የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደረገባቸው‼️
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዋና ሳጂን #እቴነሽ_አረፋይኔን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ አደረገ።
ዋና ሳጂን እቴነሽ አረፋይኔ የእስረኞችን ጥፍር የመንቀልና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን አድርሰዋል በሚል 11 ክሶች ተመስርተውባቸዋል።
የቀድሞ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ አባል የነበሩት ዋና ሳጅን እቴነሽ አረፋይኔ በሽብር ወንጀል ተፈርጀው ታስረው በነበሩ የኦነግና የአርበኞች ግንቦት ሰባት አባላት ላይ ሽንት በመሽናት፣ ጥፍር በመንቀልና በሌሎችም ዘግናኝ በተባሉ የወንጀል ድርጊቶች ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
ተከሳሿ በተለምዶ ማዕከላዊ ይባል በነበረው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ ቡድን መርማሪ ሆነው ሲሰሩ ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን በሽብር ተግባር ወንጀል ተፈርጀው በታሰሩ ዜጎች ላይ ፈጽመዋል የተባለውን የወንጀል ድርጊት አቃቤ ሕግ ለፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቦ የነበረው ክስ ያስረዳል።
ዛሬ የዋና ሳጂን እቴነሽ የዋስትና ጥያቄ ላይ ትዕዛዝ ለመስጠት ቀጠሮ ይዞ የነበረው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት የተከሳሿን የዋስትና ጥያቄ ሳይቀበለው ቀርቷል።
ተከሳሿ የዋስትና መብታቸው እንዲከበር፣ ካልሆነም አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩና ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ፤ እንዲሁም ጡት የምትጠባ ሕፃን ልጃቸውን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ትእዛዘ እንዲሰጥ ጠይቀው ነበር።
ተከሳሿ በመገናኛ ብዙሃን በቀረበብኝ ፕሮግራም ሳቢያ ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ለመውረድ ለደሕንነቴ ስለምሰጋ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንደቆይ ይፈቀድልኝ ሲሉ ጠይቀዋል።
ፍርድ ቤቱም ተከሳሿ ከቀረበባቸው ክስ ውስጥ በተለይም 1ኛ እና 2ኛ ክስ አለአግባብ ስልጣንን በመጠቀም የሙስና ወንጀል በመሆኑና ይህም እስከ 10 ዓመት እንደሚያስፈርድ በመጥቀስ የዋስትና ጥያቄው ተቀባይነት አለማግኝቱን ገልጿል።
በተጨማሪም አንድ ተጠርጣሪ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ሊቆይ የሚችለው በጊዜ ቀጠሮ ምርመራ ላይ ክስ እስኪመሰረት በመሆኑ ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እንዲወሰዱና ጉዳይቸውን በዛው ሆነው እንዲከታተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ነገር ግን በደህንነታቸው ላይ ምንም አይነት ስጋት እንዳይኖራቸው፣ ማረሚያ ቤቱም ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን እንዲያስከብር በማለት ነው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ የሰጠው።
በተጨማሪም ዋና ሳጂን እቴነሽ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መክረው ልጃቸው አብራቸው እንድትሆን ከፈለጉም ማረሚያ ቤቱ እንዲቀበላቸው አዟል።
በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ የዋና ሳጂን እቴነሽ አረፋይኔን የክስ መቃወሚያ ለመቀበል ለየካቲት 13 ቀን 2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዋና ሳጂን #እቴነሽ_አረፋይኔን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ አደረገ።
ዋና ሳጂን እቴነሽ አረፋይኔ የእስረኞችን ጥፍር የመንቀልና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን አድርሰዋል በሚል 11 ክሶች ተመስርተውባቸዋል።
የቀድሞ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ አባል የነበሩት ዋና ሳጅን እቴነሽ አረፋይኔ በሽብር ወንጀል ተፈርጀው ታስረው በነበሩ የኦነግና የአርበኞች ግንቦት ሰባት አባላት ላይ ሽንት በመሽናት፣ ጥፍር በመንቀልና በሌሎችም ዘግናኝ በተባሉ የወንጀል ድርጊቶች ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
ተከሳሿ በተለምዶ ማዕከላዊ ይባል በነበረው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ ቡድን መርማሪ ሆነው ሲሰሩ ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን በሽብር ተግባር ወንጀል ተፈርጀው በታሰሩ ዜጎች ላይ ፈጽመዋል የተባለውን የወንጀል ድርጊት አቃቤ ሕግ ለፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቦ የነበረው ክስ ያስረዳል።
ዛሬ የዋና ሳጂን እቴነሽ የዋስትና ጥያቄ ላይ ትዕዛዝ ለመስጠት ቀጠሮ ይዞ የነበረው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት የተከሳሿን የዋስትና ጥያቄ ሳይቀበለው ቀርቷል።
ተከሳሿ የዋስትና መብታቸው እንዲከበር፣ ካልሆነም አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩና ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ፤ እንዲሁም ጡት የምትጠባ ሕፃን ልጃቸውን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ትእዛዘ እንዲሰጥ ጠይቀው ነበር።
ተከሳሿ በመገናኛ ብዙሃን በቀረበብኝ ፕሮግራም ሳቢያ ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ለመውረድ ለደሕንነቴ ስለምሰጋ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንደቆይ ይፈቀድልኝ ሲሉ ጠይቀዋል።
ፍርድ ቤቱም ተከሳሿ ከቀረበባቸው ክስ ውስጥ በተለይም 1ኛ እና 2ኛ ክስ አለአግባብ ስልጣንን በመጠቀም የሙስና ወንጀል በመሆኑና ይህም እስከ 10 ዓመት እንደሚያስፈርድ በመጥቀስ የዋስትና ጥያቄው ተቀባይነት አለማግኝቱን ገልጿል።
በተጨማሪም አንድ ተጠርጣሪ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ሊቆይ የሚችለው በጊዜ ቀጠሮ ምርመራ ላይ ክስ እስኪመሰረት በመሆኑ ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እንዲወሰዱና ጉዳይቸውን በዛው ሆነው እንዲከታተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ነገር ግን በደህንነታቸው ላይ ምንም አይነት ስጋት እንዳይኖራቸው፣ ማረሚያ ቤቱም ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን እንዲያስከብር በማለት ነው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ የሰጠው።
በተጨማሪም ዋና ሳጂን እቴነሽ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መክረው ልጃቸው አብራቸው እንድትሆን ከፈለጉም ማረሚያ ቤቱ እንዲቀበላቸው አዟል።
በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ የዋና ሳጂን እቴነሽ አረፋይኔን የክስ መቃወሚያ ለመቀበል ለየካቲት 13 ቀን 2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 4 ሚሊየን ብር የሚገመት 80 ኪሎ ግራም የብር ጌጣጌጥ በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገለፀ። በዛሬው ዕለት በአዋሽ ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ግምታዊ ዋጋቸው 3 ሚሊየን 953 ሺህ 200 የሚሆኑ 80 ኪሎ ግራም የሚመዝኑ የብር ጌጣጌጦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል። በተጨማሪም ግምታዊ ዋጋቸው 661 ሺህ የሆኑ የተለያዩ አልባሳት እና መለዋዎጫዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ነው የተገለፀው። በተመሳሳይ በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ ግምታዊ ዋጋቸው 166 ሺህ 700 ብር የሆነ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በጥቅሉ በዛሬው ዕለት ብቻ 4 ሚሊየን 580 ሺህ 900 ብር የሚገመት የኮንትሮ ባንድ ዕቃ በቁጥጥር ስር መዋሉ ነው የተገለፀው።
ምንጭ፦ የገቢዎች ሚኒቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ የገቢዎች ሚኒቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ አዲስ ለተቋቋመው የብሔራዊ ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን አባላት በተዘጋጀ የመተዋወቂያ መድረክ ላይ አባላቱ ዘላቂ ሀገራዊ ትስስርን ለማሳደግ መስራት
እንዳለባቸው ተናግረው ለሌላ ሀገራት ተምሳሌት ሊሆን የሚችል ሥርዓት እንዲፈጥሩ አበረታተዋል። ኮሚሽኑ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት #ከሰላም_ሚኒስቴር ጋር በቅርበት
ይሰራል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንዳለባቸው ተናግረው ለሌላ ሀገራት ተምሳሌት ሊሆን የሚችል ሥርዓት እንዲፈጥሩ አበረታተዋል። ኮሚሽኑ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት #ከሰላም_ሚኒስቴር ጋር በቅርበት
ይሰራል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአማራ ክልል በማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች የግጭት #ተፈናቃዮች መንግሥት አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ አላቀረበልንም፤ ለተላላፊ በሽታም ተጋልጠናል ማለታቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል፡፡ ከሁለቱ ዞኖች ወደ 46 ሺህ የሚጠጋ ሕዝብ ተፈናቅሏል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ እስካሁን ዕርዳታ የደረሳቸው 2 ሺህ 700 ብቻ ናቸው፡፡ ተፈናቃዮቹ በላይ አርማጭሆና ምዕራብ ደንቢያ ወረዳዎች ባሉ ቀበሌዎች ተጠልለዋል፡፡ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አደጋ መከላከል ምግብና ዋስትና ቢሮ 2 ሺህ 500 ኩንታል ስንዴና 3 ሺህ ኩንታል አልሚ ምግብ አሰራጭቻለሁ ብሏል፡፡ ከዞኑ 200፣ ከፌደራል ደሞ 600 ተጨማሪ ኩንታል እህል እየተጓጓዘ ነው፡፡
Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ🔝
"ዛሬ #የኢትዮጵያ_ቀይ_መስቀል አዲስ አበባ ቅርንጫፍ የገንዘብ ማሰባሰቢያ እና የ6546 SMS ድጋፍ መቀበያ ስራ ለመስራት ጋዜጣዊ መግለጫ በኢትዮጵያ ሆቴል ሰጥቷል። በተጨማሪ ኢትዮ ቴሌኮም በትላንትናው ዕለት ለአዲስ አበባ ቀይ መስቀል የአምቡላንስ ድጋፍ አድርጓል። በጣም ነው ደስ ያለን! ለሌሎችም ትምህርት ይሆናል! እስኬ ከአዲስ አበባ"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ዛሬ #የኢትዮጵያ_ቀይ_መስቀል አዲስ አበባ ቅርንጫፍ የገንዘብ ማሰባሰቢያ እና የ6546 SMS ድጋፍ መቀበያ ስራ ለመስራት ጋዜጣዊ መግለጫ በኢትዮጵያ ሆቴል ሰጥቷል። በተጨማሪ ኢትዮ ቴሌኮም በትላንትናው ዕለት ለአዲስ አበባ ቀይ መስቀል የአምቡላንስ ድጋፍ አድርጓል። በጣም ነው ደስ ያለን! ለሌሎችም ትምህርት ይሆናል! እስኬ ከአዲስ አበባ"
@tsegabwolde @tikvahethiopia