TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
የኢትዮጵያ አየር መንገድ🛫

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ለ7ኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ የምርጥ አየር መንገድ ሽልማትን #አሸነፈ

አየር መንገዱ ሞሮኮ ራባት ላይ እየተካሄደ በሚገኘው 50ኛው የአፍሪካ ታላላቅ አየር መንገዶች ማህበር አመታዊ ጉባኤ ላይ አሸናፊ መሆኑ የተበሰረው።

የእውቅናው ሽልማቱ ለአየር መንገዱ በፋይናንስና ትርፋማነት አፈጻጸም ላይ ባሳየው የላቀ ደረጃ ምክንያት እንደተበረከተለት ተነግሯል።

ምንጭ፦ FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpdateSport ካፍ ቻምፒየንስ ሊግ ውጤት፦

ጅቡቲ ቴሌኮም 1-3 ጅማ አባጅፋር
አስቻለው ግርማ
ማማዱ ሲዲቤ
ማማዱ ሲዲቤ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማሳሰቢያ‼️

ወህዴግ በማህበራዊ ሚዲያ በቀን 19/03/2011 ዓ.ም #በወላይታ_ሶዶ ከተማ #ሠላማዊ_ሰልፍ እንደሚያደርግ እየገለፀ ያለ ቢሆንም የዞኑ አስተዳደር አሁን ያለውን #የፀጥታ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ፍቃድ ያልተሰጠ ስለሆነና ነባራዊ ሁኔታን በመገምገም ወደፊት የሚፈቅድ መሆኑ ታውቆ በተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮችም ሆነ አባላት የሚደረገው ቅስቀሳ ተገቢ ያለመሆኑን በመገንዘብ #ጥንቃቄ እንዲደረግ እናሳስባለን፡፡

©Wolaita ZONE Culture, tourisim and Governmental Communication Affairs Office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ🔝

በኢትዮጵያ የሚገኙ ከሰባ በላይ ፓርቲዎች ለሚቀጥለው #ምርጫ እንዲዘጋጁ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ጥሪ አቀረቡ።

ከፓርቲዎቹ መሪዎች ጋር ዛሬ ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ፤ ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ቁጥራቸው ወደ አምስት እና ስድስት ዝቅ እንደሚል ተስፋቸውን ገልፀዋል።

ለቀጣዩ ምርጫ ነፃና ፍትሃዊ መሆን የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች በጊዜ ካልተጠናቀቁ ምርጫውን ማራዘሙ የግድ አስፈላጊ ሊሆን እንደሚችል የገለፁት ደግሞ፤ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ናቸው።

ምንጭ፦ VOA አማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እውነት ተናግረክ የምታጣው ነገር ቢኖር አጠገብክ ያሉ #ሀሰት ተናጋሪ ሰዎችን ብቻ ነው!!

መልካም ቀን ይሁንልን!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ካራ ቆሬ🔝

በአሁን ሰዓት #ካራ_ቆሬ አካባቢ በተለምዶ ግራር ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ቤቶቻቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ እያደረጉ ይገኛሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኤች አይ ቪ መከላከያ መድሃኒት‼️

የኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ምንስቴር የኤች አይ ቪ መከላከያ መድሃኒት በሙከራ መልክ መስጠት እንደሚጀምር አስታወቀ። ከቫይረሱ ነፃ ለሆኑ ሰዎች  የሚሰጠዉ ይኽው መድሃኒት በእንክብል መልክ በቀን አንድ ጊዜ የሚወሰድ ይሆናል።


በምንስቴር መስሪያ ቤቱ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ቡድን መሪ ወይዘሮ ምርቴ ጌታቸዉ ለDW እንደገለፁት መከላከያ መድሃኒቱ በሙከራ መልክ በቅርቡ መሰጠት ይጀምራል።  ህክምናዉ የሚሰጠዉ ከኤች አይ ቪ ነፃ ለሆኑ ነገር ግን ለቫይረሱ #ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ነዉ።

እንደ ወይዘሮ ምርቴ የመከላከያ መድሃኒቱ ሙከራ የሚጀመረዉ የኤች አይ ቬ ስርጭት ከፍተኛ በሆነባቸዉ  15 የሀገሪቱ ክፍሎች ሲሆን በተመረጡ የመንግስት የጤና ተቋማትና USAID የተባለዉ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅት በገንዘብ በሚደግፋቸዉ የጤና ማዕከላት በነፃ ይሰጣል።

የመከከላከያ ህክምናዉ ከአሁን ቀደም ደቡብ አፍሪካን በመሳሰሉ የበሽታዉ ስርጭት ከፍተኛ በሆነባቸዉ ሀገራት ተሞክሮ አስተማማኝ ዉጤት መገኘቱን የገለፁት ወይዘሮ ምርቴ ፤ያማለት ግን ሌሎች በሽታዉን ለመከላከል የሚደረጉ የጥንቃቄ ዘዴዎችን ይተካል ማለት እንዳልሆነ አሳስበዋል።ስለሆነም ህክምናዉ ከሌሎች የመከላከያ ዘዴዎች ጎን ለጎን የሚሰጥና የጊዜ ገደብም ያለዉ ነዉ ብለዋል።

መድሃኒቱ ከመሰጠቱ በፊት የኤች አይቪ ምርምራ ማድረግን የሚጠይቅ ሲሆን ምርመራዉም በየ 3 ወሩ የሚቀጥል ይሆናል ነዉ ያሉት። የሙከራ ህክምናዉ በሚጀመርባቸዉ የጤና ተቋማት የሚገኙ የጤና ባለሙያዎችም በዝርዝር ስለሚያከናዉኗቸዉ ስራዎች የተለዬ ስልጠና መዉሰዳቸዉን ሀላፊዋ አመልክተዋል።

የሙከራ ስራዉ ሲጠናቀቅም የተገኘዉን ዉጤት መሰረት በማድረግ በመደበኛነት በየጤና ተቋማቱ መድሃኒቱን መሰጠት እንደሚጀመር ሀላፊዋ ገልፀዋል። 

የመከላከያ መድሃኒቱ ሲጀመር ኤች አይ ቬ ኤድስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚደረገዉ ጥረት እንዳይቀዛቀዝና መዘናጋት እንዳይፈጠርም ተጨማሪ ሥራዎች ለመሥራት ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ማቀዱን ሀላፊዋ ጨምረዉ አመልክተዋል። 

«ሚዲያ ላይ በደንብ «አዌርነስ» መፍጠር፣ ንቃተ ህሊናን የማሳደግ ስራዎችን መስራት ፣ይህንን መጀመር ማለት ሙሉ በሙሉ ነፃ እንሆናለንና እንደፈለግን እንሆናለን ማለት እንዳልሆነ፣ በደንብ መስራት ይኖርብናል።እንግዲህ ለወደፊት የምንሰራዉና አንዱ እቅዳችን ዉስጥ ያስገባነዉ ዋና ተግባር ነዉ።»

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወላይታ 🕊 ሲዳማ!

የወላይታና የሲዳማ ህዝቦች ሰላም ወዳድ፣ ጠንካራ #ፍቅር ያላቸውና ተለያይተው መኖር የማይችሉ መሆናቸውን አረጋግጠናል ሲሉ የሲዳማና ወላይታ ገለልተኛ አስታራቂ አባቶች ገለጹ፡፡

በህዝቦች መካከል ለዘመናት የቆየው አብሮነትና አንድነት ከጠፋ አገሪቱን ወደሚፈለገው የዕድገት ደረጃ ላይ ማድረስ ስለማይቻል ህዝቡ ሰላምና አብሮነቱን ማጠናከር እንዳለበት አባቶቹ መክረዋል።

በወላይታና ሲዳማ ተወላጆች መካከል ተከስቶ የነበረውን አለመግባባት ወደሰላም ለመመለስ ፈታኝና እልህ አስጨራሽ የእርቅ ሂደት ማለፋቸውን የተናገሩት አስታራቂ አባቶቹ ሁለቱ ህዝቦች ሰላም ወዳድ፣ እርስ በርስ ፍቅር ያላቸውና መለያየት እንደማይችሉ ማረጋገጣቸውን ገልጸዋል።

የገለልተኛ አስታራቂ ኮሚቴው ሰብሳቢ መጋቢ ጌቱ አያሌው እርቅ ለማውረድ በተደረገው ጥረት በሁለቱ ወንድማማች ህዝብ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የጥል ግድግዳ መፍረሱንና በእዚህም ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

“ሁለቱን ህዝብ ለማስታረቅ እልህ አስጨራሽና ፈታኝ ወቅት አልፈናል” ያሉት መጋቤ ጌቱ፣ ሠላምና እርቅ የማይፈልጉ ሁለቱንም ብሄር የማይወክሉ ግለሰቦች በአካልና በማህበራዊ ሚዲያ ስም የማጥፋት፣ የማስፈራራትና ተስፋ የማስቆረጥ ሥራዎችን ቢሰሩም እርቁ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸዋል።

ዕርቀ ሰላሙን ለማውረድ ከሁለቱም ብሔር አገር ሸማግሌዎች ጋር ለአራት ወራት የመከሩ ሲሆን በእዚህም ሁለቱም ህዝቦች ሰላም ወዳድ ከመሆናቸው ባለፈ እርስ በርስ የሚፋቀሩና ተለያይተው መኖር የማይችሉ ናቸው።

በህዝቦች መካከል ያለውን አብሮነትና አንድነት በመጠበቅ በአገሪቱ የሚፈለገውን እድገት ለማምጣት ተረባርቦ መስራት እንደሚገባም  አሳስበዋል፡፡

የሃዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪ መላከ ምህረት ቆሞስ አባ ጌዲዮን ብርሃን በበኩላቸው መነጣጠል የማይችሉ ሁለቱ ህዝቦች በመታረቃቸው ከማንም በላይ የተለየ ደስታ እንደተሰማቸው ነው የገለጹት።

በእርቅ ሂደት ውስጥ የሲዳማና የወላይታ አገር ሸማግሌዎች ሠላም ለማውረድ ከፍተኛ እገዛ ማድረጋቸውንና የክልሉና የሁለቱ ዞን የመንግስት አካላትም ላሳዩት ቀና ትብብር ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

የእርቀ ሠላም ጉባኤው ለኢትዮጵያውንና ህዝብን ለማበጣበጥና የአገሪቱን ሠላም ለማድፍረስ ደፋ ቀና ለሚሉ አካላት ትልቅ ትምህርት የሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

“ኢትዮጵያውያን ያለንን አብሮነትና አንድነት ካጣን ወደምናስበው የእድገት ደረጃ መድረስ ስለማንችል ቆም ብለን ልናስብ ይገባል” ሲሉም መላከ ምህረት ቆሞስ አባ ጌዲዮን አመልክተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ወጣት ፍቅርና አንድነቱን ጠብቆ በማቆየት ሰላምና ልማቷ የተረጋገጠ አገር ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ እንዳለበት አውቆ ለእዚያ መንቀሳቀስ እንዳለበትም መክረዋል፡፡

ከአላህ ዘንድ የተሰጣቸውን ትልቅ ኃላፊነት በስኬት በማጠናቀቃቸው ሀሴት እንደተሰማቸው የገለጹት ደግሞ የደቡብ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንትና የገለልተኛ አስታራቂ ኮሚቴ አባል ሃጂ አህባበብ አባ ጀማል ናቸው፡፡

የሲዳማና የወላይታ አገር ሸማግሌዎች ሰላም የሚሹ ፣ የተጎራበቱ፣ የተጋቡና የተዋለዱ መሆናቸውን ያረጋገጡበት የእርቅ ሂደት መሆኑን የገለጹት ሃጂ አህባበብ፣ ሰላም አንዲወርድ እንደኮሚቴ ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

ለአብሮነትና ለሠላም ቅርብ በሆኑ ህዝቦች መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የተከሰተው መራራቅና አለመተማመን በአሁኑ ወቅት መፈታቱንና በቀጣይም ለዘላቂ ሰላም በቅንጅት እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

በቅርቡ በሃዋሳና በሶዶ ከተማ የተካሄደው የሁለቱ ህዝቦች የይቅርታና እርቅ ኮንፈረንስ በገለልተኛ አስታራቂ ሽማግሌዎች ላለፉት አራት ወራት የተለያዩ ሂደቶችን ያለፈ መሆኑን ታውቋል፡፡

ምንጭ፦ ኢ.ዜ.አ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpateSport በስፔን አገር አቋራጭ ውድድር ሰለሞን ባረጋ አሸንፎ ሲገባ የተነሳው ፎቶግራፍ በአለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የአመቱ ምርጥ ፎቶ እጩ ሆነ። ፎቶግራፈሩን ፍሊክስ ሳንቼዝ አትሌት ሰለሞን ባረጋ መልካም እድል ሲል ተመኝቶለታል።

@tseegab @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update በሰብአዊ መብት ጥሰት፣ በሙስናና የተደራጀ ሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን #ብሔርን መሰረት ተደርጐ እርምጃ እየተወሰደ ነው በሚል የሚሰጡ አስተያየቶች የተሳሳቱ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ገልፀዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ🔝ተማሪዎች ከፌደራል ከመጡ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር ውይይት እያደረጉ ይገኛል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ኢትዮጵያ ውስጥ በአገር አቀፍ ደረጃ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሚደረግ ውይይትና ድርድር የሚመራበት ህግ /rule of engagment/ ሊዘጋጅ እንደሆነ ተሰምቷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from Afriwork (Freelance Ethiopia) (Semegn)
More than 50 jobs per week in different fields. Join this group to get projects, part time and full time jobs. @freelance_ethio
አሳዛኝ ዜና‼️

በቻይና አንድ የኬሚካል ፋብሪካ ላይ በደረሰ #ፍንዳታ 22 ሰዎች ሞቱ
በቻይና በኬሚካል ፋብሪካ ላይ በደረሰ ፍንዳታ 22 ሰዎች ሲሞቱ 22 የሚሆኑት ጉዳት ተርሶባቸዋል።

ፍንዳታው የተከሰተው በቻይና ሰሜናዊ የሂቤ ግዛት በሚገኝ ስፍራ ውስጥ ሲሆን በዚሁ አደጋ ሀምሳ የሚሆኑ ተሸከርካሪዎች ወድመዋል፡፡

በኬሚካል ፍንዳታው በአካባቢው ዓየር ላይ የጠቆረ ጭስ እና ነበልባል በማስከተል ለብክለት መንስኤ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

እንደ ሀገሪቱ መንግስት ባለስልጣናት ገለፃ 50 ያህል የእሳት አደጋ መከላከያ መኪኖች በማሰማራት ቃጠሎውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥረት ማድረጋቸውን ጠቁመዋል፡፡ 

የሀገሪቱ የዜና አውታር እንደዘገበው ፍንዳታው ነኬቢ የሻንዩ ኬሚካል ኢንዱስትሪ እኩለ ለሊት ላይ መከሰቱን ጠቁማል፡፡

ከቤጂንግ ሰሜን ምዕራብ 156 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ጂንግጂካኩ በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ2022 የሚካሄደውን ኦሎምፒክ ውድድር ለማስተናገድ ዝግጅት ላይ እንደነበረችም ነው የተጠቆመው፡፡
የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ እንደሚገኝም ነው የአካባቢው ባለስልጣናት ያስታወቁት፡፡

ቻይና ባለፉት ሶስት አስርት አመታት ከፍተኛ እድገት ካዝመዘገቡ ሀገራት ተርታ የምትመደብ ሲሆን በማእድን ማውጫዎች፣ በኢንዱስትሪና ፋብሪካዎቿ አካባቢ ያለውን ደህንነት ሁኔታ የበለጠ ለማሻሻል እየሰራች መሆጓንም ነው የሀገሪቱ ባለስልጣናት የተናገሩት፡፡

በ2015 ነሀሴ ወር በቲያንጂ ወደብ ከተማ የኬሚካል መጋዘን ፍንዳታ ተከስቶ 165 ሰዎች መሞታቸው ሚታውስ ነው ሲል አልጀዚራ በድረገጹ አስነብቧል።

ምንጭ፦ አልጀዚራ(ena)
@tsegabwolde @tikvahethiopia