#Attention😷
ባለፉት 24 ሰዓት 33 ሰዎች በኮቪድ-19 መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።
በተመሳሳይ ከተደረገው 7,487 የላብራቶሪ ምርመራ 1,851 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ትላንት 1,193 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 225,516 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 3,111 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 167,945 ሰዎች አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት 895 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ባለፉት 24 ሰዓት 33 ሰዎች በኮቪድ-19 መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።
በተመሳሳይ ከተደረገው 7,487 የላብራቶሪ ምርመራ 1,851 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ትላንት 1,193 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 225,516 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 3,111 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 167,945 ሰዎች አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት 895 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#GERD🇪🇹
የውኃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ኢትዮጵያ በመጪው ክረምት ለምታከናውነው የውሃ ሙሌት ሀገራቱ የግድብ ባለሙያዎችን ኢንዲመድቡ በይፋ ጋብዘዋል።
ሚኒስትሩ ለሱዳን የውሃ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ለግብፅ ውሃ ሚኒስቴር በላኩት ድባዳቤ ነው ሁለቱ ሀገራት የፊታችን ሐምሌ እና ነሃሴ ወር ላይ የሚከናወነውን የውሃ ሙሌት በተመለከተ የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ የሚያስችል ባለሙያን እንዲመድቡ የጋበዘዋቸዋል።
በሚኒስትሩ ደብዳቤ መሠረት ግብዣው የ3ቱ ሀገራት ብሄራዊ ገለልተኛ የሳይንስ ምርምር ቡድን (NISRG) ባቀረበው የሙሌት የጊዜ ሰሌዳ ላይ በተደረሰው መግባባት ላይ በመመርኮዝ የቀረበ መሆኑ እና በዚህም መሰረት ሙሌቱ በሐምሌ እና ነሐሴ ወር ውስጥ እንደሚከናወን ፤ በወቀቱ በሚኖር የውሃ መጠን ላይ በመመርኮዝ እስከ መስከረም ወር ሊራዘም እንደሚችል ተመላክቷል።
የግድቡ ግንባታ የደረሰበትን ሁኔታና የዝናብ ወቅት መድረሱን የጠቀሱት ሚኒስትሩ ተግባራዊና አስፈላጊ የሆነ የንግግር መድረክ ማመቻቸት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
መረጃ የሚለዋወጥ ሰው መመደብ ትክክለኛ የሆነ የመረጃ ልውውጥ ያፋጥናል፤ በአፍሪካ ህብረት ስር የሚደረገው የግድቡ ድርድር እስከሚጠናቀቅ ድረስ በሶስቱ ሀገራት መካከል መተማማን ይፈጥራል ብሏል መግለጫው፡፡
መግልጫው እንደጠቀሰው ሚኒስትሩ በጻፉት ደብዳቤ ላይ ካርቱም ውስጥ በፈረንጆቹ 2015 በሱዳን በሶስቱ ሀገራት በተፈረመው “የመርሆች ስምምነት መሰረት” በመጀመሪያው የግድቡ ሙሌት ህጎችና መመሪያዎች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን መረጃ የሚለዋወጡ ሰዎቸ ስብሰባ ለማካሄድ ፍላጎት አላት ብለዋል፡፡ [Al AIN News]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የውኃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ኢትዮጵያ በመጪው ክረምት ለምታከናውነው የውሃ ሙሌት ሀገራቱ የግድብ ባለሙያዎችን ኢንዲመድቡ በይፋ ጋብዘዋል።
ሚኒስትሩ ለሱዳን የውሃ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ለግብፅ ውሃ ሚኒስቴር በላኩት ድባዳቤ ነው ሁለቱ ሀገራት የፊታችን ሐምሌ እና ነሃሴ ወር ላይ የሚከናወነውን የውሃ ሙሌት በተመለከተ የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ የሚያስችል ባለሙያን እንዲመድቡ የጋበዘዋቸዋል።
በሚኒስትሩ ደብዳቤ መሠረት ግብዣው የ3ቱ ሀገራት ብሄራዊ ገለልተኛ የሳይንስ ምርምር ቡድን (NISRG) ባቀረበው የሙሌት የጊዜ ሰሌዳ ላይ በተደረሰው መግባባት ላይ በመመርኮዝ የቀረበ መሆኑ እና በዚህም መሰረት ሙሌቱ በሐምሌ እና ነሐሴ ወር ውስጥ እንደሚከናወን ፤ በወቀቱ በሚኖር የውሃ መጠን ላይ በመመርኮዝ እስከ መስከረም ወር ሊራዘም እንደሚችል ተመላክቷል።
የግድቡ ግንባታ የደረሰበትን ሁኔታና የዝናብ ወቅት መድረሱን የጠቀሱት ሚኒስትሩ ተግባራዊና አስፈላጊ የሆነ የንግግር መድረክ ማመቻቸት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
መረጃ የሚለዋወጥ ሰው መመደብ ትክክለኛ የሆነ የመረጃ ልውውጥ ያፋጥናል፤ በአፍሪካ ህብረት ስር የሚደረገው የግድቡ ድርድር እስከሚጠናቀቅ ድረስ በሶስቱ ሀገራት መካከል መተማማን ይፈጥራል ብሏል መግለጫው፡፡
መግልጫው እንደጠቀሰው ሚኒስትሩ በጻፉት ደብዳቤ ላይ ካርቱም ውስጥ በፈረንጆቹ 2015 በሱዳን በሶስቱ ሀገራት በተፈረመው “የመርሆች ስምምነት መሰረት” በመጀመሪያው የግድቡ ሙሌት ህጎችና መመሪያዎች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን መረጃ የሚለዋወጡ ሰዎቸ ስብሰባ ለማካሄድ ፍላጎት አላት ብለዋል፡፡ [Al AIN News]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
"ሮሃ ግሩፕ" የተሰኘ በጤና ዘርፍ የተሰማራ የአሜሪካ ኩባንያ በራሱ ወጪ የሚያስገነባው "ሮሃ የህክምና ማዕከል" ሜጋ ፕሮጀክት ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።
የመሰረት ድንጋዩን ያስቀመጡት የኢትዮጵያ ጠ/ሚር አብይ አህመድ ናቸው።
የ "ሮሃ ህክምና ማዕከል" ሜጋ ፕሮጄክት ግንባታው በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 13 "አድዋ ፓርክ" አካባቢ በ300 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ነው የሚገነባው።
የፕሮጀክቱ ግንባታ በ5 ዓመት ይጠናቀቃል ተብሏል።
የሕክምና ማዕከሉ በውስጡ 5 ሆስፒታሎች እንደሚኖሩት ተገልጿል።
በግንባታው በየዓመቱ አንድ ሆስፒታል አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ መታቀዱ ነው የተሰማው።
ሮሃ የሕክምና ማዕከል በውስጡ የነርቭና የጀርባ ፣ የህጻናትና እናቶችና የልብ ሕክምና ሆስፒታሎች ፣ የሕክምና ትምህርት ቤት እንዲሁም የጥናትና ፈጠራ እና የማገገሚያ ማዕከላት እንደሚኖሩት ተገልጿል።
ማዕከሉ 4 ሺ 200 የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ለ7 ሺህ 200 ሰዎች የስራ ዕድል ይፈጥራል ተብሏል።
#ENA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የመሰረት ድንጋዩን ያስቀመጡት የኢትዮጵያ ጠ/ሚር አብይ አህመድ ናቸው።
የ "ሮሃ ህክምና ማዕከል" ሜጋ ፕሮጄክት ግንባታው በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 13 "አድዋ ፓርክ" አካባቢ በ300 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ነው የሚገነባው።
የፕሮጀክቱ ግንባታ በ5 ዓመት ይጠናቀቃል ተብሏል።
የሕክምና ማዕከሉ በውስጡ 5 ሆስፒታሎች እንደሚኖሩት ተገልጿል።
በግንባታው በየዓመቱ አንድ ሆስፒታል አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ መታቀዱ ነው የተሰማው።
ሮሃ የሕክምና ማዕከል በውስጡ የነርቭና የጀርባ ፣ የህጻናትና እናቶችና የልብ ሕክምና ሆስፒታሎች ፣ የሕክምና ትምህርት ቤት እንዲሁም የጥናትና ፈጠራ እና የማገገሚያ ማዕከላት እንደሚኖሩት ተገልጿል።
ማዕከሉ 4 ሺ 200 የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ለ7 ሺህ 200 ሰዎች የስራ ዕድል ይፈጥራል ተብሏል።
#ENA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
ለ22 ዓመት ጅቡቲን የመሩት ፕሬዜዳንት ለተጨማሪ የስልጣን ዘመን እየተወዳደሩ ነው ! የጂቡቲ ህዝብ ለፕሬዝዳንታዊው ምርጫ ዛሬ ድምፅ በመስጠት ላይ ይገኛል። የጅቡቲው ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ ለ5ኛ ጊዜ ለፕሬዜዳንትነት እየተወዳደሩ ይገኛሉ። ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ ዛሬ ከቀትር በኋላ ድምፃቸውን ሰተዋል። ከ200 ሺህ በላይ ድምፅ ሰጪዎች የተሳተፉበት ምርጫ ምሽት ላይ ይዘጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡…
ግዜያዊ ውጤት : ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከ98% በላይ ድምፅ አገኝተዋል።
ጊዜያዊ ውጤቶች እንዳመለከቱት ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከ98% በላይ ድምፅ አግኝተው ለ5ኛ ጊዜ የጅቡቲን ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ አሸንፈዋል።
ዋነኛዎቹ ተፎካካሪዎች ምርጫው "ነፃ እና ፍትሃዊ" አይደለም ብለው እራሳቸውን ባገለሉበት የጅቡቲ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ከ21 ዓመት በላይ በሥልጣን ላይ የሚገኙት የ73 ዓመቱ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከ98% በላይ ድምፅ አግኝተዋል ተብሏል።
ይህ ጊዜያዊ ውጤት የተገለፀው ትላንት ለሊት ነው።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ጊዜያዊ ውጤቶች እንዳመለከቱት ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከ98% በላይ ድምፅ አግኝተው ለ5ኛ ጊዜ የጅቡቲን ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ አሸንፈዋል።
ዋነኛዎቹ ተፎካካሪዎች ምርጫው "ነፃ እና ፍትሃዊ" አይደለም ብለው እራሳቸውን ባገለሉበት የጅቡቲ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ከ21 ዓመት በላይ በሥልጣን ላይ የሚገኙት የ73 ዓመቱ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከ98% በላይ ድምፅ አግኝተዋል ተብሏል።
ይህ ጊዜያዊ ውጤት የተገለፀው ትላንት ለሊት ነው።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
አፍሪካ : ለረጅም ጊዜ በስልጣን ላይ የሚገኙ/እያገለገሉ ያሉ መሪዎች ፦
[official data & AFP bureaux]
- ቴዎዶሮ ኦቢአንግ ነጉኤማ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 41 ዓመታት በስልጣን
- ፖውል ቢያ (ካሜሩን) 38 ዓመታት
- ዴኒስ ሳሱ ንጉሶ (ኮንጎ) 37 ዓመታት
- ዩዌሪ ሙሴቬኒ (ዩጋንዳ) 35 ዓመታት
- ምዋስቲ III (ስዋቲኒ) 34 ዓመታት
- ኢድሪስ ዴቢ (ቻድ) 30 ዓመታት
- ሌቲስ III (ሌሴቶ) 29 ዓመታት
- ኢሳያስ አፈወርቂ (ኤርትራ) 27 ዓመታት
- ኢስማኤል ኡማር ጌሌ (ጅቡቲ) ከ21 ዓመታት በላይ
- መሀመድ VI (ሞሮኮ) 21 ዓመታት
- ፖል ካጋሜ (ሩዋንዳ) 21 ዓመታት
- ፋውሬ ግናሲንግቤ (ቶጎ) 15 ዓመታት
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
[official data & AFP bureaux]
- ቴዎዶሮ ኦቢአንግ ነጉኤማ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 41 ዓመታት በስልጣን
- ፖውል ቢያ (ካሜሩን) 38 ዓመታት
- ዴኒስ ሳሱ ንጉሶ (ኮንጎ) 37 ዓመታት
- ዩዌሪ ሙሴቬኒ (ዩጋንዳ) 35 ዓመታት
- ምዋስቲ III (ስዋቲኒ) 34 ዓመታት
- ኢድሪስ ዴቢ (ቻድ) 30 ዓመታት
- ሌቲስ III (ሌሴቶ) 29 ዓመታት
- ኢሳያስ አፈወርቂ (ኤርትራ) 27 ዓመታት
- ኢስማኤል ኡማር ጌሌ (ጅቡቲ) ከ21 ዓመታት በላይ
- መሀመድ VI (ሞሮኮ) 21 ዓመታት
- ፖል ካጋሜ (ሩዋንዳ) 21 ዓመታት
- ፋውሬ ግናሲንግቤ (ቶጎ) 15 ዓመታት
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#HawassaUniversity
ዛሬ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 270 የህክምና ዶክተሮችን አስመርቋል።
ከተመራቂዎቹ መካከል 48ቱ በተለያዩ የህክምና ስፔሻሊቲ ፕሮግራም የሰለጠኑ ናቸው።
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዶክተሮችን ሲያስመርቅ የዛሬው ለ12ኛ ጊዜ ነው።
በሌላ በኩል ፦ ከ12ኛ ዙር ተመራቂዎች መካከል ዶክተር ዮናስ ንጉሴ 3 ነጥብ 87 ውጤት በማምጣት የወርቅ ሜዳሊያ ተሻላሚ መሆን ችሏል።
በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል እስካሁን ከተመዘገቡ ውጤቶች ውስጥ ከፍተኛው በመሆንም ክብረወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።
ምንጭ፦ SRTA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ዛሬ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 270 የህክምና ዶክተሮችን አስመርቋል።
ከተመራቂዎቹ መካከል 48ቱ በተለያዩ የህክምና ስፔሻሊቲ ፕሮግራም የሰለጠኑ ናቸው።
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዶክተሮችን ሲያስመርቅ የዛሬው ለ12ኛ ጊዜ ነው።
በሌላ በኩል ፦ ከ12ኛ ዙር ተመራቂዎች መካከል ዶክተር ዮናስ ንጉሴ 3 ነጥብ 87 ውጤት በማምጣት የወርቅ ሜዳሊያ ተሻላሚ መሆን ችሏል።
በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል እስካሁን ከተመዘገቡ ውጤቶች ውስጥ ከፍተኛው በመሆንም ክብረወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።
ምንጭ፦ SRTA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የቤት ቁልፍ መረከቢያ ፕሮግራም - Tikvah.pdf
230.4 KB
የ40/60 መኖሪያ ቤት ቁልፍ መረከቢያ ፕሮግራም :
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ካስገነባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል ለተጠቃሚዎች ያስተላለፋቸውን ቤቶች ቁልፍ ለቤት ባለቤቶች ከመጋቢት 6 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ እያስረከበ እንደሚገኝ አስታውሷል።
የቤት ባለቤቶችም አስፈላጊ የሰነድ ማስረጃዎችን ይዛችሁን በPDF ፋይሉ በተገለፀው ፕሮግራም መሰረት የቤታችሁን ቁልፍ እንድትረከቡ ጥሪ ቀርቧል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ካስገነባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል ለተጠቃሚዎች ያስተላለፋቸውን ቤቶች ቁልፍ ለቤት ባለቤቶች ከመጋቢት 6 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ እያስረከበ እንደሚገኝ አስታውሷል።
የቤት ባለቤቶችም አስፈላጊ የሰነድ ማስረጃዎችን ይዛችሁን በPDF ፋይሉ በተገለፀው ፕሮግራም መሰረት የቤታችሁን ቁልፍ እንድትረከቡ ጥሪ ቀርቧል።
@tikvahethiopia
"...ዘገባው የተሰራበት መንገድ ስህተት ነው" - አቶ ሀጂ ኢብሳ
By : am.al-ain.com
ከፈነዱ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያሰከትሉ የሚችሉ ተቀጣጣይ ኬሜካሎች በብዙ ድርጅቶች መጋዘን ላይ እንደሚገኙ የሚገልጹ ዘገባዎች ስህተት ናቸው።
የመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀጂ ኢብሳ ፣ ዘገባው የተሰራበት መንገድ ስህተት እንደሆነ ከአል ዓይን ድረገፅ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ተናግረዋል።
አቶ ሀጂ ፥ "እውነታው በአዲስ አበባ ባሉ የስንዴ መጋዘኖች፣ ዩንቨርሲቲዎች፣ ሆስፒታሎችና የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን መጋዘኖች አካባቢ ፣ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙ እና ሊፈነዱ የሚችሉ ኬሚካሎች ተከማችተው ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ኬሚካሎች በተከዘኑባቸው ቦታዎች ቢፈነዱ መጋዘኖቹ ካሉበት ስፍራ ጀምሮ እስከ 250 ሜትር ባሉ ስፍራዎች ውስጥ አደጋ ሊያደረሱ ይችላሉ የሚል ነው” ብለዋል።
አክለው ፥ “እኔን ዋቢ አድርገው የተለያዩ ብዙሃን መገናኛዎች አዲስ አበባን ጨምሮ በ250 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ ባሉ ከተሞች ላይ አደጋ ሊፈጠር የሚችል ኬሚካል ተከማችቷል የሚል ዘገባ ሰርተዋል። እኔ ለነዚህ የሚዲያ ተቋማት ይሄንን መናገሬን አላስታውስም። በዚያ መንገድ ተናግሬም ከሆነ ግን በአፍ ወለምታ በስህተት ነው ፣ ለዚህም ይቅርታ እጠይቃለሁ” ብለዋል።
እነዚህን ኬሚካሎች ለማስወገድ ከአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ጋር ጥናቶችን እየተካሄዱ መሆኑን ያሳወቁት አቶ ሀጂ ፤ በያዝነው ሚያዝያ ወር ውስጥ ጥናቱ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
ከመንግስት እውቅ እንዲሁም ፍቃድ ውጪ የገቡ ኬሚካሎች ሊኖሩ እንደሚችሉ የተገለፀ ሲሆን ጥናቱ ሲጠናቀቅ የሌሎች አገራትን ልምድ ተጠይቆ ኬሚካሎችን በፍጥነት ይወገዳሉ ተብሏል።
@tikvahethiopiaBOT
By : am.al-ain.com
ከፈነዱ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያሰከትሉ የሚችሉ ተቀጣጣይ ኬሜካሎች በብዙ ድርጅቶች መጋዘን ላይ እንደሚገኙ የሚገልጹ ዘገባዎች ስህተት ናቸው።
የመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀጂ ኢብሳ ፣ ዘገባው የተሰራበት መንገድ ስህተት እንደሆነ ከአል ዓይን ድረገፅ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ተናግረዋል።
አቶ ሀጂ ፥ "እውነታው በአዲስ አበባ ባሉ የስንዴ መጋዘኖች፣ ዩንቨርሲቲዎች፣ ሆስፒታሎችና የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን መጋዘኖች አካባቢ ፣ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙ እና ሊፈነዱ የሚችሉ ኬሚካሎች ተከማችተው ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ኬሚካሎች በተከዘኑባቸው ቦታዎች ቢፈነዱ መጋዘኖቹ ካሉበት ስፍራ ጀምሮ እስከ 250 ሜትር ባሉ ስፍራዎች ውስጥ አደጋ ሊያደረሱ ይችላሉ የሚል ነው” ብለዋል።
አክለው ፥ “እኔን ዋቢ አድርገው የተለያዩ ብዙሃን መገናኛዎች አዲስ አበባን ጨምሮ በ250 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ ባሉ ከተሞች ላይ አደጋ ሊፈጠር የሚችል ኬሚካል ተከማችቷል የሚል ዘገባ ሰርተዋል። እኔ ለነዚህ የሚዲያ ተቋማት ይሄንን መናገሬን አላስታውስም። በዚያ መንገድ ተናግሬም ከሆነ ግን በአፍ ወለምታ በስህተት ነው ፣ ለዚህም ይቅርታ እጠይቃለሁ” ብለዋል።
እነዚህን ኬሚካሎች ለማስወገድ ከአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ጋር ጥናቶችን እየተካሄዱ መሆኑን ያሳወቁት አቶ ሀጂ ፤ በያዝነው ሚያዝያ ወር ውስጥ ጥናቱ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
ከመንግስት እውቅ እንዲሁም ፍቃድ ውጪ የገቡ ኬሚካሎች ሊኖሩ እንደሚችሉ የተገለፀ ሲሆን ጥናቱ ሲጠናቀቅ የሌሎች አገራትን ልምድ ተጠይቆ ኬሚካሎችን በፍጥነት ይወገዳሉ ተብሏል።
@tikvahethiopiaBOT
"...ሃሰተኛ መረጃ በማሰራጨት በአዲስ አበባ ነዎሪዎች ላይ የደህንነት ስጋት ለመፍጠር ተሞክሯል" - የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት
"አዲስ አበባን ሙሉ በሙሉ የሚያወድም ጊዜው ያለፈበት የኬሚካል ክምችት አለ" በሚል በአንዳንድ መገናኛ ብዙሃንና ማህበራዊ የትስስር ገፆች የተሰራጨው መረጃ የተዛባና የተሳሳተ በመሆኑ ፤ ነዋሪዎች የዕለተ ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን ያለስጋት እንዲያከናወን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አሳሰበ።
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እንዳስታወቀው ፥ በትናንትነው ዕለት የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የሰጠውን ጋዜጣዊ መግለጫ አንዳንድ መገናኛ ብዙሃንና የማህበራዊ የትስስር ገፆች አዛብተው አዲስ አበባን ሙሉ በሙሉ ማውደም የሚችል ጊዜው ያለፈበት የኬሚካል ክምችት አለ በማለት ሃሰተኛ መረጃ በማሰራጨት በከተማዋ ነዎሪዎች ላይ የደህንነት ስጋት ለመፍጠር እየሞከሩ ነው ብሏል።
በኤጀንሲው የተሰጠውን ጋዜጣዊ መግለጫ አዛብተው በማቅረብ፤ አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን እና የማህበራዊ ትስስር ገፆች "አዲስ አበባን ሙሉ በሙሉ ማውደም የሚችል ጊዜው ያለፈበት የኬሚካል ክምችት በተለምዶ ላፍቶ በሚባለው አካባቢ አለ" የሚል ሃሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ህብረተሰቡን የማደናገርና ከዚያም ባለፈ የደህንነት ስጋት ለመፍጠር እየሞከሩ መሆኑን አሳውቋል።
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በአ/አ አለ የተባለው የኬሚካል ክምችት ለከተማዋ ነዎሪዎች የደህንነት ስጋት የሚፈጠር አለመሆኑን ከሚመለከታቸው አካላት ያረጋገጠ ሲሆን ፤ ህብረተሰቡ በተሰራጨው የተሳሳተ መረጃ ሳይወናበድ የዕለተ ተዕለት እንቅስቃሴውን ያለምንም ስጋት እንዲያከናውን አገልግሉት መስሪያ ቤቱ አበክሮ ጥሪ አቅርቧል፡፡
More : telegra.ph/NISS-04-10
@tikvahethiopia
"አዲስ አበባን ሙሉ በሙሉ የሚያወድም ጊዜው ያለፈበት የኬሚካል ክምችት አለ" በሚል በአንዳንድ መገናኛ ብዙሃንና ማህበራዊ የትስስር ገፆች የተሰራጨው መረጃ የተዛባና የተሳሳተ በመሆኑ ፤ ነዋሪዎች የዕለተ ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን ያለስጋት እንዲያከናወን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አሳሰበ።
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እንዳስታወቀው ፥ በትናንትነው ዕለት የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የሰጠውን ጋዜጣዊ መግለጫ አንዳንድ መገናኛ ብዙሃንና የማህበራዊ የትስስር ገፆች አዛብተው አዲስ አበባን ሙሉ በሙሉ ማውደም የሚችል ጊዜው ያለፈበት የኬሚካል ክምችት አለ በማለት ሃሰተኛ መረጃ በማሰራጨት በከተማዋ ነዎሪዎች ላይ የደህንነት ስጋት ለመፍጠር እየሞከሩ ነው ብሏል።
በኤጀንሲው የተሰጠውን ጋዜጣዊ መግለጫ አዛብተው በማቅረብ፤ አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን እና የማህበራዊ ትስስር ገፆች "አዲስ አበባን ሙሉ በሙሉ ማውደም የሚችል ጊዜው ያለፈበት የኬሚካል ክምችት በተለምዶ ላፍቶ በሚባለው አካባቢ አለ" የሚል ሃሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ህብረተሰቡን የማደናገርና ከዚያም ባለፈ የደህንነት ስጋት ለመፍጠር እየሞከሩ መሆኑን አሳውቋል።
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በአ/አ አለ የተባለው የኬሚካል ክምችት ለከተማዋ ነዎሪዎች የደህንነት ስጋት የሚፈጠር አለመሆኑን ከሚመለከታቸው አካላት ያረጋገጠ ሲሆን ፤ ህብረተሰቡ በተሰራጨው የተሳሳተ መረጃ ሳይወናበድ የዕለተ ተዕለት እንቅስቃሴውን ያለምንም ስጋት እንዲያከናውን አገልግሉት መስሪያ ቤቱ አበክሮ ጥሪ አቅርቧል፡፡
More : telegra.ph/NISS-04-10
@tikvahethiopia
#Ethiopia😷
ባለፉት 24 ሰዓት 35 ሰዎች በኮቪድ-19 መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።
በተመሳሳይ ከተደረገው 7,278 የላብራቶሪ ምርመራ 1,739 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ትላንት 1,093 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 227,255 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 3,146 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 169,038 ሰዎች አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት 933 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ባለፉት 24 ሰዓት 35 ሰዎች በኮቪድ-19 መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።
በተመሳሳይ ከተደረገው 7,278 የላብራቶሪ ምርመራ 1,739 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ትላንት 1,093 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 227,255 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 3,146 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 169,038 ሰዎች አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት 933 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ሼህ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ አሚን አረፉ።
[Harun Media , Ustaz Abubeker Ahmed]
በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ በሆኑት በራያና አካባቢው ከፍተኛ እውቅና የነበራቸው እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በሸራተኑ ጉባኤ ከተመረጡት 26 ኡለሞች ውስጥ አንዱ የነበሩት ሼህ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ አሚን በአዲስ አበባ ከተማ ህይወታቸው አለፈ።
ሼህ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ በኮቪድ-19 ምክንያት ነው ህይወታቸው እንዳለፈ የተገለፀው።
ሼይኽ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ በኢልማቸው አንቱታን ያተረፉ በርካታ ደረሶችን ያፈሩ ትልቅ አሊም የነበሩ ሲሆን የራያን እና የአካባቢውን ህዝበ ሙስሊም ኢልም በማስተማር ትልቅ ድርሻ የነበራቸው ታላቅ አሊም ነበሩ።
ሼክ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ አሊሞች ማህበር ምክትል ዋና ፀሃፊ በመሆን ያገለገሉ ሲሆን የቀድሞው አል ሂጅራ መፅሄት የአረብኛው ክፍል ላይ በዋና አዘጋጅነት አግልግለዋል።
ሼይኽ ሂዝቡሏህ በ2004 ህዝበ ሙስሊሙ የመንግስትን የሃይማኖት ጣልቃ ገብነት በመቃወም ሲያካሂደው በነበረው ሰላማዊ የመብት ትግል ወቅት ከሃቅ ጎን በመቆማቸው ኢማም ከነበሩበት መስጂድ እንዲነሱ ተደርገው ለእስር ተዳርገው የቆዩ ሲሆን እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ህዝበ ሙስሊሙን በማገልገል ላይ ነበሩ።
ሼህ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ በህዝበ ሙስሊሙ የጣለባቸውን አማና ለመወጣት በቅርቡ የተካሄደውን የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠ/ምቤት ጠቅላላ ጉባኤ ለመሳተፍ መጥተው አዲስ አበባ የሰነበቱ ሲሆን የጉባኤውን ውሳኔ አፈፃፀም ተግባራዊ እስኪሆን ድረስ ወደመጡበት ላለመመለስ ወስነው በአዲስ አበባ በመጠባበቅ ላይ ሳሉ ነዉ ህይወታቸው ያለፈው።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
[Harun Media , Ustaz Abubeker Ahmed]
በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ በሆኑት በራያና አካባቢው ከፍተኛ እውቅና የነበራቸው እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በሸራተኑ ጉባኤ ከተመረጡት 26 ኡለሞች ውስጥ አንዱ የነበሩት ሼህ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ አሚን በአዲስ አበባ ከተማ ህይወታቸው አለፈ።
ሼህ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ በኮቪድ-19 ምክንያት ነው ህይወታቸው እንዳለፈ የተገለፀው።
ሼይኽ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ በኢልማቸው አንቱታን ያተረፉ በርካታ ደረሶችን ያፈሩ ትልቅ አሊም የነበሩ ሲሆን የራያን እና የአካባቢውን ህዝበ ሙስሊም ኢልም በማስተማር ትልቅ ድርሻ የነበራቸው ታላቅ አሊም ነበሩ።
ሼክ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ አሊሞች ማህበር ምክትል ዋና ፀሃፊ በመሆን ያገለገሉ ሲሆን የቀድሞው አል ሂጅራ መፅሄት የአረብኛው ክፍል ላይ በዋና አዘጋጅነት አግልግለዋል።
ሼይኽ ሂዝቡሏህ በ2004 ህዝበ ሙስሊሙ የመንግስትን የሃይማኖት ጣልቃ ገብነት በመቃወም ሲያካሂደው በነበረው ሰላማዊ የመብት ትግል ወቅት ከሃቅ ጎን በመቆማቸው ኢማም ከነበሩበት መስጂድ እንዲነሱ ተደርገው ለእስር ተዳርገው የቆዩ ሲሆን እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ህዝበ ሙስሊሙን በማገልገል ላይ ነበሩ።
ሼህ ሂዝቡሏህ ሙሐመድ በህዝበ ሙስሊሙ የጣለባቸውን አማና ለመወጣት በቅርቡ የተካሄደውን የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠ/ምቤት ጠቅላላ ጉባኤ ለመሳተፍ መጥተው አዲስ አበባ የሰነበቱ ሲሆን የጉባኤውን ውሳኔ አፈፃፀም ተግባራዊ እስኪሆን ድረስ ወደመጡበት ላለመመለስ ወስነው በአዲስ አበባ በመጠባበቅ ላይ ሳሉ ነዉ ህይወታቸው ያለፈው።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የህግ ተመራቂዎቹ አቤቱታ : በአዲስ አበባ የሚኖሩ የ2012/13 ዓ.ም የህግ ትምህርት ተመራቂዎች በፌደራል ደረጃ ለህግ ተማሪዎች ይሰጥ የነበረዉን የቅድመ ስራ ስልጠና ዳግም መሠጠት እንዲጀምር ለተለያዩ የመንግስት አካላት በፃፉት ደብዳቤ ጠይቀዋል።
@tikvahethiopia
@tikvahethiopia
#Update
ስቴም ፓወር ከቪዛ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የሥራ ፈጠራ ክህሎት እና መሰረታዊ የፋይናንስ ትምህርት ላይ ያተኮረው የመጀመሪያ ዙር ስልጠና 114 ሰልጣኞች ስልጠናቸውን ለሦስት ወር ተከታትለው አጠናቀዋል።
በመጀመሪያው ዙር ስልጠና ከተካፈሉ ሰልጣኞች የሰሯቸው ፕሮጀክቶች የተለያዩ ምዕራፎችን አልፈው በቅርቡ ሥራዎቻቸውን ለኢንቨስተሮች የሚያቀርቡ ሲሆን ከተለያዩ ድርጅቶች ጋርም ትስስር የሚፈጠርላቸው ይሆናል።
የስልጠናው ሁለተኛ ዙር ምዝገባ የተጀመረ ሲሆን በዚህ ዙር ሦስት መቶ ሰልጣኞች ይመዘገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በስልጠናው መሳተፍ የምትፈልጉ ዝርዝር መስፈርቶች እና ምዝገባውን https://telegra.ph/TRAINING-ANNOUNCEMENT-04-09 ላይ ያገኙታል።
https://forms.office.com/r/6cXD0LffWe
#STEMpower #VISA #TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ስቴም ፓወር ከቪዛ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የሥራ ፈጠራ ክህሎት እና መሰረታዊ የፋይናንስ ትምህርት ላይ ያተኮረው የመጀመሪያ ዙር ስልጠና 114 ሰልጣኞች ስልጠናቸውን ለሦስት ወር ተከታትለው አጠናቀዋል።
በመጀመሪያው ዙር ስልጠና ከተካፈሉ ሰልጣኞች የሰሯቸው ፕሮጀክቶች የተለያዩ ምዕራፎችን አልፈው በቅርቡ ሥራዎቻቸውን ለኢንቨስተሮች የሚያቀርቡ ሲሆን ከተለያዩ ድርጅቶች ጋርም ትስስር የሚፈጠርላቸው ይሆናል።
የስልጠናው ሁለተኛ ዙር ምዝገባ የተጀመረ ሲሆን በዚህ ዙር ሦስት መቶ ሰልጣኞች ይመዘገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በስልጠናው መሳተፍ የምትፈልጉ ዝርዝር መስፈርቶች እና ምዝገባውን https://telegra.ph/TRAINING-ANNOUNCEMENT-04-09 ላይ ያገኙታል።
https://forms.office.com/r/6cXD0LffWe
#STEMpower #VISA #TikvahEthiopia
@tikvahethiopia