የሸገር ፓርክ ምረቃ ስነ ስርዓት እየተካሄደ ነው!
የሸገር ፓርክ የምረቃ ስነ ስርዓት በዛሬው እለት እየተካሄደ ነው።
በፓርኩ ምረቃ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች እንዲሁም የህብረተሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል።
የሸገር ፓርክ ምረቃ ስነ ስርዓት ላይ ለፓርኩ መገንባት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለቻይና መንግስት እና ለሌሎች አካላት እውቅና ተሰጥቷል።
በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በስራ ሂደቱ ላይ ለተሳተፉ አካላት የምስጋና ስጦታ ማበርከታቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
PHOTO : Reporter /FBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሸገር ፓርክ የምረቃ ስነ ስርዓት በዛሬው እለት እየተካሄደ ነው።
በፓርኩ ምረቃ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች እንዲሁም የህብረተሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል።
የሸገር ፓርክ ምረቃ ስነ ስርዓት ላይ ለፓርኩ መገንባት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለቻይና መንግስት እና ለሌሎች አካላት እውቅና ተሰጥቷል።
በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በስራ ሂደቱ ላይ ለተሳተፉ አካላት የምስጋና ስጦታ ማበርከታቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
PHOTO : Reporter /FBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እንቁጣጣሽ ሎተሪ ዛሬ ይወጣል!
በ1ኛ ዕጣ 20 ሚሊዮን ብር ፣ በ2ኛ ዕጣ 10 ሚሊዮን ብር ፣ በ3ኛ ዕጣ 5 ሚሊዮን እንዲሁም ሌሎች በርካታ ዕጣዎችን የሚያሸልመው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ዛሬ ጳጉሜ 05/2012 ዓ/ም ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በአስተዳደሩ የእጣ ማውጫ አዳራሽ (ዕድል አዳራሽ) በቀጥታ ስርጭት በኢትቪ 1 (etv) ይተላለፋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በ1ኛ ዕጣ 20 ሚሊዮን ብር ፣ በ2ኛ ዕጣ 10 ሚሊዮን ብር ፣ በ3ኛ ዕጣ 5 ሚሊዮን እንዲሁም ሌሎች በርካታ ዕጣዎችን የሚያሸልመው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ዛሬ ጳጉሜ 05/2012 ዓ/ም ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በአስተዳደሩ የእጣ ማውጫ አዳራሽ (ዕድል አዳራሽ) በቀጥታ ስርጭት በኢትቪ 1 (etv) ይተላለፋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአዲስ አበባ በአስሩ ክፍለ ከተማ በጥናት በተደረገ ፍተሻ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ለኤፍ ቢ ሲ አስታውቋል።
በተደረገው ፍተሻ አንድ (1) ቦምብ እና አራት (4) ሽጉጦች በቁጥጥር ስር መዋሉ ነው የተገለፀው። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘም የተጠረጠሩ 180 ግለሰቦች ተይዘው ፖሊስ ምርመራ እያደረገ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ህብረተሰቡ የራሱን ሰላም በመጠበቅ ፣ ሰላምን ሊያውኩ የሚችሉ ወንጀለኞችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በተደረገው ፍተሻ አንድ (1) ቦምብ እና አራት (4) ሽጉጦች በቁጥጥር ስር መዋሉ ነው የተገለፀው። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘም የተጠረጠሩ 180 ግለሰቦች ተይዘው ፖሊስ ምርመራ እያደረገ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ህብረተሰቡ የራሱን ሰላም በመጠበቅ ፣ ሰላምን ሊያውኩ የሚችሉ ወንጀለኞችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ለፀጥታ ሲባል ማንኛውም ግለሰብ ርችት መተኮስ እንደማይችል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሳስቧል።
ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ርችት መተኮስን ምክንያት በማድረግ 'የሽብር ጥቃት' ለማድረስ እየተዘጋጁ ያሉ ግለሰቦች መኖራቸውን ፖሊስ በጥናት ስለደረሰበት እንደሆነ የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት የሚዲያ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ለኤፍ ቢ ሲ ገልጸዋል።
ስለሆነም ወንጀልን ለመከላከል ሲባል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ማንኛውም ግለሰብ ሪችት መተኮስ አይችልም ብለዋል።
ይህንን ተላልፎ ሪችት የሚተኩስ ማንኛውም ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደሚውል ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ተናግረዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ርችት መተኮስን ምክንያት በማድረግ 'የሽብር ጥቃት' ለማድረስ እየተዘጋጁ ያሉ ግለሰቦች መኖራቸውን ፖሊስ በጥናት ስለደረሰበት እንደሆነ የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት የሚዲያ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ለኤፍ ቢ ሲ ገልጸዋል።
ስለሆነም ወንጀልን ለመከላከል ሲባል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ማንኛውም ግለሰብ ሪችት መተኮስ አይችልም ብለዋል።
ይህንን ተላልፎ ሪችት የሚተኩስ ማንኛውም ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደሚውል ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ተናግረዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
animation.gif
324.9 KB
ብርሃን ባንክ የትምርት ቤቶችን ክፍያ በዲጂታል ሥርዓት ማስተናገድ ጀመረ!
የክፍያ መንገዶች በማዘመን ሒደት ትምህርት ቤቶችን በዲጂታል የክፍያ አገልግሎት ተካታች የሚያደርግ ሥርዓት መዘርጋቱን ብርሃን ባንክ አስታውቋል።
ትምህርት ሚኒስቴርም በሥርዓቱ አብሮ መሥራት ጀምሯል፡፡
ብርሃን ባንክ ሰኞ ጳጉሜን 2 ቀን 2012 ዓ.ም. በይፋ ያስጀመረው የትምህርት ቤቶች የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ‹‹ብርሃን ስኩል ፔይ›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
ወላጆች በሚያመቻቸው የክፍያ አማራጭ የልጆቻቸውን የትምህርት ቤት ክፍያዎችን ካሉበት ሆነው እንዲፈጽሙ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡
ከስማርት ስልኮች በተጓዳኝ በማንኛውም ዓይነት የሞባይል ስልክ አገልግሎት የሚሰጥበት ይህ አሠራር ፣ የትምህርት ቤት ክፍያዎች ከሞባይል በተጨማሪ በኢንተርኔት መፈጸም ያስችላል፡፡
ባንኩ ከትምህርት ቤቶች ጋር ውል በመግባት እያንዳንዱ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ተማሪ የራሱ ሚስጥራዊ መለያ ቁጥር ተሰጥቶት በዚሁ መለያ ቁጥር ወይም ኮድ አማካይነት ክፍያ የሚፈጽምበት ዘመናዊ የክፍያ ዘዴ ለወላጆች እና ተማሪዎች ማቅረቡን ባንኩ ማስታወቁን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የክፍያ መንገዶች በማዘመን ሒደት ትምህርት ቤቶችን በዲጂታል የክፍያ አገልግሎት ተካታች የሚያደርግ ሥርዓት መዘርጋቱን ብርሃን ባንክ አስታውቋል።
ትምህርት ሚኒስቴርም በሥርዓቱ አብሮ መሥራት ጀምሯል፡፡
ብርሃን ባንክ ሰኞ ጳጉሜን 2 ቀን 2012 ዓ.ም. በይፋ ያስጀመረው የትምህርት ቤቶች የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ‹‹ብርሃን ስኩል ፔይ›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
ወላጆች በሚያመቻቸው የክፍያ አማራጭ የልጆቻቸውን የትምህርት ቤት ክፍያዎችን ካሉበት ሆነው እንዲፈጽሙ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡
ከስማርት ስልኮች በተጓዳኝ በማንኛውም ዓይነት የሞባይል ስልክ አገልግሎት የሚሰጥበት ይህ አሠራር ፣ የትምህርት ቤት ክፍያዎች ከሞባይል በተጨማሪ በኢንተርኔት መፈጸም ያስችላል፡፡
ባንኩ ከትምህርት ቤቶች ጋር ውል በመግባት እያንዳንዱ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ተማሪ የራሱ ሚስጥራዊ መለያ ቁጥር ተሰጥቶት በዚሁ መለያ ቁጥር ወይም ኮድ አማካይነት ክፍያ የሚፈጽምበት ዘመናዊ የክፍያ ዘዴ ለወላጆች እና ተማሪዎች ማቅረቡን ባንኩ ማስታወቁን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ችሎት!
አቶ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በ7 ተከሳሾች ላይ አቃቤ ህግ ክስ መሰረተ።
ክሱ በ2 የተከፈለ ሲሆን፥ ከአቶ እስክንድር ነጋ እስከ 3ኛ ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ በሽብር ወንጀል ነው ክስ የተመሰረተው።
ቀሪዎቹ ከ4ኛ እስከ 7ኛ ተከሳሾች ላይ ደግሞ የእርስ በእርስ ግጭት በመፍጠር ወንጀል ነው ክስ የተመሰረተው።
ክሱ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው የተመሰረተው። በአሁኑ ወቅት ችሎቱ ጉዳያቸውን እየተመለከተ ነው።
Via Tarik Adugna (FBC)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አቶ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በ7 ተከሳሾች ላይ አቃቤ ህግ ክስ መሰረተ።
ክሱ በ2 የተከፈለ ሲሆን፥ ከአቶ እስክንድር ነጋ እስከ 3ኛ ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ በሽብር ወንጀል ነው ክስ የተመሰረተው።
ቀሪዎቹ ከ4ኛ እስከ 7ኛ ተከሳሾች ላይ ደግሞ የእርስ በእርስ ግጭት በመፍጠር ወንጀል ነው ክስ የተመሰረተው።
ክሱ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው የተመሰረተው። በአሁኑ ወቅት ችሎቱ ጉዳያቸውን እየተመለከተ ነው።
Via Tarik Adugna (FBC)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
በትግራይ ምርጫ ለሊቱ ድምፅ ሲቆጠር አድሮ ጠዋት በየምርጫ ጣብያው ውጤት ተለጥፏል።
ትላንት ጳጉሜ 4 በትግራይ የተካሄደው 6ኛው ክልላዊ ምርጫ ውጤት ፣ ድምፅ በተሰጠባቸው 2,672 የምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ ንጋት ጀምሮ የየምርጫ ጣብያው ውጤት ይፋ እየተደረገ ነው።
በመቐለ ከተማ የሚገኙ አንዳንድ የምርጫ ጣብያዎች የተለጠፈ ውጤት ህወሓት ከፍተኛ ድምፅ ማግኘቱ የሚያመለክት ሲሆን ባይቶና ፣ ሳልሳይ ወያነ ትግራይና የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ተወካዮችም የህዝብ ድምፅ ማግኘታቸውን ዶቼ ቨለ (DW) ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በትግራይ ምርጫ ለሊቱ ድምፅ ሲቆጠር አድሮ ጠዋት በየምርጫ ጣብያው ውጤት ተለጥፏል።
ትላንት ጳጉሜ 4 በትግራይ የተካሄደው 6ኛው ክልላዊ ምርጫ ውጤት ፣ ድምፅ በተሰጠባቸው 2,672 የምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ ንጋት ጀምሮ የየምርጫ ጣብያው ውጤት ይፋ እየተደረገ ነው።
በመቐለ ከተማ የሚገኙ አንዳንድ የምርጫ ጣብያዎች የተለጠፈ ውጤት ህወሓት ከፍተኛ ድምፅ ማግኘቱ የሚያመለክት ሲሆን ባይቶና ፣ ሳልሳይ ወያነ ትግራይና የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ተወካዮችም የህዝብ ድምፅ ማግኘታቸውን ዶቼ ቨለ (DW) ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የግል ትምህርት ቤቶች በ2013 አመት የትምህርት ዘመን ምዝገባ ምንም አይነት ክፍያ ጭማሪ ማድረግ እንደማይችሉ የሶማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ለSRTV አስታውቀዋል፡፡
የሶማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ ፋታህ፦
"እንደሚታወቀው ከነሃሴ 20/2012 ጀምሮ የግል ትምህርት ቤቶች ምዝገባ እየተካሄደ እንዳለ ይታወቃል። ትምህርት የሚጀምርበት ጊዜ በፌደራል እና በሚመለከታቸው አካላት ውሳኔ መሰረት ነው።
አሁን መግለፅ የምፈልገው ግን በግል ትምህርት ቤቶች የምዝገባ ወቅት ላይ በኮቪድ-19 ምክንያት ትምህርት ቤቶች በተዘጉበት ወቅት የመምህራን ደሞዝ ለመሸፈን ወላጆችን ክፍያ እንዲፈፅሙ መጠየቁ የሚታወስ ነው።
ዛሬ ላይ ድግሞ የግል ትምህርት ቤቶች የወቅቱን ሁኔታ በማየት ክፍያ የመጨመር አዝማሚያ የሚታይ በመሆኑ ጉዳዩ ከህግና ስርዓት ውጭ መሆኑን ሊረዱ ይገባል።
በዚህም ከአንዳንድ ወላጆች የደረሱን መረጃዎች በመኖራቸው የክልሉ ትምህርት ቢሮ ይህን ጉዳይ የሚከታተል ይሆናል።"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሶማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ ፋታህ፦
"እንደሚታወቀው ከነሃሴ 20/2012 ጀምሮ የግል ትምህርት ቤቶች ምዝገባ እየተካሄደ እንዳለ ይታወቃል። ትምህርት የሚጀምርበት ጊዜ በፌደራል እና በሚመለከታቸው አካላት ውሳኔ መሰረት ነው።
አሁን መግለፅ የምፈልገው ግን በግል ትምህርት ቤቶች የምዝገባ ወቅት ላይ በኮቪድ-19 ምክንያት ትምህርት ቤቶች በተዘጉበት ወቅት የመምህራን ደሞዝ ለመሸፈን ወላጆችን ክፍያ እንዲፈፅሙ መጠየቁ የሚታወስ ነው።
ዛሬ ላይ ድግሞ የግል ትምህርት ቤቶች የወቅቱን ሁኔታ በማየት ክፍያ የመጨመር አዝማሚያ የሚታይ በመሆኑ ጉዳዩ ከህግና ስርዓት ውጭ መሆኑን ሊረዱ ይገባል።
በዚህም ከአንዳንድ ወላጆች የደረሱን መረጃዎች በመኖራቸው የክልሉ ትምህርት ቢሮ ይህን ጉዳይ የሚከታተል ይሆናል።"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአፋር ክልል ሁለት ከተሞች አነስተኛ መጠን ያለው ርዕደ - መሬት መከሰቱን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።
ጳጉሜ 3 እና 4 /2012 ዓ/ም በሎግያ-ሰመራ ከተማ በተለያዩ ሰአቶች ሶስት ጊዜ በሬክተር እስኬል መለኪያ ከአንድ እስከ ሁለት የሚለካ ቀላል ርዕደ-መሬት መከሰቱን ዩኒቨርሲቲው ለኢዜአ ገልጿል።
ምንም እንኳን በክስተቱ በአካባቢው የደረሰ ጉዳት ባይኖርም በቀጣይ በአካባቢዉ ተጨማሪ ክትትል እና ጥናቶችን ማድረግ አስፈላጊ ስለመሆኑ አመላካች ነገሮች መኖራቸዉ ተገልጿል።
ርዕደ-መሬቱ የተከሰተዉ በተለይም ጳጉሜ 3 በተለያዩ ሰዓታት መሆኑ የተነገረ ሲሆን ትናንትናም ማምሻውን ጨምሮ በተለያዩ ሰአታት አራት ጊዜ ርእደ-መሬቱ በተመሳሳይ አካባቢዎች ተመዝግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጳጉሜ 3 እና 4 /2012 ዓ/ም በሎግያ-ሰመራ ከተማ በተለያዩ ሰአቶች ሶስት ጊዜ በሬክተር እስኬል መለኪያ ከአንድ እስከ ሁለት የሚለካ ቀላል ርዕደ-መሬት መከሰቱን ዩኒቨርሲቲው ለኢዜአ ገልጿል።
ምንም እንኳን በክስተቱ በአካባቢው የደረሰ ጉዳት ባይኖርም በቀጣይ በአካባቢዉ ተጨማሪ ክትትል እና ጥናቶችን ማድረግ አስፈላጊ ስለመሆኑ አመላካች ነገሮች መኖራቸዉ ተገልጿል።
ርዕደ-መሬቱ የተከሰተዉ በተለይም ጳጉሜ 3 በተለያዩ ሰዓታት መሆኑ የተነገረ ሲሆን ትናንትናም ማምሻውን ጨምሮ በተለያዩ ሰአታት አራት ጊዜ ርእደ-መሬቱ በተመሳሳይ አካባቢዎች ተመዝግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በላሬ ወረዳ ከ5,000 በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል!
በጋምቤላ ክልል በላሬ ወረዳ በጎርፍ ምክንያት ከአምስት ሺ (5,000) ሰዎች በላይ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው እደሚገኙ ከጋምቤላ ፕሬስ ሰክሬተሪያት ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ጎርፉ ከአቅም በላይ በመሆኑ ህብረተሰቡ ላይ ችግር እየደረሰ ስለሆነ አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደረግላቸው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጋርዊቺ ቢየል ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የላሬ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ኛዳክ ፓች በተደጋጋሚ በሚጥለው ዝናብ ምክናያት ቤት ንብረታቸውን ጥለው በትምህርት ቤት አጥር ጊቢ ውስጥ ተጠልለው እደሚኖሩ ተናግረዋል።
ወይዘሮዋ አክለውም ጎርፉ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው የአልባሳትና የምግብ ፍጆታ አቅርቦት መንግስት ድጋፍ እንድያደርግላቸው ጠይቀዋል፡፡
የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ጋርዊች ቢየል በበኩላቸው በተመሳሳይ ጎርፉ በወረዳው ባሉ 28 ቀበሌዎች ለጊዜው ቁጥራቸው ባይታወቅም ከተጠቀሰው ቁጥር ባላይ ተፈናቃዮች እንዳሉ ነው የተናገሩት፡፡
ተጎጅዎቹ ባለባቸው የመጠለያ እና የምግብ ችግር ለተለያዩ በሽታዎች አደሚዳረጉ ገልጸው ችግሮችን ለመቅረፍ የባለድርሻ አካላት ርብርብ እደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጋምቤላ ክልል በላሬ ወረዳ በጎርፍ ምክንያት ከአምስት ሺ (5,000) ሰዎች በላይ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው እደሚገኙ ከጋምቤላ ፕሬስ ሰክሬተሪያት ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ጎርፉ ከአቅም በላይ በመሆኑ ህብረተሰቡ ላይ ችግር እየደረሰ ስለሆነ አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደረግላቸው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጋርዊቺ ቢየል ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የላሬ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ኛዳክ ፓች በተደጋጋሚ በሚጥለው ዝናብ ምክናያት ቤት ንብረታቸውን ጥለው በትምህርት ቤት አጥር ጊቢ ውስጥ ተጠልለው እደሚኖሩ ተናግረዋል።
ወይዘሮዋ አክለውም ጎርፉ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው የአልባሳትና የምግብ ፍጆታ አቅርቦት መንግስት ድጋፍ እንድያደርግላቸው ጠይቀዋል፡፡
የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ጋርዊች ቢየል በበኩላቸው በተመሳሳይ ጎርፉ በወረዳው ባሉ 28 ቀበሌዎች ለጊዜው ቁጥራቸው ባይታወቅም ከተጠቀሰው ቁጥር ባላይ ተፈናቃዮች እንዳሉ ነው የተናገሩት፡፡
ተጎጅዎቹ ባለባቸው የመጠለያ እና የምግብ ችግር ለተለያዩ በሽታዎች አደሚዳረጉ ገልጸው ችግሮችን ለመቅረፍ የባለድርሻ አካላት ርብርብ እደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Hawassa
የሀዋሳ ከተማ ትራንስፓርት እና መንገድ ልማት መምሪያ በትራንስፓርት ዘርፍ ተጥሎ የነበረው ታሪፍ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በፊት ወደነበረበት መመለሱን ገልጿል።
አሽከርካሪዎች በወንበር ልክ መጫን አለባቸው ተብሏል ፤ ባጃጅ ሾፌሩን ጨምሮ ሶስት ሰዎችን ማሳፈር እንዳለበት ተገልጿል ፤ ከወንበር በላይ በሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
ሞተር ሳይክልን በተመለከተ አሽከርካሪው ብቻ መጠቀም እንዳለበት ከሀዋሳ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሀዋሳ ከተማ ትራንስፓርት እና መንገድ ልማት መምሪያ በትራንስፓርት ዘርፍ ተጥሎ የነበረው ታሪፍ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በፊት ወደነበረበት መመለሱን ገልጿል።
አሽከርካሪዎች በወንበር ልክ መጫን አለባቸው ተብሏል ፤ ባጃጅ ሾፌሩን ጨምሮ ሶስት ሰዎችን ማሳፈር እንዳለበት ተገልጿል ፤ ከወንበር በላይ በሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
ሞተር ሳይክልን በተመለከተ አሽከርካሪው ብቻ መጠቀም እንዳለበት ከሀዋሳ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia