በሃላይደጌ ፓርክ በተከሰተ የእሳት አደጋ እስካሁን ከ100 ኪሎ ሜትር እስኩየር በላይ ሳርና ቁጥቋጦ ወድሟል !
ባለፈው ሀሙስ ቀትር ላይ በፓርኩ ሰሜናዊ ክፍል የተከሰተውን የእሳት አደጋ በአብዛኛው መቆጣጠር እንደተቻለ የፓርኩ አስተባባሪ አቶ መሐመድ እድሪስ ተናግረዋል።
አደጋውን ለመቆጣጠር ባለፉት 3 ቀናት ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።
የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠር ፦
- የአፋር ክልል እሳት አደጋ መከላከያ ቡድን፣
- የክልሉ የልማት ድርጅቶች፣
- የአሚባራና ሃሩካ ወረዳ ነዋሪዎች እና አመራሮች
- የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ከፍተኛ ተሳትፎና ጥረት ማድረጋቸው ተገልጿል።
በአካባቢው ባለ ከፍተኛ ንፋስና ሙቀት ቃጠሎውን ፈጥኖ ለመቆጣጠር አላስቻለም ተብሏል።
እስከ ትናንት ምሽት ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ በነበረባቸው አካባቢዎች እሳቱን ለማጥፋት በተደረገ ጥረት አብዛኛውን ክፍል መቆጣጠር እንደተቻለ ተነግሯል።
ዛሬም በፓርኩ የተለያዩ ቦታዎች ላይ ተበታትነው የሚገኙ አነስተኛ እና ቀላል እሳቶችን የማጥፋት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የተጠቆመ ሲሆን አደጋው በቁጥጥር ስር የሚውልበት ደረጃ ላይ ደርሷል ተብሏል።
ለ3 ቀን በዘለቀው ቃጠሎ ከ100 ኪሎ ሜትር እስኩየር በላይ የሸፈነ ሳርና ቁጥቋጦ ሙሉ በሙሉ ውድሟል።
በቃጠሎው በዱር እንስሳት እንዲሁም በአእዋፎች ላይ ጉዳት መድረሱን ተጠቁሟል።
የእሳት አደጋው መንሰኤ #ሰው_ሰራሽ መሆኑን ተገልጿል።
ዝርዝር የአደጋው መንስኤና የጉዳት መጠን በሚመለከታቸው አካላት ተመርመሮ ይገለፃል ተብሏል። ~ ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባለፈው ሀሙስ ቀትር ላይ በፓርኩ ሰሜናዊ ክፍል የተከሰተውን የእሳት አደጋ በአብዛኛው መቆጣጠር እንደተቻለ የፓርኩ አስተባባሪ አቶ መሐመድ እድሪስ ተናግረዋል።
አደጋውን ለመቆጣጠር ባለፉት 3 ቀናት ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።
የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠር ፦
- የአፋር ክልል እሳት አደጋ መከላከያ ቡድን፣
- የክልሉ የልማት ድርጅቶች፣
- የአሚባራና ሃሩካ ወረዳ ነዋሪዎች እና አመራሮች
- የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ከፍተኛ ተሳትፎና ጥረት ማድረጋቸው ተገልጿል።
በአካባቢው ባለ ከፍተኛ ንፋስና ሙቀት ቃጠሎውን ፈጥኖ ለመቆጣጠር አላስቻለም ተብሏል።
እስከ ትናንት ምሽት ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ በነበረባቸው አካባቢዎች እሳቱን ለማጥፋት በተደረገ ጥረት አብዛኛውን ክፍል መቆጣጠር እንደተቻለ ተነግሯል።
ዛሬም በፓርኩ የተለያዩ ቦታዎች ላይ ተበታትነው የሚገኙ አነስተኛ እና ቀላል እሳቶችን የማጥፋት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የተጠቆመ ሲሆን አደጋው በቁጥጥር ስር የሚውልበት ደረጃ ላይ ደርሷል ተብሏል።
ለ3 ቀን በዘለቀው ቃጠሎ ከ100 ኪሎ ሜትር እስኩየር በላይ የሸፈነ ሳርና ቁጥቋጦ ሙሉ በሙሉ ውድሟል።
በቃጠሎው በዱር እንስሳት እንዲሁም በአእዋፎች ላይ ጉዳት መድረሱን ተጠቁሟል።
የእሳት አደጋው መንሰኤ #ሰው_ሰራሽ መሆኑን ተገልጿል።
ዝርዝር የአደጋው መንስኤና የጉዳት መጠን በሚመለከታቸው አካላት ተመርመሮ ይገለፃል ተብሏል። ~ ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዛሬ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ በቃሉ ወረዳ በ07 ቀበሌ የቃሉ ኢስላሚክ ዩኒቨርሲቲ እና የተውፊቅ ሙስጂድ ግንባታ የማስጀመሪያ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።
የመሰረት ድንጋዩ የተቀመጠው በኡስታዝ አቡበክር አህመድ ሲሆን በስነ ስርዓቱ ላይ ኡስታዞች እና መሻይኾች ተገኝተው ነበር።
Photo : Ustaz Abubeker Ahmed
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የመሰረት ድንጋዩ የተቀመጠው በኡስታዝ አቡበክር አህመድ ሲሆን በስነ ስርዓቱ ላይ ኡስታዞች እና መሻይኾች ተገኝተው ነበር።
Photo : Ustaz Abubeker Ahmed
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
እነ አቶጃዋር መሃመድ ላንድ ማርክ ሆስፒታል ተወሰዱ ! እነ አቶ ጃዋር መሃመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ አቶ ሃምዛ ቦረና ዛሬ ጥዋት ላንድ ማርክ ሆስፒታል መወሰዳቸውን የኦሮሞ የፖለቲካ እስረኞች ጠበቆች ቡድን አሳውቋል። ትላንት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በአቶ ጃዋር ፣ አቶ በቀለ ፣ በአቶ ሀምዛ እና አቶ ደጀኔ የህክምና ጉዳይ ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የሰጠውን…
እነአቶ ጃዋር ዛሬ ከላንድ ማርክ ሆስፒታል ወደ ቃሊቲ ተመልሰዋል።
በላንድ ማርክ ሆስፒታል የህክምና ክትትል ላይ የነበሩት አቶ ጃዋር መሃመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ ሀምዛ ቦረና ዛሬ ከሆስፒታል ወጥተው ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት መመለሳቸውን ከኦሮሞ የፖለቲካ እስረኞች ጠበቆች ቡድን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
እነ አቶ ጃዋር በላንድ ማርክ ሆስፒታል ለ12 ቀናት ክትትል አድረገዋል።
የጤናቸው ሁኔታ በመሻሻሉ ነው ከሆስፒታል የወጡት።
እንደ ጠበቆቻቸው ገለፃ ፖለቲከኞቹ ለ40 ቀናት የምግብ አድማ አድርገው ፥ በኃላም ላንድ ማርክ ሆስፒታል ድረስ በመሄድ ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ እና ሱፐር ኢንቴንደንት ሁሴን ሸቦ ተማፅነዋቸው አድማውን አቁመዋል።
እነ አቶ ጃዋር አድማውን ባቆሙበት ወቅት እነደተገለፀው አድማውን ያቆሙት ጥያቄያቸው ምላሸ አግኝቶ ሳይሆን ፤ "ሃኪሞቻቸው ፣ የአገር ሽማግሌዎች እና ፖለቲከኞች ባደረጉት ልመና እና፣ ጫና በርትቶባቸው እንደሆነ መገለፁ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
በላንድ ማርክ ሆስፒታል የህክምና ክትትል ላይ የነበሩት አቶ ጃዋር መሃመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ ሀምዛ ቦረና ዛሬ ከሆስፒታል ወጥተው ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት መመለሳቸውን ከኦሮሞ የፖለቲካ እስረኞች ጠበቆች ቡድን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
እነ አቶ ጃዋር በላንድ ማርክ ሆስፒታል ለ12 ቀናት ክትትል አድረገዋል።
የጤናቸው ሁኔታ በመሻሻሉ ነው ከሆስፒታል የወጡት።
እንደ ጠበቆቻቸው ገለፃ ፖለቲከኞቹ ለ40 ቀናት የምግብ አድማ አድርገው ፥ በኃላም ላንድ ማርክ ሆስፒታል ድረስ በመሄድ ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ እና ሱፐር ኢንቴንደንት ሁሴን ሸቦ ተማፅነዋቸው አድማውን አቁመዋል።
እነ አቶ ጃዋር አድማውን ባቆሙበት ወቅት እነደተገለፀው አድማውን ያቆሙት ጥያቄያቸው ምላሸ አግኝቶ ሳይሆን ፤ "ሃኪሞቻቸው ፣ የአገር ሽማግሌዎች እና ፖለቲከኞች ባደረጉት ልመና እና፣ ጫና በርትቶባቸው እንደሆነ መገለፁ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
በ5 የሶማሊ ክልል ተወላጅ ወጣቶች ኢንቨስት የተደረገ "ሚና" የተሰኘ የውሃ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ተመረቀ !
ሚና የውሃ ፋብሪካ በ80 ሚሊየን ብር ወጪ በፋፈን ዞን ጉርሱም ወረዳ ደገህሌ ከተማ የተገነባ ሲሆን ዛሬ ተመርቋል።
ፋብሪካው በአምስት የክልሉ ተወላጅ ወጣቶች ኢንቨስት የተደረገ ነው።
በሰአት 12 ሺህ ሊትር ፣ በቀን 288,000 የታሸገ ውሃ የሚያመርት ሲሆን ፤ በ28 ሺህ ካ.ሜ ላይ አርፏል።
በምርቃት ስነ ርዓቱ ላይ ተገኝተው ፋብሪካውን የመረቁት የሶማሊ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሙስጠፌ ፥ በሶማሊ በተፈጠረው አስተማማኝ ሰላምና ለውጥ አማካኝነት በርካታ ኢንቨስተሮች ወደ ክልሉ ለመሳብ መቻሉን ገልፀዋል።
PHOTO : Abdulkadir
@tikvahethiopia
ሚና የውሃ ፋብሪካ በ80 ሚሊየን ብር ወጪ በፋፈን ዞን ጉርሱም ወረዳ ደገህሌ ከተማ የተገነባ ሲሆን ዛሬ ተመርቋል።
ፋብሪካው በአምስት የክልሉ ተወላጅ ወጣቶች ኢንቨስት የተደረገ ነው።
በሰአት 12 ሺህ ሊትር ፣ በቀን 288,000 የታሸገ ውሃ የሚያመርት ሲሆን ፤ በ28 ሺህ ካ.ሜ ላይ አርፏል።
በምርቃት ስነ ርዓቱ ላይ ተገኝተው ፋብሪካውን የመረቁት የሶማሊ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሙስጠፌ ፥ በሶማሊ በተፈጠረው አስተማማኝ ሰላምና ለውጥ አማካኝነት በርካታ ኢንቨስተሮች ወደ ክልሉ ለመሳብ መቻሉን ገልፀዋል።
PHOTO : Abdulkadir
@tikvahethiopia
#Attention😷
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ከተደረገው 5,895 የላብራቶሪ ምርመራ 1,413 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ በተመሳሳይ በ24 ሰዓታት ውስጥ 10 ሰዎች ሞተዋል።
ትላንት 1,669 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 175,467 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 2,550 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 143,710 ሰዎች አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት 467 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose #Tikvah
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ከተደረገው 5,895 የላብራቶሪ ምርመራ 1,413 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ በተመሳሳይ በ24 ሰዓታት ውስጥ 10 ሰዎች ሞተዋል።
ትላንት 1,669 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 175,467 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 2,550 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 143,710 ሰዎች አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት 467 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose #Tikvah
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ለኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፦
ለኣክሱም ዪኒቨርስቲ ኤክስቴንሽን /ኢ- መደበኛ/ እንዲሁም መደበኛ የሁለተኛ ድግሪ (ማስተርስ) ተማሪዎች ት/ት የሚጀሙሩበት ቀን ጥሪ አቀረበ።
- ለነባር ወይም ስንየር የኤክስተንሽን(ኢ-መደበኛ) ድግሪ ተማሪዎች ከመጋቢት 11/2013ዓ/ም ጀምሮ እንዲገቡ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፤
- ከመጋቢት 15 -16/2013ዓ/ም ባለው ጊዜ ለሁሉም #መደበኛ# የሁለተኛ ዲግሪ(ማስተርስ) ተማሪዎች የአንደኛ ሴሚስተር ኖርማል ምዝገባ ይካሄዳል።
- ለሁሉም የኤክስተንሽን (ኢ-መደበኛ) ማስተርስ ተማሪዎች ከመጋቢት 18-19/2013ዓ/ም ባለው ጊዜ የአንደኛ ሴሚስተር ኖርማል ምዝገባ ያደርጋሉ።
(ጌታቸው ካሕሱ /የአክሱም ዩኒቨርስቲ አዲስ አበባ ጉዳይ ማስፈፀሚያ ጽ/ቤት ሃላፊ)
@tikvahethiopia
ለኣክሱም ዪኒቨርስቲ ኤክስቴንሽን /ኢ- መደበኛ/ እንዲሁም መደበኛ የሁለተኛ ድግሪ (ማስተርስ) ተማሪዎች ት/ት የሚጀሙሩበት ቀን ጥሪ አቀረበ።
- ለነባር ወይም ስንየር የኤክስተንሽን(ኢ-መደበኛ) ድግሪ ተማሪዎች ከመጋቢት 11/2013ዓ/ም ጀምሮ እንዲገቡ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፤
- ከመጋቢት 15 -16/2013ዓ/ም ባለው ጊዜ ለሁሉም #መደበኛ# የሁለተኛ ዲግሪ(ማስተርስ) ተማሪዎች የአንደኛ ሴሚስተር ኖርማል ምዝገባ ይካሄዳል።
- ለሁሉም የኤክስተንሽን (ኢ-መደበኛ) ማስተርስ ተማሪዎች ከመጋቢት 18-19/2013ዓ/ም ባለው ጊዜ የአንደኛ ሴሚስተር ኖርማል ምዝገባ ያደርጋሉ።
(ጌታቸው ካሕሱ /የአክሱም ዩኒቨርስቲ አዲስ አበባ ጉዳይ ማስፈፀሚያ ጽ/ቤት ሃላፊ)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Attention😷 በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ከተደረገው 5,895 የላብራቶሪ ምርመራ 1,413 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ በተመሳሳይ በ24 ሰዓታት ውስጥ 10 ሰዎች ሞተዋል። ትላንት 1,669 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል። በአጠቃላይ 175,467 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 2,550 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 143,710 ሰዎች አገግመዋል። በአሁን ሰዓት…
የዛሬ መጋቢት 5 ሁኔታ ፦
24% national positivity rate.The higest so far!
በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአራት ሰው አንድ ሰው በኮቪድ ተይዞዋል ወይም ኮቪድ ሊኖርበት ይችላል እንደማለት ነው።
ከ20% በላይ የበሽታው ስርጭት የሚታይባቸው ክልሎች/ከተማ አስተዳደሮች ፦
1. ሲዳማ-39%
2. ኦሮሚያ-38%
3. ድሬዳዋ-25%
4. ሐረር-25%
5. አዲስ አበባ-24%
እነዚህ ቁጥሮች ምን ማለት እንደሆኑ አለመገንዘብ በእራስ እና በሀገር ላይ ሞት እንደማወጅ ይቆጠራል።
ያዕቆብ ሰማን
የሕክምና አገልግሎት ዳይሬክተር
ጤና ሚኒስቴር
#SPHMMC
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
24% national positivity rate.The higest so far!
በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአራት ሰው አንድ ሰው በኮቪድ ተይዞዋል ወይም ኮቪድ ሊኖርበት ይችላል እንደማለት ነው።
ከ20% በላይ የበሽታው ስርጭት የሚታይባቸው ክልሎች/ከተማ አስተዳደሮች ፦
1. ሲዳማ-39%
2. ኦሮሚያ-38%
3. ድሬዳዋ-25%
4. ሐረር-25%
5. አዲስ አበባ-24%
እነዚህ ቁጥሮች ምን ማለት እንደሆኑ አለመገንዘብ በእራስ እና በሀገር ላይ ሞት እንደማወጅ ይቆጠራል።
ያዕቆብ ሰማን
የሕክምና አገልግሎት ዳይሬክተር
ጤና ሚኒስቴር
#SPHMMC
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
65 ሺህ ብር ወድቆ ያገኘው ወጣት በታማኝነት ለባለቤቱ መለሰ።
በምዕራብ ጎንደር ዞን በቋራ ወረዳ የአይሰጋ ቀበሌ ነዋሪና የጎሚስታ ስራ የሚሰራው ወጣት #ያዩ_ሁነኛው መህሩም ተራራ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ 65 ሺህ ጥሬ ብር ያገኘ ቢሆንም ገንዘቡ ለጠፋበት ለአቶ ሰለሞን ጫቅሌ ምንም ሳይቀንስ 65 ሺህ ብሩን በታማኝነት እንደመለሰለት የቋራ ኮሚኒኬሽን መረጃ ያሳያል።
አቶ ሰለሞን ፥ ገንዘቡን ላገኘለት ወጣት 10 ሺህ ብር ቢሰጠውም ወጣቱ ገንዘቡ አልቀበልም በሚል ሙሉ ታማኝነቱ እና ደግ ስራውን ከፈጣሪው ማግኘት በመፈለጉ ሊቀበለው አለመቻሉን ገልጿል።
ወጣቱ ሰርተን ከምናገኘው ገንዘብ ውጭ የሰው ገንዘብ መጥቶ ሊጠቅመን ይልቅና የራሳችንንም ይዞብን ስለሚጠፋ ሁላችንም የሰው ገንዘብ የሰው ከመሆኑ በዘለለ ለኛ ስለማይጠቅም ሁላችንም ፈጣሪ ሰርተን የምናገኘውን በረከት ያደርግልን ዘንድ ጎን መዋል ይኖርብናል ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
ከሳምንታት በፊት #ጉሌድ_ኢብራሂም_ኡመር የተባለ በጅጅጋ ከተማ በባጃጅ ሹፍርና የተሰማራ ወጣት የትራንስፖርት አገልግሎት የሰጣቸው እናት 300,000 ብር (ሶስት መቶ ሺህ ብር) በባጃጁ ላይ ረስተው ቢወርዱም የብሩ ባለቤት የሆኑትን እናት በመፈለግ የተቀመጡበት ቦታ ድረስ ሄዶ መልሶላቸው ነበር፤ በማህበራዊ ሚዲያም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ለወጣት ጉሌድ ኢብራሂም ኡመር ምስጋና ሲያቀርቡ ነበር።
ለዚህ ተግባሩ የሶማሊ ክልል ፕሬዜደንት አቶ ሙስጠፌ መሀመድም ምስጋና አቅርበውለት እንደነበር አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
በምዕራብ ጎንደር ዞን በቋራ ወረዳ የአይሰጋ ቀበሌ ነዋሪና የጎሚስታ ስራ የሚሰራው ወጣት #ያዩ_ሁነኛው መህሩም ተራራ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ 65 ሺህ ጥሬ ብር ያገኘ ቢሆንም ገንዘቡ ለጠፋበት ለአቶ ሰለሞን ጫቅሌ ምንም ሳይቀንስ 65 ሺህ ብሩን በታማኝነት እንደመለሰለት የቋራ ኮሚኒኬሽን መረጃ ያሳያል።
አቶ ሰለሞን ፥ ገንዘቡን ላገኘለት ወጣት 10 ሺህ ብር ቢሰጠውም ወጣቱ ገንዘቡ አልቀበልም በሚል ሙሉ ታማኝነቱ እና ደግ ስራውን ከፈጣሪው ማግኘት በመፈለጉ ሊቀበለው አለመቻሉን ገልጿል።
ወጣቱ ሰርተን ከምናገኘው ገንዘብ ውጭ የሰው ገንዘብ መጥቶ ሊጠቅመን ይልቅና የራሳችንንም ይዞብን ስለሚጠፋ ሁላችንም የሰው ገንዘብ የሰው ከመሆኑ በዘለለ ለኛ ስለማይጠቅም ሁላችንም ፈጣሪ ሰርተን የምናገኘውን በረከት ያደርግልን ዘንድ ጎን መዋል ይኖርብናል ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
ከሳምንታት በፊት #ጉሌድ_ኢብራሂም_ኡመር የተባለ በጅጅጋ ከተማ በባጃጅ ሹፍርና የተሰማራ ወጣት የትራንስፖርት አገልግሎት የሰጣቸው እናት 300,000 ብር (ሶስት መቶ ሺህ ብር) በባጃጁ ላይ ረስተው ቢወርዱም የብሩ ባለቤት የሆኑትን እናት በመፈለግ የተቀመጡበት ቦታ ድረስ ሄዶ መልሶላቸው ነበር፤ በማህበራዊ ሚዲያም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ለወጣት ጉሌድ ኢብራሂም ኡመር ምስጋና ሲያቀርቡ ነበር።
ለዚህ ተግባሩ የሶማሊ ክልል ፕሬዜደንት አቶ ሙስጠፌ መሀመድም ምስጋና አቅርበውለት እንደነበር አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
ሃሳብን ለመግለፅ መሳድብን ምን አመጣው ?
ባለፉት 2 ቀናት የቲክቫህ አስተያየት መስጫ እንዲከፈት ተደርጎ ብዙ ታዝበናል ፤ ይህ የሀገራችንን የማህበራዊ ሚዲያው ሁኔታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ሆኖ አግኝተነዋል።
ስድብ፣ ጥላቻ፣ሰዎችን ለማሸማቀቅ አንገት ለማስደፋት መሞከር፣ያለማስረጃ፣ ያለምንጭ መናገር ተላምደነው አብረን መኖር ከጀመርን ሰነባብተናል።
ብዙ ሺዎች ሃሳባቸውን በአግባቡ የሚገልፁ ቢኖሩም የጥቂቶች ስድብ፣ጥላቻ ብዙዎችን ይመርዛል።
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሆነ በማንኛውም ቦታ ሃሳብን ለመግለፅ መሳደብ /ሰዎች ማሸማቀቀ፣ አንገት ማስደፋት አይጠበቅብንም። በጨዋ ቋንቋ ማስረዳት ከቻልን እሰየው ፣ የማንግባባት ከሆነ ደግሞ ሌላ ጊዜ ከስሜታዊነት ነፃ ስንሆን መነጋገሩ መልካም ነውም
ከኛ ተቃራኒ ሃሳብ ሲገጥመን ፥ ለምን በትህትና ማስረዳት አቃተን ? ወንድሜ ፣ እህቴ ይህ እንዲህ ነው፤ ሃሳብን /ሃሳብሽን አልደግፈውም በዚህ ምክንያት ... ፤ እስቲ እንዲገባኝ አስረዳኝ/አስረጂኝ ... እያልንም ማውራቱ እንዴት ከበደን ?
ጥላቻ፣ ተቃራኒ ሃሳብ ለማስተናገድ አለመፈለግ፣ በቡድን ማሰብ/መፍረድ ፣ ጅምላ ፍረጃ፣ ሰዎችን ማሸማቀቅ ፣ ተጎዳን የሚለው ላይ መሳለቅ ውሎ አድሮ ሀገርን አደጋ ላይ መጣሉ አይቀርም።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት የጥላቻ ንግግርን በመቃወም ከክልል ክልል የዞርነው ውጤቱን ስላወቅን ነው።
ቲክቫህ መደበኛ ሚዲያ አይደለም ፤ እርስ በእርስ መረጃ ለመቀያየር ፣ ስለሀገር ጉዳይ የምንመክርበት፣ ለተቸገሩት የምንደርስበት ፕላት ፎርም ነው።
ጋዜጠኛው፣ሃኪሙ፣ነጋዴው፣ባለሃብቱ፣ ተቃዋሚው፣ ባለስልጣኑ ፣ ተማሪው፣ አስተማሪው የቲክቫህ አባል ነው።
ቲክቫህ ውስጥ ስድብ ፈፅሞ አይፈቀድም ፤ ተሳዳቢዎችን የመምከር ከፍ ሲል ከአባልነት የመቀነስ ስራ እንሰራለን።
@tikvahethiopia
ባለፉት 2 ቀናት የቲክቫህ አስተያየት መስጫ እንዲከፈት ተደርጎ ብዙ ታዝበናል ፤ ይህ የሀገራችንን የማህበራዊ ሚዲያው ሁኔታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ሆኖ አግኝተነዋል።
ስድብ፣ ጥላቻ፣ሰዎችን ለማሸማቀቅ አንገት ለማስደፋት መሞከር፣ያለማስረጃ፣ ያለምንጭ መናገር ተላምደነው አብረን መኖር ከጀመርን ሰነባብተናል።
ብዙ ሺዎች ሃሳባቸውን በአግባቡ የሚገልፁ ቢኖሩም የጥቂቶች ስድብ፣ጥላቻ ብዙዎችን ይመርዛል።
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሆነ በማንኛውም ቦታ ሃሳብን ለመግለፅ መሳደብ /ሰዎች ማሸማቀቀ፣ አንገት ማስደፋት አይጠበቅብንም። በጨዋ ቋንቋ ማስረዳት ከቻልን እሰየው ፣ የማንግባባት ከሆነ ደግሞ ሌላ ጊዜ ከስሜታዊነት ነፃ ስንሆን መነጋገሩ መልካም ነውም
ከኛ ተቃራኒ ሃሳብ ሲገጥመን ፥ ለምን በትህትና ማስረዳት አቃተን ? ወንድሜ ፣ እህቴ ይህ እንዲህ ነው፤ ሃሳብን /ሃሳብሽን አልደግፈውም በዚህ ምክንያት ... ፤ እስቲ እንዲገባኝ አስረዳኝ/አስረጂኝ ... እያልንም ማውራቱ እንዴት ከበደን ?
ጥላቻ፣ ተቃራኒ ሃሳብ ለማስተናገድ አለመፈለግ፣ በቡድን ማሰብ/መፍረድ ፣ ጅምላ ፍረጃ፣ ሰዎችን ማሸማቀቅ ፣ ተጎዳን የሚለው ላይ መሳለቅ ውሎ አድሮ ሀገርን አደጋ ላይ መጣሉ አይቀርም።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት የጥላቻ ንግግርን በመቃወም ከክልል ክልል የዞርነው ውጤቱን ስላወቅን ነው።
ቲክቫህ መደበኛ ሚዲያ አይደለም ፤ እርስ በእርስ መረጃ ለመቀያየር ፣ ስለሀገር ጉዳይ የምንመክርበት፣ ለተቸገሩት የምንደርስበት ፕላት ፎርም ነው።
ጋዜጠኛው፣ሃኪሙ፣ነጋዴው፣ባለሃብቱ፣ ተቃዋሚው፣ ባለስልጣኑ ፣ ተማሪው፣ አስተማሪው የቲክቫህ አባል ነው።
ቲክቫህ ውስጥ ስድብ ፈፅሞ አይፈቀድም ፤ ተሳዳቢዎችን የመምከር ከፍ ሲል ከአባልነት የመቀነስ ስራ እንሰራለን።
@tikvahethiopia
#Gambella
ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ በሰው እና በቤቶች ላይ ጉዳት ደረሰ።
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ ፑኩሙ ቀበሌ ንፋስ ቀለቀቅሎ በጣለ ዝናብ በርካታ ቤቶችና ሰው ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለፀ፡፡
የፑኩሙ ቀበሌ ሊቀመንበር አቶ ጆን ኡጁዋቶ እንዳሉት በቀን 04/2013 ዓ.ም ከምሽቱ 5 አካባቢ ንፋስ ቀላቀሎ በጣለው ዝናብ በቀበሌው ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል ብለዋል፡፡
በደረሰው ጉዳትም 55 የቆርቆሮና 20 የሳር ቤቶች በድምሩ 75 መኖሪያ ቤቶች እንዲሁም ትምህርት ቤትን ጨምሮ አራት የመንግስት ተቋማት ላይ ጉዳት መድረሱን ጠቁመው በ3 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል አደጋ መድረሱን አመልክተዋል፡፡
በመሆኑም በደረሰው አደጋ መልሰው ለመቋቋም የወገንና የመንግስት ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል፡፡
የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጋትቤል ሙን ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች መልሶ ለማቋቋም ኤጀንሲው ከሚመለከታቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በጋራ ይሰራል ብለዋል፡፡
በአደጋው የደረሰ ተጨማሪ ጉዳት እንዳለ ለማጣራት እና እርዳታ ለማሰባሰብ ከተለያየ አካላት የተውጣጣ ቡድን ወደ ስፍራው እንደሚላክ አስረድተዋል፡፡
ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች የፕሬዜዳንት አቶ ኡሞድ ኡጁሉን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች ቦታው ላይ በመገኘት ምልከታ ማድረጋቸውን የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ በሰው እና በቤቶች ላይ ጉዳት ደረሰ።
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ ፑኩሙ ቀበሌ ንፋስ ቀለቀቅሎ በጣለ ዝናብ በርካታ ቤቶችና ሰው ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለፀ፡፡
የፑኩሙ ቀበሌ ሊቀመንበር አቶ ጆን ኡጁዋቶ እንዳሉት በቀን 04/2013 ዓ.ም ከምሽቱ 5 አካባቢ ንፋስ ቀላቀሎ በጣለው ዝናብ በቀበሌው ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል ብለዋል፡፡
በደረሰው ጉዳትም 55 የቆርቆሮና 20 የሳር ቤቶች በድምሩ 75 መኖሪያ ቤቶች እንዲሁም ትምህርት ቤትን ጨምሮ አራት የመንግስት ተቋማት ላይ ጉዳት መድረሱን ጠቁመው በ3 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል አደጋ መድረሱን አመልክተዋል፡፡
በመሆኑም በደረሰው አደጋ መልሰው ለመቋቋም የወገንና የመንግስት ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል፡፡
የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጋትቤል ሙን ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች መልሶ ለማቋቋም ኤጀንሲው ከሚመለከታቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በጋራ ይሰራል ብለዋል፡፡
በአደጋው የደረሰ ተጨማሪ ጉዳት እንዳለ ለማጣራት እና እርዳታ ለማሰባሰብ ከተለያየ አካላት የተውጣጣ ቡድን ወደ ስፍራው እንደሚላክ አስረድተዋል፡፡
ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች የፕሬዜዳንት አቶ ኡሞድ ኡጁሉን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች ቦታው ላይ በመገኘት ምልከታ ማድረጋቸውን የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#አሪፍፔይ
አሪፍ ፔይ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ አክሲዮን ማህበር ለመመስረት የሚያስችለውን የመጀመሪያ ምስረታ ጉባኤ አካሂዷል።
አሪፍ ፔይ 31 የአክሲዮን አባላት ያሉት ሲሆን እያንዳንዳቸው ባለአንድ ሺህ ብር የሆኑ 140 ሺህ አክሲዎኖች አሉት።
አክሲዮኑ በገንዘብ እና በአይነት 140 ሚሊዮን ብር ካፒታል እንዳለው ተገልጿል።
አሪፍ ፔይ ስራው ምንድነው ?
አርፊ ፔይ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ አርፍ ፔይ ATM /ኤቲ ኤም/ ካርድን በመጠቀም ክፍያን ለመፈፀም የውሃ፣ መብራት፣ ስልክ፣ ሬስቶራንት ውስጥ ክፍያ ለመፈፀም እና ሌሎች ክፍያዎችን ለመፈፀም ኤቲኤም ካርዶችን ለማንበብ የውጭ ሀገር ካርዶችን ተቀብሎ ክፍያ መፈፀም እና ሌሎች አገልግሎቶችን ይሰጣል ሲሉ አስረድተዋል።
የጥሬ ገንዘብ ግብይትን ወደ ኤሌክትሮኒስ የመቀየር ስራን በስፋት ሰራለሁ የሚለው አሪፍ ፔይ በአንድ ወር ውስጥ ወደ ስራ ለመግባት አቅዶ እየሰራ መሆኑን አሳውቋል።
ምንጭ፦ አሪፍ ፔይ ፣ ኢቢኤስ
@tikvahethiopia
አሪፍ ፔይ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ አክሲዮን ማህበር ለመመስረት የሚያስችለውን የመጀመሪያ ምስረታ ጉባኤ አካሂዷል።
አሪፍ ፔይ 31 የአክሲዮን አባላት ያሉት ሲሆን እያንዳንዳቸው ባለአንድ ሺህ ብር የሆኑ 140 ሺህ አክሲዎኖች አሉት።
አክሲዮኑ በገንዘብ እና በአይነት 140 ሚሊዮን ብር ካፒታል እንዳለው ተገልጿል።
አሪፍ ፔይ ስራው ምንድነው ?
አርፊ ፔይ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ አርፍ ፔይ ATM /ኤቲ ኤም/ ካርድን በመጠቀም ክፍያን ለመፈፀም የውሃ፣ መብራት፣ ስልክ፣ ሬስቶራንት ውስጥ ክፍያ ለመፈፀም እና ሌሎች ክፍያዎችን ለመፈፀም ኤቲኤም ካርዶችን ለማንበብ የውጭ ሀገር ካርዶችን ተቀብሎ ክፍያ መፈፀም እና ሌሎች አገልግሎቶችን ይሰጣል ሲሉ አስረድተዋል።
የጥሬ ገንዘብ ግብይትን ወደ ኤሌክትሮኒስ የመቀየር ስራን በስፋት ሰራለሁ የሚለው አሪፍ ፔይ በአንድ ወር ውስጥ ወደ ስራ ለመግባት አቅዶ እየሰራ መሆኑን አሳውቋል።
ምንጭ፦ አሪፍ ፔይ ፣ ኢቢኤስ
@tikvahethiopia
ከአንድ አመት በላይ ያለምንም ስራ የተቀመጡት ሃኪሞች ፦
በአማራ ክልል 450 በላይ (ቁጥሩ ከዚህም ከፍ ሊል ይችላል) የህክምና ትምህርታቸውን ተከታትለው ያለስራ የተቀመጡ ሃኪሞች/ዶክተሮች/ ለከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና እየተዳረጉ ይገኛሉ።
ወደስራ መሰማራት ሳይችሉ ከቀሩ ሃኪሞች መካከል የቲክቫህ አባላት የሆኑም ይገኙበታል።
ሃኪሞቹ ከአንድ አመት በላይ ለሚሆን ጊዜ ያለስራ የተቀመጡ ሲሆን ለሚመለከታቸውን የመንግስት አካላት አቤት ቢሉም የተሰጣቸው መልስ "በጀት የለንም" የሚል እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌሎች ክልሎች እንዳይሰሩም የቋንቋ ጉዳይ ፈተና እንደሆነባቸው ገልፀዋል።
የሃኪሞቹ ጥያቄ ዛሬም ድረስ ባይቋረጥም መፍትሄ አልተገኘም ፤ በዚህም ለከፍተኛ የስነልቦና ጫና ተዳርገዋል።
ከነሱ አልፎም ቤተሰቦቻቸውን ለስነ ልቦና ጫና ዳርጓል።
በሀገራችን የህክምና ትምህርት የሚከታተሉ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ፣ ከታች ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ ለቀለም ትምህርት ብቻ ቦታ እየሰጡ የመጡ፤ ዩኒቨርሲቲ ከተገባ በኃላም ከባድ 7 ዓመታትን አልፈው ነው የሚመረቁት።
ሃኪሞቹ ለበርካታት አመታት ያህል በስንት ጥረት እና ትግል እዚህ ደርሰው ከፍተኛ የሃኪም እጠረት ባለበት ሀገር ስራ ላይ መሰማራት አለመቻላቸው እንደሚያሳዝናቸው ገልፀዋል።
የቲክቫህ አባላት እንዳሉት ከነሱ ብዙ ነገር ቤተሰቦቻቸው ቢጠብቁም እንኳን ለቤተሰቦቻቸው ሊሆኑ እራሳቸውን ችለው ከቤት መውጣት አልቻሉም።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በአማራ ክልል 450 በላይ (ቁጥሩ ከዚህም ከፍ ሊል ይችላል) የህክምና ትምህርታቸውን ተከታትለው ያለስራ የተቀመጡ ሃኪሞች/ዶክተሮች/ ለከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና እየተዳረጉ ይገኛሉ።
ወደስራ መሰማራት ሳይችሉ ከቀሩ ሃኪሞች መካከል የቲክቫህ አባላት የሆኑም ይገኙበታል።
ሃኪሞቹ ከአንድ አመት በላይ ለሚሆን ጊዜ ያለስራ የተቀመጡ ሲሆን ለሚመለከታቸውን የመንግስት አካላት አቤት ቢሉም የተሰጣቸው መልስ "በጀት የለንም" የሚል እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌሎች ክልሎች እንዳይሰሩም የቋንቋ ጉዳይ ፈተና እንደሆነባቸው ገልፀዋል።
የሃኪሞቹ ጥያቄ ዛሬም ድረስ ባይቋረጥም መፍትሄ አልተገኘም ፤ በዚህም ለከፍተኛ የስነልቦና ጫና ተዳርገዋል።
ከነሱ አልፎም ቤተሰቦቻቸውን ለስነ ልቦና ጫና ዳርጓል።
በሀገራችን የህክምና ትምህርት የሚከታተሉ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ፣ ከታች ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ ለቀለም ትምህርት ብቻ ቦታ እየሰጡ የመጡ፤ ዩኒቨርሲቲ ከተገባ በኃላም ከባድ 7 ዓመታትን አልፈው ነው የሚመረቁት።
ሃኪሞቹ ለበርካታት አመታት ያህል በስንት ጥረት እና ትግል እዚህ ደርሰው ከፍተኛ የሃኪም እጠረት ባለበት ሀገር ስራ ላይ መሰማራት አለመቻላቸው እንደሚያሳዝናቸው ገልፀዋል።
የቲክቫህ አባላት እንዳሉት ከነሱ ብዙ ነገር ቤተሰቦቻቸው ቢጠብቁም እንኳን ለቤተሰቦቻቸው ሊሆኑ እራሳቸውን ችለው ከቤት መውጣት አልቻሉም።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ዶ/ር ገነነ ተፈራ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
የኢትዮጵያ ባዮዳይቨርሲቲ ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ገነነ ተፈራ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።
ኢንስቲትዩቱ በዶ/ር ገነነ ህልፈት የተሰማውን ሃዘን ገልጿል።
የዶ/ር ገነነ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ ኮተቤ ቅድስት ኪደነምህረት ቤተክርስቲያን በ8:00 እንደሚፈፀም ተገልጿል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የኢትዮጵያ ባዮዳይቨርሲቲ ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ገነነ ተፈራ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።
ኢንስቲትዩቱ በዶ/ር ገነነ ህልፈት የተሰማውን ሃዘን ገልጿል።
የዶ/ር ገነነ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ ኮተቤ ቅድስት ኪደነምህረት ቤተክርስቲያን በ8:00 እንደሚፈፀም ተገልጿል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT