TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
አፋር🕊ሱማሌ!!

ሰሞኑን በአፋርና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈጥሮ የነበረውን #ግጭት ለመፍታት የሁለቱ ክልሎች የሃይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች #ተስማሙ

በቅርቡ በሁለቱ ክልሎች የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ የሁለቱ ክልሎች የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሰላም ሚኒስቴር ዴኤታና ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በውይይቱም የተፈጠረውን ግጭት  ለመፍታት የሁለቱ ክልሎች የሃይማኖት መሪዎችና የሃገር ሽማግሌዎች መስማማታቸው ነው የተገለፀው።

ከዚህ ባሻገርም የተፈጠረውን ግጭት  መንስኤ ለማጣራትና ግጭቱ ዳግም እንዳይከሰት ለማድረግ ከሁለቱ ክልሎች  የተውጣጣ የጋራ ኮቴ ተቋቁሟል።

በውይይቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ኡስታዝ አቡበክር ሁለቱ ህዝቦች በሃይማኖት በባህል እና በጋብቻ ተሳስረው የኖሩ በመሆናቸው በመካከላቸው መሰል ግጭት መፈጠሩ አግባብ አለመሆኑን ተናግረዋል።

ስለሆነም የሁለቱ ክልሎች የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በቀጣይ ምንም ዓይነት ግጭት እንዳይከሰትና ሰላምና ለማውረድ መስማማታቸውን ገልፀዋል።

ስለሆነም የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ከስምምነት ባሻገር ወደ ህብረተሰቡ ወርደው ለጋራ  ሰላም መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

የሰላም ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ #ዘይኑ_ጀማል በበኩላቸው መንግስት በአካባቢው ግጭት ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዚህ መሰረትም ከሁለቱ ክልሎች ርዕሰ መስተዳድሮች እና የፀጥታ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ የጋራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ የግጭቱን መንስኤ ለማጣራት እና ዳግም እናዳይከሰት ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

ከዚህ ባለፈም መንግስት በአካባቢው ሰላምን ለማስፈን ለሚሰራው ስራ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን  ጠቁመዋል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰላም🕊በአፋርና ሶማሌ #አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈጠረውን ግጭት #ለማስቆም ስምምነት ላይ ተደርሷል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፋሲል ከነማ‼️

የፋሲል ከነማ ደጋፊዎች አሳፍሮ ከባህርዳር ወደ ጎንደር በማምራት ላይ ያለ አውቶብስ #ተገልብጦ በሰው ህይወት እና አካል ላይ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል።

የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ደጋፊዎቹ ትናንት በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 12ኛ ሳምንት በባህርዳር ከተማ እና ፋሲል ከነማ መካከል ከተደረገው ጨዋታ በኃላ ወደ ጎንደር እየተመለሱ ጣራ ገዳም በሚባል አካባቢ ሲደርሱ ነው የመኪና አደጋው ያጋጠማቸው።

በአደጋውም የሁለት ደጋፊዎች ህይወት ሲያልፍ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ደጋፊዎች ላይም የተለያየ መጠን ያለው የአካል ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።

በተሽከርካሪ አደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ደጋፊዎች በጎንደር ሆስፒታል እና በአዲስ ዘመን ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ መሆኑን የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ አስታውቋል።

የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ በደጋፊዎቹ ህይወት ማለፍ እና በደረሰው ጉዳት የተሰማውን መሪር ሀዘን ገልጿል።

“ለክለባቸው ሲሉ ህይዎታቸውን ያጡ ለክለባቸው ታምነው የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉ ደጋፊዎች ታሪካቸው በመላው የፋሲል ከነማና የስፖርት ቤተሰብ ስማቸው በወርቅ መዝገብ ተፅፎ እስከወዲያኛው ሲዘከር ይኖራል” ሲልም ክለቡ አስታውቋል።

Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቅዱስ ጊዮርጊስ🔝የቅዱስ ጊዮርጊስ #ደጋፊዎች እና #ተጫዋቾች በፋሲል ከነማ ሁለት ደጋፊዎች ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዱራሜ🔝ዛሬ ዱራሜ ላይ በከፋ ዞን ለሞቱ የከንባታ ተወላጆች የሃዘን መግለጫ እና ሻማ የማብራት ፕሮግራም ተካሂዷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዴፓ!!

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) #አዲሱን አርማውን በዛሬው እለት ይፋ አደረገ።

አዴፓ ባሳለፍነው መስከረም ወር ባካሄደው 12ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ ላይ ነበር የአርማ #ለውጥ እንዲደረግ ውሳኔ ያሳለፈው።

ፓርቲው በድርጅታዊ ጉባዔው አዲሱ አርማ  መደቡ ከላይ አረንጓዴ መሃል ላይ ጎህ ሲቀድ የሚኖር ቀለም (ቢጫ) ሆኖ ከግርጌ ቀይ እንዲሆን መወሰኑ ይታወሳል።

እንዲሁም መሃሉ ላይ የስንዴ ዘለላ እና የኢንዱስትሪ ምልክት በግራ እና በቀኝ እንዲሆን የአባይ ወንዝ እና መጽሃፍም በአርማው መሃል ላይ እንዲካተት በውኖ ነበር።

በዚህም መሰረት የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) አዲሱ አርማውን በዛሬው እለት በፌስ ቡክ ገፁ ይፋ አድርጓል።

ምንጭ፦ ፋና
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የትግራይ ክልል መንግስት~ለጉዞ አድዋ ተጓዦች የሰጠው ምላሽ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Alert አርባ ምንጭ🔝

#በነጭ_ሳር_ብሄራዊ_ፓርክ የእሳት አደጋ ሳይደርስ እንዳልቀረ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል። የሚመለከተው አካል ጉዳዩን እንዲከታተለውም ጥሪ አቅርበዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአምቦ ከተማው እርቅ‼️

የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከዛሬ ጀምሮ #የተኩስ_ማቆም ውሳኔ አሳልፈዋል። ከዚህ በተጨማሪም የኦነግ ሰራዊት በጥቂት ቀናት ውስጥ ካለበት ጫካ ወጥቶ ወደ ካምፕ እንዲገባም ውሳኔ አሳልፈዋል። መንግስት እና ኦነግ ውሳኔዎችን ያሳለፉት የኦሮሞ አባ ገዳዎች ህብረት በዛሬው እለት በአምቦ ከተማ ባዘጋጀው የእርቅ ስነ ስርአት ላይ ነው።

በዛሬው እለት በተዘጋጀው የእርቅ ስነ ስርዓት ላይ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትና የኦነግ ከፍተኛ አመራሮች፣ አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲቄዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ ወጣቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች እና የአምቦ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይም መንግስት እና ኦነግ በኦሮሞ ባህል መሰረት ኮርማ በሬ በማረድ በይፋ የእርቅ ስነ ስርአት ፈጽመዋል።

ሁለቱም አካላት ከዚህ በኋላ ወደ ደም #መፋሰስ እንደማይገቡ እንዲሁም ያለፈውን ነገር በመተው ስለወደፊቱ ብቻ በጋራ ለመስራት በእርቅ ስነ ስርዓቱ ቃል ገብተዋል። በመድረኩ ላይ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ከስምምነት የደረሱባቸው ዝርዝር የውሳኔ ነጥቦች ይፋ ተደርጓል።

ዝርዝር ስምምነቱንም የቴክኒክ ኮሚቴውን በመወከል የፖለቲካ ተንታኝ እና አክቲቪስት አቶ ጀዋር መሃመድ ያቀረቡ ሲሆን፥ ሁለቱንም አካላት በማነጋገር በዝርዝር ውሳኔው ላይ መደረሱን አስታውቀዋል። በዚሀም መሰረት ከዛሬ ጀምሮ በመንግስት እና በኦሮሞ ነፃነት ግንባር መካከል ጦርነት መቆሙን አስታውቀዋል።

ወደ ግጭት የሚያስገቡ ትንኮሳዎችን ሙሉ በሙሉ መከልከሉን እንዲሁም አንዱ በሌላው ላይ ከዚህ በኋላ መግለጫ ማውጣት ሙሉ በሙሉ መከልከሉንም ገልፀዋል። የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሰራዊት ካለበት ቦታ በሙሉ ትጥቅ ፈትቶ ወደ ካምፕ እንዲገባ መወሱን እና ይህም ከበቂ ጥበቃ ጋር በክብር አቀባበል ወደ ካምፕ እንዲገቡ እንዲደረግ መወሰኑንም ገልፀዋል።

ሰራዊቱን ወደ ካምፕ የማስገባት ስራም በ20 ቀን ውስጥ መጠናቀቅ እንዳለበት ተወስኗል ያሉት አቶ ጃዋር፥ ከእዚህም ውስጥ 10 ቀናት ዝግጅት የሚደረግበት፤ ቀሪው 10 ቀናት ደግሞ ሰራዊቱ ወደ ካምፕ የሚገባበት ነው ብለዋል። ወደ ካምፕ የማስገባት ሂደቱም በሶስት ደረጃዎች ተከፋፍሎ ይካሄዳል ያሉ ሲሆን፥ በዚህም የመጀመሪያም ወደ ወረዳ ከተሞች እንዲሰባሰቡ፣ በመቀጠል ወደ ተዘጋጀላቸው ካምፕ እንዲገቡ ማድረግ በመጨረሻም የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት አቀባበል ማድረግ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዚህ ወቅት ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን እና ይህን ተላልፎ የተገኘ ማንኛውም አካል ላይ መንግሰት ህግን የማስከበር ስራ እንዲሰራ ተፈቅዶለታል ብለዋል። የኦነግ ሰራዊት ካምፕ ከገባ በኋላም አጠቃላይ ስልጠና እንዲወስዱ ተደርጎ የመንግስት የፀጥታ አካላት መቀላቀል ለሚፈልጉ እንደሚያሟሉት መስፈርት እንዲቀላቀሉ መወሰኑንም አስታውቀዋል።

ከዚህ ውጭ ያሉት ደግሞ እንደየፍላጎታቸው በፈለጉት ዘርፍ ስልጠና ወስደው እንዲሰማሩ ድጋፍ እንደሚደረግም አስታውቀዋል። ወደ ካምፕ የገባው ሰራዊትን አያያዝም የቴክኒክ ኮሚቴው በየጊዜው እየሄደ የሚጎበኝ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሰራዊት አባላት እስካሁን ላጠፉት ጥፋት ይቀርታ መደረጉንም የቴክኒክ ኮሚቴው ተወካይ አቶ ጀዋር አስታውቀዋል። ኤፍ ቢ ሲ እንደዘገበው ከላይ የተዘረዘሩትን ስምምነቶች ጥሶ የተገኘ ማንኛውም አካል ላጠፋው ጥፋት ተጠያቂ እንደሚደረግም ነው የገለፁት።

የኦሮሞ አባ ገዳዎች ህብረት ያዘጋጀው የእርቀ ሰላም መድረክ ባሳለፍነው ማክሰኞ በአዲስ አበባ የኦሮሞ ባህል ማዕከል መካሄዱ ይታወሳል። በመድረኩ ላይም የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) በመካከላቸው የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ተስማምተዋል።

እንዲሁም የኦነግን የታጠቀ ሰራዊት ትጥቅ ለማስፈታት እና ሰራዊቱን ወደ ካምፕ ለማስገባት እንዲሁም ሌሎች ስምምነት ላይ የተደረሱ ጉዳዮችን ለማስፈፀም 71 አባላት ያለው የቴክኒክ ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን፥ የቴክኒክ ኮሚቴውም ከምሁራን 11፣ ከአባ ገዳዎች 54፣ ከኦዲፒ 3 እንዲሁም ከኦነግ 3 አባላት ያለው ነው።

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰላም🕊የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከዛሬ ጀምሮ #የተኩስ_ማቆም ውሳኔ አሳልፈዋል!

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔውን ዛሬ ጀምሯል፡፡ የክልሉ ም/ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካዔል የመንፈቅ ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ የትግራይ ተወላጆች ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች መፈናቀላቸው እንደቀጠለ ነው ብለዋል። በክልሉ ሁከት ለመፍጠር የተደረገው ሙከራም በጸጥታ ሃይሎችና #በሕዝቡ ትብብር ከሽፏልም ሲሉ ገልፀዋል፡፡

via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia