TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እኛም ኮራን በናተ...
እውነት ኮራን በናተ...


@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Irreechaa2019

የሆራ አርሰዴ ኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል!

PHOTO: FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከትምህርት ሚኒስቴር!

ውድ የቲክቫህ ቤተሰቦች በትምህርት ሚንስቴር "እኛ ለኛ "የበጎ ፍቃደኞች መርሃ ግብር ላይ በበጎ ፈቃደኝነት የሰራችሁት ሥራ ለብዙ ህጻናት የመማሪያ ቁሳቁሶችን እንድናደርስ አስችሎናል፡፡

ባለፈው የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን በጋራ በ 30 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ አልባሳትን በአገራችን የተለያዩ ክፍሎች በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ትምህርታቸውን ላቋረጡ እና ባግባቡ ላልተከታተሉ ተማሪዎች ይውል ዘንድ በእርዳታ መልክ መለገሳቸው የሚታወስ ነው።

ስለሆነም እነዚህን አልባሳት ለክልሎች በአግባቡ ለይቶ ለማሰራጨት ይረዳን ዘንድ ከሰኞ መስከረም 26 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 11:00 ድረስ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ አልባሳትን የመለየት ስራ ለመስራት እቅድ ስለያዝን በዚህ ሁለተኛ ዙር ላይ በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለመስጠት የምትፈልጉ ሁሉ፡ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች በመመዝገብ በዚህ በጎ ስራ ላይ አሻራችሁን እንድታኖሩ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የመመዝገቢያ ስልክ ቁጥሮች

+251911485705
+251944260072

ከትምህርት ሚንስቴር "እኛ ለእኛ" የበጎ ፍቃደኞች መርሃ ግብር!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሟቾች ቁጥር 100 ደርሷል፤ ኢንተርኔት በበርካታ የሀገሪቱ ከተሞችም ተዘግቷል!

በኢራቅ ዋና ከተማ ባግዳድና አከባቢዋ 6 ቀናትን ባስቆጠረው ታቀውሞ የሞቱት ሰዎች 100 ደርሰዋል። በኢራቅ የተለያዩ ክፍሎች የሀገሪቱን መንግስት በመቃውም ተቃውሞ ከተቀሳቀሰ ስድስት ቀናትን አስቆጥሯል። በዚህ ታቃውሞ በርከት ብለው በመሳተፍ ላይ የሚገኙት ወጣቶች ሲሆኑ  ሙስናን ፣ ስራ አጥነትን እና ዝቅተኛ መንግስት አገልግሎትን በመቃወም ነው ተቃውሟቸውን እያሰሙ የሚገኙት፡፡

#የኢንተርኔት_አገልግሎት በበርካታ የሀገሪቱ ከተሞች ተቋርጧል። ዛሬ ጥዋት ለጥቂት ሰዓት ተከፍቶ የነበረ ቢሆንም የኢራቅ መንግስት ዳግም እንዲዘጋ አድርጎታል። ኢንተርኔት በተከፈተበት ወቅት የኢራቅ ዜጎች #VPN በመጠቀም በርካታ አሳዛኝና ለማየት የሚከብዱ ቪድዮዎችን ሲያጋሩ ነበር።

#IRAQ

•100 ሰዎች ሞተዋል
•4000 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል
•በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታስረዋል
•ሙሉ በሙሉ በሚል ደረጃ ኢንተርኔት ተዘግቷል

@tsegabwolde @tikvahethiopia
BAGHDAD

#DijlahTV -- ባልታወቁ ቡድኖች ጥቃት ደርሶበት ስርጭቱ ቆሟል!

#ArabicNrtTV -- ማንነታቸው እስካሁን ባልታወቁ ቡድኖች ጥቃት ደርሶበት ስርጭቱን ለማቆም ተገዷል። የጣቢያው ሰራተኞችም ታስረዋል።

#AlArabiyaTV -- ይህ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጭምብል ባጠለቁ ቡድኖች ጥቃት ተፈፅሞበታል። ፈፃሚዎቹ እነማን እንደሆኑ አልታወቀም።

#Baghdad
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሆራ አርሰዲ ኢሬቻ በዓል በሰላም ተጠናቋል!

በቢሾፍቱ የተከበረው የሆራ አርሰዲ ኢሬቻ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል።

የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ አቶ ግርማ ሃይሉ እና የቢሾቱ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አለምፀሃይ ሽፈራው የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ አርሰዲ ኢሬቻ በዓላት በሰላም መከበርን አስመልክተው በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሃላፊው በመግለጫቸው ትናንት በአዲስ አበባ እና በዛሬው ዕለት በቢሾፍቱ የተከበረው የኢሬቻ በዓል እሴቱን በጠበቀ መልኩ ሁሉንም ብሄር ብሄረሰቦች በማሳተፍ በሰላም መጠናቀቁን ገልጸዋል።

በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅም አባ ገዳዎች፣ ፎሌዎች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት በቅንጅት መስራታቸውን የገለጹት ሃላፊው፥ለዚህ ውጤታማ ስራቸውም ምስጋና አቅርበዋል።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethioia
#Irreechaa2019 ኢሬቻ ሆራ አርሰዲ! #ቢሾፍቱ

PHOTO: OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ETHIOPIAN FEDERAL POLICE COMMISSION

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበር ህዝቡ ላደረገው ቀና ትብብርና ድጋፍ ምስጋናውን አቅርቧል። የኢሬቻ ክብረ በዓል መስከረም 24 እና 25 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማና በቢሾፍቱ መከበሩ ይታወሳል።

ለዚህ ክብረ በዓል በሰላም መከበር ህዝቡ ላደረገው ቀና ትብብርና ድጋፍ ኮሚሽኑ ምስጋናውን አቅርቧል። በፀጥታ ጥበቃው ላይ የተሰማሩት የሰራዊቱ አባላት የተሰጣቸውን አገራዊ ተልዕኮ በብቃት በመወጣት የታለመውን ግብ ማሳካታቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል።

“ለዚህ ስኬት ትልቁን ድርሻ የተወጣችሁ አባገዳዎች፣ ወጣቶች እና የበዓሉ ታዳሚዎች ለፀጥታ አስከባሪ አካላት ያሳያችሁት ቀና ትብብር አርአያነት ያለው ተግባር ነው” ብሏል።

”ህዝብና ፖሊስ አብሮ ተባብሮ ከሰራ የማንሻገረው የሰላምና የደህንነት ችግር አለመኖሩን አረጋግጠናል” በማለት፤ የኢትየጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ምስጋናውን ገልጿል።

ETHIOPIAN FEDERAL POLICE COMMISSION

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሙዚቀኛ ኤልያስ መልካ የስንብት ፕሮግራም መስከረም 26 ቀን 2012 ከቀኑ 5 :30 ላይ ቤተሰቦቹ፣ የሞያ አጋሮቹ እንዲሁም ወዳጆቹ በተገኙበት በብሔራዊ ቴአትር ይካሄዳል። የቀብር ሥነ ስርአቱም ከቀኑ በ9 ሰአት በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን ይከናወናል።

Via Jonny Ragga
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ATAYE

"...እንደገና የተኩስ ልውውጥ ተጀምሯል!" የአጣዬ ከተማ ነዋሪ

ኤፍራታና ግድም አካባቢ ያለውን የፀጥታ ችግር መንግሥት በአስቸኳይ ሊቆጣጠረው ይገባል ሲሉ ነዋሪዎች ጠየቁ። በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አጣዬ አካባቢ ከትናንት ጀምሮ የፀጥታ ችግር መከሰቱን ይታወቃል፡፡ የፀጥታ መደፍረሱ ትናንት በቁጥጥር ሥር የዋለና ዛሬ ረፋድም አንጻራዊ መረጋጋት እንደነበረ የተገለጸ ቢሆንም እንደገና የተኩስ ልውውጥ መጀመሩን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

አስተያየታቸውን ለአብመድ የሰጡ አንድ የአጣዬ ነዋሪም ተከታዩን ብለዋል፦ ‹‹ከቤታችን አልወጣንም፤ ከባድ ተኩስ እየተሰማ ነው፤ ማን እንደሚተኩስ አናውቅም፤ መከላከያ፣ ፖሊስ፣ ልዩ ኃይል አሉ፤ የታጠቁ ኃይሎችም በተራሮች አካባቢ አሉ፤ ከባድ መሣሪያ ጭምር እየተተኮሰ ነው›› በተጨማሪም አስተያየት ሰጪው ሱኒ መውጫ እና አቡበከር ተራራ አካባቢ እየተተኮሰ መሆኑን ያስታወቁት ነዋሪው ከትናንት ጀምሮ ከባድ ስጋት ውስጥ እንደሆኑ አመልክተዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-10-06

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአጣዬ ከተማ አስተዳድር ከንቲባ ጌታቸው በቀለ...

"ከተማው ዙሪያ እና አላላና ይምሎ በሚባሉት ቀበሌዎች የከባድ መሣሪያ ጭምር ተኩስ አለ፤ ሁለት ሠላማዊ ሰዎች ይምሎ ቀበሌ 'ሞሉ በር' አካባቢ ቆስለው ሆስፒታል መግባታቸውንም ሰምቻለሁ።..."ሦስት ቦንብ፣ አንድ ክላሽ ከአራት ካዝና ጋር ታጥቆ ባልተፈቀደ አካባቢ ሲንቀሳቀስ የነበረ ግለሰብ 'ቁም!' ሲባል አልቆምም ብሎ በተከፈተ የተኩስ ልውውጥ ህይዎቱ ካለፈ በኋላ ነው ትናንት የፀጥታ መደፍረስ ያጋጠመው፤ ግለሰቡ ታጥቆ ይንቀሳቀስ የነበረው 01 ቀበሌ አካባቢ ነበር።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia