TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.7K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
Forwarded from Deleted Account
ኢትዮ ላይፍ ሪል ስቴት(Ethio Life Real Estate)
ዉድ ደንበኞቻችን,ድርጅታችንን ባስተዋወቅነዉ መሠረት መጥተው ስለጎበኙን እያመሠገን መረጃው ላልደረሶት ያለን ቦታ ዉስን በመሆኑ እስከ መስከረም 30 ብቻ በሚቆየው የ 30% ቅድመ ክፋያ ተጠቃሚ ፈጥነው ይሁኑ።
>የግንባታ ቦታ - ቦሌ(ወሎ ሰፈር)-Bole,Wollo sefer
>0920725945 & 0910931987
>0988115004 & 0945675714
>ለቢሮ, ለሱቅ, ለሬስቶራንት, ለሾው ሩም እና የመኖሪያ አፓርታማዎች G+16
>የግንባታ ደረጃ - Finishing work (Block work)
>ስራ ተቋራጭ- ባማኮን ኮንስትራክሽን
____ከ8 ካሬ እስከ 180ካሬ አለ_______
በ 480,000ብር ብቻ ቦሌ ላይ የሱቅ ባለቤት ይሁኑ!
አፓርታማ-
ባለ 2 መኝታ-128 ካሬ, 133 ካሬ, 144ካሬ
ባለ 3 መኝታ-166 ካሬ, 186 ካሬ, 187ካሬ
****ቅድመ ክፍያ 30% እስከ መስከረም 30 ብቻ*****
Building Facilities
> 6 Elevators
> Escalators
> Security camera
> Open down
> Circulation area
> 3 floor underground parking
> And many more modern technologies.
****Your life time property****
አዴፓ⬆️የአዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ በነገው የኢህአዴግ ጉባኤ ላይ ለመካፈል ወደ #ሀዋሳ ለመጓዝ ዝግጅት ላይ ይገኛል።

ምንጭ፦ አቶ ንጉሱ ጥላሁን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አርሲ ዩኒቨርሲቲ⬆️የመደበኛ ነባር ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ጥቅምት 7-8 እንደሆነ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማስታወቂያ⬆️የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የነባር እና የአዲስ ተማሪዎች የምዝገባ ቀን እንደሚከተለው ነው፦

ነባር ተማሪዎች ጥቅምት 1 እና 2
አዲስ ተማሪዎች ጥቅምት 5 እና 6

© www.aastu.edu.et
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ወ/ሮ ሙፈሪያት ከሚል⬇️

በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ ሂደት ከመደገፍና ከማሳደግ ውጪ ሌላ #አማራጭ እንደሌለ የደኢህዴን ሊቀ መንበር በመሆን በድጋሚ የተመረጡት ወይዘሮ #ሙፈሪያት_ካሚል ገለፁ።

ሊቀ መንበሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል 10ኛው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) ድርጅታዊ ጉባዔ #መጠናቀቅን ተከትሎ ለጉባኤተኛው የማጠቃለያ መልእክት አስተላልፈዋል።

ወይዘሮ ሙፈሪያት በማጠቃለያ ንግግራቸው፥ ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት በለውጥ ሂደት ላይ መሆኗን ገልፀው፤ የደኢህዴን አባላት፣ አመራሮች እና ጉባዔተኛው ለውጡ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መስራት አንዳለባቸው ገልፀዋል።

ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለውን ሀገራዊ ለውጥ #ለማደናቀፍ ሌት ተቀን የሚሰሩ ሀይሎች እንዳሉ ሊቀመንበሯ ገልፀዋል።

እነዚህ ሀይሎች 10ኛው የደኢህዴን ጉባዔ እንዳይሳካም ሲንቀሳቀሱ ነበር ያሉት ወይዘሮ ሙፈሪያት፤ ከሀዋሳ ውጪ በህዝቦች መካከል #ግጭት ለመፍጠር ገንዘብ ተመድቦላቸው #ሲንቀሳቀሱ እንደነበረ ከክልሉ የፀጥታ ሀይሎች ጋር በተሰራ ስራ ለማወቅ መቻሉን አንስተዋል።

የደኢህዴን አባላት፣ አመራሮች እና ጉባዔተኛው ይህንን በመገንዘብ እነዚህን የጥፋት ሀይሎች በንቃት መጠበቅና ማጋለጥ ያስፈልጋል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለውን ሀገራዊ የለውጥ ሂደት ከመደገፍና ካማሳደግ ውጪ ሌላ አማራጭ የለም ያሉት ሊቀ መንበሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት፥ ከዚህ ውጨ ያለው አማራጭ #የጥፋት አማራጭ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

ስለዚህ የለውጥ ጉዞውን በማሳከት ሂደት የደኢህዴን አባላት፣ አመራሮች እና የጉባኤተኛው ሚና አጅግ የላቀ መሆኑንም አስገንዝበዋል።

ከነገ ጀምሮ #በሀዋሳ ከተማ የሚካሄደው 11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በማድረግ እንዲሁም የተጀመረውን የህዳሴ ጉዞ ከዳር ለማድረስ የሚደረገውን ርብርብ መቀጠል ይኖርብናል ሲሉም ተናግረዋል።

በኢህአዴግ ጉባኤ ላይ የሚሳተፉ የደኢህዴን ጉባዔተኞች ልክ በደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባዔ ላይ ያደረጉትን የነቃ ተሳትፎ፣ ዴሞክራሲያዊ ሂደትና ሰላማዊ ሁኔታን እንዲያስቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ሊቀ መንበሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት አክለውም፥ 10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባዔ በዚህ መልኩ የተሳካ ሆኖ በመጠናቀቁም እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን ብለዋል።

ጉባዔው የተሳካ እንዲሆን የሀዋሳ ከተማ እና የሲዳማ ዞን እንዲሁም የልግ ባለሀብቶች ላደረጉልት አቀባበል እንዲሁም የኢህአዴግ ጉባዔን ለማስተናገድ እያደረጉ ላለው ዝግጅት ለአመራሩ እና ለህዝቦች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ መረጃ‼️

(ሼር ይደረግ)

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቅለው በምዕራብ ወለጋ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ከ70 ሺህ የማያንሱ ዜጎቻችንን አስቸኳይ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።

ከብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር ባደረግነው ውይይት መሰረት ለኦሮሚያ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ቢሮ በአፋጣኝ ሰብዓዊ እርዳታዎች ለማድረስ ተስማምተናል።

በዚህም መሰረት በአዲስ አበባና በአካባቢው የምትኖሩ ለሰብዓዊ እርዳታ ገር ልብ ያላችሁ ጽኑ ኢትዮጵያዊያን የተለመደው ርብርባችሁ ይጠበቃል።

#የማይበላሹ_ምግቦች

መኮረኒ
ሩዝ
ፉርኖ ዱቄት
ዘይት
ሴሪፋም /ፋፋ/
ብስኩት /ጋቤጣ/

#የንጽህና_ቁሳቁሶች

ሳሙና
ኦሞ
ሳኒታይዘር
የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ /ሞዴስ/

#አልባሳት

ብርድ ልብስ
ነጠላ ጫማ

የተለያዩ አልባሳት (ያገለገሉም ቢሆን)
እነዚህን ቁሳቁሶች ብቻ ለግዜው የፊታችን ሰኞ እና ማክሰኞ እኛ በምናዘጋጀው ግዜያዊ መረከቢያ ቦታ ታደርሱልን ዘንድ በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።

ቦታው #የሀገር_ፍቅር_ቴአትር ቅጥር ግቢ (ሰኞና ማክሰኞ መስከረም 28 እና 29 ብቻ) ጫካ ያደሩ ህፃናትና እናቶች አረጋውያንና ደካሞች ከምንም በላይ "የኢትዮጵያዊያን ያለህ!" እያሉ ነው።

#ሰብዓዊነት_ይቅደም !!
(ከአንድ ግዜ በላይ ሼር በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነትዎን ይወጡ)

ከያሬድ ሹመቴ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#updateሀዋሳ ዶ/ር ዐብይ⬇️

የኢህአዴግ ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በ11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ላይ ለተሳተፍ #ሀዋሳ ከተማ ገብተዋል።

11ኛው የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ድርጅታዊ ጉባዔ “ሀገራዊ አንድነት ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል ከነገ ጀምሮ በሀዋሳ ከተማ ይካሄዳል።

በድርጅታዊ ጉባዔው ላይ ለመሳተፍም የኢህአዴግ ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዛሬው እለት ሀዋሳ ከተማ ገብተዋል።

በተጨማሪም የኢህአዴግ ምክትል ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን ድርጅታዊ ጉባዔው ላይ ለመሳተፍ ሀዋሳ ደርሰዋል።

እንዲሁም የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባኤ ተሳታፊዎችም ሃዋሳ ከተማ መድረሳቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ልዩ ሀላፊ አቶ ፍፁም አረጋ አስታውቀዋል።

11ኛው የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) 11ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ ነገ ጠዋት ላይ በሀዋሳ ከተማ እንደሚጀምር ይጠበቃል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለተፈናቀሉ ዜጎችን ለመርዳት የባንክ ሂሳብ⬇️

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝና ከምስራቅ ወለጋ ዞን አጎራባች ወረዳዎች #የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመርዳት የባንክ ሂሳብ ተከፈተ፡፡

ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ካማሺ ዞን እና በምስራቅ ወለጋ ዞን ስር በሚገኙ አጎራባች ወረዳዎች ውስጥ የፀጥታ ችግር መፈጠሩ ይታወሳል፡፡

በዚህም ምክንያት ከ20 በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉና ከ70 ሺ በላይ ዜጎች ከንብረትና ቄያቸው መፈናቀላቸው ይነገራል፡፡

እነዚህን የተፈናቀሉ ዜጎች ለመርዳት የባንክ ሂሳብ መከፈቱን ኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በድረ ገፁ አስፍሯል፡፡

ድጋፍ ለማድረግም በኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ 937719፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000259030138፣ በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ 1000072131111 መጠቀም እንደሚቻል ተነግሯል፡፡

ከአራት ቀናት በላይ በእግራቸው በመጓዝ ነቀምቴ ከተማ የገቡት ተፈናቃዮች በአሁኑ ሰዓት በመምህራን፣ በቴክኒክና ሙያ፣ በነርሲንግ ኮሌጆችና በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተጠልለዋል፡፡

#የነቀምቴ ከተማ ነዋሪዎች የምግብና አልባሳት #ድጋፍ እያደረጉላቸው እንደሆነም ተነግሯል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር FM 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ መረጃ‼️

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝና ከምስራቅ ወለጋ ዞን አጎራባች ወረዳዎች #የተፈናቀሉ ዜጎችን #በገንዘብ ለመርዳት የምትፈልጉ፦

በኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ
937719

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000259030138

በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ
1000072131111

#ሼር

ምንጭ፦ ኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከነቀምት⬆️

"ፀግሽ የ07 እናቶች በዚህ መልኩ ለተፈናቀሉ ወንድምና እህቶቻቸው እንዲሁም ልጆቻቸው ምግብ ሲያዘጋጁ ነበር። #እውነተኛ እናትነታቸውን አሳይተዋል! ቦንሳ ከነቀምት"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ⬆️የ2011 ዓ.ም የነባር እና አዲስ ተማሪዎች መግቢያ ቀናት ይፋ ተደርጓል ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በነገው እለት #በሀዋሳ ከተማ በሚጀመረው11ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የሚጠበቁ ጉዳዮች፦

▪️በነሐሴ ወር 2007 በመቀሌ ከተማ ተደርጎ በነበረው 10ኛ የኢህአዴግ ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎችን መሠረት በማድረግ ባለፉት ሦስት ዓመታት የተሠሩ ሥራዎች ሪፖርት ቀርበው ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በጥልቀት ከገመገመ በኋላ ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚያሳይ እና ለ12ተኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የሚሆን ሰነድ እንደሚያዘጋጅ ይጠበቃል፡፡

▪️ሁሉም የግንባሩ አባል ፓርቲዎችና ድርጅቶች በቅርቡ ባካሄዷቸው ጉባኤዎች የመረጧቸውን አዳዲስ የማዕከላዊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባሎቻቸውን በዚህ ጉባኤ በማሳተፍ አዲስ የኢህአዴግ ምክር ቤት ይመሠርታሉ፡፡

▪️ወቅታዊ የሀገሪቱ ሁኔታ በጥልቀት ይገመገማል፤ ለውጡን ለማስቀጠል አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ፤ የቀጣይ አቅጣጫዎች ይመላከታሉ፡፡

▪️ባለፈው መጋቢት ወር ጥልቅ ተሐድሶውን ተከትሎ የተቀመጡ አቅጣጫዎች እና በተደረገውን የአመራር ለውጥ የተሠሩ ተግባራት ይገመገማሉ፡፡

▪️አዲስ የኢህአዴግ ምክር ቤት መመሥረቱን ተከትሎ የድርጅቱን ሊቀ-መንበርና ምክትል ሊቀ-መንበር #ይመረጣል፡፡

የጉባኤው ተሳታፊዎች ከአራቱም ብሔራዊ ድርጅቶች የተወከሉ ከእያንዳንዳቸው 250 በአጠቃላይ 1000 በቀጥታ በምርጫውና በውሳኔዎች ዙርያ በድምጽ የሚሳተፉ ይሆናሉ፡፡

በልዩ ሁኔታ የ11ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ተሳታፊዎች በታዛቢነት የሚገኙ ግን ድምጽ (የማይሰጡ ተሳታፊዎች፡-

-ሴቶችና ወጣቶች
-አጋር ድርጅቶች
-የተለያዮ የኅብረተሰብ ክፍሎች
-ማኅበራት
-ፌዴሬሽኖች
-ዩኒቨርሲቲዎች
-የፌዴራል ተቋማት ኃላፊዎች
-ልማታዊ ባለሀብቶች

የ11ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ መክፈቻ ላይ የሚሳተፉ፦

• የሠራዊት አመራሮች
• አርቲስቶች
• ስፖርተኞች
• ታዋቂ ግለሰቦች
• ተፎካከሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጥቅሉ አንድ ሺህ 900 ተሳታፊዎች ይኖራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia