TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#update ኤርትራዊ አርቲስት ካሕሳይ በርሀ የአሸንዳንና አዲስ አመት በዓልን ምክንያት በማድረግ የሁለቱም ህዝቦች ግኑኝነት እንዲጠናከር ዛሬ መቐለ ገብቷዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በድጋሚ...#ጥብቅ ማሳሰቢያ⬇️

"...ከምንም በላይ የግልና የቡድን ጥቅሞቻችሁን #ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማስጠበቅ እየቻላችሁ በተለያዩ ወንጀሎችና ሰላምን የማደፍረስ #እኩይ ተግባራት ላይ ለመሰማራት #የምታስቡ አካላት ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ እያሳሰብኩ በማንኛውም የህዝብን ፀጥታ #በሚያደፈርሱና ህዝብን ከህዝብ #በሚያጋጩ ህገወጥ ተግባራት ላይ ተሰማርቶ የተገኘ እንዲሁም ለእንደዚህ አይነት ህገወጥ ተግባራት በምንም መልኩ ትብብር ያደረገ አካል ላይ ህግን ተከትሎ አስፈላጊውን #እርምጃ ለመውሰድ መንግስት #ቁርጠኛ እንደሆነ በጥብቅ ለማሳወቅ እወዳለሁ፡፡"

◾️◾️ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ◾️◾️

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አፋልጉኝ⬆️ቴዎድሮስ አለነ ብዙነህ የእናት ስም መረሳ የትውልድ ቦታ ሁመራ ሢሆን አሁን ያለበት ቦታ አክሱም ነው ተብሎ ይታሠባል ያለበትን የሚያቅ 0939978326 በዚ ስልክ ይደውልልኝ ፈላጊ ወንድሙ እና አባቱ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
"አብረን ከፍ እንበል"

ከዝቅታው እንነጠል
ከሀኬቱ ከቶማታው እንገለል
ከክፋቱ ካሉባልታው እንከለል
አብረን ሆነን አብረን ከፍ እንበል
ከመቀናናት
ከመቆራቆስ
ከመተናናቅ
እንጠንቀቅ!
ከመጠላላት
ከመኮናነን
ከመጠቋቆም
እንቁም!
ከመዛዛት
ከመካሰስ
ከመጠበቅ
እንራቅ!
ከስሜታዊነት
ከጭፍንነት
ጥራዝ ከመንጠቅ
እንወቅ!
ከመበታተን
ከመለያየት
ከመገንጠል
እንነጠል!
አንድ ሆነን
አንድ እንሁን
ሁላችን የኢትዮጵያ ልጆች
የታላቅ አካል ብልቶች
ልዩ የሆንን ህብሮች
አንዳችን ለአንዱ ህይወቶች
የማንዘረዝ እውነቶች
የማንደበዝዝ ውበቶች
አንድ አካል ስንሆን ብዙዎች
ብዙዎች ስንባል አሀዶች
ካነሰው ሀሳብ እንነጠል
ከወረት ግንድ እንገንጠል
በፍቅር ላይ እንጠልጠል
በአብሮነት ካዝማ እንቸከል
እንደ ሰንደቅ እንተከል
ኑ! ከፍ ብለን አብረን ከፍ እንበል
ከዝቅታው እንነጠል
ከሀኬቱ ከቶማታው እንገለል
ከክፋቱ ከአሉባልታው እንከለል
በፍቅር ሆነን አብረን ከፍ እንበል
ከመናናቅ
ከመበላለጥ
ተመተናነስ
እንፈወስ!
ከመነጣጠቅ
ከመበላላት
ከመዘራረፍ
እንግዘፍ!
ከመከዳዳት
ከመዛዛት
ከመገዳደል
እንጉደል
ከመደባባት
ጥላ ከመውጋት
ከመጠራጠር
እንጠር!
ካለመከበር
ካለመታወቅ
ካለመታመን
እንዳን!
ከማደግደግ
እንደግ
ከመዘራጠጥ
እንለወጥ
ከመልመጥመጥ
እንብለጥ
ከማስመሰል
እንብሰል
ከመዋሸት
እንሟገት
ከማማረር
እንምረር
ሁላችን የኢትዮጵያ ልጆች
የታላቅ ሰውነት ብልቶች
የሺ ዘመናት እውነቶች
በአንድ አካል ያለን ህዋሶች
የአንደኛው ህመም ስሜቶች
እንዳፍንጫ እንደ ዓይን ቅርቦች
ለሌላው ስቃይ አልቃሾች
እንደ ምላስ እንደ ጥርስ ፍቅረኞች
የልስላሴና የጥንካሬ ውህዶች
ከልስላሴው ጣእምን
ከጥንካሬው ሀይልን
በመተጋገዝ ሰጭዎች
በአንድ አፍ ለዘላለሙ
እሰከ መቃብር ነዋሪዎች
ሁላቸችን የኢትዮጵያ ልጆች
ልዩ የሆንን ህብሮች
አንዳችን ለሌላው ህይወትች
የማንሰረዝ እውነቶች
የማንደበዝዝ ውበቶች
አንድ አካል ስንሆን ብዙዎች
ብዙዎች ስንባል አሀዶች
ኑ! ከፅንፈኝነት እንነጠል
በሀይል ከማመን እንከለል
ከፀብ ርስት እንገለል
ከፍ ብለን አብረን ከፍ እንበል
ከዝቅታው ከሲኦሉ ከመቀመቅ በርባሮሱ
ሀከጂኒ ኤላው ከገደሉ ከገሀናም ከእጦረጦሱ
ከትውልድ በካይ ጦሱ
ከቂም ከበቀል ጉርሱ
ከመጠፋፋት ሱሱ
ከመጎደል ብቻ ምሱ
ሀገር ከሚያወድም መንፈሱ
ኑ በፅናት ሆነን ከፍ እንበል
ከግለኝነት እንገንጠል
በፍቅር ላይ እንጠልጠል
ከፍ ብለን አብረን ከፍ እንበል
በመሞላላት
በመተጋገዝ
በመደጋገፍ
እንረፍ
በመከባበር
በመተሳሰብ
በመመካከር
እንክበር!
በመወያየት
በመነጋገር
በመደማመጥ
እንብለጥ!
ከመካረር
እንማከር
ብረት ከማንሳት
አንሳሳት
ከመሰናዘር
እንነጋገር
ከመቆራቆዝ
እንፈወስ
ዘር ከመቁጠር
እንጠር
ጎሳን ከማሰብ
እንሰብሰብ
ነገን ከመርሳት
አንሳት
ኑ የኢትዮጵያ ልጆች
አንዳችን ለአንዳችን ህይወቶች!
ኑ!

#አበባው_መላኩ

#ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን የአዲስ አመት ዋዜማ ኮንሰርት ለሌላ ጊዜ የተሸጋገረው በዕለቱ መንግስት አዳራሹን ለዝግጅት በመፈለጉ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የቴዎድሮስን ኮንሰርት አልሰረዘም አዘጋጆቹ በትህትና ተጠይቀው ነው ለቀጣይ ግዜ የተሸጋገረው።

#ብዙ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያ በመንግስት ላይ እንዲሁም የአመራሮችን ስም በመጥቀስ ዘለፋ እና የስም ማጥፋት ላይ ስላሉ ጥንቃቄ ይደረግ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ⬆️

የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በክልሉ በተፈጠረዉ የፀጥታ መደፍረስ ለተጎዱ የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች የመኝታ፣ ፍራሽና የታሸጉ ምግቦች እርዳታ ሰጥቷል፡፡ የዩኒቨርሲቲዉ አመራር ይህንን የወሰነዉ ነዋሪዎቹ በከፍተኛ ሁኔታ መጎዳታቸዉን ከግንዛቤ በማስገባት ነዉ፡፡ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶ/ር #አብዱላዚዝ_ኢብራሂም "ህብረተሰቡ መልሶ እንዲቋቋምና ከተማዋ ወደ ቀደመ ሰላሟ እንድትመለስ የሚቻለንን ሁሉ ከማድረግ ወደኋላ አንልም" ብለዋል።

©ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ከስድስት ወራት በኋላ የሁሉም የስኳር ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚጠናቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ ተናግረዋል። ግንባታቸው በተለያዩ ምክንያቶች ተጓቶ የነበሩ የስኳር ፕሮጀክቶች አሁን ላይ የማጠናቀቂያ ስራ እየተሰራ መሆኑ ነው የተገልፀው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት በባህርዳር ከተማ ከብአዴን አመራሮች ጋር ባደረጉት ምክክር ላይ ነው፡፡

©አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ⬆️

በአዲስ አበባ ከተማ ልደታ 01 ቀበሌ ቶሎሳ ሰፈር መኮንኖች ክበብ የአርበኞች ግንቦት 7 አመራሮችን እና አባላትን ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።

©Go(TikvahEthiopia)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በቂ #መረጃ በሌለኝ ጉዳይ ላይ ባለመዘባረቅ ለሀገሬ ሰላም የበኩሌን አስተዋጽኦ አደርጋለሁ"

©Kubra Bahiru
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ መደበኛ ስብሰባውን ጀምሯል። የኢህአዴግ ምክር ቤት ፅህፈት ቤት የህዝብና የውጭ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሳዳት ናሻ እንደገለፁት ኮሚቴው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።

©FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት⬇️

የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ከሰኔ 16 የቦንብ ጥቃት ጋር በተያያዘ ቦንቡን በማፈንዳት እና የፈነዳውን ቦንብ በማቀበል የተጠረጠሩ #ጥላሁን_ጌታቸው እና #ብርሀኑ_ጃፋር የተባሉ ግለሰቦች ላይ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ 7 ቀን ፈቀደ፡፡

ፖሊስ የምርመራውን ጊዜ የጠየቀው ተጨማሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ ለማሰባሰብ ብሎም ከሰኔ 12 እስከ 16/2010 ዓ.ም ተጠርጣሪዎች ያደረጉትን የስልክ ልውውጥ የሚያስረዳ ከኢትዮ-ቴሌኮምና ከብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ማስረጃ ለመቀበልና ተያያዥ የምርመራ ስራዎችን ለማከናወን ነው ብሏል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia