አስቸኳይ‼️ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ዩኒቨርሲቲዎች የ2011 ዓ.ም. የተማሪዎች የምዝገባ ቀን በድጋሜ መራዘሙን በይፋዊ #ፌስቡክ ገፃቸው እና በተቋማቸው ግቢ ውስጥ በለጠፉት ማስታወቂያ ላይ ገልፀዋል፦
. አክሱም ዩኒቨርሲቲ
. ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
. ዲላ ዩኒቨርሲቲ
. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
. ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
. አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ
. ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ
. ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ
. ወለጋ ዩኒቨርሲቲ
. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
. ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ(esp.)
. ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ
. ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ
. ወሎ ዩኒቨርሲቲ
. ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
. አምቦ ዩኒቨርሲቲ
. ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ
. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
. አርሲ ዩኒቨርሲቲ
ማሳሰቢያ፦ የተለወጠ ወይም የተሳሳተ መረጃ ካለ በፍጥነት አሳውቃችኋለሁ ወይም ማስተካከያ ሰጥበታለሁ።
#ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
. አክሱም ዩኒቨርሲቲ
. ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
. ዲላ ዩኒቨርሲቲ
. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
. ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
. አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ
. ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ
. ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ
. ወለጋ ዩኒቨርሲቲ
. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
. ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ(esp.)
. ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ
. ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ
. ወሎ ዩኒቨርሲቲ
. ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
. አምቦ ዩኒቨርሲቲ
. ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ
. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
. አርሲ ዩኒቨርሲቲ
ማሳሰቢያ፦ የተለወጠ ወይም የተሳሳተ መረጃ ካለ በፍጥነት አሳውቃችኋለሁ ወይም ማስተካከያ ሰጥበታለሁ።
#ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው #ለመመለስ ከአካባቢው ነዋሪዎችና ከአገር ሽማግሌዎች ጋር ለመስራት በዝግጅት ላይ መሆኑን የብሔራዊ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
የአካባቢው ነዋሪዎችና ለጋሽ ድርጅቶች የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመርዳት ያሳዩት ተነሳሽነት ከፍተኛ ቢሆንም ከችግሩ ስፋት አንጻር #ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ ለኢዜአ እንደተናገሩት የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ #በባህላዊና #ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓት ዕርቅ ለማውረድ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ ነው።
በተለይ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ የየአካባቢው ነዋሪዎችና የመንግስት አካላት በተገኙበት እርቅና ሰላም የማውረድ ስራ ይሰራል ብለዋል።
ኮሚሽኑ ተፈናቃዮቹ ከሚገኙበት የኦሮሚያ ክልል መንግስት ጋር በቅንጅት በመስራት ላይ ሲሆን ድጋፉን ለማጠናከር ተጨማሪ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው መላኩንም ገልጸዋል።
ኮሚሽኑ እስካሁን ከአካባቢው ለተፈናቀሉ ዜጎች 17 ሺህ 468 ኩንታል ስንዴ ሩዝና አልሚ ምግብ፣ 146 ሺህ 194 የመመገቢያ ቁሳቁስ መጠለያና አልባሳትና 1 ሺህ 101 ካርቶን የዱቄት ወተት ወደ ስፍራው መላኩን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ለተፈናቀሉ ዜጎች ከዳሸን ባንክ አምስት ሚሊዮን ብር ድጋፍ ሲደረግ ከቡራዩና አካባቢዋ ለተፈናቀሉም እንዲሁ በሲውዘርላንድ የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን 600 ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል።
ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው ሰሞኑን ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ተፈናቅለው በምዕራብና ምስራቅ ወለጋ 10 ወረዳዎች የሚገኙ ሰዎች ቁጥር 91 ሺህ 348 ደርሷል።
▪️በተጨማሪ በመላው አገሪቱ በመደበኛነት #በድርቅ አደጋ የሚረዱ ከሰባት ሚሊዮን በላይ ዜጎች ያሉ ሲሆን ለጋሽ አካላት የተለመደ ትብብራቸው እንዲያደርጉ ጠይቋል።
በተለይ ዲያስፖራው፣ ባለሃብቶችና ሌሎችም ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ የቀረበ ሲሆን ይህንን ለመምራት የሚያስችል ኮሚቴ መዋቀሩንም ገልጸዋል።
በቅርቡ በምዕራብ ጉጂ፣ በጌዲኦ፣ በሶማሌና በቡራዩ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ በባህላዊ ስነ-ስርዓት የሕዝብ ለሕዝብ ስራ መሰራቱ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአካባቢው ነዋሪዎችና ለጋሽ ድርጅቶች የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመርዳት ያሳዩት ተነሳሽነት ከፍተኛ ቢሆንም ከችግሩ ስፋት አንጻር #ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ ለኢዜአ እንደተናገሩት የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ #በባህላዊና #ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓት ዕርቅ ለማውረድ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ ነው።
በተለይ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ የየአካባቢው ነዋሪዎችና የመንግስት አካላት በተገኙበት እርቅና ሰላም የማውረድ ስራ ይሰራል ብለዋል።
ኮሚሽኑ ተፈናቃዮቹ ከሚገኙበት የኦሮሚያ ክልል መንግስት ጋር በቅንጅት በመስራት ላይ ሲሆን ድጋፉን ለማጠናከር ተጨማሪ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው መላኩንም ገልጸዋል።
ኮሚሽኑ እስካሁን ከአካባቢው ለተፈናቀሉ ዜጎች 17 ሺህ 468 ኩንታል ስንዴ ሩዝና አልሚ ምግብ፣ 146 ሺህ 194 የመመገቢያ ቁሳቁስ መጠለያና አልባሳትና 1 ሺህ 101 ካርቶን የዱቄት ወተት ወደ ስፍራው መላኩን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ለተፈናቀሉ ዜጎች ከዳሸን ባንክ አምስት ሚሊዮን ብር ድጋፍ ሲደረግ ከቡራዩና አካባቢዋ ለተፈናቀሉም እንዲሁ በሲውዘርላንድ የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን 600 ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል።
ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው ሰሞኑን ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ተፈናቅለው በምዕራብና ምስራቅ ወለጋ 10 ወረዳዎች የሚገኙ ሰዎች ቁጥር 91 ሺህ 348 ደርሷል።
▪️በተጨማሪ በመላው አገሪቱ በመደበኛነት #በድርቅ አደጋ የሚረዱ ከሰባት ሚሊዮን በላይ ዜጎች ያሉ ሲሆን ለጋሽ አካላት የተለመደ ትብብራቸው እንዲያደርጉ ጠይቋል።
በተለይ ዲያስፖራው፣ ባለሃብቶችና ሌሎችም ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ የቀረበ ሲሆን ይህንን ለመምራት የሚያስችል ኮሚቴ መዋቀሩንም ገልጸዋል።
በቅርቡ በምዕራብ ጉጂ፣ በጌዲኦ፣ በሶማሌና በቡራዩ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ በባህላዊ ስነ-ስርዓት የሕዝብ ለሕዝብ ስራ መሰራቱ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
162,400➕ባለፉት 3 ቀናት ብቻ TIKVAH-ETHIOPIAን የተቀላቀላችሁ 4,000 (አራት ሺ) ኢትዮጵያዊያን እንኳን ወደ ሁላችን ቤት መጣችሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለመላው ኢትዮጵያዊያን‼️
"በመላው አገሪቱ በመደበኛነት #በድርቅ_አደጋ የሚረዱ ከሰባት #ሚሊዮን በላይ ዜጎች አሉ ለጋሽ አካላት የተለመደ #ትብብራቸው እንዲያደርጉ ተጠይቋል።"
.
.
አንዳንዶቻችን ይሄን ረስተነው ይሆን በትንንሽ ጉዳዮች ተለያይተን እየተባላን የምንውለው?? ዛሬም በብሄር ተከፋፋለን የምንበሻሸቀው?? በጥላቻ ተሞልተን ስንሰዳደብ የምንውለው?? ዛሬም ሀገራችን #ለጋሾች እጃቸውን እንዲዘረጉላት #እየተማፀነች ነው። ዛሬም በሀገራችን በድርቅ አደጋ የሚረዱ በሚሊዮኖች ናቸው። ወገኖቼ ይህን ታሪካችንን እስከወዲያኛው ልንቀይር ይገባናል። ይህን መጥፎ ስም የምንቀይረው #በፌስቡክ ብሽሽቅ እና ስድብ፤ ግለሰቦች እና ቡድኖች በሚሰጡን አጀንዳዎች እየተባላን አይደለም‼️ ተባብረን ሰርተን ከዚህ የደህነት እና የችግር ስም መውጣት አለብን‼️
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፀጋአብ ወልዴ~ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በመላው አገሪቱ በመደበኛነት #በድርቅ_አደጋ የሚረዱ ከሰባት #ሚሊዮን በላይ ዜጎች አሉ ለጋሽ አካላት የተለመደ #ትብብራቸው እንዲያደርጉ ተጠይቋል።"
.
.
አንዳንዶቻችን ይሄን ረስተነው ይሆን በትንንሽ ጉዳዮች ተለያይተን እየተባላን የምንውለው?? ዛሬም በብሄር ተከፋፋለን የምንበሻሸቀው?? በጥላቻ ተሞልተን ስንሰዳደብ የምንውለው?? ዛሬም ሀገራችን #ለጋሾች እጃቸውን እንዲዘረጉላት #እየተማፀነች ነው። ዛሬም በሀገራችን በድርቅ አደጋ የሚረዱ በሚሊዮኖች ናቸው። ወገኖቼ ይህን ታሪካችንን እስከወዲያኛው ልንቀይር ይገባናል። ይህን መጥፎ ስም የምንቀይረው #በፌስቡክ ብሽሽቅ እና ስድብ፤ ግለሰቦች እና ቡድኖች በሚሰጡን አጀንዳዎች እየተባላን አይደለም‼️ ተባብረን ሰርተን ከዚህ የደህነት እና የችግር ስም መውጣት አለብን‼️
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፀጋአብ ወልዴ~ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የትምህርት ሚንስትሩ ዶክተር ጥላዬ ጌቴ እንደተናገሩት፤ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን #የፀጥታ_ችግሮች እንዳይከሰቱ ጥቅምት 2 ቀን 2011 ዓ.ም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ህዝባዊ #ውይይት በተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች ይካሄዳል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት⬇️
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከሰቱ #የጸጥታ ችግሮችን አስቀድሞ መከላከል እንዲቻል በአገር አቀፍ ደረጃ ህዝባዊ ውይይት እንደሚካሄድ የትምህርት ሚንስትር ዶክተር #ጥላዬ_ጌቴ ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሰላማዊና ደህንነታቸው የተረጋገጠ ለማድረግ ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችና ከክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ጋር መወያየታቸውንም አክለዋል።
ባለፈው የትምህርት ዘመን በተወሰኑ የመንግስት የከፍተኛ ተቋማት በተነሱ #ግርግሮች ምክንያት የሰው ህይወት ማለፉና ንብረት መውደሙ ይታወሳል።
የትምህርት ሚንስትሩ ዶክተር ጥላዬ ጌቴ በተለይ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን መሰል ችግሮች እንዳይከሰቱ ጥቅምት 2 ቀን 2011 ዓ.ም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ህዝባዊ #ውይይት በተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች ይካሄዳል።
“በትምህርት ተቋማት ውስጥ የተማሪዎች ዋነኛ ተግባር መማርና መመራመር ነው” ያሉት ሚንስትሩ፤ መንግስት ተቋማቱ ከማንኛውም የጸጥታ ችግር ነጻ ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ ከመቸውም ጊዜ በላይ አበክሮ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከ11ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ጎን ለጎን የጸጥታ አካላትን ባሳተፈ መልኩ ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች እና ከክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ስለ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የጸጥታ ችግሮችና #መፍትሄዎቻቸው መወያየታቸውንም
አውስተዋል።
ይህም መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት መስጠቱን እንደሚያሳይ ገልጸው፤ ዘንድሮ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚቀላቀሉ ተማሪዎች ወደ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት ከመመለሳቸው በፊት ውይይት እንደሚያደርጉም ተናግረዋል።
በተያያዘ ዜና ዶክተር ጥላዬ ጌቴ በትምህርት ፍኖተ ካርታ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄደው ውይይት በርካታ ጠቃሚ ግብአቶች የተገኙበት እንደነበረ ጠቁመዋል።
በቅርቡ ፍኖተ ካርታውን በተመለከተ “የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት ትልቅ ህዝባዊ ውይይት በአዳማ ከተማ ይዘጋጃል” ብለዋል።
እስካሁን ባለው ሂደት የተገኙ ግብዓቶችን በማካተት ፍኖተ ካርታው እንደሚሻሻልም ገልጸዋል።
በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መግቢያ ያሟሉ 149 ሺህ ተማሪዎች በተለያዩ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መመደባቸውን ከትምህርት ሚንስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከሰቱ #የጸጥታ ችግሮችን አስቀድሞ መከላከል እንዲቻል በአገር አቀፍ ደረጃ ህዝባዊ ውይይት እንደሚካሄድ የትምህርት ሚንስትር ዶክተር #ጥላዬ_ጌቴ ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሰላማዊና ደህንነታቸው የተረጋገጠ ለማድረግ ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችና ከክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ጋር መወያየታቸውንም አክለዋል።
ባለፈው የትምህርት ዘመን በተወሰኑ የመንግስት የከፍተኛ ተቋማት በተነሱ #ግርግሮች ምክንያት የሰው ህይወት ማለፉና ንብረት መውደሙ ይታወሳል።
የትምህርት ሚንስትሩ ዶክተር ጥላዬ ጌቴ በተለይ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን መሰል ችግሮች እንዳይከሰቱ ጥቅምት 2 ቀን 2011 ዓ.ም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ህዝባዊ #ውይይት በተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች ይካሄዳል።
“በትምህርት ተቋማት ውስጥ የተማሪዎች ዋነኛ ተግባር መማርና መመራመር ነው” ያሉት ሚንስትሩ፤ መንግስት ተቋማቱ ከማንኛውም የጸጥታ ችግር ነጻ ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ ከመቸውም ጊዜ በላይ አበክሮ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከ11ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ጎን ለጎን የጸጥታ አካላትን ባሳተፈ መልኩ ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች እና ከክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ስለ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የጸጥታ ችግሮችና #መፍትሄዎቻቸው መወያየታቸውንም
አውስተዋል።
ይህም መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት መስጠቱን እንደሚያሳይ ገልጸው፤ ዘንድሮ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚቀላቀሉ ተማሪዎች ወደ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት ከመመለሳቸው በፊት ውይይት እንደሚያደርጉም ተናግረዋል።
በተያያዘ ዜና ዶክተር ጥላዬ ጌቴ በትምህርት ፍኖተ ካርታ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄደው ውይይት በርካታ ጠቃሚ ግብአቶች የተገኙበት እንደነበረ ጠቁመዋል።
በቅርቡ ፍኖተ ካርታውን በተመለከተ “የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት ትልቅ ህዝባዊ ውይይት በአዳማ ከተማ ይዘጋጃል” ብለዋል።
እስካሁን ባለው ሂደት የተገኙ ግብዓቶችን በማካተት ፍኖተ ካርታው እንደሚሻሻልም ገልጸዋል።
በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መግቢያ ያሟሉ 149 ሺህ ተማሪዎች በተለያዩ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መመደባቸውን ከትምህርት ሚንስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የአዳማ ኢንደስትሪ ፓርክ የምረቃ ስነ ስርዓት እየተካሄ ይገኛል። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ፣ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ #ለማ_መገርሳና የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው፣ ዶ/ር #አርከበ_ኤቁባይ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ተገኝተዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵየ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ የኢትዮጵየ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዳማ⬆️
በ2ኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በመንግስት ለመገንባት ከታቀዱት የኢንዱስትሪ ፖርኮች 2ኛው የሆነው የአዳማ የኢንዱስትሪ ፓርክ በዛሬው ዕለት በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #አብይ_አህመድ ተመርቋል።
©Fitsum Arega
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በ2ኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በመንግስት ለመገንባት ከታቀዱት የኢንዱስትሪ ፖርኮች 2ኛው የሆነው የአዳማ የኢንዱስትሪ ፓርክ በዛሬው ዕለት በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #አብይ_አህመድ ተመርቋል።
©Fitsum Arega
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኦነግ⬇️
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ ድርጅታቸው #ትጥቁን ለመፍትት ከመንግስት ጋር አለመስማማቱን ተናገሩ። አቶ ዳውድ ከዋልታ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ"ኦነግ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው ትጥቅ ፈተኖ ነው የሚለውን መረጃ አስተባብለዋል።
አቶ ዳውድ ለዋልታ ሲናገሩ "እኛ ትጥቅ እንድንፈታ የተስማማንበት ስምምነት የለም። #የታጠቀው አካል ትጥቅ #ይዞ እያለ እኛ ትጥቅ #የምንፈታበት ምክንያት የለም።" ብለዋል። አክለውም "ትጥቅ መፍታት የሚባል sensitivity ጥያቄ ነው። ትጥቅ ፈቱ መባልም አንፈልግም። ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚመጣው አንዱ ትጥቅ የሚፈታ አንዱ ትጥቅ የሚያስፈታ ይመስላል። የሀገሪቱ ሰላም እንዲጠበቅ ኦነግ ያለው ሚና ምን እንደሚሆን ነው የተስማማነው።" ሲሉ ለዋልታ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አቶ ዳውድ ሰኔ 16 በጠቅላ ሚንስትሩ ላይ በተደረገው #የግድያ ሙከራ ድርጅታቸው እንዳልተሳተፈ ገልፀዋል። በቡራዩና በአዲስ አበባ በተፈጠሩ ግጭቶችም ኦነግ አለመሳተፉን ሊቀመንበሩ ገልፀዋል።
አቶ ዳውድ በበደኖና በአርባ ጉጉ በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰው ጭፍጨፋ #በገለልተኛ አካል #እንዲጣራ የኦነግ ፍላጎት መሆኑን አንስተዋል።
#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ ድርጅታቸው #ትጥቁን ለመፍትት ከመንግስት ጋር አለመስማማቱን ተናገሩ። አቶ ዳውድ ከዋልታ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ"ኦነግ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው ትጥቅ ፈተኖ ነው የሚለውን መረጃ አስተባብለዋል።
አቶ ዳውድ ለዋልታ ሲናገሩ "እኛ ትጥቅ እንድንፈታ የተስማማንበት ስምምነት የለም። #የታጠቀው አካል ትጥቅ #ይዞ እያለ እኛ ትጥቅ #የምንፈታበት ምክንያት የለም።" ብለዋል። አክለውም "ትጥቅ መፍታት የሚባል sensitivity ጥያቄ ነው። ትጥቅ ፈቱ መባልም አንፈልግም። ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚመጣው አንዱ ትጥቅ የሚፈታ አንዱ ትጥቅ የሚያስፈታ ይመስላል። የሀገሪቱ ሰላም እንዲጠበቅ ኦነግ ያለው ሚና ምን እንደሚሆን ነው የተስማማነው።" ሲሉ ለዋልታ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አቶ ዳውድ ሰኔ 16 በጠቅላ ሚንስትሩ ላይ በተደረገው #የግድያ ሙከራ ድርጅታቸው እንዳልተሳተፈ ገልፀዋል። በቡራዩና በአዲስ አበባ በተፈጠሩ ግጭቶችም ኦነግ አለመሳተፉን ሊቀመንበሩ ገልፀዋል።
አቶ ዳውድ በበደኖና በአርባ ጉጉ በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰው ጭፍጨፋ #በገለልተኛ አካል #እንዲጣራ የኦነግ ፍላጎት መሆኑን አንስተዋል።
#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia