እና ሌሎችም ተገኘተው ነበር ፤ ምንም እንኳን አማፂያን የሀገራት መሪዎች በደህንነት ምክንያት በስነ ስርዓቱ ላይ እንዳይገኙ ቢያስጠነቅቁም።
ፕሬዜዳንት ማክሮን ፥ በስነስዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ፥ “ቻድን ማንም እንዲያስፈራራት አልፈቅድም” ሲሉ ተደምጠዋል።
ለቻድ መረጋጋት እና አንድነት ድጋፋቸውን እንደሚያደርጉ ገልፀው፥ ነገር ግን ወታደራዊ ተተኪዎቹ ወደሲቪል አስተዳደር በሰላም እንዲመለሱ አሳስበዋል።
የቀድሞ የቻድ ፕሬዝዳንት ኢድሪስ ዴቢ ባለፈው ሰኞ ዕለት በሃገሪቱ ሰሚናዊ ክፍለ ግዛት ከአማጽያኑ ጋር የሚዋጉትን ወታደሮች በውጊያው ግንባር ተገኝተው በመጎብኘት ላይ ሳሉ ቆስለው ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
“...ቻድን ማንም እንዲያስፈራራት አልፈቅድም” - የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት
የቀድሞ የቻድ ፕሬዝዳንት ኢድሪስ ዴቢ ቀብር ስነስርዓት ዛሬ በትውልድ አካባቢያቸው አቅራቢያ ተፈፀመ።
የቀብር ስነስርዓቱ በትውልድ አካባቢያቸው ከመፈፀሙ ቀደም ብሎ በኒጃሚን በነበረ ስነስርዓት የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ የኮንጎ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ቺሲዲኬ እና ሌሎችም ተገኘተው ነበር ፤ ምንም እንኳን አማፂያን የሀገራት መሪዎች በደህንነት ምክንያት በስነ ስርዓቱ ላይ እንዳይገኙ ቢያስጠነቅቁም።
ፕሬዜዳንት ማክሮን ፥ በስነስዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ፥ “ቻድን ማንም እንዲያስፈራራት አልፈቅድም” ሲሉ ተደምጠዋል።
ለቻድ መረጋጋት እና አንድነት ድጋፋቸውን እንደሚያደርጉ ገልፀው፥ ነገር ግን ወታደራዊ ተተኪዎቹ ወደሲቪል አስተዳደር በሰላም እንዲመለሱ አሳስበዋል።
የቀድሞ የቻድ ፕሬዝዳንት ኢድሪስ ዴቢ ባለፈው ሰኞ ዕለት በሃገሪቱ ሰሚናዊ ክፍለ ግዛት ከአማጽያኑ ጋር የሚዋጉትን ወታደሮች በውጊያው ግንባር ተገኝተው በመጎብኘት ላይ ሳሉ ቆስለው ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#NEBE
ዛሬ ማምሻውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መግለጫ ከሃገሪቱ የምርጫ ህግና የስነ ምግባር አዋጅ በተጻረረ መልኩ "ለአመጽ የሚጋብዝና በግለሰቦች ወይም ቡድኖች ላይ ስጋትን የሚያጭር ቋንቋ" ን የሚጠቀሙ ፓርቲዎች እና እጩዎችን አሳስቧል።
ፓርቲዎች እና እጩዎች ግጭት ቀስቃሽ ከሆኑ ንግግሮች እና ድርጊቶች እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል፡፡ ህጉ የማይከበር ከሆነ እርምጃዎችን እንደሚወስድ አሳስቧል።
* የምርጫ ቦርድ መግለጫ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ዛሬ ማምሻውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መግለጫ ከሃገሪቱ የምርጫ ህግና የስነ ምግባር አዋጅ በተጻረረ መልኩ "ለአመጽ የሚጋብዝና በግለሰቦች ወይም ቡድኖች ላይ ስጋትን የሚያጭር ቋንቋ" ን የሚጠቀሙ ፓርቲዎች እና እጩዎችን አሳስቧል።
ፓርቲዎች እና እጩዎች ግጭት ቀስቃሽ ከሆኑ ንግግሮች እና ድርጊቶች እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል፡፡ ህጉ የማይከበር ከሆነ እርምጃዎችን እንደሚወስድ አሳስቧል።
* የምርጫ ቦርድ መግለጫ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የመራጮች ምዝገባ ተራዘመ።
የመራጮች ምዝገባ መራዘምን አስመልክቶ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ምሽት መግለጫ ሰጥቷል።
ቦርዱ የመራጮች ምዝገባ ቀን ማጠናቀቂያ ዛሬ መሆኑን ተከትሎ የስራ ሂደቱን ያጋጠሙትን ችግሮች መመርመሩን ገልጿል።
በዚህም መሰረት ፦
1. የመራጮች ምዝገባ በግማሽ የአገሪቱ ክፍሎች ዘግይቶ በመጀመሩ
2. በጊዜው በተጀመረባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባ መረጃዎች እጦት እና በሌሎች ምክንያቶች ለመመዝገብ ጊዜ በመውሰዱ
3. የመራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቁ በቀሩት ጥቂት ቀናት በአንድ ምርጫ ጣቢያ 1500 ሰው ብቻ መመዝገብ በመቻሉ የተነሳ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በሚገኙ የተወሰኑ ምርጫ ጣቢያዎች ምዝገባ በመቋረጡ እና ተጨማሪ ምርጫ ጣቢያዎች በመክፈት ሂደት ክፍተት በመፈጠሩ ቦርዱ የመራጮች ምዝገባ እንዲራዘም ወስኗል።
በዚህም መሰረት ፦
1. የመራጮች ምዝገባ እጅግ ዘግይቶ በጀመረባቸው በአፋር እና በሶማሌ ክልል የመራጮች ምዝገባ ለሶስት ሳምንት ተራዝሟል ። ይህም ማለት የመራጮች ምዝገባ ግንቦት 06 ቀን 2013 የሚጠናቀቅ ይሆናል።
2. የመራጮች ምዝገባ ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች በተስተጓጎለባቸው ሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ለሁለት ሳምንት ተራዝሟል ይህም ማለት የመራጮች ምዝገባ ሚያዝያ 29 ቀን 2013 የሚጠናቀቅ ይሆናል።
3. የመራጮች ምዝገባ እስካሁን ድረስ ባልተጀመረባቸው እና የጸጥታ ችግር ባለባቸው ቦታዎች በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ሆሮጉድሩ እና ቄለም ወለጋ የመራጮች ምዝገባን የማስጀመር እንቅስቃሴዎችን እየተደረገ ይገኛል።
4. 1500 ሰዎቸን መዝግበው በጨረሱ ምርጫ ጣቢያዎች ተጨማሪ ንኡስ ምርጫ ጣቢያዎችን መክፈት የሚቀጥል ይሆናል።
* ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የመራጮች ምዝገባ መራዘምን አስመልክቶ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ምሽት መግለጫ ሰጥቷል።
ቦርዱ የመራጮች ምዝገባ ቀን ማጠናቀቂያ ዛሬ መሆኑን ተከትሎ የስራ ሂደቱን ያጋጠሙትን ችግሮች መመርመሩን ገልጿል።
በዚህም መሰረት ፦
1. የመራጮች ምዝገባ በግማሽ የአገሪቱ ክፍሎች ዘግይቶ በመጀመሩ
2. በጊዜው በተጀመረባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባ መረጃዎች እጦት እና በሌሎች ምክንያቶች ለመመዝገብ ጊዜ በመውሰዱ
3. የመራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቁ በቀሩት ጥቂት ቀናት በአንድ ምርጫ ጣቢያ 1500 ሰው ብቻ መመዝገብ በመቻሉ የተነሳ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በሚገኙ የተወሰኑ ምርጫ ጣቢያዎች ምዝገባ በመቋረጡ እና ተጨማሪ ምርጫ ጣቢያዎች በመክፈት ሂደት ክፍተት በመፈጠሩ ቦርዱ የመራጮች ምዝገባ እንዲራዘም ወስኗል።
በዚህም መሰረት ፦
1. የመራጮች ምዝገባ እጅግ ዘግይቶ በጀመረባቸው በአፋር እና በሶማሌ ክልል የመራጮች ምዝገባ ለሶስት ሳምንት ተራዝሟል ። ይህም ማለት የመራጮች ምዝገባ ግንቦት 06 ቀን 2013 የሚጠናቀቅ ይሆናል።
2. የመራጮች ምዝገባ ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች በተስተጓጎለባቸው ሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ለሁለት ሳምንት ተራዝሟል ይህም ማለት የመራጮች ምዝገባ ሚያዝያ 29 ቀን 2013 የሚጠናቀቅ ይሆናል።
3. የመራጮች ምዝገባ እስካሁን ድረስ ባልተጀመረባቸው እና የጸጥታ ችግር ባለባቸው ቦታዎች በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ሆሮጉድሩ እና ቄለም ወለጋ የመራጮች ምዝገባን የማስጀመር እንቅስቃሴዎችን እየተደረገ ይገኛል።
4. 1500 ሰዎቸን መዝግበው በጨረሱ ምርጫ ጣቢያዎች ተጨማሪ ንኡስ ምርጫ ጣቢያዎችን መክፈት የሚቀጥል ይሆናል።
* ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT